en
Feedback
Prosperity Party Dire Dawa - ብልፅግና

Prosperity Party Dire Dawa - ብልፅግና

Open in Telegram

የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ቴሌግራም ገፅ ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን ይከታተሉ!

Show more
407
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-130 days
Posts Archive
"የኃሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና'' የአረንጓዴ አሻራ እምርታችን ለሁለንተናዊ ብልፅግናችን! አምስት የስኬት አመታት #DIREPROSPERITY
"የኃሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና'' የአረንጓዴ አሻራ እምርታችን ለሁለንተናዊ ብልፅግናችን! አምስት የስኬት አመታት #DIREPROSPERITY

ማህበረሰብ ተኮር የልማት ስራዎች ላይ በመረባረብ ሀገራዊ ብልፅግናችንን ዕውን እናደርጋለን። #DIREPROSPERITY | ህዳር 15/ 2017 በድሬዳዋ አስተዳደር የ2017 የምርት ማሰባሰብ ንቅናቄ በቢዮ አዋሌ ክላስተር ለገቢራ ገጠር ቀበሌ ተካሄደ። ሰብል በደቦ የማሰባሰብ ስራው የተከናወነው ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ የደረሰውን ሰብል እንዳያበላሽ አርሶ አደሩን ለማገዝ ነው። አርሶ አደሩን በደቦ የማገዝ ስራው መከናወኑ መሬቱን ለቀጣይ ስራ ለማዘጋጀት አንዲሁም የህብረተሰቡን የመተጋገዝ ዕሴት ለማጠናከር ይጠቅማል ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር መርሀግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት ተናግረዋል። የሀገር ዳር ድንበር ከማስጠበቅ ባሻገር ማህበረሰብን በሚጠቅሙ መሰል በጎ ተግባራት ላይ መሳተፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በሰብል ማሰባሰብ ዘመቻው ላይ የተሳተፉት የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ገልፀዋል። በማሽላ አጨዳው ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፓሊስና የድሬዳዋ ፓሊስ አባላት ተሳትፈዋል። #DIREPROSPERITY سوف نحقق ازدهارنا الوطني من خلال العمل على أعمال التنمية الموجهة نحو المجتمع. #دري_الإزدهار | 24 نوفمبر 2024 نفذت إدارة دريدوا حملة تعبئة الحصاد لعام 2017 في مجموعة بيو أوالي في منطقة لغابرا الريفية. تم تنفيذ أعمال جمع المحاصيل في ديبو لمساعدة المزارعين على منع الأمطار غير الموسمية من إتلاف المحاصيل. قال عمدة إدارة دريدوا، السيد خضير جوهر، عندما أطلق البرنامج، إن العمل على مساعدة المزارعين في ديبو مفيد لإعداد الأرض لمزيد من العمل وأيضًا لتعزيز قيمة التعاون لدى المجتمع. وإلى جانب حماية حدود البلاد، أكد أفراد قوات الدفاع الوطني الذين شاركوا في حملة جمع المحاصيل أنهم سيواصلون تعزيز مشاركتهم في الأنشطة الجيدة التي تعود بالنفع على المجتمع. شارك في حصاد الذرة الرفيعة العمدة إدارة دريدوا السيد خضير جوهر ورئيس مكتب حزب الازدهار دريدوا السيد إبراهيم يوسف والقيادات العليا والمتوسطة في الإدارة وأعضاء جيش الدفاع الوطني والشرطة الفيدرالية وشرطة دريدوا. #دري_الإزدهار

ከድህነት አዙሪት ወደ ብልጽግና ተምሳሌት! አምስት የስኬት አመታት #DIREPROSPERITY
ከድህነት አዙሪት ወደ ብልጽግና ተምሳሌት! አምስት የስኬት አመታት #DIREPROSPERITY

የብልጽግና ፓርቲ የአምስተኛ አመት ምስረታ በዓል አከባበር እንደቀጠለ ነው ከታችኘው የፓርቲ መዋቅር ጀምሮ እስከ ፌደራል ተቀማት ድረስ በተለያዩ ሁነቶቸ እየተከበረ ነው፡፡ በደም ልገሳ ፣ በከተማ ጽዳት ፣ የባለፉት የፓርቲው ስኬቶችን አውደርይ በማዘጋጀትና ለሕዝብ በማስተዋወቅ እንዲሁም የበጎ አድራጎት ማከናወን ተጠቃሾ ናቸው፡፡ በዛሬው ዕለት በአድዋ ሙዚየም  በተከበረው በብልጽግና ፓርቲ የፌደል ተቋማት አደረጃጀት አምስተኛ ዓመት የማጠቃለያ መርሃ ግብር የፓናል ውይይት ተካሂዷል፡፡ በርሃ ግብሩ በብልጽግና ፓርቲ  የሕዝብና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር ዶ/ር ቢቂላ ሂሪሳ መድረክ መሪነት የፓርቲ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ባለፉት አምስት ዓመታት ፓርቲ ያመዘገባቸውን ስኬቶች አንስተዋል፡፡ በውይይቱ ተሳታፊ የነበሩት የውጭ ገዳይ ሚኒስቴር ዴዔታ ምስጋኑ አረጋ ጎረቤትን ያስቀደመ እንዲሁም የአገራችን ብሔራዊ ጥቅም ያቀደመ ጠንካራ የዲፕማሲ ስራዎች በመሰራታቸው አገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅናና ሽማት ያገኘችነት መሆኑን አንስተዋል፡፡ በብልጽግና ፓርቲ የፌደራል ተማት አደረጃጀት የፖለቲካ ኮሚቴ ሰብሳቢና በሕዝብ ተወካዮች የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስተር ክቡር ዶ/ር ተስፋዬ በልጂጌ በኩላቸው የኢትዮጵያን ስብራቶችን በመጠገን ቅቡልነት ያለው ጠንካራ አገረ መንግስት ለመገንባት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አገራችን ባካሄደችው የአገር በቀል የኢኮኖሚክ ሪፎርም የአገር ውስጥ ምርትና ምርታማነት በማሳደግ እንዲሁም ዝቅተኛ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በተለያዩ አማራጮች በመደገፍ የኑሮ ጫና ለመቀነስ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ የገንዝብ ሚኒስትር ክበር አቶ አህመድ ሺዴ ናቸው፡፡ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በፓናሉ እንደገለጹት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስና እንደገና መስራት ፣ የተማሪዎች የምገባ ስርዓት መዘርጋት የተቻለበት እንዲሁም በኮሪደር ልማት ሰው ተኮር የልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀው ፓርቲው ቃል በተግባር የማረጋገጥና የአገራችን ብልጽግና በአጭር ግዜ ውስጥ እውን ለማድረግ በተግባር እያሳየ ያለ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ #DIREPROSPERITY

የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ “የሀሳብ ልዕልና ፤ ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደ የፓናል ውይይት በፎቶ ስላይድ

የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ “የሀሳብ ልዕልና ፤ ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ በደመቀ ሁኔታ የፓናል ውይይት ተካሄደ። #DIREPROSPERITY | ህዳር 14/ 2017 የብልፅግና ፓርቲ ራዕይ በ2023 ኢትዮጵያን በፖለቲካ ከአፍሪካ ተምሳሌት የሆነች ሀገር ማድረግ፣ በኢኮኖሚ ከአፍሪካ ካደጉ አምስት ጠንካራ ሀገራት ተርታ ማሰለፍ፣ በውጭ ግንኙነት ሀገራዊ ጥቅምን፣ ክብርና ሉዓላዊነትን ያማከለ፣ በቀጠናው ተደማጭነቱና ተፅዕኖ ፈጣሪነቱ የጎላ ግንኙነት በመፍጠር እንዲሁም በ2040 ኢትዮጵያን ከዓለም በኢኮኖሚ የበለፀጉ አስራ አንድ ሀገሮች ተርታ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ መሆኑን በመድረኩ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የገለፁት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ናቸው። በድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ አካታችና አቃፊ በመሆኑ የነዋሪውን የቆየ አብሮነት፣ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ዕሴቶችን ይበልጥ የሚያጠናክሩ ትርክቶችን በማስረፅ ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና ሊያሻገሩ የሚችሉ የተለያዩ ለውጦችን ባለፉት አምስት ዓመታት አከናውኗል ሲሉ ክቡር ከንቲባው አክለው ተናግረዋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶች የብልፅግና ፓርቲ እሳቤ ውጤቶች መሆናቸውን የገለፁት አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ ናቸው። ጠንካራ ተቋማዊ ሪፎርምና ግንባታ፣ ዘላቂ ሠላም፣ ጠንካራ ኢኮኖሚ፣ አምራች ኢንዱስትሪ፣ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ማሻሻልና ምገባ መርሃ-ግብር፣ ጤና፣ ግብርና፣ የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የስራ ዕድል ፈጠራ፤ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና የኑሮ ውድነት ችግርን መቀነስ ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት የነዋሪውን ጥያቄ መነሻ በማድረግ በተሰሩ ስራዎች የተገኙ ድሎች መካከል ዋነኞቹ ናቸው ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በፓናል ውይይቱ መክፈቻ ንግግራቸው ተናግረዋል። በፓናል ውይይቱ ላይ “የብልፅግና ፓርቲ የአምስት ዓመታት ጉዞ'' በሚል ፅሑፍ የቀረበ ሲሆን በቀጣይ የተገኙ ድሎችን በበለጠ ስኬት ለማስቀጠል ከፍተኛ አቅም ተፈጥሮበታል። በፓናል ውይይቱ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ፣ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን፣ የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ከሪማ አሊ፣ የብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ዶ/ር ሠማ ጥሩነህ፣ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ምክትልና የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻኪር አህመድ፣ የአስተዳደሩ ካቢኔ አባላትና ሌሎች የፓርቲና የአስተዳደሩ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል። #DIREPROSPERITY بمناسبة الذكرى الخامسة لتأسيس حزب الازدهار وعقدت حلقة نقاش تحت شعار "سيادة الأفكار من أجل الازدهار المتكامل". #دري_الإزدهار | 23 نوفمبر 2024 وفي كلمته الافتتاحية على المنصة كان السيد خضير جوهر، عمدة إدارة دريدوا المحترم تتمثل رؤية حزب الازدهار في جعل إثيوبيا دولة نموذجية في أفريقيا سياسيا بحلول عام 2023 (حسب التقويم المحلي )، وأن تصنف ضمن أقوى خمس دول في أفريقيا اقتصاديا، والتركيز على المصلحة الوطنية والشرف والسيادة في العلاقات الخارجية، وإقامة علاقات متميزة بنفوذها. ونفوذها في المنطقة، وجعل إثيوبيا واحدة من أكثر إحدى عشرة دولة ازدهارًا اقتصاديًا في العالم بحلول عام 2040 (حسب التقويم المحلي). وأضاف العمدة المحترم في السنوات الخمس الماضية أن حزب الازدهار هو جزء من إدارة دريدوا وقد أجرى العديد من التغييرات التي يمكن أن تؤدي إلى الازدهار المتكامل من خلال غرس الرواية التي تعزز القيم القديمة للتضامن الأخوة في المنطقة المقيمين. صرح السيد إبراهيم يوسف رئيس مكتب فرع دريدوا لحزب الازدهار أن الإنجازات التي تم تسجيلها في المجالات السياسية والاقتصادية والاجتماعية خلال السنوات الخمس الماضية هي نتيجة لأفكار حزب الازدهار. قال إبراهيم يوسف، رئيس مكتب فرع حزب الازدهار في دريدوا، في كلمته الافتتاحية إن إصلاح وبناء مؤسسي قوي، سلام مستدام، اقتصاد قوي، صناعة إنتاجية، تحسين مستوى المدارس وبرامج التغذية، الصحة، الزراعة، البصمة الخضراء، إرث الفوءاد، خلق فرص العمل؛ ، ضمان الأمن الغذائي وخفض مشكلة تكلفة المعيشة هما الإنجازان الرئيسيان للأعمال التي تم تنفيذها بناءً على مطالب السكان في السنوات الخمس الأخيرة من التغيير في حلقة المناقشة. وتم في الحلقة النقاشية تم تقديم وثيقة بعنوان "الرحلة الخمسة سنوات لحزب الازدهار"، ولها إمكانات كبيرة لمواصلة المكاسب التي تحقق في المستقبل. وفي حلقة النقاش، حضر معالي عمدة إدارة دريدوا السيد خضير جوهر، والسيد إبراهيم يوسف رئيس مكتب فرع دريدوا لحزب الازدهار كنائب العمدة، السيدة فتحية عدن، رئيسة مجلس إدارة دريدوا، السيدة كريمة علي، نائب رئيس المجلس الإداري لدريداوا، مقر حزب الازدهار وحضر الحفل رئيس بناء القدرات السياسية الدكتور سما تيرونه، ونائب مكتب فرع دريدوا لحزب الازدهار ورئيس بناء القدرات السياسية السيد شاكر أحمد، وأعضاء مجلس الإداري وغيرهم من القادة العاليين والوسطيين للحزب والإدارة. #دري_الإزدهار

የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት በመካሄድ ላይ ነው። የፓናል ውይይቱ “የሀሳብ ልዕልና ፤ ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ነው። በድሬዳዋ አስተዳደር ከህዳር 01 ጀምሮ በተለያዩ ኩነቶች ሲከበር የቆየው የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በዛሬው ዕለት በሚካሄደው የፓናል ውይይት ይጠቃለላል። #DIREPROSPERITY تعقد الان حلقة نقاشية بمناسبة الذكرى الخامسة لتأسيس حزب الازدهار. تجري الان حلقة النقاش بعنوان “سيادة الأفكار من اجل الازدهار متكامل"؛ من قبل إدارة دريدوا. وستختتم الذكرى الخامسة لحزب الازدهار، والتي احتفلت بها إدارة دريدوا منذ العاشر 10 من نوفمبر 2024، بحلقة النقاش التي ستعقد اليوم. #دري_الإزدهار

የብልፅግና ፓርቲ 5ተኛ ዓመት ምስረታ በዓል በድሬዳዋ አስተዳደር በክቡር ዶክተር አሊ ቢራ መታሰቢያ ፓርክ በባህል ፌስቲቫል ተከበረ። #DIREPROSPERITY | ህዳር 13/ 2017 ከህዳር 01 ጀምሮ በተለያዩ ኩነቶች በደመቀ ሁኔታ በመከበር ላይ የሚገኘው የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር በባህል ፌስቲቫል የተከበረ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅ/ፅ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻኪር አህመድ ፌስቲቫሉ በዋናነት የፓርቲውን ያለፉ 5 ዓመታት የሚዘክሩ ስኬትና ድሎችን ለማጉላት የተዘጋጀ ነው ሲሉ በፌስቲቫሉ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ተናግረዋል። የባህል ፌስቲቫሉ ከምሽቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በልዩ ልዩ ሙዚቃዊ ድራማዎች፣ ግጥም እንዲሁም ህብረ ብሄራዊ አንድነትን የሚገልፁ ውዝዋዜዎች፣ ጥዑመ ዜማዎችና ሰርከስ ቀርቦበታል። በፌስቲቫሉ ላይ የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻኪር አህመድ፣ የፓርቲው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ በአስተዳደሩ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣ የፓርቲው አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል። #DIREPROSPERITY