602
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1230 days
Posts Archive
602
በድንገት አይደለም
አንዳንዴ አንዳንድ ልጆች እንዲው በድንገት ፀሎት አቆምኩኝ በድንገት ቃል ማንበብ አቆምኩ ይሉኛል እኔም
መስሏቹ እንጂ በድንገት አይደለም ያቆማቹት እላቸዋለሁ፤ ምን ለማለት ፈልጌ መሰላቹ... በድንገት የሚመጣ ድካም የለም ልላቹ ነው፤ አይኖቻችን በየቀኑ ያንንም ይሄንን እያዩ፤ ልባችን ደግሞ አይናችን ያየውን እያሰበ ፣ እግሮቻችን ጌታ በሌለበት እየዞረ እንዴት በድንገት ደከምኩ ይባላል ? ? ከዚህ በፊት ትዝ ይላቹ ከሆነ "መንፈሳዊ ህይወት እንክብካቤ ይፈልጋል " ብያቹ ነበር ፤ በዚች አለም ውስጥ የክርስትና ህይወት በምርጫና በመጠን ካልተኖረ በስተቀር ትክክለኛውን የክርስቶስ ህይወት መስሎ መቀጠል አይቻልም፤ የተሰጠን ህይወት ከምታስቡት በላይ በፈተና የተሞላ ነው፤ ለዚህ ህይወት ደግሞ የሚጎዳውን እና የሚጠቅመውንም ነገር የምትመርጡለት እናንተው እራሳቹ ናቹ ፤ ትናንት ድንገት በሚመስል መልኩ ቀስ በቀስ በሚኖር ልክ ባልሆነ ህይወት ከጌታ እግር ስር ሳይታወቃቸው ጠፍተው የቀሩ ብዙ ልጆች አሉ ስለዚህ የተወደዳቹ አሁንም ቢሆን ምርጫው የናንተው ነው የቱ ይሻላቿል ፤ ሳታውቁት እያሰመጣቹ ካላቹበት አለማዊ ነገር ነቅታቹ በሚወዳቹ በጌታ እቅፉ ስር መዋል ወይስ እያመቻቻቹ እንደ ቀድሞ መቀጠል...? 602
1 ጴጥሮስ 1 (1 Peter)
3-5፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል።
602
✍️ በጸጋ ላይ አትዋሹ!!
**
✍ ጸድቃችኋልና እንደፈለጋችሁ በኃጢአት ተጨመላለቁ የሚል የጸጋ ወንጌል አስተማሪ ጆሮዬ ሰምቶ አያውቅም ካለም ደግሞ ፈጽሞ የክርስቶስን ሥራ የሚያንቋሽሽ ከአባት ሳይሆን ከአጋንንት የሆነ ትምህርት ነው!!
📌 ከኃጢአት ለመሸሽ ወደ ጸጋ ይሮጣል እንጂ ጸጋ ተይዞ ወደ ኃጢአት አይሮጥም!!
✍️ ብዙ የተማረ ብዙ ይወዳል እንጂ ብዙ ኃጢአት አይሰራም!!
✍ ኃጢአትን በጸጋ ከካዱ በሗላ ጸጋ ለኃጢአት ፈቃድ ይሰጣል ማለት ጸጋ ላይ መዋሸት ነው!!
📌 ስለምን ጸጋ ላይ ዋሸህ?
✍ መንፈስ ቅዱስ 👉 አንዴ ድኛለሁና እንደፈለግኩ የኃጢአት ጭቃ አቦካለሁ እንዳትል የሚረዳህ የጸጋው መንፈስ ነው!!
📌 ጸጋ ለኃጢአት ፈቃድ ያሳጣል!!
✍️ ባልሽ በጣም ስለሚያፈቅርሽ ምንም ብታደርጊ አይተውሽም ማለት ባልሽ ላይ እንደፈለግሽ ማመንዘር ትችያለሽ የሚል አቻ ፍች የለውም!! 👉 አላዋቂ መተርጉማን ካልተረጎሙልሽ በቀር!!
✍️ በአብ ፊት ክርስቶስ ድፍረት የሆነለት ሰው የድፍረት ኃጢአት አይገዛውም!!
📌 ጸጋው የሰጠን በአብ ፊት የመቅረብ ድፍረት እንጂ ኃጢአት የመሥራት ድፍረት አይደለም!!
✍️ እውነተኛ አማኝ እግዚአብሔር ኃጢአትን እንደሚጠላ እርሱም ኃጢአትን ይጠላል!!
📌 ኃጢአት አንተን በመግደል አፍቃሪህን መስቀል ላይ ያንጠለጠለ ጠላትህ ነው!!
✍️ እንዲሁ በጸጋ እያላችሁ በኃጢአት ጭቃ የምትጨማለቁም ካላችሁ ከእንግዲህ አትጨማለቁ.....ይልቁን በጸጋው አርነት ውጡ!!
#ፀጋ_ተወርቶ_ኃጢአት #ሕግ_ተወርቶ_ጽድቅ_የለም!!
#ሕግ_ተወርቶ_ኃጢአት
#ፀጋ_ተወርቶ_ጽድቅ_ግን_አይቀሬ_ነው!!
📌 #መስቀል_ላይ_የዋለው_ፍቅር ከኃጢአት ያልመለሰው ሰው #ሲና_ላይ_የተገለጠው_ድንጋይ አያቆመውም!!
📌 ድንጋይ ከያዙ አገልጋዮች ተጠበቁ!!
✍️ በጸጋ ላይ አትዋሹ!!
#ሄኖክ_አሸብር
602
ኢየሱስ ጌታ ነው ።
Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen Amen
602
"ህክምናዬ የኔ መድሀኒት *4
ያይኛል እኮ ልቤ ሲንሸራተት
ያይኛል እኮ ሲያቅተኝ ዳገት መውጣት
ያይኛል እኮ ሆድ ሲብሰኝ ስሆን ለብቻ
ያደርግልኛል ሁሉንም የሀዘን መቋጫ"
💗ህክምናዬ💗
መልካም ቀን 🙏🥰🙏
602
ሰውን መሸነፍ የምትችሉት በፍቅር ብቻ ነው ።
1 ቆሮንቶስ 13 (1 Corinthians)
4፤ ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤
5፤ የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤
6፤ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤
7፤ ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል።
8፤ ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል።
602
ሰዎች ወንጌል እንዲያመሳክሩ የሚያደርጋቸው
1# የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ማጣት
2# ፍርሀት
3# ሻክም ማጣት ለሚጠፉ ሰዎች ግድ የለሽነት
4 # ሌላ ጊዜ እመሰክራለሁ የሚል ስበብ
5 # ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ብቻ መታው ምስክርነት ወንጌል እንድንመሰክር ያደርገናል
በእግዚአብሔር ቃልና በመንፈሰ ቅዱስ በመሞላት የወንጌል ምስክር መሆን ይቻላል ፣ወንጌል ላለመናገር የምናቀርባቸው ማንኛው ምክኒያት ሚዛን አያደፉም ።
1 ቆሮንቶስ 9 (1 Corinthians)
16፤ ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።
602
Repost from GMTV.ጂኤም ቲቪ HEAD OFFIC ETHIOPIA
በእግዚአብሔር ቤት ስንኖር በምን እናድግ?
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
✍️የእግዚአብሔር ቤት እድገት" የሚለው አማኞች በእምነታቸው እና ከእግዚአብሔር ጋር ባላቸው ግንኙነት ሲያደጉ የቤተክርስቲያኑን በቁጥር እና በመንፈስ ማስፋፋት ነው ። ይህ እድገት ስለ አካላዊ ህንፃዎች ብቻ ሳይሆን ስለ አማኞች መንፈሳዊ ለውጥ ነው።
✍️የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር መኖሪያችሁ ሲሆን በሰላም ትኖራላችሁ። መመሪያ፣ ጥበቃ፣ ማዳን፣ መንፈሳዊ በረከት እና የዘላለም ደህንነት አለህ። ከፍቅሩ በጭራሽ አትለዩም።
✍️በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ የተተከሉ ሰዎች በአምላካችን አደባባይ ውስጥ ብቻ ሳይሆን "በእርጅናቸው ፍሬ ይፈራሉ፤ ትኩስ ይሆናሉ" (መዝሙር 92፡14) ።
✍️አንድ ህጻን ከተወለደ በኃላ ማደግ ባለበት ጊዜ ካላደገ ለቤተሰቦቹ ትልቅ ፈተና ሆኖ ይቀራል።እንድሁም አንድ አማኝ በቤተክርስቲያን ውስጥ ማደግ ባለበት ነገር ካላደገ ከራሱም ተርፎ ለቤተክርስቲያኒቱ ሸክም ነው።
“ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥15
ክርስቲያኖች ማደግ ያለባቸው ጉዳዮች
●●●●●●●●●●●●●●●●●●●●●●●
❶በእምነትና በመታዘዝ መንፈስ እንደግ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
➣“ለመታዘዝ ባሪያዎች እንድትሆኑ ራሳችሁን ለምታቀርቡለት፥ ለእርሱ ለምትታዘዙለት ባሪያዎች እንደ ሆናችሁ አታውቁምን? ወይም ለሞት የኃጢአት ባሪያዎች ወይም ለጽድቅ የመታዘዝ ባሪያዎች ናችሁ።”
— ሮሜ 6፥16
❷.በፍቅር፣እርስበርስ በመዋደድ መንፈስ ማደግ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
➣“ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ፤”
— ኤፌሶን 4፥15
➣“እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።”
— ዮሐንስ 13፥35
➣“ማንም፦ እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥20
❸.በመልካም መንፈስ ማደግ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
📌መንፈስ የተባለ ሁሉ የሚጠቅም አይደለም።በአንተ ውስጥ ያለው መንፈስ መልካምነትን ስጎድል በክፉ ይተካካሉ።
➣“ዳንኤልም መልካም መንፈስ ስላለው ከአለቆችና ከመሳፍንት በለጠ፤ ንጉሡም በመንግሥቱ ሁሉ ላይ ይሾመው ዘንድ አሰበ።”
📌አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ዘንድ ስበላሽብን
— ዳንኤል 6፥3
➣“የእግዚአብሔርም መንፈስ ከሳኦል ራቀ፥ ክፉም መንፈስ ከእግዚአብሔር ዘንድ አሠቃየው።”
— 1ኛ ሳሙኤል 16፥14
❹.በቅን ልብ እግዚአብሔርን በሚፈልግ መንፈስ ማደግ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
➣“እግዚአብሔርንም መፍራት ባስተማረ በዘካርያስ ዘመን እግዚአብሔርን ይፈልግ ዘንድ ልብ አደረገ እግዚአብሔርንም በፈለገ ጊዜ እግዚአብሔር ነገሩን አከናወነለት።”
— 2 ዜና 26፥5
⏭“ስለዚህም የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን ፈጽሞ ስለ ተከተለ ኬብሮን እስከ ዛሬ ለቄኔዛዊው ለዮፎኒ ልጅ ለካሌብ ርስት ሆነች።”
— ኢያሱ 14፥14
❺.በጸሎት ጉልበት ማደግ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
➣“ጸሎትዋንም በእግዚአብሔር ፊት ባበዛች ጊዜ ዔሊ አፏን ይመለከት ነበር።”
— 1ኛ ሳሙኤል 1፥12
🗣ሐና በጸሎት የተጋች ሴት ናት።ምንም እንኳ በፈተና የተከናነበች ሴት ቢትሆንም አይኗን ከእግዚአብሔር አልመለሰችም።ለሐና የጠነከረ ፈተና ቢኖራትም 💪ጠንካራ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ስታቀርብ ቆይታለች።ነገር ግን ሀዘንተኞችን የሚያጽናና አምላክ በጊዜው ስመጣ እንቧዋን እንደአበሳት እናያለን።
🗣በጸሎት የተጋ ሰው በረከት፣ከራሱም አልፎ ለአከባቢው፣ለሃገሪቱም ጭምር ነው።
ጸሎት ያስመልጣል፣መውጫንም ያበጃል👇👇
👉 ዳንኤል 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ናቡከደነፆርም በነገሠ በሁለተኛው ዓመት ናቡከደነፆር ሕልም አለመ፤ መንፈሱም ታወከ፥ እንቅልፉም ከእርሱ ራቀ። ³ ንጉሡም፦ ሕልም አልሜአለሁ፥ ሕልሙንም ለማወቅ መንፈሴ ታውኮአል አላቸው። ¹¹ ንጉሡም የሚጠይቀው ነገር የቸገረ ነው፤ መኖሪያቸው ከሰው ጋር ካልሆነ ከአማልክት በቀር በንጉሡ ፊት የሚያሳየው ማንም የለም አሉ። ¹³ ትእዛዝም ወጣ፥ ጠቢባንንም ይገድሉ ዘንድ ጀመሩ፤ ዳንኤልንና ባልንጀሮቹንም ይገድሉ ዘንድ ፈለጉአቸው። ¹⁶ ዳንኤልም ገብቶ ፍቺውን ለንጉሡ የሚያስታውቅበት ጊዜ ይሰጠው ዘንድ ንጉሡን ለመነ።
¹⁹ #የዚያን_ጊዜም_ምሥጢሩ_በሌሊት_ራእይ_ለዳንኤል ተገለጠለት፤ ዳንኤልም የሰማይን አምላክ አመሰገነ።
²⁰ ዳንኤልም ተናገረ እንዲህም አለ፦ ጥበብና ኃይል ለእርሱ ነውና የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ፤
²¹ #ጊዜያትንና_ዘመናትን_ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል።
²² #የጠለቀውንና_የተሠወረውን_ይገልጣል፤ #በጨለማ_ያለውን_ያውቃል፥ ብርሃንም ከእርሱ ጋር ነው።
²³ ጥበብንና ኃይልን የሰጠኸኝ፥ እኛም የለመንንህን ነገር አሁን ያስታወቅኸኝ፥ አንተ የአባቶቼ አምላክ ሆይ፥ የንጉሡን ነገር አስታውቀኸኛልና እገዛልሃለሁ አመሰግንህማለሁ።
❻.በተዋረደ ልብ እርሱን እየፈለግን እንደግ
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
➣“የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበረውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።”
— መዝሙር 51፥17
📌ነገሮቻቸውን ያከናወን ዘንድ እግዚአብሔር ከቅኖች መንደር አይርቅም።
➣“እግዚአብሔር ከዮሴፍ ጋር ነበረ፥ ሥራውም የተከናወነለት ሰው ሆነ፤ በግብፃዊው ጌታውም ቤት ነበረ።”
— ዘፍጥረት 39፥2
➣“እግዚአብሔርም ከዮሴፍ ጋር ነበረ፤ ምሕረትንም አበዛለት፥ በግዞት ቤቱም አለቃ ፊት ሞገስን ሰጠው።”
— ዘፍጥረት 39፥21
📌ለኢየሱስ የተመረጠ ሰው ዝምብሎ እንደ ተፈታ ፈረስ ሳይሆን የአምላኩን ቀንበር በላዩ ላይ እንዳለው የሚገነዘብ ብልጥ ሰው ነው።የእግዚአብሔር ቀንበር እንደ ጠላት ቀንበር አንገትን የሚያጎብጥ አይደለም።
➣“ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤”
— ማቴዎስ 11፥29
➣“የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥21
❼.በመልካም አነጋገር እንደግ
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
📌በክርስትና ያደረገ ህይወት ሰውንም እግዚአብሔርንም አይበድልም።ይህ ማለት በክርስቲያን ንግግር ሰው አይሰናከልም ማለት ነው።
➣“እግዚአብሔርን በቃላችሁ አታክታችኋል። እናንተም፦ ያታከትነው በምንድር ነው? ብላችኋል። ክፉን የሚያደርግ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ መልካም ነው፥ እርሱም በእነርሱ ደስ ይለዋል፤ ወይስ፦ የፍርድ አምላክ ወዴት አለ? በማለታችሁ ነው።”
— ሚልክያስ 2፥17
📌እግዚአብሔር በኢዮብ ንግግር አልከፋም
➣“እርሱ ግን አንቺ ከሰነፎች ሴቶች እንደ አንዲቱ ተናገርሽ፤ ከእግዚአብሔር እጅ መልካሙን ተቀበልን፥ ክፉ ነገርንስ አንቀበልምን? አላት። በዚህ ሁሉ ኢዮብ በከንፈሩ አልበደለም።”
— ኢዮብ 2፥10
📌በመጨረሻም አንተ የእግዚአብሔር ሰው ሆይ👇👇
“ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 3፥18
602
1 ብር ለአንድ ወገን!/ 9400 Ok ብለቹ በመላክ 1 ወገን ይርዱ 9400 Ok ብለው ከላኩ በህዋላ 👇
➡️ስም እስከነ አባት እና
➡️ስልክ ቁጥሮን
በዚህ አካውንት ይላኩልን 👇
< @skat_nati_19 >
9400 ok ብለው አንድ ወገን ስለ ረዱልን ከልብ እናመሰግናለን🙏
ለጓደኞችዎ forward በማረግ እነሱም አንድ ወገን እዲረዱ ያድርጉ
Donate 1 Birr per day by using your mobile phone and sending OK to 9400!
Our communities, vulnerable to natural and man-made disasters, need your support!
We live for humanity!
ለሰብዓዊነት እንኖራለን !
602
ኢየሱስ ክርስቶስ
እርሱ፦
👉በማቴዎስ ወንጌል፥ የህግና ነቢያት ፍጻሜ
👉በማርቆስ ወንጌል፥ መከራ ተቀባዩ አገልጋይ፣
👉በሉቃስ ወንጌል፥ አዳኙ የሰው ልጅ፣
👉በዮሐንስ ወንጌል፥ ስጋ በመልበስ በመካከላችን ድንኳኑን የዘረጋው አምላክ
👉በሮሜ ኃጢአተኞችን የሚያጸድቀው
👉በ1ኛና 2ኛ ቆሮንጦስ፥ በትንሳኤው የፍጥረታት በኩር ሆኖ ሞትን ድል የነሳው
👉በገላቲያ መልእክት፥ ከህግ አርነት የሚያወጣው
👉በኤፌሶን መልእክት፥ የቤተክርስቲያን ራስ የሆነው
👉በፍልጵሲዩስ መልእክት፥ ራሱን ባዋረደው መጠን ከፍ ከፍ የተደረገው
👉በቆላስይስ መልእክት፥ የበላይና የፍጥረት በኩር የሆነው
👉በ1ኛና 2ኛ ተሰሎንቄ ፥ በዓለም ሁሉ ላይ ሊፈርድ የሚመጣው
👉በዕብራዊያን መልእክት፥ ለዘላለም በማይለወጥ ክህነት የተሾመው
👉በያእቆብ መልእክት፥ የስነ ምግባር አስተማሪ የሆነው
👉በ1ኛና 2ኛ ጴጥሮስ፥ መከራን በመቀበል ለክርስቲያኖች ሁሉ ምሳሌ የሆነው
👉በ1ኛ 2ኛና 3ኛ የዮሐንስ መልእክት፥ ኃጢአታችንን በደሙ ሊያነጻ የዓለም መድኃኒት ሆኖ በስጋ የተገለጠ የሕይወት ቃል፣ እርሱም እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት
👉በይሁዳ መልእክት፥ ልዑል ገዢ
👉በየዮሐንስ ራእይ፥ የጌታዎች ጌታ ሆኖ ሊነግስ የሚመጣ፤
ይህንን ኢየሱስን ያልተቀበለች ነፍስ ከእግዚአብሄር መንግስት እድል ፋንታ የላትም!
ለዚያች ነፍስ ወዮላት!
ንጉሱ ሳይመጣ በእምነትና በንሰሃ ወደ ንጉሱ ትመለከት ዘንድ ወንጌል ለፍጥረታት ሁሉ ይሰበካል!
ብቻውን የደህንነት መንገድ የሆነውን የገፋች ነፍስ የተረገመች ናት!!
.
.
.
ኢየሱስ
602
መዳን በእምነት ለሚቀበሉ ሁሉ የቀረበ የእግዚአብሔር ነፃ ስጦታ ነው ይህ መዳን ግን ለሰዎች የሚደርሰው በወንጌል ስብከት ነው ስለዚህ ወንጌል መሰበክ አለበን እስራኤላውያን ግን ዕድሉ እያላቸው ባለመታዘዛቸው ምክንያት መዳን ወደ አሕዛብ ዘንድ በሰፊው ደርሷል ምክንያቱም አሕዛብ በእምነት ስለታቀበሉ ደኑ አይሁድ ግን የሕግ ሥርዓት ለመፈፀም ስሞክሩ በክነው ቀሩ
