Best kerim
Open in Telegram
اهدنا الصراط المستقيم ، فلقد تعبنا من الطرق الملتوية #شمس التبريزي +251938704306
Show more2 408
Subscribers
+124 hours
+77 days
+2630 days
Posts Archive
2 408
መድሕ የመሻኢኾቻችን የአባቶቻችን ውርስ ነው። የ አሏህ እና የረሱለሏህን ፍቅር በልባችን እየዘራ ከሐበሾች ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ውድ ባህላችን ሆኖ ከመሻኢኾቻችን ዘመን አንስቶ ወደ’ኛ ደርሷል።
Huda production መድህ እና ሌሎች ኢስላማዊ የ ኪነ–ጥበብ ስራዎችን የሚሰራ ፕሮዳክሽን ነው። ዘመኑን በመጠነ፣በተጠና እና ምዘናዎችን ባሟላ መንገድ የተለያዩ ስራዎችን you tube ላይ ለታዳሚያን ማካፈል ጀምሯል።
ከስር የተቀመጠው የ huda production ይፋዊ ቻናል ነው። subscribe እያደረግን
ቤተሰብ እንሁን!
Link
https://youtube.com/@huda_production?si=9aRZx9XjRy_k-sAa
2 408
«የሌሊት ማብቂያ (የፈጅር) ነፋሻማ አየር ልትነግርህ የምትፈልገው ምስጢር አላት፤ ስለዚህ ተመልሰህ አትተኛ።» ሰይዲ ጃላሉዲን አል ሩሚ (ቀደሰላሁ ሲረሁ)
ከፈጅር (ለይል) መልስ ጸሐይ ብቅ እስከምትል ድረስ አትተኙ ይላሉ። በሰሞነኛ ሰአት አቆጣጠር እስከ 12:15 ድረስ ማለት ነው። አረፍ ማለት ግድ ከኾነም ከዚህ ሰአት በኋላ ቢሆን እርሱ ለአጭር ደቂቃዎች።
ማልዶ መንቀሳቀስ በረካ ነው፤ በረከቱ ለማንም የተሰጠ ነብያችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ለሕዝባቸው ኹሉ ይህን ሰአት እንዲባረክለት ለምነውለታል።
አላህ ይህን በረከት የማግኘትን ልምድ ይረዝቀን ♥
2 408
Repost from Best kerim
ተሰውፍን በአጭሩ!
ብዙዎች ስለተሰውፍ ምንንነት ይጠይቃሉ ሱፊስ ማን ነው? ብለው ይጠይቃሉ፡፡ ከባሕር ሥፋትና ጥልቀት የሚልቀውን ተሶውፍ በጥቂቱ ለመረዳትና በጉዞው ላይ ለመገኘት መሠረታዊ ተብለው የተቀመጡ ምልከታዎችን ማጤን ያስፈልጋል፡፡
ተሰውፍ የሚለው ቃል የመጣው "ሶፋእ" (ጥራት/ንጽህና) ከሚለው ቃል ሲሆን ትርጉሙም ከአላህ ምርጥ መልእክተኛ (ሙስጠፋ) ﷺ ጋር ልብን ማጥራት ማለት ነው። ዋነኛ ዓላማውም ልብን አላህን ከሚያስቆጡ ነገሮች ሁሉ ማጽዳት ነው።
የስሙ አመጣጥ አስመልክቶ አቡል ፈትህ አል-ቡስቲ የተባሉትን ምሁር ግጥም እንዲህ ይላል፦
تَنازَعَ الناسُ في الصوفيِّ واختَلَفوا .. قديماً وظَنّوهُ مُشتَقاً مِنَ الصوفِ
ولستُ أَمنَحُ هذا الاسمَ غيرَ فَتىً .. صَفا فَصوفيَ حتى سُمِّيَ الصوفي
የግጥሙን ይዘት ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ ይላል፡
ሰዎች ስለ ሱፊ ምንነት ተከራከሩ፣ ከሱፍ ጨርቅ የተወሰደ መስሏቸውም ተሳሳቱ።
እኔ ግን ይህን ስም የምሰጠው ልቡ ለጠራና (ሶፋእ) ለነጻ ሰው ብቻ ነው፣ ልቡ ስለጠራም "ሱፊ" ተባለ።
በፊቅህ ሕግጋት(ሸሪዓ) እና በተሰውፍ (መንፈሳዊነት) መካከል ያለው ግንኙነት
ፊቂህ (ሸሪዓ) እና መንፈስ (ተሰውፍ) መካከል መነጣጠል የማይችል ግንኙነት መኖሩንም በርካታ ዑለሞች ይናገራሉ ለዚህም በዋናነት ዝነኛ የኾነውን የኢማም ማሊክ ንግግርም ይጠቅሳሉ እንዲህ ይላሉ፡
‹‹ ሸሪዓን (ፊቂህን) ተምሮ ተሰውፍን (መንፈሳዊነትን) ያልተከተለ ሰው አመጸኛ (ፋሲቅ) ይሆናል፡፡ ተሰውፍን ተከትሎ ሸሪዓን (ፊቂህን) ያላስከተለ ሰው ደግሞ ውሸታም (ዘንደቃ) ይሆናል፡፡ ሁለቱን መሰበሰበ የቻለ ግን እውነተኛውን መንገድ(ሐቂቃ) አገኘ፡፡››
ምክንያቱም ዕውቀት ብቻውን ደረቅ መረጃ ነው። ተሰውፍ ግን "ኢህሳንን" (አላህን እንደምታየው ሆነህ መገዛትን) ያስተምራል። ተሰውፍ ከሌለ አንድ ሰው በዕውቀቱ ተጠቅሞ ለኃጢያት ሰበብ መፈለግና ህግጋትን ማጣመም ይጀምራል።
በሌላ በኩል የዲኑን ህግጋት (ፊቂህ) ሳያውቅ በመንፈሳዊ (በተሶውፍ) መንገድ የሚጓዝ ሰው፣ በአልረህማናዊ (ከአላህ በሆኑ) ስሜቶች እና በሸይጧናዊ ግፊቶች መካከል ያሉ የሚመጡ ነገሮችን (ዋሪዳን) መለየት አይችልም። እንደ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል አንዳንድ ሰው በህልሜ ታዘዝኩ እያለ ሸሪዓን የሚቃረን ስራ ሊሰራ ይችላል።
የውጭውን ህግ (ፊቂህ) እና የውስጡን መንፈሳዊ ጥራት (ተሶዉፍን) ያጣመረ ሰው ብርሃን ላይ ይሆናል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ሰይዲ ዐብዱልቃድር አልጂይላኒ (ቀደሰላሁ ሲረሁ) የገጠማቸውን ፈተና በተለያዩ መጽሐፋቸው ላይ አንስተውታል፡፡ ከላይ ባነሳነው መንገድ የተደራጀ ዕውቀት እንዴት ባለቤቱን እንደሚጠብቅ ለማሳየት የሰይዲ ዐብዱልቃድር ጂይላኒ (በ561 ሂጅራ ያለፉ) ታሪክ እንዲህ ሲል አውግቷል፦
ኢማም ዐብዱልቃዲር ጂይላኒ (ቁዲሰ ሲረሁ) ለብቻቸው አምልኮ ላይ ሳሉ፣ አንድ ትልቅ ብርሃን ታያቸው ከዚያም ቀጥሎ አንድ እንዲህ የሚል ድምጽ ሰሙ፡ ‹‹አንተ ዐብዱልቃድር ሆይ! እኔ ጌታህ ነኝ፣ ለሌሎች እርም ያደረግኩትን ላንተ ፈቅጄልሃለሁ፣ ግዴታዎችንም (ሶላት፣ ጾም...) ከአንተ ላይ አንስቻለሁ!..››
እርሳቸውም ወዲያውኑ "አንተ የተረገምክ ሰይጣን ሆይ! ጥፋ" አሉት። ብርሃኑ ወደ ጨለማ ተቀየረ፤ ሰይጣኑም እንዲህ አለ፦ "በዚህ ዘዴ ከዚህ በፊት 70 የሚሆኑ የአላህ ወዳጆችን (አውሊያዎችን) ከመንገዳቸው አስወጥቻለሁ። ዐብዱልቃድር ሆይ ዕውቀትህ አዳነህ!"
ኢማም ጂይላኒም (ቁዲሰ ሲረሁ) በትህትና እንዲህ አሉ፡ "አይደለም፣ በአላህ ችሮታና ዕውቀት ነው የዳንኩት" የዚህ ዋነኛ ምክንያቱን ስናጤን አላህ ጸያፍ ነገርን እንደማያዝ እና ግዴታዎችን ከነቢያት እንኳን እንዳላነሳ ስለሚያውቁና ስለተረዱ ነው፡፡ ፊቂህንና ተሶውፍን በማጣመር መረዳት ከየትኛውም ምድራዊ ኾነ እርኩስ መናፍስጥ ተንኮል እንድንጠበቅ ይረዳናል፡፡
በሸሪዓ እና በሐቂቃ መካከል ያለው ልዩነት
በሸሪዓ (ፊቂሀዊ ሕግጋት) እና ሐቂቃ (እውነት) መካከል ስላለው ልዩነት ኢማም አል-ቁሸይሪ እንዲህ አስረድተዋል፦
ሸሪዓ (ፊቂህ) ባሪያ የመሆን ግዴታን መወጣት ነው (ውዱእ ማድረግ፣ የሶላት እርከኖችን መጠበቅ፣ ወደ ቂብላ መዞር… ወዘተ)
ሐቂቃ (እውነት) የአላህን ጌትነት መመስከር ነው (በሶላት ውስጥ ልብ መገኘቱ፣ ትህትና እና እርግጠኝነት…) ይጠቀሳሉ፡፡
በሐቂቃ (በመንፈስ) ያልተደገፈ ሸሪዓ (ፊቂህ) ተቀባይነት የለውም፤ በሸሪዓ (በህግ) ያልተገደበ ሐቂቃ ደግሞ ውጤት የለውም (አይሳካም)።
ምሳሌ፦ ሶላት በስርዓቱ መስገድ "ሸሪዓ" ሲሆን፣ በሶላት ውስጥ መመስጥ (ኹሹዕ) ደግሞ "ሐቂቃ" ነው።
የአላህ ወዳጅነት (ዊላያ) የሚገኘው በብልሃት ሳይሆን አላህ ዘንድ በሚኖር ጥንቃቄ (ወረዕ) ነው፡፡ የአላህ ወዳጅነት የሚገኘው በሶላት ብዛት ብቻ ሳይሆን እርም የሆኑ ነገሮችን በመራቅ እንደሆነም መረዳት ያስፈልጋል፡፡
በአንድ ወቅት አንድ ሰው ነቢያችንን ﷺ ስለ ግዴታዎች ጠይቆ ከሰጡት ትዕዛዛት ውጭ "ከዚህ ምንንም አልጨምርም፣ ምንንም አልቀንስም፡፡" ያለውን ሰው ነቢዩ "የጀነት ሰውን ማየት የሚፈልግ ይህን ሰው ይይ" ማለታቸውን ማስታወስ እንችላለን፡፡
የአላህ መልእክተኛ ﷺ ለአቡ ሁረይራ እንዲህ ሲሉ መክረውታል፡ "እርም የሆኑ ነገሮችን ተጠንቀቅ፣ አላህን በማምለክ ከሰው ሁሉ በላይ ትሆናለህ።"
ጃዕፈሩ አስ-ሳዲቅ እንዲሁ እንዲህ ይላሉ፦ "አንድ ሳንቲም የምታክል የሀራም ገንዘብን መተው፣ አላህ ዘንድ 80 ጊዜ ከሚደረግ ሐጅ ይበልጣል።"
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እና የልጅ ልጃቸው ሐሰን ታሪክም እዚህ ጋር መነሳት ይችላል፡፡ ሐሰን ልጅ እያለ የሰደቃን ተምር ሊበላ ሲል ነቢያችን ﷺ ከአፋ አውጥተው "እኛ ሰደቃ አይፈቀድልንም" በማለት የሐላልን አስፈላጊነት አስተምረዋል።
የአላህ ወዳጅነትን (ዊላያን) ለመጎናጸፍ ዑለማዎች የሚመክሩትን አራት ተግባራዊ ነጥቦችን በመጥቀስ ጽሑፌን ላጠናቅ፡
ልብን ማጽዳት፦ ውስጣችንን ከምቀኝነት፣ ከይዩልኝ (ሪያእ) እና ከአላህ ውጭ በሆኑ ነገሮች ከመጠመድ ማጽዳት የመጀመሪያና የሁልጊዜ ትግላችን መኾን አለበት።
ዚክር ላይ መዘውተር፦ አላህን በብዛት ማውሳት ሌላኛው መንገድ ነው።
ሐላልን ብቻ ለመፈለግ መታገል፦ በምግብ፣ በንግድ እና በግንኙነቶች ሁሉ ሐላልን በጥብቅ መከተል።
መሠረታዊ አምልኮዎችን መጠበቅ፦ ግዴታዎችን (ፈርድ) እና የሱና ሶላቶችን አዘውትሮ ማከናወን እንዲሁ የሚመከር መንገድ ነው።
እነዚህን የተለያዩ ውብ ነገሮች ማጣመር የቻሉ ሸይኾችን በሚገባ መከተል ወደ አላህ መንገድ ለመድረስ ሁነኛው መንገድህ ነው። መለኪያህን ልታደርግ የሚገባውም የፊቂህና የተሰውፍ እሴቶችን በማየት እንጂ የተለያዩ ዓለማዊና ቁሳዊ አለያ ተዓምራትን በመጠበቅ ሊኾን አይገባም።
አላህን ይህን መንገድ በትዕግስት ከሚጓዙት ባሮቹ መካከል ያድርገን!
መንገዱ ላይ ላለፉት ኹሉ ምሕረትን ይለግስ!
#አልፋቲሓ
2 408
Repost from Best kerim
#ከተሪሞቹ_መንደር
ሐቢብ ዐብዱልቃድር (ቀደሰላሁ ሲረሁ) እንዲህ ይላሉ፡- [ « በሌሊት የኢማም አል-ሐዳድን ራቲብ (ዊርድ) የሚያደርግ ሰው አሁንም አለን??!! ምናልባት አንድ ወይም ሁለት ሰው ለብቻው ያደርገው ይሆናል...»
ሸይኽ ዐብደላህ ባሰውዳን (ቀደሳለሁ ሲረሁ) እንዲህ ብለዋል፡- « ይህ ራቲብ (ዚክር) በመካ እና በመዲና መስጂዶች (ሐረም) ውስጥ በአንድ ድምጽ ይባል ነበር። በሐድረሙት (የመን) የሚገኙ ቤቶችንም ስናልፍ፣ ከመግሪብ ወይም ከዒሻእ በኋላ የኢማም አል-ሐዳድ ራቲብ ድምፅ የማይሰማበት ቤት አልነበረም። እንዲሁም ከሱብሒ በኋላ “አል-ዊርድ አል-ለጢፍ” ይባል ነበር። አሁን ግን የሚያዘወትረው ሰው መኖሩን አላውቅም?!»
ሐቢብ ዐብዱልቃድር ንግግራቸውን በመቀጠል እንዲህ አሉ፡- « ምናልባት የሚያዘወትር ሰው ሊኖር ይችላል፣ ግን ለብቻው ነው የሚያነበው። ለምን ለሚስቱና ለልጆቹ አያስተምርም?! ለምንስ አብሯቸው አይቀራም?! ይህን ቢያደርጉ አላህ የሸይጣንን ክፋት፣ የሸይጣን ሰራዊትን ተንኮል፣ የጂንን ተንኮል፣ እንዲሁም በላእዎችንና አደጋዎችን ከእነርሱ ይከላከልላቸው ነበር።
★★★
ንጋት ከፈጅር በኋላ እንዲሁም አመሻሽ ጀምሮ ዊርደ ለጢፍ የተሰኘውን ዚክር ቤት ውስጥ በጋራ እና በግል ለመቅራት ብንጥር በጣም ጥቅም አለው። ከኢሻ በኋላ ወይም በፊት እንዲሁ ዊርድ ራቲብ ኢማም ሐዳድን ብንቀራ ተጠቃሚ እንሆናለን።
በነገራችን ላይ የኢማም ሐዳድ (ቁዲሰ ሲረሁ) በርካታ አሻራዎች ዛሬም ድረስ ሐረመይን ላይ ይገኛሉ። በተለይ መዲና የሰይዳችን ሑጅር ላይ የተጻፉ ግጥሞችን ልብ ብለው ከተመለከቷቸው የኢማም ሐዳድ (ቀደሰላሁ ሲረሁ) ናቸው። እነዚህ የየመን ዐሊሞች ለሙስሊሙ ዑማ ያበረከቱት ውለታ ብዙ ነው። ከሐገራችን ጋር የነበራቸውም ቁርኝት ልዩ ነበር። በርካቶቹ ነባር ዐሊሞቻቸው ስማቸው ጎን "ሐበሺይ" የሚለውን ቅጥያ ለማግኘትም ሐገራችን መጥተው የኖሩም እንደነበሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የእነዚህን ጠንካራ ሰንሰለት ያላቸውን ዐሊሞች በርካታ ዚክሮቻቸው ተሰብስቦ የሚገኝበት "ኹላሳ" የተሰኘው ኪታብ ከላይ ያነሳኋቸውን ዚክሮች ጨምሮ በርካታ የተደራጁ ዚክሮች ይገኙበታል። ያዘጋጁትም ሸይኽ ሐቢብ ዑመር ቢን ሐፊዝ (ሐፊዘሁላሁ ተዓላ) ናቸው።
የሸይኽ ዐዲል ሙሰላ ላይ በቋሚነት ከጠዋት እስከማታ መድረሳቸው ላይ የሚቀራ ሲኾን ማንም ሰው ቢለው ጥቅም የሚያገኝበት የኾነ የዚክርና አውራድ ዊርድ ይኖረዋል።
አላህ ከተጠቃሚዎች ያድርገን ♥
2 408
ስክሮል የምናደርገውን ነገር ለመቀነስ ከሚረዱ ነገሮች አንዱ ለይለን ወነሀራ ያሉ ዚክሮችን ማብዛት ነው። ከአምስት ወቅት ሰላቶች በኋላ ያሉ ዊርዶችህን ከጠበቅክ፣ የዕለት የቁርኣንና የሰለዋት ዊርድ ከጨመርክ ጥቂት ገጽ የንባብ ልማድ ከዳበርክ ኢንሻአላህ ስክሮል አይበዛም፣ ጉዳቱም እየቀነሰ ይሄዳል። ከዚህ ውጭ ያለ የሚበዛ ስክሮል የአዕምሮ ዐቅም ይሰልባል። በተለይ ለጎረምሳ ወጣቶች ነው ይህ ምክር ወሳኝ ነው። ጥሩ ኃይል ባላችሁ ጊዜ ጥሩ ንባብ አዳብሩበት።
ሐያ ሐያ ♥
2 408
«‘ደላኢለል ኸይራት’ በተሰኘው የሰለዋት ኪታብ ውስጥ ያሉትን ሰለዋቶች በጥልቀት አስተንትነህ ከተመለከትክ፣ ሰለዋቶቹ በሙሐመዳዊ ብርሃን ውስጥ ለረጅም ጊዜ ሲገለበጥ የኖሩ፤ የአላህ መልእክተኛን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደሚወድ ንጹሕ ልብ የፈሰሱ መንፈሳዊ ስጦታዎች (ፈይዶች) መሆናቸውን በእርግጠኝነት ትረዳለህ።»
ሰይዲ ፈውዝ ኮናቲ (ማላዊ ሸይኽ)
የሰለዋትን ፍቅር ከሚጨምሩ ዕለታዊ የሰለዋት ዊርዶች መካከል ዝነኛው የኢማም ጀዙል የሰለዋት ስብስቦች "ደላኢለል ኸይራት" ይሰኛል። እኛም ሐገር ያሉ ቀደምት መሻኢኾች ከእነዚህ የሰለዋት አደራደር ጋር የሚመሳሰል እጅግ ውብ የተባሉ ስንኞችን የያዙበት የሰለዋት ኪታቦች አሉን። ከእነርሱም መካከል በቅርብ ጊዜ አባባ ሾንኬ (ቁዲሰ ሲረሁ) ያዘጋጁትን "ሰለዋት አሽሻፊያ" የተሰኘውን ዕለታዊ የሰለዋት ዊርድ አይቻለሁ።
አላህ መሰል የሰለዋት ዊርዶችን ያግራልና 🤲
#መውሊድ
2 408
#የመውሊድ_በረከት ከአንጋፋ የታሪክ ድርሳናት
በጥንት ዘመን በበስራ ከተማ ይኖር የነበረ አንድ አይሁዳዊ ነበረ። ይህ አይሁዳዊ አንድ ሙስሊም ጎረቤት ነበረው። ሙስሊሙ ጎረቤቱ በየዓመቱ የረቢዒል አወል ወር ሲመጣ የመውሊድን በዓል በደመቀ ሁኔታ ያከብር ነበር። ለዚህም ዝግጅት ብዙ ገንዘብ ያወጣና ድግስ ይደግስ ነበር።
ከብዙ ዓመታት በኋላ የአይሁዳዊው ሚስት ሙስሊሙ ጎረቤታቸው በየዓመቱ የሚያዘጋጁትን ይህን ዝግጅት ተመልክታ ባሏን ጠየቀችው። "ይህ ሙስሊም ጎረቤታችን በየዓመቱ በዚህ ወር እንዲህ በደመቀ ሁኔታ የሚያከብረውና ገንዘቡን የሚያወጣው ለምንድነው?!" ስትል ትጠይቃለች። አይሁዳዊውም ሲመልስ፦ "እነሱ 'ሙሐመድ' ብለው የሚጠሩት ነቢያቸው የተወለደበት ወር ስለኾነ ነው" ብሎ ይመልሳል።
የአይሁዳዊው ሚስት ይህን ስትሰማ በልቧ እንዲህ ስትል ተመኘች፦
«ጌታዬ ሆይ! ይህ ነቢይ እውነተኛ ከሆነና አንተ ዘንድ የተወደደ ከሆነ በሕልሜ አሳየኝ።» በዚያችው ሌሊት በሕልሟ ታላቅ ግርማ ሞገስ ያለውንና በብርሃን የተከበበን ሰው አየች። በዙሪያውም እንደ ሻማ የሚያበሩ ሰሐቦች (ባልደረቦችም) ነበሩ። "ይህ እንደ ጨረቃ የሚያበራው ሰው ማነው?" ብላ ጠየቀች። መልሱም "ይህማ ሐሺሚዩ ሙስጠፋ (የተመረጡት ነቢይ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ናቸው" የሚል ነበር።
በሕልሟ ወደ ረሱል (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ቀርባ "እኔ ማን ነኝና ነው የእርስዎን እይታ ለማግኘት የታደልኩት?!" ብላ ስትጠይቃቸው፣ እርሳቸውም "በአንቺ ላይ የሂዳያ (የመመሪያ) ብርሃን እንደሚመጣ ባላውቅ ኖሮ ጥሪሽን አልመልስም ነበር" አሏት።
ሴቲቱ በማግስቱ ጠዋት ስትነቃ ልቧ በእምነት ተሞልቶ ነበር። የሚገርመው ግን አይሁዳዊው ባለቤቷ በማለዳ ተነስቶ ለድግስ (መውሊድ) የሚሆን ስጋና ምግብ ሲያዘጋጅ አገኘችው። "ይህ ምንድነው? ለምንድነው ድግስ የምትደግሰው?" ብላ ስትጠይቀው፣ እርሱም "ትላንት ማታ በህልምሽ ያየሽውና ያመንሽበት ነቢይ ለእኔም በህልሜ መጥተው አብስረውኛል" በማለት እርሱም የእስልምናን እምነት እንደተቀበለ ነገራት።
በመጨረሻም ሁለቱም ባልና ሚስት እስልምናን ተቀብለው ለነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ክብር መውሊድን በጋራ አከበሩ።
***
መውሊድ ማለት የአላህ መልእክተኛን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መወለድ በማሰብ ሰዎችን በማብላት፣ ከወዳጆች ጋር ተሰባስቦ እርሳቸውን ማወደስና መማማር፣ ለተለያዩ ጉዳዮች ዱዓ መቀማመጥን ያጠቃለለ ታላቅ የሱፍዮች #እሴት ነው። ለተለያዩ ዘመን አመጣሽ ችግሮች ውስጣዊ ፈውስ የሚገኝበት ሥርዓት ነው። ከዚህ ሥርዓት ውስጥ አላህ አያስወጣን።
2 408
ከነቢያችን ﷺ ፍቅር ጥቂቱ
ባለቤታቸውን ሲጠሯት ምን ይሏታል መሰለህ፡
ያ ዓኢሽ፣ ያ ሑመይራእ፣ ያ ዓወይሽ ....
ሶሉ ዐለል ሐቢብ
ቀልበክ የጢብ ♥
