en
Feedback
Merega Tv = Ethio 360Media

Merega Tv = Ethio 360Media

Open in Telegram
8 780
Subscribers
-424 hours
-157 days
-1130 days
Posts Archive
"በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት የተከፈተው በትግራይ አቅጣጫ ብቻ አይደለም። በኦሮሚያም ቤንሻንጉልም በሶማሌ ክልልም በጋምቤላም በኩልም ነው።……ተወግተን ስናሸንፍ ትግራይ የምትባል ሀገር እንመሰርታለን።" ጌታቸው ረዳ፣ በግብፅ ሚዲያ ቀርቦ የተናገረው ጌታቸው ረዳ በግብፅ ሚዲያ ላይ እንግዳው ሆኖ ቀርቧል። ሚዲያው የፕሬዝዳንት ሲሲ ሚዲያ ነው። ያቋቋመው እሱ ነው። እዚህ ሚዲያ ላይ የሚሰሩ ሰዎች እንግዳ ሆነው የሚቀርቡ ሰዎች በግብፅ የደህንነት መስሪያ ቤት እውቅናና ተልዕኮ ነው። በዚህ ሚዲያ ላይ ማንኛውም የፖለቲካ ሰው ወይም የኔ ቢጤ ቀርቦ ትንታኔ አይሰጠም። ሚዲያው የፕሬዝዳንት ሲሲ ትልቁ ተወንጫፊ ሚሳኤሉና የተልዕኮ ማስፈፀሚያ መሳሪያው ነው። ጌታቸው በዚህ ሚዲያ ላይ እንዴት ቀረበ ብሎ መጠየቅ አያስፈልግም። ከላይ እንዳልኳችሁ በዚህ ሚዲያ ላይ የሚቀርቡ ሰዎችን የሚመርጠው፤ እውቅናና ፍቃድ የሚሰጠው የግብፅ የደህንነት መስሪያቤት ነው። ጌቾን በቀላሉ ወደዛ ያስገቧትም ደህንነቶ ናቸው። ወያኔና ግብፅ ምን ያህል ፍቅር ላይ እንዳሉ ከዚህ በላይ ሌላ ማስረጃ የለም። ጌታቸው ከጋዜጠኛው የቀረበለትን ጥያቄ በሚገባ መልሷል። ተዋግተን አዲስ አበባ ከገባን በህዝብና በክልሉ መንግስት ድምፅ መሰረት ትግራ የምትባል አገር እንመሰርታለን ብሏል። እኛ ብቻ ሳንሆን ኦሮሞውም ጉምዙም ሶማሌውም ጋቤላውም አገር መሆን ይፈልጋል። ለዚህም አሁን ተጣምረን እየተዋጋን ነው። አሁን በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት የተከፈተው በትግራይ አቅጣጫ ብቻ አይደለም በኦሮሚያም ቤንሻንጉልም በሶማሌ ክልልም በጋምቤላም በኩልም ነው። እኛም ከነሱ ጋር አብረን እየሰራን ነው በቅርቡ የአብይ አሕመድን መግንሥት በውጊያው እናሸንፋለን፤ ይሄንንም ማሳካት የሚያስችሉ ስራዎች ተሰርተው እየተጠናቀቁ ነው ትንሽ ነው የቀረን ብሏል። ጋዜጠኛው ዋና ዋና ጥያቄዎችን ያደረገው የህወሓትን የወደፊት እቅድ ምንም እንደሆነ መለየት ላይ ነበር። እሱንም አለሳልሶ ጠይቆ ከጌታቸው ረዳ በቂ መልስ አግኜቷል። ተዋግተን ካሸነፍን ህዝብና የትግራይ መንግስት ተመካክረው አገር እንሆናለን እኛም ብቻ ሳንሆን ኦሮሞ ጉምዝ ሱማሌ ጋቤላው ከኛ ጋር ተመሳሳይ ፍላገት ኖሮት አብሮን እየሰራ ነው ብሎ ለጋዜጣጠኛው ጥያቄ ተጊቢውን መልስ ሰቶታል። በርግጥ ጌታቸው በግብፅ መንግስት ሚዲያ ላይ የቀረበው እንዲሁ አይደለም። ሰዎቹ አብረው በጋራ አገሪቱን ለማፍረስ እየሰሩ ስለሆነ ምን ያህል የጋራ አላማ ቢኖሯቸውም ነው እንዲህ በዚህ በተመረጠ ሚዲያ ላይ ቀርቦ እንግዳ የሆነው ማለትም አያስፈልግም። ህወሓት አሁን ላይ የሚያደርገው ውጊያና አንዳንድ አለማቀፍ ድርጅቶችና የተወሰኑ አገራት በኢትዮጵያ ላይ ለምን ጫና እንደሚያደርጉ ከዚህ ጀርባ ማን ምን እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። ጌታቸውም ዛሬ በትክክለኛው ሚዲያ ትክክለኛው ማንነቱን ይዞ ከነስሙ ለኢትዮጵያውያን አሳውቋል። (ሱሌማን አብደላ)

#Ethiopia የወሎ ህዝብ መግባት ባለበት አውድ ሁሉ እየተፋለመ ውጤት ማምጣት ይኖርበታል !!! ህዝባችንን ማድረግ ያለብንን ነገር በማድረግ ከረሀብ እና ከበሽታ ቆፈን ልንታደገው ይገባል ። በነዚህ ሴረኛ ፣ዘራፊዎች እና ሀገር አፍራሾች መገዛት አልፈልግም የሚል ጠንካራ አቋም ያለው ማህበረሰብ እነሡ እስኪመጡ ሳይሆን ያሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ የሚገባቸውን በመስጠት በረሀብ የሚንገላታውን ህዝባችንን ልንታደገው ይገባል ፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ አሸባሪው እና ዘራፊው ቡድን ዕድል ካገኘ ሰሜን ወሎን ብቻ አይደለም ደቡብ ወሎንም አልፎ የማይሄድበት ሁኔታ አይኖርም ዋናው ነገር ዘራፊው እና ጨፍጫፊው ቡድን እየመጣበት ያለውን ድርጊት በመረዳት የመጀመሪያው የአሸናፊነት ስነ ልቦና መላበስ ያስፈልጋል ፤ እኛም እነሱም እንተዋወቃለን ስለ ጦርነት እነሱ አውቀው እኛ ሳናውቅ የቀረንበት ሁኔታ የለም ፡፡ በየደረጃው ያለው የተቆጣው ህዝባችን በጦርነት ቀጠና ውስጥ ለሚገኘው የወሎ ማህበረሰብ ሊደርስ ይገባል ፡፡ በወሎ ግምባር ጁንታው የማፅዳትና የያዛቸውን ቦታዎች የማስለቀቅ ጉዞው እጅግ በዘገየ ቁጥር ሌላ አስከፊ የሆነ የረሀብ እና የበሽታ ቀውስ እያስከተለ ነው በመሆኑም ከጦርነት የተረፈውን በረሀብ ቸነፈር ከማለቁ በፊት እንድንደርስለት !! ሲፈጠርም ክፋት የወለደውን ዘራፊ ቡድን የያዛቸውን ቦታዎች በአፋጣኝ ማስለቀቅ ተገቢ ነው !! ጊዜ የምንሰጠው ጉዳይ መሆን የለበትም !!! ትኩረት ለወሎ ግምባር

🌼2014🌼 እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሰን ... አዲሱ አመት የሰላም እና የከፍታ ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ... 🌼መልካም በአል 🌼

የተረጋገጡ አዳዲስ መረጃዎች ==================== -ትናንት በእስታይሽና መርሳ ማዶ ስብሰባ የተቀመጠ የትህነግ አመራር እዛው ስብሰባ ላይ እያሉ በድሮን ተመተዋል። -ካለፈው ሐሙስ ጀምሮ በድሮን በታገዘ በተወሰደው መብረቃዊ ብዛት ያለው የህውሃት ክፍለጦሮች ተደምስሰዋል። ትህነግ አንዱን ክፍለጦር ያደራጀው ከ1600 እስከ 2000 ባለው የታጣቂ ቁጥር ነው። -ከጋይንት እስከ ጋሸና ባለው መስመር በነበረው አውደ ውጊያ በትንሹ ከ10 ሺህ በላይ የሚሆን ጀሌ ከጥቅም ውጪ ሆኗል ! -የአፋር ግምባር አሁንም ለህወሓት የኤርታሌ እሳተ ገሞራ እንደሆነበት ነው። ከሀሙስ ጀምሮ እስከ ትናንት እሁድ ድረስ ሙከራ አድርጎ አልተሳካለትም። በአፋር በራኽሌ ግንባር ባደረገው ሙከራ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ሃይል ተመትቷል። ነገርግን ያመለጡት በጣት የሚቆጠሩ ናቸው ተብሏል። -እዛው በአፋር ከቅዳሜ ጀምሮ በሃሮ እና በዙሪያው በተካሄደው ውጊያ ከ3500 በላይ የጁንታው አስክሬን ተቆጥሯል። የአፋር ወጣቶች አሁንም ጀብዱ እየፈፀሙ ናቸው። *ትናንት ስለመከላከያ ምዝገባ ጽፌ ነበር። በተለይ ዐማራ ክልል ለመከላከያ እየተሰጠው ያለውን ኮታ ማሟላት እየቻለ አይደለም። ለምሳሌ፣ የባለፈው ዙር መከላከያ ስልጠና አፈፃፀም ስንመለከት፦ -ኦሮምያ ክልል ከ40,000 በላይ ሰልጣኝ መልምሎ 38,000 ማጣሪያውን አልፈው ወደ ስልጠና ማእከል አስገብቷል፣ -ሲዳማ ክልል ከ12,000 መልምል 10,420 አስገብቷል፣ - አማራ ክልል ከ8,600 ምልምል 7,412 ብቻ ማጣሪያውን አልፈው ወደ ስልጠና ገብተዋል። ከዚህ መረጃ ተነስተን ዐማራ በመከላከያ ተቋም ውስጥ የብሄር ተዋፅኦ ከረጅሞ ጊዜ አኳያ ምን ሊመስል እንደሚችል መገመት ቀላል ነው። ስለዚህ የተቀናጀ ቅስቀሳና ግፊት ያስፈልጋል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ መከላከያ ክዶናል፣ ሽጦናል፣ ጦርነቱን መከላከያ እያገዘ አይደለም፣ የመከላከያ ተቋም በአንድ የብሄር የበላይነት ተይዟል ብትል የሚሰማህ የለም። መፍትሄው ግልጽና ግልጽ ነው ለሁሉም እኩል የወጣውን የቅጥር ማስታወቂያ መጠቀም ብቻ! *ሁለተኛው ጉዳይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ ንፁሐን ግለሰቦችን በቂምና ባሻጥር የጁንታ ታርጋ እየለጠፉ ስማቸውን የሚያጠፉ፣ የሚያሳስሩና አለፍ ሲል እርምጃ እንዲወሰድባቸው ያደረጉ ሰዎች አሉ። አሁንም አንዳንዶቹ ከባለሀብቶች ገንዘብ ለመቀበል፣ ሌላኞቹ ደግሞ በቆዬ ቂም በቀል ጁንታ እያሉ ወቅታዊ ጉዳዩን ለግል ፍላጎት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። ገንዘብም ለማግኘት ሆነ የቆየ ቂም በቀልን ለመወጣት በዚህ አሻጥር የተሰለፉ ሰዎች ከድርጊታቸው ቢቆጠቡ መልካም ነው እላለሁ! *ሦስተኛው ጉዳይ ከሰሞኑ በአማራ ባንክ ስም የተከፈቱ በርከት ያሉ የፌስቡክ ገፆችና ቴሌግራም ቻናሎች የተለያዩ መልክቶችን እያስተላለፉ ይገኛሉ። እንዲያውም ባንኩ ሥራ መጀመሪያ ፕሮግራሙን እንዲሁም አዲሱን አመት ምክንያት በማድረግ እስከ መስከረም አምስት ድረስ የሚቆይ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም መዘጋጀቱን ጽፈዋል። ነገርግን አማራ ባንክ ፌስቡክም፤ ቴሌግራምም ምንም አይነት ማህበራዊ ሚዲያ ገፅ የለውም። ባንኩ ገና በምሥረታ ላይ ነው። እንደዚህ አይነት የሽልማት እድሎችን ሊያዘጋጅ አይችልም። መረጃው ትክክለኛ ቢሆን ኖሮ ማስታወቂያው በቴሌቭዥ፤ በሬድዮና ጋዜጣ ይተላለፍ ነበር። (በታደለ ጥበቡ)

photo content

ልዩ መረጃ‼️ አሸባሪው ህወሓት በአፋር ክልል ዳሎልን ለመቆጣጠር ያደረገው ሙከራ በአፋር ክልል ልዩ ሀይል እና ሚሊሻ ከሽፏል፡፡ #Ethiopia : ህወሓት በክለሉ በበርሃሌ ወረዳ በርካቶችን ገድሏል፣ አቁሱሏል፣ ከቤት ንብረታቸውም አፈናቅሏል እንዲሁም ቅርሶችን አውድሟል፡፡ ቡድኑ በከባድ መሳሪያ ጥቃት ቢፈጽምም የአፋር ልዩ ሃይል አባላት ባላቸው አነስተኛ መሳሪያ በማጥቃት ትልቅ ጀብድ እንደፈጸሙ የዞን 3 ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አሊ በስፍራው ለሚገኘው ባልደረባቸን ነግረውታል፡፡ አሁን ላይም ልዩ ሃይሉ ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው፡፡ በአሸባሪው ቡድን ከቀያቸው የተፈናቀሉ ከ6 ሺህ በላይ ዜጎች ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የገለጹት አቶ መሀመድ፥ ድጋፉ በቂ ባለመሆኑ ትኩረት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

photo content

እጅግ አስቸኳይ❗️❗️❗️ በአሜሪካ የለምትገኙ የሀገር ልጆች ይህ የሙዚቃ ዝግጅት እንዳይደረግ በስልክ እየደወላችሁ አሳስቡ። # አንድነትለኢትዮጲያ # UnityForEthiopia # TPLFisaTerroris tGroup : Telphon# 17034186800 Guest.correspondence@hilton.com በዚህ ቁጥር እየደወላቹ ይሄ ዝግጅት የጦር መሳርያ ለመግዛትና ንጹሀን ወገኖችን ለመጨፍጨፍ ስለሆነ ሆቴሉ ባስቸኩዋይ እንዲሰርዝ ማድረግ አለብን ኢትዮጵያዊ በሙሉ መረባረብ አለበት።

photo content
+1

(ሀብታሙ አያሌው) በወንበዴው እና በሽብርተኛው ቡድን በህወሓት በንፋስ መውጫ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ ብቻ ከ900 ሺህ ብር በላይ ተዘርፏል። በበርካታ ከተሞች ባንኮች ተዘርፈዋል። የአማራ ብድርና ቁጠባ ተዘርፏል። ወድሟል። ፩ አብይ አህመድ ሆይ "እጅ በአፍ የሚያስጭን ተዓምር" ጠብቁ ያልከን ይሄንን ነበር ወይስ ሌላ እንጠብቅ ? ከአማራ ህዝብ ስንት ፐርሰንቱ ተጨፍጭፎ ምን ያህል ንብረት ከወደመ በኋላ ይሆን ያንተ ተዓምር የሚጀምረው ? ፪ ለመሆኑ አንድ ሄሊኮፕተር የሌለው ዱቄት አደረኩት ያልከው ቡድን በአማራ ክልል ወስጥ "ብረት ለበስ" ከባድ መሳሪያዎች እያሽከረከረ ህዝብ እና ንብረት ሲያወድም የኢትዮጵያ አየር ኃይልም ሆነ ያንተ ድሮን የት ነው ያሉት ? ምንስ እየሰሩ ነው ? በእርግጥስ አሉ ?

photo content

አሜሪካ አቀረቀረች- ኢትዮጵያ ቀና አለች ቁጣው ከላይ ነው !! ~~~~~~~~~~~~~~~~~ ውርደት ፣ ሃዘን ፣ ስብራት ፣ ሽንፈት ..... ኦ አሜሪካ !! አሜሪካ ዛሬ ኢትዮጵያውያንን ቅስም እሰብራለሁ ፣ ህዝቧን አንበረክካለው ፣ ትልቁን የቅጣት በትር አሳርፍባታለሁ ብላ ያቀደችበት ቀን ነበር ። ሆኖም የኒዮርኩ ቀጠሮ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን እኛ እንዳሰብነው ሆነ ። ኢትዮጵያ አላጎነበሰችም !!! ቀና አለች እንጂ !! በአንፃሩ አሜሪካ ኢትዮጵያ ላይ ያወጠነችውን መፈፀም ካለመቻሏ በላይ በካቡል ወሽመጥ ሰባሪ ፣ አንገት አስደፊ ውርደት ገጠማት ። ዜጎቿን ከታሊባን ይታደጋሉ ተብለው የከተላኩ ስልጡን ሰራዊቶቿ መካከል 12 ተገደሉ ። ቁጥራቸው እስካሁን ያልታወቀ አፍጋኒስታናውያን ተሰው ፤ ካቡል በደም ታጠበች !! ጆ ባይደን መግለጫ እየሰጡ መንግስታቸው በአፍጋኒስታን የገጠመውን ውርደት መግለፅ ተስኗቸው በቴሌቪዥን ፊት አንገታቸውን ሰበሩ !! እንባ ተናነቃቸው ! ቃላት ጉሮሮአቸውን አልፈው አልወጣ አላቸው !!! የሚሉት ጠፋቸው !! የሰውየው የዛሬው ሁኔታ ለብዙ ፓለቲከኞቻቸው መሳለቂያ ሆኗል!! የዶናልድ ትራምኘ ልጅ ጆን ትራምኘ ጁኒየር Donald Trump Jr. " this is what weakness looks like" ብሎ ትዊት አድርጓል። ኢትዮጵያዊያን ኒዮርክ ላይ በሆነው ሃሴት ስናደርግ ፣ አሜሪካውያን ካቡል ላይ ባዩት ክስተት ሃዘን ቅሳማቸው ሰብሮታል ። ኢትዮጵያ ላይ ክፋትን ሲጎነጉን የከረመ አይምሮአቸው አቅሉን ስቶ ፣ ክፉ አይኖቻቸው በእንባ ተሞልቶ ፣ ቀልባቸው ተበትኖ ዋይታ ላይ ናቸው ። አዎ ቁጣው ከላይ ነው !!

photo content
+2

በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ ነፋስ መውጫ ከተማ የዩኤስ አይ ዲ ቅርንጫፍ የሆነው ኤፍ-ኤች ኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን መዘረፉ ተገለጸ፡፡ በደቡብ ጎንደር ዞን ላይ ጋይንት ወረዳ ነፋስ መውጫ ከተማ የሚገኘው የዩኤስ አይ ዲ ቅርንጫፍ የሆነው ኤፍ-ኤች ኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ንብረቶች ውድመት እና ዘረፋ እንደተፈጸመባቸው የድርጅቱ ኀላፊ ተናግረዋል፡፡ የኤፍ-ኤች ኢትዮጵያ የላይ ጋይንት ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አንተነህ አዳሙ እንዳሉት በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የሠራተኞች መኖሪያ ቤትን ጨምሮ፣ የእህል መጋዘኖች፣ በርካታ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ ወድሟል። የተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች እና ጋራዥም ሙሉ በሙሉ ወድሟል ነው ያሉት። መኪናን ጨምሮ 25 የፕሮጀክቱ የሞተር ሳይክሎች በወራሪው ቡድን መዘረፋቸውን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። አቶ አንተነህ ለአደጋ ጊዜና ለሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች አገልግሎት የሚውል 4 ሺህ 551 ኩንታል በላይ እህል በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን መወሰዱንም አረጋግጠዋል።

#Ethiopia : ቻይና 🇨🇳 ሩሲያ 🇷🇺 ህንድ 🇮🇳 ኬንያ 🇰🇪 አሁን በተካሄደው የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ጣልቃ ገብነትን እንደማይቀበሉ ገልፀው የኢትዮጵያ ጉዳይ ለኢትዮጵያ ተውላት ብለዋል ❗️

photo content

ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል።

photo content
+3

በሀገርና በሀገሪቱ ሰራዊት ላይ ክህደት በመፈፀም ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው። የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ የጦር ፍርድ ቤት ባስቻለው ወታደራዊ ፍርድ ቤት አስር ተከሳሾች ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሰሩት ወንጀል መጠን የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር አፍራሽ አሸባሪዎች ጋር ሚስጥራዊ ግንኙነት በመፍጠር የሀገር ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል፣ ክህደት በመፈፀም አሸባሪዎቹን የህወሓት ጁንታ ለመቀላቀል ማሴር፣ ለሸኔ መረጃ ማቀበል፣ ከግዳጅ ቀጠና በመሸሽ የወገን ጦርን ለአደጋ ማጋለጥ፣ ያለ በቂ ምክንያት ሲቪሎችን መግደል፣ የበላይን ትዕዛዝ ችላ በማለት ለንፁሐን ሞት ምክንያት መሆንና የመንግሥትና የህዝብን ወታደራዊ ንብረትን ይዞ ለመሸሽ ሙከራ ማድረግ የሚሉ ክሶች ዋነኛ ጭብጥ ሆኖ ቀርቧል፡፡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን ሲመረምር ቆይቶ ተከሳሾች እራሳቸውን መከላከል ባለመቻላው የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ በዚህ መሰረት፡- 1. ሻለቃ ክፍሌ ካሳይ በ17 አመት ፅኑ እስራት፣ 2. ኮሎኔል ክፍሌ ፍሰሃዬ በ14 ከ 2 ወር ፅኑ እስራት፣ 3. ሀምሳ አለቃ መብራቱ ጥላዬ በ18 አመት ፅኑ እስራት፣ 4. መሰረታዊ ወታደር መኮንን ክንፈ በ13 አመት ፅኑ እስራት፣ 5. ሀምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ በ11 አመት እስራት፣ 6. ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ በ11 አመት ፅኑ እስራት፣ 7. ምክትል ክፍሌ ንጉስ በ9 አመት ፅኑ እስራት፣ 8. ኮሎኔል ካሱ ሀብቱ በ11 አመት ከ2 ወር፣ 9. ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ በ8 አመት ፅኑ እስራት እና 10. ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ በ10 አመት ከ2 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡ በቀጣይም ከ150 በሚበልጡ ተጠርጣሪዎች ላይ የፍርድ ሂደት እንደሚታይ ተገልጿል፡፡

#ምስራቅ_ወለጋ : "የነዋሪዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ የአካባቢው የፀጥታ ኃይል ሊጠናከር ይገባል" - ኢሰመኮ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በኦሮምያ ክልል፣ ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ጊዳ ኪራሙ ወረዳ ነሃሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. በአካባቢው ተሰማርተው የነበሩ የፀጥታ ኃይሎች ወደ ሌላ አካባቢ መንቀሳቀሳቸውን ተከትሎ፣ ነሃሴ 12 ቀን 2013 ዓ.ም. የ”ኦነግ ሸኔ” ናቸው በተባሉ ታጣቂዎች በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ብሔርን መሰረት ያደረገ ጥቃት ማድረሳቸው በከፍተኛ ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገለፀ። ነሃሴ 12/2013 ዓ.ም. በታጣቂዎች በተፈጸመው ጥቃት ከ150 በላይ ነዋሪዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና ሌሎች ሰዎች እንዳስረዱት ኮሚሽኑ አሳውቋል። በዚህ የተነሳ ሌላው የወረዳው ነዋሪዎች፣ በተለይ ሴቶችና ሕጻናት ወደ አጎራባች አካባቢዎች መሸሻቸውንና በቀጣይ ቀናት ከነዋሪዎች የተውጣጡ ሰዎች ብሔርን መሰረት ያደረገ የአጸፋ ጥቃት በማድረሳቸው 60 ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎችም ወደ አማራ ክልልና ወደ ኪራሙ ከተማ መፈናቀላቸውን ኮሚሽኑ ገልጿል። በአሁኑ ወቅት የፀጥታ ኃይሎች ወደ አከባቢው በመመለሳቸው ጊዳ ኪራሙ ወረዳ የተረጋጋ መሆኑን ነዋሪዎች ያስረዱ ቢሆንም በጊዳ ኪራሙና በሌሎች አጎራባች ወረዳዎች አሁንም ድረስ የፀጥታ ስጋት አለ ብሏል። ኢሰመኮ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ክትትሌን ቀጥላለሁ ያለ ሲሆን ፥ የአካባቢው ፀጥታ የደረሰበት አስጊ ደረጃ ወደ አጎራባች አካባቢዎች እንዳይዛመትና የበለጠ ሰብአዊ ቀውስ እንዳያደርስ አስቸኳይ እርምጃ አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።