en
Feedback
Merega Tv = Ethio 360Media

Merega Tv = Ethio 360Media

Open in Telegram
8 780
Subscribers
-424 hours
-157 days
-1130 days
Posts Archive
photo content
+1

#Ethiopia : የኢትዮጵያ መንግስት 7 የተመድ ሰራተኞች በ72 ሰአታት ውስጥ ከአገር እንዲወጡ ትእዛዝ አስተላለፈ *********** የኢትዮጵያ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስር በተለያዩ ኤጀንሲዎች ውስጥ የሚሰሩ 7 የውጭ አገር ዜጎች በ72 ሰዓት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ ትእዛዝ ማስተላለፉን የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢቲቪ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት የመንግሥታቱ ድርጅት ባልደረቦች በአገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ህገ ወጥ ሥራ ሲሠሩ የተገኙ መሆናቸውም ነው የተገለፀው። የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት ሰባት የውጭ አገር ዜጎች 1- የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ ተወካይ UNICEF ሚስ አዴል ኮደር 2- የዩኤን የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ግራንት ሊያቲ 3- የዩኤን የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ተወካይ ሚስ ጋዳ ኤልታሂር ሙዳዊ፣ 4- የዩኤን የሰላምና ልማት አማካሪ ከውሲ ሳንቼሎቲ 5- የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮ ባልደረባ ሶኒ ኦኒግ ቡላ 6- የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት UNOCHA ምክትል አስተባባሪ ሰኢድ መሀመድ ሀርሲ 7- የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት UNOCHA ኃላፊ ሚስ ማርሲ ቪጎዳ ናቸው።

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አቶ ኡሞድ ኡጁሉን የክልሉ ርዕሠ-መስተዳድር አድርጎ መርጧል፡፡ አቶ ኡሞድ ኡጁሉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ የክልሉ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም ከህዳር 1/2011 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ ርእሠ መስተዳድር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ለቀጣይ አምስት ዓመታት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው እንዲያገለግሉ ተመርጠዋል። [ ጋምቤላ ኮሙኒኬሽን ]

#Ethiopia : የሲዳማ ክልል ም/ቤት አቶ ደስታ ሌንዳሞን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መረጠ

ዶክተር ይልቃል ከፋለ የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሆነው ተሾሙ። የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ እያካሄደ በሚገኘው የመሥራች ጉባኤ ዶክተር ይልቃል ከፋለን የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አድርጎ ሾሟል። ዶክተር ይልቃል ቃለ መሃላ ፈፅመዋል። ዶክተር ይልቃል ፥ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲን ፕሬዝዳንት የመሩ ሲሆን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮንም በኃላፊነት መርተዋል።

photo content
+3

ኦነግ በኦሮሚያ ያሰለጠናቸውን ወታደሮች በይፋ በአደባባይ አስመረቀ! ******************* ከኦነግ ወታደራዊ የምረቃ ትእይንትና ሂደት መገንዘብ እንደሚቻለው የኦሮሚያ ክልል መንግስትም ሆነ በአብይ አህመድ የሚመራው የፌደራል መንግስት በኩል ለስልጠናው ሙሉ ድጋፍ ያልተለየው መሆኑ ነው።

የሱዳን መንግሥት የኢትዮጵያ ወታደሮች በአወዛጋቢው አዋሳኝ የድንበር አካባቢ ጥቃት ሰነዘሩብኝ ሲል ከሰሰ። ከሱዳን ጦር የወጣው መግለጫ፤ ከኢትዮጵያ በኩል የተሰነዘረውን "ጥቃት መመከት" መቻሉን አመልክቷል።የኢትዮጵያ መንግሥት ከሱዳን በኩል ለቀረበበት ክስ አስካሁን በይፋ የሰጠው ምላሽ የለም።የሱዳን ጦር ተሰነዘረብኝ ስላለው ጥቃት ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳብራራው ክስተቱ ያጋጠመው ኡማ ናራኪት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው ብሏል። የሱዳን ሉአላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበርና ጦር አዛዥ ጄነራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሐን ከኢትዮጵያ በኩል ጥቃት የተሰነዘረብን ቅዳሜ ዕለት ነበር ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።ጄነራሉ በቅርቡ ሱዳን ውስጥ ተሞክሮ ከሸፈ የተበላውን መፈንቅለ መንግሥት በማስታወስ፤ ክሰተቱ ጦሩ ሱዳንን እየጠበቀ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።የኢትዮጵያ መንግሥት በጉዳዩ ላይ እስካሁን በይፋ ያለው ነገር ባይኖርም፤ አል-ጀዚራ የኢትዮጵያ ባለስልጣናትን በመጥቀስ እንደዘገበው በሱዳን ደንበር አካባቢ የኢትዮጵያ ጦር ምንም አይነት እንቅስቃሴ አላደረገም፤ የተባለው ጥቃትም አልተፈጸምም። በተመሳሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር መንግሥታቸው በሁለቱ አገራት መካከል በድንበር ይገባኛል ምክንያት የተከሰተውን አለመግባባት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። Via BBC

photo content

photo content
+1

መልካም የመስቀል በአል እንዲሆን እንመኛለን!!!

ልዩ መረጃ‼️ #Ethiopia : የአፋር ክልል ልዩ ሀይልና ሚኒሻዎች በአብአላ በኩል ወደ ትግራይ ክልል ዘልቆ በመግባት 4 የትግራይ ከተማዎችን መቆጣጠራቸው ተነገረ ይህ በኢንዲህ እንዳለ በአሁን ሰአትም ከመቀሌ በ30ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኘውና ለመቀሌና ለጁንታው ሀይል ቁልፍና እስትራቴጂክ ከተማ የሆነችውን ምላዛት የምትባል ከተማን በአፋር ሀይሎች ቁጥጥር ስር መሆኖ ተረጋግጦል፡፡

2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም እንዲከበር አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ 2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም እንዲከበር ወቅታዊውን የፀጥታ ሁኔታ ያገናዘበ ዕቅድ በማውጣት እና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አስፈላጊውን የፀጥታ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በየዓመቱ በመስከረም ወር አጋማሽ ቀናቶች ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት አንዱ የመስቀል በዓል ነው፡፡ በበዓሉ በርካታ የሃገራችን ብሄር ብሄረሰቦችና የውጭ ሃገር ዜጎችም ጭምር የሚታደሙበት በመሆኑ ወቅታዊውን የፀጥታ ሁኔታ ያገናዘበ ዕቅድ በማውጣት እና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በዓሉ በሠላም እንዲከበር የአ/አበባ ከተማ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የአ/አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር አገራችን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር ልዩ ዝግጅነት ከመደረጉም ባሻገር ለፀጥታ ኃይሉ በበጎ ፈቃደኝነት አጋዥ የሆኑ በቅርቡ የተመረቁ ከ27ሺ በላይ ወጣቶች በፀጥታው ሥራ ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዲሆኑ አስቀድሞ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡ በዓሉ ከመስቀል አደባባይ ባሻገር በተለያዩ አድባራት በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት ስለሚከበር ከኮሮና ቫይረስ ስርጭት ስጋት አንፃር ህብረተሰቡ የኮቪድ ፕሮቶኮልን ባሟላ ሥነ-ሥርዓት ተሳታፊ እንዲሆን ፖሊስ አሳስቧል፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች በየአካባቢያቸው በዓሉን ሲያከብሩ እና ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጡ የከተማችን ነዋሪዎች እንደወትሮው ሁሉ የፖሊስን መስተንግዶና ትዕዛዝ በማክበር ተባባሪ እንዲሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዓሉ በሰላም እንዲከበር ለማስቻል በህገ መንግስታችን እውቅና የሌላቸው ባንድራዎች ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ መልዕክቶችንና አርማዎችን በዓሉ በሚከበርባቸው ቦታዎች ላይ ይዞ መገኘት የተከለከለ መሆኑን ገልፆ መላው የፀጥታ ሃይሉ የተከለከሉ ነገሮችን በህግ አግባብ ለመቆጣጠርና ለማስከበር አስፈላጊው መመሪያ መሰጠቱን ፖሊስ አስታውቋል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከተፈቀደላቸው አካላት ውጪ ሪቺት መተኮስ የተከለከለ ከመሆኑም በሻገር ተቀጣጣይና ስለታማ ነገሮችን በዓሉ ወደ ሚከበርባቸው ቦታዎች ይዞ መምጣት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት መስከረም 16 የሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ የሚያከናውነውን ተግባር በመደገፍ የከተማችን ነዋሪዎች የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙም በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የመረጃ ስልኮች 011-1 11-01-11 ወይም በነፃ የስልክ መስመር 991 መረጃ መስጠት እንደሚቻል ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በተያያዘ ዜና መሰከረም 16 ቀን 2014ዓ/ም በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ድረስ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁትን መንገዶች ዝግ መሆናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡ በዚህም መሰረትከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባ፤ ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ፤ ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት፤ ከፒያሣ አካባቢ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቸርችር ጎዳና ቴዎድሮስ አደባባይ፤ ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ፤ ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ፤ ከሲኒማ ራስ በጎላ ሚካኤል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን የኋላ በር መግቢያ፤ ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ፤ ከባሻ ወልዴ ችሎት በኦርማ ጋራዥ ወደፉል ውኋ መስኪድ የሚወስደው መንገድ ንግድ ማተሚያ ቤት፤ ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የመወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ፤ ከጦር ኃይሎች፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ እና ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ መንገዱ የሚዘጋ መሆኑን ገልጿል፡፡ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ሲሆን፣ ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እና ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሴፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገዱ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም ከሳሪስ እና ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ከባድ ተሸከርካሪዎች መንገዱ አጎና ሲኒማ ጋር የሚዘጋ ይሆናል፡፡በመሆኑም ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን ማስተላለፉን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ካርቱም — Update 🌾 ካርቱም ጭንቅ ጥብብ ብሏታል!! ሁሉም የሀገር ውስጥና የውጭ በረራዎች ተቋርጠዋል!! በመንግስት ተቋማት ዙሪያ ከፍተኛ ተኩስ እየተሰማ ነው!! መፈንቅለ መንግሥቱን የመሩት የውጭ ሃይሎች መሆናቸው ውስጥ ለውስጥ እየተራገበ ሲሆን ሱዳናዊያን ወጣቶች የካርቱምን መንገዶች ሊያጥለቀልቁ በማኀበራዊ ሚዲያ እየተጠራሩ ነው!! 👊 ኢትዮጵያን የነካ የለውም በረካ‼

በሱዳን የተደረገው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አልተሳካም ሲል የመንግስት ቴሌቪዢን በዛሬው ዕለት መዘገቡ ተነግሯል። መንግሥት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራውን ለመቆጣጠር እርምጃዎች እየወሰደ እንደሚገኝ መግለፁ ተዘግቧል። በመፈንቅለ መንግስቱ በዐባይ ወንዝ ማዶ በኦምዱርማን የሚገኘውን የመንግሥት ሬዲዮን ጣቢያን የመቆጣጠር ሙከራ እንደነበር ነው የተሰማው።

ደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ከአብዬ ግዛት መውጣታቸውን እንደማትቀበል አስታወቀች። የደቡብ ሱዳን መንግስት በአብዬ ግዛት በሰላም ማስከበር ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲወጡ ሱዳን ያቀረበችውን ጥያቄ ውድቅ አደረጓል።የተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ረዳት ሚኒስትር ዣን ፒዬር ላክሮይክስ ባለፈው ሳምንት ደቡብ ሱዳንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ መግለጫ ሰተዋል። የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ልዑክ እና በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም በፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ፣በአብዬ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል እንደ ሱዳን ፖስት ዘገባ።የደቡብ ሱዳን መንግስት መግለጫው በተጨማሪ በአወዛጋቢው ክልል ውስጥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይልን ለመተካት ሱዳን ያቀረበችውን ጥሪ ውድቅ ማድረጎን አስታውቋል። “በዚህ ሁኔታ የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ይህ ኃይሉ የተሰጠውን ተልዕኮ በሙያ እና በገለልተኝነት እያከናወነ ባለበት ወቅት የኢትዮጵያ ጦር እንዲወጣ በሚደረገው ጥሪ እንደማይስማማ ለመግለፅ እንወዳለን” ብሏል መግለጫው።የደቡብ ሱዳን መንግሥት የአብዬን ግዛት ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝ ፓለቲካዊ ሂደት እንዲጀመር ጥሪውን በድጋሚ ያቀርባል ሲል አክሏል።

በአገር መከላከያ ሚኒስቴር በዕጩ መኮንንነት ለሚማሩ ተመልማዮች የወጣ የቅጥር ማስታወቂያ የአገር መከላከያ ሠራዊት የተጣለበትን አገርና ህዝብን የመጠበቅ ተልዕኮውን በአኩሪ ገድል እየፈፀመ የሚገኝ ጀግና ሠራዊት መሆኑን በተግባር እያስመሰከረ ይገኛል። ይህንኑ ህዝባዊ ሰራዊት ለማጠናከር የዘመኑን ወታደራዊ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለመጠቀም የሚያሰችል የሁሉንም ብሄሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ ወጣቶችን በመመልመል ተኪ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮችን ለማፍራት እንዲያስችል ብቃት ያላቸው ወጣቶች በውትድርና ሙያ ዕጩ መኮንንነት በኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ አስመርቆ መመደብ ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የመመልመያ መስፈርቶች መሰረት በፍቃደኝነት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ይገልፃል። 1- የምልመላ መስፈርት ~በህዝቦች ሉአላዊነትና አንድነት የሚያምኑ እና በፅናት ለማገልገል ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑ። ~ ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅቶች ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ። ~ ከአሁን በፊት የመከላከያ ፣ የፖሊስ እና የክልል ልዩ ሃይል አባል ያልነበሩ። ~በወንጀል ይሁን በፍታብሄር ተከሶ የፍርድ ቤት ክርክር የሌለባቸው። ~ ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ፡፡ ~ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውና ከተለያዩ አጉል ሱሶች የራቁ። ~ትዳር ያልመሰረቱና ልጅ ያልወለዱ፤ ~ስልጠና ካጠናቀቁ በኋላ ለ10 ዓመት ለማገልገል የውል ግዴታ የሚገቡ ፤ ~ ከቀበሌ መስተዳድርና ከፖሊስ የፅሁፍ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ። 2- የትምህርት መስፈርት ~ 12ኛ ክፍል (የመሰናዶ ትምህርት) ያጠናቀቁ በወቅቱ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መግቢያ ነጥብ ያላቸው። ~የድግሪ ምሩቅ ለሆኑ እውቅና ካለው ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የተመረቁ። ~የዲፕሎማ ምሩቅ ከሆኑ Level – 4 (Advanced Diploma) ሆኖ እውቅና ካለው የትምህርት ተቋም የ”Level – 3 ‘ ያለፉ። ~ የመግቢያ ፈተና ያለፉ ፣ የሳይኮሜትሪክ እና የመስክ ፈተና ወሰደው መኮንን ለመሆን የሚያስችል ነጥብ ማሟላት የሚችሉ። 3- ሁሉም ተመዝጋቢዎች ~ወደ ወታደራዊ አካዳሚ ሲገቡ የ 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ፣ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መልቀቂያ ሰርተፍኬት ፣ የዲግሪ ተመራቂዎች ኦሪጅናል ቴምፖራሪና ስቱደንት ኮፒ (Student copy) እና የዲፕሎማ ተመራቂዎች የትምህርት ማሰረጃዎችና ሰርተፍኬት ይዞ መገኘት አለባቸው። 4- የምልመላ ቦታና ጊዜ ~ለአዲስ አበባ እና አከባቢው ተመዝጋቢዎች በመከላከያ መኮንኖች ክበብ ፊት ለፊት ባለው ሚሊተሪ ፖለስ በር በመግባት የመረጃና ማስረጃ ቢሮ አካባቢ ሲሆን፣ ~ ለክልል ተመዝጋቢዎች በየአካባቢያችሁ ባሉ የቀበሌ ፣ የወረዳ አስተዳደርና የፀጥታ ወይም ሚሊሻ ፅ/ቤት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፣ ~የምዝገባ ጊዜው ከ መስከረም 1 ቀን 2014 ዓ/ም እስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ይሆናል ፡፡ በሁሉም የምልመላ ጣቢያዎች ዝርዝር የመመልመያ መስፈርቶች ተለጥፎ የሚገኙ መሆኑን እንገልፃለን። የአገር መከላከያ ሚኒስቴር

ብዙ መኪና ይፈለጋል። … ፈላጊው UN ነው። የሚፈልገውም ወደ ትግራይ ክልል የእርዳታ እህል የሚያደርስበት የመኪና እጥረት ስለገጠመው እንደሆነ ገልጿል። የመኪና እጥረቱም ዋነኛ ምክንያት "… የእርዳታ እህል ጭነው ወደ መቀሌ የሚገቡ ሹፌሮችም ሆኑ መኪኖች ስለማይመለሱ እንደሆነ ነው ፈላጊው UN ያስረዳው። ቤርሙዳ … … ካለፈው ወር ከሐምሌ 12 ጀምሮ ወደ ትግራይ ክፍለ ሃገር ከገቡ 466 የጭነት መኪኖች መካከል በተአምር የተመለሱት 38 ብቻ ሲሆኑ የሰብዓዊ እርዳታ ጭነው ወደ ትግራይ ከተጓዙ የከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች መካከል እስከ አሁን 428 ተሽከርካሪዎች ከክልሉ ሳይወጡ በዚያው እምጷ ቀሊጦ ብለው መቅረታቸውን ትናንት UN ዘግይቶ ቢልለኔ ስዩም ቀደም ብለው ተመካክረው ጉዳዩን ይፋ አድርገዋል። … እናም አለ ጋሽ ተመድ… እናም እባካችሁ… እባካችሁ… እባካችሁ… "በትግራይ ለሚኖሩ በራብ፣ በጠኔ፣ በጥም ለተጎዱ ሰዎች የሕይወት አድን እርዳታ ለማድረስ ቁጥሩ እጅግ ብዙ የሆነ የጭነት መኪናዎች ያስፈልጉናል። ስለዚህ እባካችሁ መኪና ያላችሁ… ብሏል። … UN መኪኖቹን ከመሀል ሀገር ካሉ ባለ ሀብቶችና ግለሰቦች ወይም ከመንግሥት ድርጅቶችና በተመሳሳይ የእርዳታ ሥራ ላይ ከተሰማሩ አካላት ላይ ነው ተኮናትሮ ነበር እርዳታውን ወደ መቀሌ እንዲያመላልሱለት ያደርግ የነበረው። መኪኖቹ ከጅቡቲና ከሰመራ የእርዳታውን እህል ጭነው ወደ ትግራይ ይገባሉ። ትግራይ ከገቡ በኋላ የእርዳታ እህሉን አራግፈው ሲያበቁ እንደገና ሌላ ተጨማሪ የእርዳታ እህል ለማምጣት መመለስ ሲገባቸው ነገር ግን እኒያኑ መኪኖች የትግሬ ጦር እንዲረከባቸው ይደረግና በቀጥታ ለህወሓት ሠራዊት ማመላለሻነትና በወረራ ወደያዙአቸው የዐማራ ክልል በማሰማራት ከዐማራ ላይ የዘረፈውን ሁሉ ጭኖ ወደ መቀሌ ማመላለሻ ያደርጉታል። UN ነዳጅም አብሮ ስለሚልክ የነዳጅ ችግርም የለባቸውም። ጎበዝ በደንብ እኮ ነው የሚናበቡት። … ይሄ አስፀያፊ ድርጊት ነው። ህወሓት ለተራበው ህዝብ፣ ቆሜለታለው ለምትለው ህዝብ እንኳ የማትራራ ፍጥረት ናት። ምዕራባውያኑ የስለት ልጃቸው ስለሆነች ምንም ብታጠፋ አይቆጧትም። የሰሜን ዕዝን ሠራዊት ስትረሽን ለምን አላሏትም። አልተቆጧትም። ተኩስ አቁሙን ጥሳ ዐማራና አፋርን ስትወር፣ ስትዘርፍ፣ ስትገድል ትንፍሽ አላሉም። አሁን ደግሞ ይሄን አስፀያፊ ድርጊት ስትፈጽም እያዩ ጭራሽ " ተጨማሪ መኪና እንፈልጋለን አሉ እንጂ መኪኖቹን መልሺ ለማለት እንኳን አልደፍሩም። … ትግራይ ተራበ ሲል የሚውለው ወትዋች የሂዊ ካድሬ ሁላም ስለዚህ የሂዊ ሌብነት አንዳች አይተነፍስም። ዝም፣ ጭጭ፣ ነው የሚለው። ህወሓት የምትፈልገው ብዙ ሚልዮን ትግሬዎች በራብ፣ በችጋርና፣ በጥም ሞተው በሞታቸው መነገድ ነው። በሞታቸው ቦለጢቃ መሥራት ነው። … የሚገርመው ነገር ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚሠራው የድል ዜና ላይ የሚነገረው ቃል ነው። " ከዐማራ ክልል በብዙ ቢልየን የሚገመት ንብረት ዘርፎ ወደ ትግራይ በመመለስ ላይ የነበረ የወራሪው ትግሬን ጦር ከነጫነው ንብረቱ የአየር ኃይላችን አውድሞታል።" ይልልሃል። የወደመው ንብረት የዐማራ ነው። ተሽከርካሪዎቹም የኢትዮጵያውያን ናቸው። ማነው የሚጎዳው? ለማንኛውም ትግራይ ከገባ የማይመለስ መኪና ማከራየት የምትፈልጉና ከባድ መኪኖች ያላችሁ ዜጎች ምላሻችሁን UN በፍጥነት ይጠብቃል።

photo content

photo content
+2