en
Feedback
Brown Empire

Brown Empire

Open in Telegram
831
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+630 days
Posts Archive

I hate pity Specially when it comes from the dissemble heart/mind (ምንም አለመስራታቸዉን በሰላም ከማይቀበሉ ሰዎች ልብ ሲመጣ፣ ላልተጠየቁበት ስንፍናቸዉ ትልቅን ነገር በማሳነስ ጊልታቸዉን ለማብረድ ከሚሞክሩ) hate it. When ever ቴዲ ታደሰ and ጂጂ pops on the radio my heart finds her place again, my soul starts to confide that she still want some more time, not ready to give up on everything. But all of a sudden ምፅም የሚል አይጠፋም። ምፅ ጂጂ እኮ ሱሱ ነዉ እንዲህ ያረጋት… ምፅ ቴዲ እኮ homless ሆነ 😓 አስቡት ሁለት የሀገር ስም በበጎ ያስነሱ፣ በሚገርም ድምፅ ግጥምና ዘመን አይሽሬ በሆነ ዜማ ለዉብ ልጅነቶቻችን እና ወጣትነቶቻችን ሳዉንድ ትራክ የሆኑንን ሰዎች በሚያምር እና ስንት በሰሩልን ትዉስታቸዉ እንዳናነሳቸዉ ቀለሙን ትተን ጥላሸቱን አጥቅሰን ስማቸዉን በማጥቆር አዛኝ ለመምሰል መሞከር እንዴት እንደሚደብር? የወደደ ከቀለም ነዉ ትዝታዉ። ከማዘን መዉደድ ይበልጣል። መዉደድ sees the potential in you and try to embrace that, መዉደድ lets you be, can fathom the most inconvenience things can happen to anybody anytime. ማዘን ማሳነስ አለዉ፣ ንቀት እና በዛ ሰዉ ተስፋ መቁረጥ አለዉ። ያ ሰዉ በነበረዉ በቂ ተሳትፎ አለማመን አለዉ። ብቃትን እንደሌለ መደምሰስ አለዉ። ሰዉ መሆንን፣ የህይወት አጋጣሚዎችን ፣ የሰዎችን ምርጫ አለመቀበል አለዉ። Love don't pity, it only loves and have faith in you. Hope they know they did a good job on giving a whole generation a beautiful child hood, sweet memory and nostalgia to our youth. Hope they know ኢትዮጲያ ሲባል ሚኒሊክ እና ሀይለስላሴ እንደሚባል ሁሉ ጂጂ እና ቴዲ ታደሰ እንደሚባል፣ hope they know they have served their audience well and they are the brand name of Ethiopian music industry. 🤎 i hope they know ተሳትፎአቸዉ በቂ እንደሆነ። hope they find peace.

My depression comes from lots of things but mainly it comes from asking what my purpose is in this life? አስቡት when you're a plus one in a gathering and you don't know why you're there, or you're in a bus full of people and there is no sit for you, you have to stand all the way and you’re tired. I feel like that, everyday. There are times I hoped for a higher power to give all our misery a rest because it's all too much for our design. I would be happy if there is a God and make my(our) life easier but I’m just purposelessly lucky to appear in a non problematic area to live my miserable life in peace and most aren’t. Cause they are dying a purposeless death everyday … their impulsive aggression ሲነሳባቸዉ ሀገር በሚያደፈርሱ ሲበርድላቸዉ በሚሰክኑ ጥጋበኞች ምክንያት በተነሳ ጦርነት ፣ በትንሽ እርዳታ በሚፈታ ርሃብ፣ ፀጉሩን ብቻ ማቆጣጠር በሚችል ዱርዬ በሚፈጠር ጄኖሳይድ፣ በቅናተኛ ባል ገጀራ ምክንያት etc መሞት አይነፋም። Asking a purposeful death for a purposeless life sounds funny but witnessing that everyday and living through it knowing you're not the shit as you have been told growing up is sarcastically painful. ሌለዉ ቢቀር መኖር was cool if capitalism did not exist to make you work hard for your purpose less life. And everyone had the audacity to ask “why are you sad?” First of why aren't you? Are you okay? your country is in chaos, why aren't you sad? በሾቀ economy እና inflation ምክንያት ልብስ እና ምግብ (basic necessities) በዉድ ዋጋ እየሸመትን በየትኛዉ ገንዘብ፣ ሰላም እና እረፍት ነዉ ደስታን afford የምናደርገዉ? Aren’t we struggling everyday? why aren't you sad? And your value measured by handling all this crap you're not made for, why aren't you sad? There is an on going stupidity in the air, no common sense, everyone siding with their own ዘር፣ ሀይማኖት ምናምን why aren't you sad? People are cruel to each other, why aren't you sad? I'm sad because I'm not dumb, senseless or stupid. I care enough knowing me caring wouldn't bring any change in this life and that makes me powerless and purpose less in a so much promised life. Every process in life we going through or we working our ass off ምናምን just to make our purposeless self purposefully purposeless 😂. ከዛስ? we die. And the world continues. The show must go on, It’s just the characters that has to be changed. We’re all an experience, a mice in a laboratory:) ደስታ is overrated, peace is everything. And I hope that to every living being.

ተወልጄ ያደግኩት እዚሁ እየሱስ 41 ነዉ። በመሀል close to 8 years አልነበርኩም፣ i have lived around ጎተራ እና ሀያት አካባቢ complete chaos 🤢! እየሱስ ለከተማ ቅርብ ከሚባሉት ሰፈሮች ዉስጥ አንዱ ነዉ፣ አረንጓዴ ነዉ፣ ፀጥ ያለ ነዉ። ለሆነ ፊልም ተብሎ የተሰራ መቼት ይመስላል። በተለምዶ የራስ ካሳ ሰፈር ተብሎ የሚጠራዉ ሰፈር ረጃጅም በአያቶቻችን እድሜ የሚገመቱ ባህር ዛፎች እና ፂማቸዉ መሬት የነካ እድሜ ጠገብ ፅዶች ማየት የተለመደ ነዉ። በዳመና ግዜ የtwilightቷን forks washingtonን በፀሀይ ጏዜ ደግሞ ያ ሀመልማል ላይ የዮዲትን ሰፈር ይመስላል። እንዲያዉም አረንጓዴ ጣሪያ ያለዉ የአረጋዉያን መርጃም አለ። ( you can always come to visit), tent ዉስጥ አይደለሁም እንጂ አንዳንዴ ነቅቼ በመስኮቴ ወደዉጪ ሳይ ጓሳ መንዝ ዉስጥ ያለሁ ይመስለኛል። waking up to ቅዳሴ፣ አጥንት የሚቆረጥም ቀዝቃዛ አየር እና birds chirping is very usual like you are a charachter from an old book. I recently have moved into almost my dream house and im loving it. ለስሙ የቆሙ የመንገድ ላይ መብራቶች አሉን፣ የማይበሩ፥ the only thing my village lacks is path lighting and because of that the dark gets dark as it get. And its a night mare to new people that want to move in. አህያ፣ ባጃጅ እና አንዳንድ ሰዎች ባይኖሩበት it would have the potential to be the ideal place of perfection,uthopia. (okay lets leave አህያ out of it cause they are bae😍(ጭነታቸዉና ነጂዎቻቸዉ ነዉ የሚደብሩት መሰለኝ(in the other hand ደሞ ነጂዎቻቸዉ have a family to feed too:( well call our village uthopia but a bit disfunctional))) 3 ቤተክርስትያን አካባቢዉ ላይ አለ። እየሱስ፣ ማርያም እና ሚካኤል። የማርያም እና የሚካኤል ለት ጠጠር መጣያ የለም። idk why they usually ignore እየሱስ 😅, if i was thiest i would be pals with him, “ንቀህ ተዋቸዉ” እለዉ ነበር (even if thats exactly what he did 🤣) የተጠቃ ነገር/ሰዉ ሁሉ የኔ ጉዳይ ይመስለኛል። i have this rescuer instiniction. And i hate it. And there is ጋሽ ሰሀሉ፣ a very old man with እጅ አልሰጥም vibe, ከቤታቸዉ ጠዋት ወጥተዉ ከመሬት በትንሽ ርቀት ላይ የሚገኝ ጭንቅላታቸዉን አጎንብሰዉ እየጎተቱ ከሰአት አካባቢ ኬላ ይደርሳሉ(for those of you who don’t know ከእየሱስ ኬላ የ10 ደቂቃ መንገድ ነዉ) የት እንደሚሄዱ እስከዛሬ አላየሁም but rumor has it, its ጠጅቤት። ማታም በዛዉ ቀስታ እያዘገሙ ቤታቸዉ ይመለሳሉ። and I’m jealous of his consistency, his strength to wake up every morning and decide to leave his bed for sthg that he loves. Something that our generation lacks. Something that I lack.

So I had a disagreement last time with someone I know And it’s because they claimed I’m no unique and is replaceable, which is the obvious, cause I remind that to my self every time to humble my authentic self. It’s not news that we’re all not that important and the world isn’t rotating around our irrelevant existence, But It makes me question why do people take advantage of time? What’s the most expensive gift you can give to someone you call your own? Isn’t it time? Your presence? Your touch, your perspective? Personality? Experience? what is there to give for us to be labeled as irreplaceable or unique? Do we need A tail? A six-finger? A third boob? Do we have to be a fucken unicorn? We abuse being together and the perks of little things when we get close to stg we adored once. we can not see the chance we’re given to be that “unique” we glorify so much we forgot we’re also random being that can be replaceable. Don’t let anyone to make you feel less or ተራ It's important to remember that our worth and value as human beings cannot be determined by others' opinions or judgments. Instead, we must find it within ourselves and embrace our uniqueness as a strength rather than a weakness.

photo content

photo content

መልመዴ አይቀር ስማ ዋልኩኝ ዛሬን በጉም ማታን በጭለማ ብሩህ ነው ነገማ መች ተነካ በጋው ለችፍ ችፍ ዝናብ ለድንገቴ ሂያጅ ጉም ሀምሌን ያለፈ ሰው ልቡ አይደነግጥም::

ከእጄ ላይ በሚያሳዝን አለቃቀስ ትንሽ ሰውነቱን እያፈራገጠ በአባቴ ሰፊ እጅ አፈፍ ተደርጎ ይሄዳል... የሰፈሬን ጭጋጋማ ጠዋት ሁልጊዜም የምገልጠው በዚህ ሀዘን ነው:: ለምንድነው ትቼው የምሄደው? ለምን ወለድኩት? ትንሽ ቆይቶ የናት ፍቅር የማይገባው ልበ ቀዝቃዛ ልጅ አጎረምሳለሁ:: ዞር ብዬ ዞር ስል ጥርሱን ሳላየው ይነቅላል..ዞር ብዬ ዞር ስል ፂም ያቆጠቁጣል... ዞር ብዬ ዞ..ር የወደዳትን እንዴት እንደሚያናግር ሳያውቅ ልቡ ተሰብሯል... <<የኔ ልጅ? ምነው>> ብለው እንኳ ለአመል ባ'ፉ <<እማ>> እንደሚለኝ ባውቅም <<ልቡ ግን <<የት ነበርሽ?>> እንደሚለኝ እገምታለሁ.. ራሱን የምዳብሰው ተኝቶ ካገኘሁት በሁዋላ ነው.. አይኖቹን የምስመው ትንሽ መዳፎቹን እንደ ኩከምበር የዛሉ አይኖቼ ላይ ለቴራፒ ጣል የማደርገው ከእውቅናው ውጪነው... ቅርበቴን አያውቅልኝም ..እንደሚሉኝ አመሻሹ ላይ ውጪ ውጪ ሲያይ አምሽቶ ጨለማው በልቡ ያለችን ተስፋ እፍ ሲልበት ተስፋቆርጦ ለእንቅልፍ እጅ ይሰጣል... ያኔ ከማያልቀው መንገድ ተርፌ እግሮቼን እየጎተትኩ እገባለሁ... ብዙ እንዳልጠበቀ በትንሽ አእምሮው የተሳለች የመጀመሪያ ጠይም ማሪያሙን በየጨዋታው በወድቆ መባበሉ እና ለመብላት መለመኑ መሀል ሲያስብ እንዳልዋለ ጧ ብሎ ከተኛበት ጎኑ ላይ እጋደማለሁ... ሰውነቱን መልኩን እየመረመርኩ ከሁሌ <<ደህና ነው'ኣቸው>> በላይ ያለእውቅናዬ የሆነው ካለ እመረምራለሁ:: እንደዶክተር በተኛበት አይኑን እከፍታለሁ... ነጩም ነጭ ቡኒውም ደህና.... በጆሮው ጠጋ ብዬ ቃል ሳያወጣ ወደውስጥ <<ውድድ>> በል ስለው እንደሚለኝ ቃል ሳላወጣ ልል እሞክራለሁ.. በደመነፍስ እንዲሰማኝ የለህም የምለውን አምላክ አቆላምጠዋለሁ... <<እግዚአብሄርዬ ፍቅሬን በመለኮት አንሾካሹክልኝ...... 📷:)

photo content

ዘመነኞች ነን... ዘመን ደሞ ብዙ ያሳያል... ግዜ አይደለ እንዲህ ያለውን በሽታ አምጥቶ ያልገነንን የማንታሰበውን ደቂቃን ነገሮችን ባለግዜ ያደረገን? ...የሰው ልጅ ገላን ያህል ፈራሽ በስባሽ ቆሻሻ ነገር ተሸክሞ እየዞረ የሚሸት ትቦ ሽንት ቤት ላይ ተጠይፎ ምራቁን እንጢቅ ያደርጋል... ለእንዲህ እንዲህ አይነት ነገር ጥርስ ቢኖረኝ... ክትክት ብዬ እንድስቅ... ኢቺ እቺ ጢቅጢቅታ ተከማችታ እና ቋምጠው የሚበሉት ምግብ ተከማችቶ ሲወጣ ነው የሀገር ቆሻሻ የሚሆነው... እኔ ይሄን የተረዳሁ ለምን እነሱ ባለአምሮዎቹ ያን አይረዱም... ጥርስ የቅርብ ዘመዴ ነው በመሀላችን አፍ የሚባል ሁለት እንደየሰው ፍጥረት የተለያየ መጠን ያላቸው ከንፈር በሚባሉ ነገሮች የተለየን ቢሆንም ጥርስ የቅርብ ዘመዴ ነው:: እንዲህ ለክፉ ቀን እንድስቅበት ባይበደረኝም.. ጆሮም ጋ ቅርበት አለን እንደ አፍ እና ቤተሰቦቹ ባይሆንም... ጆሮ ነው በቅንፉ ወጥሮ አፉ ላይ ሳልንቀሳቀስ የሚያስቀምጠኝ... እንደጠባቂ እንደዘበኛ ይሰራዋል... ተጠባቂዎቹ አፍና አፍንጫ ናቸው ይሄ አፍንጫ የሚባለው እንደአፍ ለፍላፊ እና ግማታም አይደለም:: ዝምተኛ ነው ያገኘውን ሁሉ እንደአፍ አያግበሰብስም የሚወጣውንም የሚገባውንም እያጣራ ነው... ሀሳቢ እና ይሉኝተኛ ነው:: በፊት በፊት እንዲህ ሳንረክስ በፊት ዶክተሮች ላይ ነበር የምንሰካው ...ያስቃል ግን ዶክተሮች ታካሚን ንፅህናውን እንዲጠብቅ ሲመክሩ የበሰበሰ ወይም ሶስት ቀን ያልፋቁትን ጥርሳቸውን በኛ አፍነው ነው? አያስቅም ታዲያ? አሁንማ በየተራው ህብረተሰብ አፍ ላይ ተሰክተን ስንቱን አሸተትነው? የቡናውየቂቤው የበሶው የወተት የእንቁላል የቀይ ወጥ የተልባ የነጭ ሽንኩርት የአብሽ የቢራ የአረቄ ትምባሆው የተጠራቀመ ሽገን የባዶ ሆድ ኧረ ስንቱን.... ሰው ሰው የሚመስለው ከላይ ሲታይ ብቻ ነው ውስጡን ለእኛ ለእኛ ይተውት.... ግን ይሄ ሁሉ አላማረረንም ነበር ..ያማረረን ተጠቅመው ሲጥሉን በአግባቡ የምንበሰብስበትን ነገር አልሰሩልንም:: ልክ ዶክተሮች ሰርጀሪ ለሚያደርጉለት ታካሚያቸው አንስቴዢያው ሳይሰራ በግድየለሽነት እና ምንም አይሆንም በሚል ቸልታ ሰርጀሪ እንደሚሰሩት እኛም ላይ የሰው ልጅ እንደሱ አይነት ግፍ እየሰራብን ነው:: ወይ እንዳንቆይ ላንዴ ብሎ ሰርቶናል እንዳንሞት የማንበሰብስ አገር አብካች አቆሻሽ አርመጥማጭ አድርጎናል... ከነሞባይል ካርድ ላስቲክ የውሀ ፕላስቲክ ኮርኪ እና ክዳን ከሲጋራ ቁር ጋር በየመንገዱ በንፋስ ስንላጋ በዝናብ ስንታጠብ በጭቃ ስንለወስ እንውላለን.... ግፍ አይሆንም? ለእኛም ለእናንተም? የናንተው ማስክ ፊርማ: ከከንፈር ጋር በመተባበር የሊፕስቲክ ማህተም 💋 #ማስክኢዝዘኒውቆሻሻ

photo content

አብረን ስንሆን ስንሆን: ሰማይ ሴት ይሆናል:: መሀፀኑን ከፍቶ .. ለከፈከፍ አፈር ለንቃቃት መሬት ይሳሳና ይዘንባል:: ሲዘንብ .. የጠወለጉት ይፈካሉ እድሜያቸው እንደ እድሜያችን ፀሀይ ውጣት ድረስ እንደሆነ ያውቃሉ... ይኸው ክረምት አመት መጣ ልቤ ጭጋግ ውስጥ ቆሜ ለስንቱ አልፎ ሂያጅ አቃቂርን ሳወጣ.. ካልወደዱት የፃ'ይ ብርሀን ካላመኑት ጠፍ ጨረቃ ድንግዝግዙ በስንት ጣሙ በእውር ድንብር መዳሰሱ እስኪገኝ ነው የልብ አውቃ:: 📷 Awetahegn Ephrem

photo content

ዲር ፒሰስ... ፆም ገባ እኮ አትፆሚም ይሉኛል:: እቺን መከረኛ መሀተብ ካንገቴ እያዩ ...በረቡእ አጣፍጬ በጠበስኩት ጥብስ ጣእም ያጣ ህይወቴን ላጣፍጥ አድፍጬ ሲያዩኝ ተገርመው እየፆምኩ እኮ ነው:: አንተ በሌለህበት ምን ፍስክ አለና? ከፍቅር ...ከእቅፍ ...ከመሳም ከመተሻሸት ...ከድምፅህ ...ከቅርበትህ ...ከጠረንህ ...ከሜንት ትንፋሽህ ...ከቀልድህ ከንግግርህ .....እየፆምኩ ነው:: ብታይ (ማህተቤ)መስቀሌ ተሸረፈች ከሄድክ በሁዋላ ...ካንገቴ ላይ አውልቄ ፀጉሬን ሸብ አደረኩባት... ያንተን ንዴት በሷ ልወጣ ..ልንቃት ፈልጌ ባንተ የገባሁትን እልህ በሷ ላክክሰው ጨፍራራ ፀጉሬን ሰብስቤ አንዴ ሸብ ሳደርግባት የትንሽዬ አካሏ ግማሽ እጄ ላይ ቀረ:: ከመሰበሯ በፊት ...የተጣላን ሰሞን አያቴ ቤት ሶፋ ላይ ቀስ አድርጌ ጥያት ወጣሁ:: እሷን እንዳንተ አንቅሮ መተው ቀላል አልነበረም:: ለምን ብትል ሳትሰለች አንገቴ ዙሪያ ተጠምጥማ አቅፋኛለች:: ያለ ቦታዋ አንገቴ ላይ ስትቀመጥ ማንነቴን አታንፀባርቂውም ሀሳብሽ እና እኔ እንቃረናለን ብላ በመስቀልነቷ አልተመፃደቀችብኝም:: መስቀል ሳልሳለም ቤተስኪያን ደጅ ሳልረግጥ አንድ ሳንሆን አንድ ላይ ቆይተናል ...ይታይህ እንግዲህ ...ያውም አቅፋኝ እኮ ነው:: እና ልቤ ስብር ያለ ግዜ ... በውስጥ ለውስጥ ብስጭት ራሱን ባልገለጠ ሀዘን ...አይታኝ እንደምታዝንብኝ ነፍስ እንዳላት ነገር ቀስ ብዬ ከኪሴ አውጥቼ ሶፋው ላይ ጥያት መአት ታክሲ ተሳፍሬ ቤቴ ሄድኩ:: በበነጋታው ከአጎቴ ልጅ የደራ ወሬ መሀል <<እንኪ መሀተብሽን ረስተሽ >> ተብዬ እጄ መሀል በትዝብት ተመለሰች:: ጡቶቼ መሀል ለብቻዬ ሳይሆን በኩራት ከሹራቦቼ በላይ አኖራት ነበርና የሚያውቀኝ ያውቃት ነበር:: አንድ ቀን ነው ጥላኝ ያደረች... ከዛ በሁዋላ ግን ይመስለኛል ቅር ብሏታል ...ሁሌም ፊቷ ወደጀርባ ይገለበጥ ጀመር:: ደሞ ሌላ ግዜ ትዝ ብለኸኝ ጨለማ መሀል ቆሜ ስተክዝ የቅርብ የአንተ ተወካይ እሷ ነችና አሽቀንጥሬ ወደማይታየኝ ጥቁር ፅልመት ወረወርኳት .. በነጋታው በሬን ስከፍት የጠዋቷ ፀሀይ ሳትስመኝ በፊት የቤቴ በር መክፈቻ ላይ ተንጠልጥላ አገኘሁዋት.... ስጠይቅ አባቴ ካትክልቱ መሀል አንስቶ እንዳስቀመጠልኝ ነገሩኝ:: አልቅሳለች መሰል በውሀ ብስብስ ብላለች:: ለመጨረሻ ግዜ ልረሳህ ደቂቃዎች የቀሩ ቀን ባለሁ ግዜ ያልተፃፈልኝ ቅሽርሽር የይቅርታ ደብዳቤህ ደረሰኝና ምንም የማይለወጥ ስሜቴን የማይመታ ልቤን እንደበፊቱ የማይርዱ ጣቶቼን እየታዘብኩ አንብቤ ስጨርስ ስለሌለ ነገኣችን እርግጠኛ እንድትሆን አስቤ ልፅፍልህ በእልህ ጨፍራራ ፀጉሬን በሷው ሸብ አድርጌ ስክርቢቶ ላነሳ ስል ስሜቴ ላይ ትንሽ ብሽቀት እና ለምስኪን አካሏ የማይገባ ሀይል ነበረበትና ቀሽ አለች.. 💔 ምፅ ትንሽዬ ጉማጅ አካሏን መዳፌ መሀል አስቀምጬ ሁለት ነገር አሰብኩ.. 1 ልቤን ትመስላለች::(አሰባበሯ) 2 እየበነነ የጠፋውን ላንተ ያለኝን ስሜት.. (የመጨረሻው ቻው) 📷 Hilena Tafesse

ዝናብ ይጥላል.. ነጎድጏዳማ... ዝናብ እወዳለሁ..በተለይ እንዲህ ተኝቼ ..ነጎድጏድ ግን እጠላለሁ... እፈራለሁ:: ሽንቴ መቷል ማታ እንቅልፍ እንዲወስደኝ ብዬ የጠጣሁት ሶስት ቢራ ተጠራቅሞ ሆዴን ሞልቶት ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ.. ስነሳ ነጎድጏዱ ይንጎደጎዳል... ሽንቴን እያሯሯጥኩ ሸንቼ ኮምፈርቴ ውስጥ ጥቅልል ብዬ ገባሁ:: ልጅ እያለሁ አባቴ ጋቢ ውስጥ እገባ ነበር.. አባት አባት የሚል ሽታውን እየማኩ ከፍርሀቴ ልደበቅ ሰውነቱን ከፍቼ የመግባት ያህል እምሰዋለሁ... ከፍ ስል ከኔ በምታጥር አንዲት ጏደኛዬ ...መንገድ ላይ ዝናብ ይዞን ሰማይ ካስገመገመ ትልቅ ሰውነቴ ትንሽ ሆኖ እቅፏ ውስጥ ይሟሽሻል... አልንቀሳቀስም መሄድ መራመድ ያቅተኛል... አድጌ ለፍቅር ከበቃሁ በሁዋላ ደሞ አብረውኝ በነበሩ ወንዶች ... ያኔ ግን ምን አስተዋልኩ? ከፍርሀትም የሚበልጥ ሌላ ፍርሀት እንዳለ.. እንደዛ ነፍሴን የሚያስበረግገኝን ነገር እርግጠኛ ባልሆንኩበት ሰው ከመታቀፍ በላይ አልፈራውም ነበር ለካ... የውሸቴን ይመስል ይሆን? እንዲያቅፈኝ ፈልጌ ይመስለው ይሆን? ምናምን በሚባሉ የማይረቡ ጥያቄዎች ስወጠር ነጎድጏዱ ያልፋል:: እናም ምን ተማርኩ ?.. አስፈሪ የሚመስለው ሁሉ ከቻሉት እንደሚያልፍ... ከዛ በሁዋላ ነው የምደገፈው ነገር መሻት የተውኩት:: ግን ደሞ እንደብቸኝነት የሚያስፈራ ነገር የለም:: አለም ላይ ይሄ ሁሉ ህዝብ እየተርመሰመሰ ብቻዬን የሆንኩበት ምክንያት ግራ ይገባኛል... አንዳንዴ ብቻዬን ልሞት ይሆን የተሰራሁት ብዬ አስብና በደረቅ ሌሊት ድመት ስለማርባት አስባለሁ:: እዛ የልጅነት ማስታወሻ ብዬ ያስቀመጥኩት ሻንጣ ውስጥ ካሉ ወረቀቶች መሀል ለወደፊት ልጆቼ ያወጣሁላቸውን ስሞች እስጣቸውና በነሱ እየጠራሁዋቸው እያዋራሁዋቸው በፑርርፑርታቸው ታጅቤ እተኛለሁ:: ቢያንስ ከነሱ ውጪ ወተው አፈር ላይ እንዲፀዳዱ ብቻ ብጠብቅ ነው:: ሌላ ምንም! አልፈራቸውም.. የወደድኳቸውን ያህል ባይወዱኝ ግድየለኝም.. ፍቅሬ በዝቶ ይሆን ብዬ አልጨነቅም ... ማለት ያለብኝን ኤዲት አላረግም .. ዝምብዬ እወዳቸዋለሁ..ቢበዛ እቃዬን እንጂ ልቤን አይሰብሩም.. አየበረደኝ እያየ ጃኬት አውልቆ መስጠት ፊልም እንደሚመስለው አሪፍ ነኝ ባይ አልቀየማቸውም:: ማጉረስ ቲያትር እንደሚመስለው ቺርስ ሳይል እንደሚጠጣ እጄን መያዝ መደባበስ ድራማ እንደሚያረገው ቀዝቃዛ ዘመነኛ ነኝ ባይ አይደብሩኝም:: አንዳንዴ ሻማ አብርቶ ለምን ፍርፍር አይሆንም ሰርቶ ካልጠበቀኝ ወይንም የጡት ማሲያዣዬን ቁጥር ሰልሎ ፓንትና ጡት መያዣ ገዝቶልኝ የምርቃት ካልተናጨን ምኑን አብሮኝ ሆነ... ሳላስበው ካልሳመኝ ግምባሬን በእጆቹ ገፍቶ ከቁጢጤ ካልጣለኝ ካልተላፋኝ በልፊያው መሀል እየሳሳ በቆነጠጠኝ ቁንጥጫ የውሸት ካላስለቀሰኝ ... ምናምን ምን ያረግልኛል? ... አብሮኝ ሆኖ አብሮኝ ካልሆነ... ምን ያደርጋል? ለእንደሱ ለእንደሱማ ቁጡው ቅዱስ ገብሬልዬ ይሰልለኝ የለም ወይ? እነዚህ ነገሮች ካልሆኑ በህይወት መኖሬን ወጥቼ በመግባቴ ብቻ እንዴት እለካዋለሁ? መንገድ ላይ ያሉት ሰዎች እያዩኝ ባይሆንስ? የማወራው ባይሰማቸው ስራ ቦታዬ ላይ ሰው ወንበር ላይ ተቀምጬ ያልታዘዝኩትን ስራ እየሰራሁ ቢሆንስ ወይንም መስሎኝ ቢሆን... ፍቅር ሲኖር ...ሰው ሲኖር ...ደስታውም ሀዘኑም ልብ ይሞላል መሳቅ ማልቀሱ ማውራት መዝናናቱ የልብ መቁሰል መሻሩ ስማችን በሌላ ሰው መጠራቱ ሁሉ .. መኖራችንን ይነግረናል:: ቢሆንም ግን እንደዚህ እንደዛሬ ሲስገመገም አብሮኝ ሆኖ ጀርባውን ሰቶ ከሚያድር "ፍቅር ኦቨር ሬትድ ነው" ብሎ ከወዲሁ ልቡን ካደነደነ ሰው አልጋልብሴ በስንት ጣሙ ...ከብርድም ከነጎድጏድም ይደብቀኛል ... ማን ያውቃል ከእንዲህ አይነቱ ሰውና ከውጪው ብርድ ማን ይበልጥ እንደሚቀዘቅዝ? ... ይቅር... ምናልባት ድመት ማርባትሳይሻል አይቀርም.. ቢያንስ ቢያንስ አልፎ አልፎ ጭራቸውን መርገጥ ነው ... ሲሞነጭሩኝ መኖሬን አውቀዋለሁ... 📷 shalom b shalom

photo content