en
Feedback
Rohobot

Rohobot

Open in Telegram
602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
Here is the e-book of እንደገና በህይወት መኖር /ሪቫይቫል ለኢትዮጵያ/ Read and share it to brothers and sisters “እግዚአብሔርም ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላልና፦ እኔን ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤”   — አሞጽ 5፥4 All the praise be to our great God

እምነት ቢሞላ ዕውቀት ቢከበኝ ልሳን መናገር ትንቢት ቢኖረኝ ሥጋዬን ለእሳት ብሰጥ ፈቅጄ ባልነፍግ ለድሆች ያለኝን ከእጄ ፍቅር የሌለው እልፍ ደግነት ጌታ የሌለበት መንፈሳዊነት ወዴት ወዴት ነው ይህ ከንቱ ጉዞ በሃሜት ታዝሎ በቂም ተይዞ ዞሮ ለማን ነው ይህ ጥል ግርግር አቤል ከቃየል የማይሆን አጥር ጐራ ለይቶ ይቅር ማድሩ የእውነት ፍቅር ይግባ መንደሩ የባላንጣችን ደስታው ይደፍርስ በፍቅር ዘምተን ሰላም እንመለስ የቁርሾን ዘመን ይበቃ ብለነው መዘናጠሉ ነው ወዲያ እንጣለው      ፍቅር ይበቀለው

🔥ርዕስ: "የተከፈተ ሰማይ/Sammii Banama"      በወንድም ኬፋ ፈዬ 🔥የተከፈተ ሰማይ ማለት የእግዚአብሔር ልዩና መለኮታዊ ጉብኝት ማለት ነው(God Special and divine Visitations)          ✍️ሕዝቅኤል 1:1-3 "በሠላሳኛው ዓመት በአራተኛው ወር ከወሩም በአምስተኛው ቀን በኮቦር ወንዝ በምርኮኞች መካከል ሳለሁ ሰማያት ተከፈቱ፥ የእግዚአብሔርንም ራእይ አየሁ። ንጉሡ ዮአኪን በተማረከ በአምስተኛው ዓመት ከወሩም በአምስተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል በከለዳውያን አገር በኮቦር ወንዝ ወደ ቡዝ ልጅ ወደ ካህኑ ወደ ሕዝቅኤል መጣ። የእግዚአብሔርም እጅ በዚያ በእኔ ላይ ሆነች"          ✍️ማቴዎስ 3:16-17 "ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፡ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡ አለ"          ✍️ሐዋርያት 7:55-56 "መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና። እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ፡ አለ"          ✍️ሐዋርያት 10:11-15 " ሰማይም ተከፍቶ በአራት ማዕዘን የተያዘ ታላቅ ሸማ የሚመስል ዕቃ ወደ ምድር ሲወርድ አየ፤ በዚያውም አራት እግር ያላቸው ሁሉ አራዊትም በምድርም የሚንቀሳቀሱት የሰማይ ወፎችም ነበሩበት። ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚልም ድምፅ ወደ እርሱ መጣ። ጴጥሮስ ግን፡ ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ አንዳች ርኵስ የሚያስጸይፍም ከቶ በልቼ አላውቅምና፡ አለ። ደግሞም ሁለተኛ፡ እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው፥ የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ" 🔥ሰማይ ሲከፈት የሚሆነው ነገር (Sammiin yeroo nurratti banamuu ta'aan)፦ 👉. የእግዚአብሔርን ራዕይ ማየት ይሆናል(ሕዝቅኤል 1:1)=> Mul'ata Waaqayyoo ni argita. 👉. እግዚአብሔር ቃል ወይም መልዕክት ወደ አንተ/ቺ  ይመጣል(እግዚአብሔር በቃሉ የልቡን ሀሳብ ይናገራል)(ሕዝቅኤል 1:3)=> Dubbiin Waaqayyoo gara kee in dhufa. 👉. የእግዚአብሔር እጅ በአንተ/ቺ ላይ ይሆናል(ሕዝቅኤል 1:3)=> Harkii Waaqayyoo sii gargaaruu sirratti dhufa. 👉. የእግዚአብሔር መንፈስ በሀይል ይወርድብሃል(ማቴ 3:15-16)=> Haffurii Waaqayyoo sirra buufata. 👉. የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ክርስቶስን በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ ማየት ይሆናል (ሐዋርያት 7:55-56)=> Ulfina Waaqayyoo kan ta'ee Yesusiin Mirga Abbaasaatti nii argita. 👉. የእግዚአብሔር ድምፅ ይመጣል(ማቴ 3:17; ሐዋርያት 10:15)=> Sagaleen Waaqayyoo gara kee in dhufa. 🔥ሰማይን የሚያስከፍት(Dhimmoota Sammii sirratti bansiisan keessaa)፦ 👉1.የንስሐ ሕይወት ሰማይን ያስከፍታል(Jireenya Qalbii jijjirachuu qabaachuu):- ንስሐ የእግዚአብሔርን ፍርድ ሊያስቀይር የሚችል ኃይል አለው። ዮሐንስ በኃይለኛና ትልቅ ድፍረት ንስሐ እንዲገቡ ይናገር ነበር። - ንስሐ በእግዚአብሔር ፊት ራስን ማዋረድ ነው። - ንስሐ ማለት መጸጸት ነው - ንስሐ ፍሬ አለው። ዮሐንስ ለዚህ ነው የንስሐ ፍሬ አድርጉ ያለው። 👉2. ኢየሱስ ሲሰበክ ሰማይ ይከፈታል (Yesus Kristoos Yeroo Lallabnuu)፦ ምንም እንኳ ዮሐንስ ከኢየሱስ የስድስት ወር ታላቅ ቢሆንም ዮሐንስ ኢየሱስን ሲሰብክ ሰማይ ተከፈተ። እስጢፋኖስ ኢየሱስ ሲሰብክ ሰማይ ተከፈተ። ምንም እንኳን አምላክ ቢሆንም በአንተ እጠመቃለሁ አለው።      => ሐዋርያት 7:1-56     => ማቴዎስ 3:1-17 👉3. መከባበርና መፈቃቀር(Walkabajuu fi waljaalachuun yoo jiraatee) ሲኖር ሰማይ ይከፈታል። => አለመከባበር ሰማይን ያዘጋል። ሁሉን ሰው ማክበር ይገባል። 🔥በኢየሱስ ክርስቶስነ ስም በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ሰማይ በአንጻራችን የተከፈተ ይሁን። 🔥በሕዝቅኤል ላይ የተከፈተው ሰማይ፤ በአንተ/ቺ (በእኛ) ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይከፈት። 🔥በጴጥሮስ ላይ የተከፈተው ሰማይ በአንተ/ቺ (እኛ) ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተከፈተ ይሁን። 🔥 በእስጢፋኖስ ላይ የተከፈተው ሰማይ በአንተ/ቺ (እኛ) ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተከፈተ ይሁን ። 🔥በኢየሱስ ላይ የተከፈተው ሰማይ በአንተ/ቺ(እኛ) ላይ የተከፈተ ይሁን።

photo content

እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የውልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 💥💥በዓሉ የሰው ልጆችን ለማዳን በማይገባው ስፍራ እንዲገኝ እንደ በግ ለመሞት በበረት እንዲገኝ የአለምን ኃጢአት ለመሸከም ለመሞት በግ ሆኖ የተገኘው ኢየሱስ ስለ ሰው ልጆችን ለማዳን እንደሆነ አውቀን የምናመሰግንበት በዓል ይሁን።

ለሰው ብለን አምሮብን እንገኛለን ፣በሰው ፈት ቆሸሸን መገኘት አንፈልግም ፣በእግዚአብሔር ፈትም በውስጣዊ ማንነታቸን አመሮብን መገኘት አለብን ሰው ፈትን ያያል እግዚአብሔር ልብን ያያል ።

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።

Voice message00:26

እንኳን ለ2018 ዓ/ም ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ "ወዳጅ ሆይ፥ በጎ የሆነውን እንጂ ክፉን አትምሰል። በጎ የሚያደርግ ከእግዚአብሔር ነው፤ ክፉን የሚያደርግ ግን እግዚአብሔርን አላየውም።" - 3ኛ ዮሐንስ 1፥11 መልካም በዓል

20260106_000804.jpg7.62 KB

በዚቺ ምድር ለአንድ ነገር እሮጣለሁ የኢየሱስን ፍለጋውን እከተላለሁ በዚቺ ምድር ለአንድ ነገር እታገላለሁ መምህሬን እንድመስለው እሻለሁ..

ለሁሉ ነፍስ ዘሪ ነህ ፍጥረት ያላንተ ባዶ ነው በአፍህ ቃል ጸንቶ ቆሟል ሁሉ አንድ ብሎ ቢራመድ በአንተ ነው ሁሉ ባዶ ጨለማ አንዳች በማይገኝበት ከሌለው ይህን ሁሉ ሞልተሃል አቤት ችሎታህ ያስብላል ሁሉ ባዶ ጨለማ አንዳች በማይገኝበት ከሌለው ይህን ሁሉ ፈጥረሃል አቤት ችሎታህ ያስብላል ቃላት የማይገልጽህ የማትብራራ የማትሰፈር የማትሰላ ልክህ ከቋንቋዎች ሰፈር የለ አንተ እራስህ አንተነህ ልክህ ከቁጥሮች መንደር የለ አንተ እራስህ አንተ ነህ ልክህ ከቋንቋዎች ሰፈር የለ አንተ እራስህ አንተነህ ልክህ ከቁጥሮች መንደር የለ አንተ እራስህ አንተ ነህ የሰማዩን ደመና በጥበብ ቆጥረሃል መብረቅ ሊታዘዝህ እነሆኝ ይልሃል የምድሩን ውሃ በእፍኝህ የቋጠርክ የምስራቁን ንፋስ በምድር ላይ የበተንክ ለማዕበሉ ትዕቢት ገደብ ይሁን ያልህ ሁሉን አሰልፈህ ስርአት ያስያዝህ በፍጥረትህ ታይተህ መደመም ሆነብኝ በማይነጥፍ አንደበት ማመስገን ይብዛልኝ በቃላት መደርደር በስንኝ ቋጠሮ ማን አክትሞ ያውቃል ስላንተ ዘርዝሮ ስራህ ለጠቢባን ሆናቸው መፍዘዣ አጥንተው እንዳያርፉ የእድሜ ልክ መጓዣ በጠብታ እውቀት ስንቱ አንጋጦ ቀረ ላይጨርስ ጀምሮ ዝንት አለም ቆፈረ ለኔ ግን በርቶልኝ የመስቀልህ እውነት ስራዬ አደረኩት ፍቅርህን መቀኘት አየሁ (4) በፍጥረቱ እግዚአብሄርን አየሁ አየሁ (4) በእጁ ስራ እግዚአብሄርን አየሁ አየሁ (4) ሰማዩን ሳይ እግዚአብሄርን አየሁ አየሁ (4) እራሴን ሳይ እግዚአብሄርን አየሁ ትልቅ ነው እግዚአብሔር ትልቅ ነው (2) ተምሬአለሁ እግዚአብሔር ትልቅ ነው (2) አይቻለሁ እግዚአብሔር ትልቅ ነው(2) አውቄአለሁ እግዚአብሔር ትልቅ ነው(2)

#መግቢያ ቅድስና በእብራይስጥ "ቅዱስ" በግሪክ ቋንቋ "ሐጅሶ" ሲሆን ቀጥተኛ ትርጉሙ ለእግዚአብሔር ክብርና አገልግሎት የተለየ ማለት ነው:: ይህም ሰዎች (ዘፀ28-:-41) እንስሳት (ዘፀ13-:-2) ቦታዎች (ዘፀ3-:-5) ቀኖች (ዘፀ2-:-3) ወይም ማናቸውም ነገር ለእግዚአብሔር ከተለየ ቅዱስ ሊባል ይችላል:: ከመጽሀፍ ቅዱስ አገላለጽ አኳያ አንድ ሰው ስጋውን መንፈሱንና ነፍሱን ከሚያረክስ ኃጢአት በመራቅና በመለየት ራሱን ለአምላኩ ለእግዚአብሔር መለየት ማለት ነው:: (ዕብ12-:-14,1ጴጥ1-:-15,2ዜና29-:-5)         #የቅድስና_ምንነት ➣ቅድስና የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው::(1ጴጥ1-:-15) ➣  ቅድስና የእግዚአብሔር አንዱ ባሕርይ ነው::(1ተሰ4-:-3,1ሳሙ2-:-2) ➣  ቅድስና ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆን ነው::(ዘፀ28-:-36) ➣  ቅድስና ለአንድ ለታወቀ አላማና ግብ ላለው ሕይወት መለየት ነው::(2ዜና29-:-5) ➣  ቅድስና ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣና ለተቀዳሹ በረከት የሚሆን ስጦታ ነው::(ዕብ12-:-14)       #የቅድስና_መሰረት ✔ ክርስቶስን ለመምሰል በሚደረገው የሕይወት ሂደት ላይ የተመሰረተ ነው:: (1ቆሮ11-:-1) ✔  ቅድስና በመዳንና በጽድቅ መሰረት ላይ የታነጸ እድገት ያለው ሕይወት ነው:: ይህም ያለ ደህንነትና ጽድቅ ቅድስናን ማምጣት አንችልም ማለት ነው::(ኤፌ4-:-24) ✔  ቅድስና 3 መሰረታዊ ትርጉሞች አሉት:- 1, መለየት - ይህም ከኃጢአት፣ ከራስ ምኞትና ከሰይጣን አሰራር (ኢሳ52-:-11-12) 2, መሰጠት - ለእግዚአብሔር ብቻ ራስን መስጠት (2ዜና29-:-5) 3, ንጽህና - ከኃጢአትና ከሚያረክስ ነገር ንጹህ መሆን (ዘፀ19-:-10) (ፍጹም ቅድስና)             #የቅድስና አስፈላጊነት ለማን ነው? #እግዚአብሔርን_ለማክበር_ለሚፈልግ ሁሉ ◈  ቅድስና እግዚአብሔርን የምናከብርበትና የምንፈራበት መንገድ ነውና:: ◈ እግዚአብሔርን በሙሉ ልብ የመውደድ ውጤት ነው:: (ማቴ22-:-37) ◈ ለእግዚአብሔር በደስታ የመገዛት ሕይወት ነው:: (ዕብ13-:-20-21) ◈  ለአገልግሎት ብቃት መሰረት ነው:: (ዘፀ19-:-22) ◈  ክብሩን የመጠማትና የመፈለግ ሕይወት ነው:: (ቆላ3-:-24) #ለክርስቶስ_ሕይወት_መገለጫ_ለሚሆን_ሁሉ ➣  እርሱን በሚመስል ሕይወት ለመመላለስ ነው:: (1ጴጥ2-:-21) ➣  የክርስቶስ ንጽህና በእኛ ላይ መታየት አለበትና (1ዮሐ1-:-9) #ለመንፈስ_ቅዱስ_ስራ_ለመመቸት_ለሚፈልግ ሁሉ ➣ በመንፈስ ሆኖ ከስጋ ምኞት ለመራቅ ይቻላልና:: (ሮሜ8-:-5,ሮሜ8-:-13,ሮሜ8-:-4,ገለ5-:-5,25,ሮሜ12-:-11,15-:-13) ➣  መንፈስ ቅዱስን ላለማሳዘን ይጠቅማልና:: (ኤፌ4-:-30) #ከሌሎች_ጋር_አብሮ_ለመኖር ለሚፈልግ ሁሉ ☑  የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎችን በማፍራት ከሌሎች ጋር ያለንን ህብረት ለማጠናከር ይጠቅማልና (ገለ5-:-22-23) ☑  የጠፉትን ለማዳን ይጠቅማልና (ኢሳ6-:-1-6)               #የቅድስና #መገኛ #መንገዶች 1, #በአማኞች መለየት ◈ቃሉን በማጥናት (ዮሐ17-:-17-19,ኤፌ5-:-26,1ጢሞ4-:-5,ያዕ1-:-25) ◈   ቃሉን ከሚያውቁ አገልጋዮች ጋር ሕብረት በማድረግና በመንፈስ ቅዱስ ስር ሆኖ በመማር (ኤፌ4-:-11-13,1ተሰ3-:-10,1ዮሐ2-:-27) 2, ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እራሱን መስዋዕት በማድረግ በደሙ ቀደሰን (ዕብ13-:-12,1ዮሐ1-:-9) 3, በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ በመሆን እንቀደሳለን:: (ማቴ3-:-15-17,ሮሜ8-:-9,ሉቃ2-:-50-52) 4, ጌታ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሆኖ በሚሰራው ስራ (ሮሜ8-:-2,13,ገለ5-:-17,22)       የቅድስና ደረጃዎች 1, የመዳንን ደረጃ የሚያስገኝ ቅድስና (1ቆሮ6-:-11,1-:-2,ኤፌ1-:-1,ቆላ1-:-2,ዕብ10-:-10) 2, የሚያድግ ቅድስና ፡- 1, በቅድስና ሕይወት ተጠብቆ መኖር (2ጴጥ3-:-17), ☑የቅድስናን ፍሬ በማፍራት መኖር (መዝ132-:-18) ቅድስናን ፍጹም ለማድረግ እራስን ከሚያረክስ ነገር በማንፃት መኖር (2ቆሮ7:-1) ዘወትር እራስን ለእግዚአብሔር በመስጠት መኖር (ሮሜ8-:-13,1ጴጥ1-:-22) ፍጹም እንከን የሌለው ቅድስና - ይህ አይነቱ ቅድስና የሰማያዊ አካልን ስንለብስ የሚሆነው ቅድስና ነው::(1ዮሐ3-:-2,1ቆሮ13-:-10,ዕብ12-:-23,1ተሰ3-:-13) የቅድስና አቅጣጫዎች በሁለንተና የሰው ተፈጥሮ (በስጋ፣ በነፍስና በመንፈስ) (1ተሰ5-:-23) በአካሄድ፣ በአለባበስ፣ በአነጋገር ወ.ዘ.ተ:: በኑሮ ሁሉ (1ጴጥ1-:-15-16,1ቆሮ10-:-31) የቅድስና በረከቶች እግዚአብሔርን በክብሩ ማየት (ዘፀ33-:-17-20,ዕብ12-:-14,ማቴ5-:-8,መዝ84-:-4-12) ከክርስቶስ ጋር የጠበቀ ሕብረትን ማግኘት (ዕብ2-:-11-13) የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች መሰጠት(1ቆሮ1-:-7) የተስፋውን በረከት መውረስ (ኢያ3-:-5) እግዚአብሔር አምላካችን ከአማልክትና ከማንኛውም ነገር ሁሉ የተለየ በመሆኑ ቅዱስ ተባለ:: እግዚአብሔር አምላካችን ቅዱስ በመሆኑ ለእርሱ የተለዩ ሰዎችም ሁሉ ቅዱሳን ይባላሉ:: ሰው በክርስቶስ ስራ አምኖ አማኝ ሲሆን ቅዱስ ይባላል:: በሕይወቱ ሁሉ በቅድስና ያድጋል:: በክርስቶስ ዳግም መምጣት ቅድስናውም ፍጹም ይሆናል:

ዘዳግም 33 (Deuteronomy) 26፤ ይሹሩን ሆይ፥ በሰማያት ላይ ለረድኤትህ፥ በደመናትም ላይ በታላቅነት እንደሚሄድእንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም። 27፤ መኖሪያህ የዘላለም አምላክ ነው፥ የዘላለምም ክንዶች ከአንተ በታች ናቸው፤ ጠላትህን ከፊትህ አውጥቶ፡— አጥፋው ይላል። 28፤ እስራኤልም ተማምኖ፥ የያዕቆብም ምንጭ ብቻውን፥ እህልና የወይን ጠጅ ባለባት ምድር ይኖራል፤ ሰማያቱም ጠልን ያንጠባጥባሉ። 29፤ እስራኤል ሆይ፥ ምስጉን ነህ፤ በእግዚአብሔር የዳነ ሕዝብ እንደ አንተ ማን ነው? እርሱ የረድኤትህ ጋሻ፥ የከፍተኛነትህም ሰይፍ ነው። ጠላቶችህም ይገዙልሃል፤ አንተም ከፍታቸውን ትረግጣለህ።

ሙሉዬን_ውሰደዉ_Illasha_fekadu_ኢላሻ_ፍቃዱ@ARC256k.mp39.61 MB

ሰለሞን ምን ነካው??ምን ሆኖ ነው??🤔🤔 ሰለሞን እግዚአብሔርን #ከልቡ_ይወድ አልነበረ እንዴ??? ሰለሞን እግዚአብሔርን በፀሎት ሲፈልግ እግዚአብሔር የሚገኝለት፣የለመነው የሚሰጠው ሰው አልነበረ እንዴ??? እንደ እግዚአብሔር ያለ አምላክ የለም ብሎ አልነበረ እንዴ??? አባቱ ዳዊት "ሰው ሁን" ብሎ የመከረውን ምክር ምነው ዘነጋው?? ከእግዚአብሔር ለምኖ የተቀበለው ጥበቡስ ለዚህ ጊዜ ምነው ከልቡ ጠፋ??ምነው መጨረሻ ላይ ሳተ??🙄ምን አይነት ክፉ መንፈስ አግኝቶት ልቡን አጣመመበት?? እግዚአብሔርን ትቶ ለሌሎች አማልዕክት መስዋዕት ማቅረብ ለምን ጀመረ?? ምነው የእግዚአብሔርን ህግ መተላለፍ ጀመረ?? እንደ አባቱ ዳዊት እስከመጨረሻው እግዚአብሄርን መከተል እንዴት አቃተው??? 👉#በሴት_ፍቅር_እግዚአብሔርን_ለወጠ💔💔 የሴት ፍቅር👉ልቡ ወደ አማልዕክት እንዲያዘነብል አደረገው💔 ልቡ ለእግዚአብሄር መገዛትን አቆመ💔 ምን ነካው ሰለሞን ማለቴን ትቼ ወንድሜ ሆይ ተጠንቀቅ ማለትን ልጀምራ!! አዎ አሁን እግዚአብሔርን ከልቤ እወዳለሁ!! እለት እለት እግዚአብሔርን የምናፍቅ ህልውናው እንዲነካኝ የምጓጓ ሰው ነኝ!!! ነገ ምን መጥቶ ይለውጠኝ ይሆን???እንደ ሰለሞን የሴት ፍቅር ወይስ እንደ ይሁዳ የገንዘብ ፍቅር??? እግዚአብሔርን አምጣና ይሄንን እንካ የሚል  ድርድር🤝 ውስጥ እራሴን አገኘው ይሆን??? በል በል ወንድሜ አስተውል!!!ልብህን ለእግዚአብሔር አስገዛ!!እለት ተእለት ወደ ፀጋው ዙፋን በእምነት ቅረብ!! ሀይልን ለምን!!ክፉ መንፈስን ተዋጋ!!መጨረሻዬን አሳምርልኝ በል!!💞ዛሬም ነገም ልውደድህ እያልክ ፀልይ!! እግዚአብሔር መውደድህን ቀጥል!!

ኢየሱስ እኛ ሊያድነን የቻለው ራሱን ከመስቀል ሞት ባለማዳኑ ነው።
የሮሜ ወታደሮች ፣ የተቸነከረው ሚስማር ፣ ኢየሱስን ማስቆም ችለው ሳይሆን ፤ የሞተው ለዓለም ሁሉ ኃጢአት መስዋዕት መሆን ስላለበት እና ለአባቱ በመታዘዝ ፈቃዱን ለመፈፀም ነበር።            ጳውሎስ ፈቃዱ "የተሰቀለው"

"ያለውና የነበረው፣ የሚመጣውም፣ ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ፣ አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ" ይላል። ራእይ 1:8 ከመጀመሪያው አንሥቶ እስከ ፍጻሜው ድረስ አምላካችን ከእኛ ጋር ነው! የሚያስፈራን ነገር ምንድን ነው? ይህንን የማይካድ እውነታ ሊለውጥ የሚችል ነገር ምን ሊከሰት ይችላል? ሁልጊዜ ያለው፣ ሁልጊዜ የሚጠነቀቅልንና ለእኛ ሕይወትንና ድነትን ለማምጣት የሚሠራው አምላክ የእርሱ ነን። ነገ ወይም ቀጣዩ ቀን በእኛ ላይ የሚደርስብን ነገር ምንም ይሁን፣ ዕጣ ፈንታችን አልፋና ዖሜጋ በሆነው፣ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው በሚኖረውና ዘላለማዊ ሕይወትን ለእኛ ባዘጋጀው ላይ የተደገፈ ነው።

ከትልቅ ባለ ስልጣን ጋር ለመገናኘት ቀጠሮ መያዝ ያስፈልጋል ያውም በስንት ሙከራ ፣ከእግዚአብሔር ጋር ግን ለመገናኘት ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግም በማንኛውም ሰአት፣ በማንኛውም ጊዜ በማንኛውም ሁኔታ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ህብረት ማድርግ ይቻላል ፣ሁሉን ያለ ቀጠሮ መስተናገድ የሚችል እግዚአብሔር ብቻ ነው ፣ያለ ቀጠሮ ስለምናገኘው እግዚአብሔር ሊቃልብን አይገባም ያለ ቀጠሮ የምንገኘው እግዚአብሔር በቀጠሮ ከምናገኘው ባለ ስልጣን ይበልጣል ።