en
Feedback
Rohobot

Rohobot

Open in Telegram
602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
🟠 እምነታችሁን የሚያስጥሉ ነገሮች ደግሞ አሉ። ሁለት ናቸው። አንደኛው ሀጢያት ነው፥ ሁለተኛው አለመፀለይ ነው። ስለአለመፀለይ ባለፈው ፅሁፍ ስላነሳሁ ዛሬ ሀጢያት እንዴት እምነትን እንደሚያስጥል ልንገራችሁ። እኛ ሰው በሀጢያት የዘላለም ሀጢያቱን ሊያጣ አይችልም ስንል ሰው በተለያየ ድካም ውስጥ ሆኖ እንኳን እምነቱን መጠበቅና በእግዚአብሔር መደገፍ እስከቻለ ብቻ ነው። ምክንያቱም ሀጢያት ሲደጋገም የሚያመጣው ትልቅ አደጋ አለ። “ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤ ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፥ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፥ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ” (ዕብ 3፡12-13)። ሀጢያት በመጀመሪያዎቹ ጊዜዎች ያታልላል። በሀጢያት የሚፀና ሰው ግን ልቡ እልከኛ ይሆናል። ያ አልከኝነት በእርሱ ውስጥ ክፉና የማያምን ልብ ይፈጥራል። አስተዋላችሁት? አንድ እያለቀሰ ጌታን የተቀበለ ሰው በሀጢያት እየተታለለና በታለለው ሀጢያት እየፀና ሲሄድ ኢየሱስ አያስፈልገኝም፤ እግዚአብሔር የሚባል የለም ወደሚል ደረጃ ሊደርስ ይችላል። ይሄን መፅሀፍ ቅዱስ ይነግረናል። በሌላ ቃልም ላስረዳችሁ። በዕብራውያን ላይ ህሊናችን ከሞተ ስራ ወይም ከሀጢያት እንደነፃ ይናገራል። “የክርስቶስ ደም እንዴት ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ሥራ ሕሊናችሁን ያነጻ ይሆን?” (ዕብ 9፡14)። ከቃሉ እንደምንረዳው ይሄ ህሊና የተጎዳው በሀጢያት ነበር፤ ከዚያም በክርስቶስ ደም ነፃ። አንዳንድ ሰዎች ተመልሰው ይሄን ህሊና በሀጢያት ማቆሸሽ ይጀምራሉ። ይሄ ልክ ቆዳችሁን በጋለ ብረት እንደመተርኮስ ነው። ህሊና በሀጢያትና ባለመታዘዝ ይቆስላል። ቆዳችሁን ደጋግማችሁ በጋለ ብረት ከተረኮሳችሁት ቆዳችሁ ምንም አይነት ስሜት የማይሰማው ይሆናል። ልክ እንደዚህ ጳውሎስ እንዲህ አለ “በኋለኞች ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንትን ትምህርት እያደመጡ፥ ሃይማኖትን ይክዳሉ ይላል፤ በገዛ ሕሊናቸው እንደሚቃጠሉ ደንዝዘው…” (1ጢሞ 4፡1)። እነዚህ ሰዎች ሃይማኖትን የካዱት ህሊናቸው ተቃጥሎ፤ ከዚያም ደንዝዞ ነው። ሕሊና ሲጣል ደግሞ እምነት ይጠፋል። “እምነትና በጎ ሕሊና ይኑርህ፥ አንዳንዶች ሕሊናን ጥለው፥ መርከብ አለ መሪ እንደሚጠፋ፥ በእምነት ነገር ጠፍተዋልና” (1ጢሞ 1፡19)። አስተዋላችሁት? እነዚህ ሄሜኔዎስና እስክንድሮስ የተባሉ ሰዎች ህሊናዬን ጥዬ በሀጢያት እያቆሰልኩት ልኑር ብለው ሲያስቡ እምነታቸው ጠፋ። መርከብ አለመሪ እንደሚጠፋ ማለት መርከብ የሌለው መሪ ከድንጋይ ይጋጫል በማዕበሉና ንፋሱ ይገለበጣል፤ ወዳልፈለገው አቅጣጫ ይወሰዳል። ከዚያም ያ መርከብ ይጠፋል። እንዲሁ ደግሞ ህሊናቸውን ከሀጢያት የማይጠብቁ ሰዎች ድንገት የሆነ ቀን እምነታቸው ጠፍቶ፤ እግዚአብሔር ላይ ሲያፌዙ ታገኟቸዋላችሁ። ስለዚህ ሀጢያት በቀጥታ የዘላለም ሕይወትን ማጥፋት አይችልም። ከሰው ድካም ሁሉ የእግዚአብሔር ምህረትና ፀጋ ይበረታል። የዳንነውም በስራ ሳይሆን በፀጋ ነው። ነገር ግን ፀጋውና ምህረቱ የተሰጡን በፅድቅ ለመኖር እንጂ በሀጢያት በርትቶ ለመኖር አይደለም። ጨክኖ ክርስቶስን መከተልና ከድካም መውጣት ያስፈልጋል እንጂ በድካም ለሚኖሩ ሰዎች ሁልጊዜ በድካም ብትኖሩ ችግር የለውም የሚል የመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርትና እንደዛ የሚመስል ሃሳብ እንኳን የለም። ያ የሀጢያት ድካም ህሊናን ወደ ማደንዘዝና ወደ ልብ እልከኝነት መርቶ ጌታ ክርስቶስን እንዳያስክድ መጠንቀቅ እጅግ ወሳኝ ነው። 📱 የአምላኬ ቃል አፕሊኬሽንን በማውረድ የየእለት ዲቮሽኛል ታገኛላችሁ @Lovedface

#እርስ_በእርሳችሁ💙 1.እርስ በርሳችሁ አትጣሉ (ዘፍ 45÷24) 2.እርስ በርሳችሁ ሐሰት አትነጋገሩ (ዘሌ 19÷11) 3.እርስ በርሳችሁም ተስማሙ ማር (9÷50) 4.እርስ በርሳችሁ አታንጎራጉሩ (ዮሐ 6÷43) 5.እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ (ሮሜ 12÷10) 6.እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ (ሮሜ 12÷10) 7.እርስ በርሳችሁ በአንድ ሀሳብ ተስማሙ (ሮሜ 12÷16) 8.እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ (ሮሜ 13÷8) 9.እርስ በርሳችሁ በአንድ ሐሳብ መሆንን ይስጣችሁ (ሮሜ 15÷5-6) 10.እርስ በርሳችሁ ተቀባበሉ (ሮሜ 15÷7) 11.እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ (ሮሜ 16÷16) 12.እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ (1ኛ ቆሮ 11÷33) 13.እርስ በርሳችሁ እንደ አገልጋዮች ሁኑ (ገላ 5÷13) 14.እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ (ገላ 5÷15) 15.እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሱ (ኤፌ 4÷2) 16.እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ሩህሩሆች ሁኑ (ኤፌ 4÷32) 17. በመዝሙርና በመንፈሳዊ ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ (ኤፌ 5÷19) 18.እርስ በርሳችሁ ትዕግስትን አድርጉ (ቆላ 3÷13) 19.እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገስፁ (ቆላ3÷16) 20.እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተፅናኑ (1ኛ ተሰ 4÷18) 21.እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ (1ኛ ተሰ 5÷11) 22.እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ (1ኛ ተሰ5÷12-13) 23.እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ (1ኛ ተሰ 5÷15) 24.እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ (ዕብ 3÷13) 25.እርስ በርሳችሁ አትተማሙ (ያዕቆ 4÷11) 26.እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ (ያዕቆ 5÷16) 27.እርስ በርሳችሁ እንግድነትን ተቀባበሉ (1ኛ ጴጥ 4÷9) 28.እርስ በርሳችሁ አገልግሉ (1ኛ ጴጥ 4÷10) 29.እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትህትናን እንደ ልብስ ታጠቁ (1ኛ ጴጥ5÷5) ተቀላቀሉ አብሬን ወንጌል እንስራ

#እርስ_በእርሳችሁ💙 1.እርስ በርሳችሁ አትጣሉ (ዘፍ 45á24) 2.እርስ በርሳችሁ ሐሰት አትነጋገሩ (ዘሌ 19á11) 3.እርስ በርሳችሁም ተስማሙ ማር (9á50) 4.እርስ በርሳችሁ አታንጎራጉሩ (ዮሐ 6á43) 5.እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ (ሮሜ 12á10) 6.እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ (ሮሜ 12á10) 7.እርስ በርሳችሁ በአንድ ሀሳብ ተስማሙ (ሮሜ 12á16) 8.እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ (ሮሜ 13á8) 9.እርስ በርሳችሁ በአንድ ሐሳብ መሆንን ይስጣችሁ (ሮሜ 15á5-6) 10.እርስ በርሳችሁ ተቀባበሉ (ሮሜ 15á7) 11.እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ (ሮሜ 16á16) 12.እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ (1ኛ ቆሮ 11á33) 13.እርስ በርሳችሁ እንደ አገልጋዮች ሁኑ (ገላ 5á13) 14.እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ (ገላ 5á15) 15.እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሱ (ኤፌ 4á2) 16.እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ሩህሩሆች ሁኑ (ኤፌ 4á32) 17. በመዝሙርና በመንፈሳዊ ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ (ኤፌ 5á19) 18.እርስ በርሳችሁ ትዕግስትን አድርጉ (ቆላ 3á13) 19.እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገስፁ (ቆላ3á16) 20.እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተፅናኑ (1ኛ ተሰ 4á18) 21.እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ (1ኛ ተሰ 5á11) 22.እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ (1ኛ ተሰ5á12-13) 23.እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ (1ኛ ተሰ 5á15) 24.እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ (ዕብ 3á13) 25.እርስ በርሳችሁ አትተማሙ (ያዕቆ 4á11) 26.እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ (ያዕቆ 5á16) 27.እርስ በርሳችሁ እንግድነትን ተቀባበሉ (1ኛ ጴጥ 4á9) 28.እርስ በርሳችሁ አገልግሉ (1ኛ ጴጥ 4á10) 29.እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትህትናን እንደ ልብስ ታጠቁ (1ኛ ጴጥ5á5) ተቀላቀሉ አብሬን ወንጌል እንስራ http://t.me/Jesus_is_your_power      ✝ ይ🀄️ላ🀄️ሉን ❤   🎯     ♡         âă…¤    âŒ˛  ʲᵒᶦⁿ    ˡᶦᵏᵉ  ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ

Repost from N/a
+7
የዮሐንስ_ወንጌል_1ኛ2ኛና_3ኛ_መልዕክቱ_ማብራሪያ.pdf3.94 MB

የአምላኬ ቃል አፕሊኬሽን ቨርዥን 16.0 ፊቸሮች 🔸ሙሉ በሙሉ ያለኢንተርኔት የሚሰራ 🔸ሶስት (3) የመፅሀፍ ቅዱስ ትርጉሞች (አዲሱ መደበኛ ትርጉም፣ የ1962/1955 ትርጉም እና አምፕሊፋይድ ባይብል - እንግሊዝኛ) 🔸የየእለት ዲቮሽናል ከማንቂያ ጋር 🔸የጥናት ማኑዋሎች፣ ትምህርቶችና ጥቅሶች 🔸የቃላትና ጥቅስ መፈለጊያ 🔸ማስታወሻ መያዣ 7ስክሪን ላይ widget መለጠፍ ያስችላል 🔸ሌሎችም ብዙ ተግባሮች… በጣም እወዳችኋለሁ፡ የተወደደ ወንድማችሁ አማኑኤል ከበደ @Lovedface @emanuelkebede

+1
Resilience short Kibru .pdf15.31 MB

የጭፈራው ቤት ወደ ቸርች የተለወጠበት አስገራሚ ታሪክ ቦንኬ | the disco house turn to church #evangelist Reinhard Bonnke ለማድመጥ 👇👇👇👇 https://t.m
የጭፈራው ቤት ወደ ቸርች የተለወጠበት አስገራሚ ታሪክ ቦንኬ | the disco house turn to church #evangelist Reinhard Bonnke ለማድመጥ 👇👇👇👇 https://t.me/luciuschristian

ህልውና_ድንቅ_ዝማሬ_ከአዲስ_ኪዳን_ካህናት_ቤተክርስቲን_ኳየር_ጋር_Ethiopan_protestant_song.m4a7.05 MB

የአንጋፋው ወንጌላዊ ቢሊግርሃም የህይወት ታሪክ ክፍል 1 | Billy grahams biography part 1 great evangelist 👇👇 @luciusradioprogram
የአንጋፋው ወንጌላዊ ቢሊግርሃም የህይወት ታሪክ ክፍል 1 | Billy grahams biography part 1 great evangelist 👇👇 @luciusradioprogram

ወደ ራስ መመልከት (የማቴዎስ ወንጌል 7 ) ------------ 1-2፤ እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል። 3፤ በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም? 4፤ ወይም ወንድምህን፦ ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ። 5፤ አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ። @robhot @robhot

መቅረት አይታሰብም ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፈረንስ በባሌ ሮቤ ሙሉ ወንጌል ቁ1 ቤተክርስቲያን ግንቦት 15-17 https://t.me/robhot https://t.me/robhot
መቅረት አይታሰብም ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፈረንስ በባሌ ሮቤ ሙሉ ወንጌል ቁ1 ቤተክርስቲያን ግንቦት 15-17 https://t.me/robhot https://t.me/robhot

                   ቀላል አልነበረም          ዘማሪት ዊንታና ኑረዲን #ᴀᴍᴀᴢɪɴɢ #Gospel  #Songs   #share_ይደረግ 🙏 ⌚️5:12 ደቂቃ | 💾 °.°𝙢𝙗 #react አድርጉት (👍❤️🙏🔥😘💯😮 ) sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯 Facebook | Telegram | Youtube | Instagram | Imo | X(Twitter) | sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯 🎸🎺#ኢየሱስ እንደቃሉ ይመጣል🎺

victorious_spiritual_warfare_amharic.pdf

ዶ/ር ደረጀ ከበደ የዛሬ አምስት ዓመት "ዘኪዎስ እኔ ነኝ " በሚል ያጋራን መዝሙር ። 👇👇 @luciusradioprogram

ሪቫይቫል ምንድን ነው? ምንስ አይደለም? ከተስፋዬ ሮበሌ (1) "የሪቫይቫል" ቀዳማይ ግብ፣ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት እንጂ፣ ልሳንና ተኣምር አይደለም! የጸጋ ስጦታዎችም ቀዳማይ ግብ፣ እውነተኛ የሕይወት ተሐድሶና የሰዎች ድነት (ሰዎች ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸውና ጌታቸው መቀበላቸው) ነው! (2) "ሪቫይቫል" ነገን እውን ይሆናል ብለን የምንጠብቀው ክሥተት ሳይሆን፣ ዛሬን የምንተገብረውና የምንኖረው ክርስቲያናዊ ሕይወት ነው! እውነተኛ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት ባለበት ቦታ ሁሉ "ሪቫይቫል" አለ:: ይህ በሌለበትም ቦታ "ሪቫይቫል" የለም! (3) ዛሬ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በልዩ "በሪቫይቫል" ውስጥ ነች የሚሉ ሰዎችን አስተሳሰብ በጭራሽ አልጋራም:: ምክንያቴም አንደኛ እነርሱ "ሪቫይቫል" የሚሉትን ሁካታ መጽሐፍ ቅዱስ "ሪቫይቫል" ስለማይለው:: ሁለተኛ ከየትኛውም የታሪክ ጊዜ ይልቅ የክርስቶስ ወንጌል የተነቀፈበት ይህ ወቅት "ዘመነ ሪቫይቫል" ሊሆን አይችልም (በእኔ የድነት ዘመን ማለቴ ነው):: ሦስተኛ በርካታ ሰዎች ወደ ትክክል ወዳልሆነ ሃይማኖትና ወደተሳሳተ እምነት እየጎረፉ ያሉበት ወቅት በመሆኑ:: (4) "ሪቫይቫል" የመጻኢ ዘመን ክሥተት ነው ብለው ያስተማሩ ሰዎች ጎዳና ስተው ሕዝብን አስተው የተገኙት "ሪቫይቫል" የመጻኢ ዘመን ክሥተት ነው በሚለው ጠማማ አስተሳሰባቸው ምክንያት ነው! (5) ሐዲስ ኪዳን "በመጨረሻው ዘመን" መንፈሳዊ ተሐድሶ ይሆናል ሲለን፣ ዘመነ ሐዲስን በጥቅሉ የሚጠቅስ እንደ ሆነ ልብ ይሏል! ስለዚህ ነገ "ሪቫይቫል" ይሆናል የሚለው አስተሳሰብ ለአውሬውና ለአባይ ነባዮቹ እየዳረገን እንደሚገኝ ልብ ይሏል! (according to Historical Premillennialism OR Dispensationalism Theology ከሺህ ዓመቱ በፊት ያለው መጻኢ ዘመን ብሩህ አይደለም):: (6) እግዚአብሔር አምላክ ለኢትዮጵያውያን ብቻ አመጣለሁ ያለው "ሪቫይቫል" የለም! አምላክ ሕዝቦችን ሁሉ የሚያውቀው በክርስቶስ ኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ አማካይነት ብቻ ነው! በዚህ አግባብ ኢትዮጵያውያንና ኬኒያውያን ወይም የግብፅ ክርስቲያኖች አንዳችም ልዩነት የላቸውም:: ኢትዮጵያ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግማ መጠቀሷ ጥንታዊት አገር መሆኗን እንጂ በክርስቶስ ቤዞታዊ ሥራ ውስጥ ልዩ ቦታ እንዳላት ሊያሳይ አይችልም! "ለማርያም በዐሥራት የተሰጠች ነች" ወይም "ኢትዮጵያውያን ልዩና ምርጥ ሕዝቦች ናቸው" የሚለው አስተስሰብ መንፈሳዊ ዘረኝነት ነው (መንፈሳዊ "ወያኔነት" ነው)! በቅዱሳት መጻሕፍት ኢትዮጵያ የሚለው ስም ከተጠቀሰው በላይ ባቢሎን፣ ግብፅ፣ ሮም ፣ ግሪክ...የሚሉ ስሞች በስም ተጠቅሰዋል:: በብዛት መጠቀሳቸው በክርስቶስ ድነታዊ ውጀት ውስጥ ልዩ ጥቅም ወይም ቦታ እንዳላቸው በጭራሽ አያሳይም! ያለመጠቀስም ከድነት አያጎድልም—ለምሳሌ አገረ አሜሪካንን ይመለከቷል:: አልተጠቀሰችም ግን የጠንካራ ሚስዮናውያን እናት ምድር መሆኗን ማን ይክዳል? (ለበለጠ ማብራሪያ "አባይ ነባይ" መጽሐፍን ይመለከቷል):: (7) ሁሌም ተኣምራት ሰዎችን ወደ መንፈሳዊ ለውጥም ሆነ ብስለት ያደርሳሉ ብሎ ማሰብ ትክክል አይደለም:: ተኣምራት እውን ስለሆነ ብቻ ነፍሳት ዳኑ የዳኑትም ታነጹ ማለት አይቻልም:: ለምሳሌ ከግብፅ የወጣው የእስራኤል ሕዝብ በተኣምር ባሕር ሲከፈል ማየቱና ሰማያዊ መና መብላቱ የጥጃ ጣዖት ሠርቶ ከግብፅ ባርነት ዐርነት ያወጣኝ ይህ ጥጃ ነው ከማለት አላቀበውም:: "ከሙታን መኻል አንዱ ሄዶ ክርስቶስን ቢሰብክላቸው ቤተሰቦቼ ያምኑ ነበር" ያለውን ሰው፣ ስብከተ ወንጌልን የማያምን ሰው፣ ተኣምራትን ሊያምን እንደማይችል ወንጌል በግልጽ ነግሮታል:: ስለዚህ ተኣምራት ባለበት ቦታ ሁሉ የነፍሳት ድነትና የሕይወት ለውጥ አለ የሚለው አስተሳሰብ ትክክል አይደለም:: (8) "ሪቫይቫል" በአምላክ በጎ ፈቃድና እርሱን ከልብ በመሻት እውን የሚሆን እንጂ፣ በሰዎች ክህሎትና በግርግር የሚፈጠር አይደለም! ያልሆነን ሆነ ብሎ ማውራት የሐሰት ምስክሮች እንጂ የወጌል ዐርበኞች አያደርገንም:: (9) "ሪቫይቫል" በእግዚአብሐር መንፈስ ረዳኢነት እውን ክሥተት በመሆኑ ምክንያት፣ በመንፈስ ቅዱስ ነጂነት (አፊዎትነት) እውን የሆኑትን የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የሚያስወድደን እንጂ፣ እርሱን ጥለን ነባዮችን እንድናሳድድ የሚያደርገን አይደለም! እንግዲያው ቅዱሳት መጻሕፍትን ማጥናትና ማስጠናት "የአእምሮ ሰው" የሚያሰኝ "ሪቫይቫል" ጤናማ ሊሆን በጭራሽ አይችልም:: በውኑ አምላክ ያሰበልንን ነባዮች ያስቀሩብናልን? ያላሰበልንንስ እጅ ጠምዝዘው ሊሰጡን ይችላሉ? እንግዲያው መንቀዥቀዡ ከምን የመነጨ ይሆን? በአጭሩ እነዚህን ዘጠኝ ነጥቦች ያለማወቅና በዚህ እንጻር ያለመኖር:- (1) በአባይ ነባዮች ይስበላል! (2) ተኣምራት ናፋቂ ያደርጋል (3) ቅዱሳት መጻሕፍትን እያነበቡና እይተነተኑ ከመኖር ይልቅ በአባይ ነባዮች የውሸት ትንቢትና መገለጥ እንድንዳረግ ያደርጋል (4) መንፈሳዊ "ወያኔነት" (ዘረኝነት) እንዲጣባን ዕድል ይሰጣል:: ወዘተና ወዘተ ይህ እኔ ስለ "ሪቫይቫል" ያለኝ አንቀጸ ሃይማኖት ነው! ይህን ሐቅ እንደ አሸንክታብ ዐንገቴ ላይ አንጠልጥዬው እንደምኖር፣ እንደምሰብከው፣ እንደማስተምረው... ታቅፌው እንደምሞት ዓለም ይወቅልኝ! ሠናይ ውእቱ

2017 በእግዚአብሔር የምንሰራበት  አመት https://t.me/robhot https://t.me/robhot ♻️ sʜᴀʀᴇ ◈🈴 join

ታማኝ_ነው_ሔኖክ_አሰፋ_Tamang_new_New_gosple_song_Henok_Assefa_Official.m4a4.30 MB