en
Feedback
Kolfe P.P - ብልፅግና

Kolfe P.P - ብልፅግና

Open in Telegram
1 671
Subscribers
No data24 hours
-177 days
-8030 days
Posts Archive
ትውልን በጠንካራ የትምህርት ስርዓት ውስጥ እንዲያልፉ ማድረግ የነገዋን ኢትዮጵያ መሠረት በአለት ላይ እንደማስቀመጥ ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና በሁሉም ፕሮግራሞቹ ላይ ቃሉን በተግባር የሚኖር ፓርቲ ነው። በምርጫ ማኒፌስቶ በገባነው ቃል መሠረት የትምህርት ስርዓታችን ሰፊ ማሻሻያ ተደርጎበት የአሁንና የመጭው ትውልድ ፍላጎት እና ጥቅምን በሚያስጠብቅ መልኩ እየተዘረጋ ያለ ስርዓት ነው። ትምህርት ላይ ፓርቲያችን ብልፅግና  ሁለት ተነጣጥለው የማይታዮ ስራዎች እንዳሉ በማመን እየሰራባቸው ነው። ጥራትና ተደራሽነት ሁለቱም የየብቻ ውጤት አልቦ ናቸው። ጥራት ያለው ግን ተደራሽ ያልሆነ ትምህርት ስርዓት ቢዘረጋ ፍትሃዊነትን ያጓድላል። ለተወሰነው የህብረተሰብ ክፍል እድል ሰጥተን የተወሰነውን እንነፍጋለን ማለት ነው። ይህ ደግሞ የማይሆን ነው። ለዚህም ተደራሽነት ላይ አንደራደርም ማለት ነው። ተደራሽነት ላይ ሰርተን ጥራቱን ካላስጠበቅን ትምህርት ከንቱ ልፋትና ድካም ይሆናል። የመከነ፣ ጊዜውን በከንቱ ያባከነ ትውልድ ይፈጠራል። ይህ ደግሞ ዛሬንም ነገንም እንደመግደል ይቆጠራል። ለዚህ ነው ፓርቲያችን ለተደራሽነትም ለጥራትም ሳይነጣጠሉ የሚሰራው። አለምን የሚቀይሩ ፈጠራዎችን ለመፍጠር መማር ወሳኝ ነው። በትምህርት የታነፀ ትውልድ ሀገርን ይገነባል። አዳዲስ ለአለም የሚያስፈልጉ እና የሚጠቅሙ ፈጠራዎች በተማረ ትውልድ የሚመጡ ናቸው። ትውልን በጠንካራ የትምህርት ስርዓት ውስጥ ተምረው እንዲያልፉ ማድረግ የነገዋን ኢትዮጵያ መሠረት በአለት ላይ እንደማስቀመጥ ነው። መማር ምክንያታዊ ትውልድን ይፈጥራል። ምክንያታዊ ትውልድ ሲፈጠር ለሚሰራውም፣ ለሚሰማውም፣ ለሚሰማራበትም ጉዳይ ምክንያት ይኖረዋል። በሚያደርገው ጉዳይ የመጨረሻ ውጤቱን እና ጥቅሙን ያውቃል። ትውልድ በምክንያት የማይንቀሳቀስ ከሆነ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በብቃት አይወጣም። የራሱን አሻራ ከማስቀመጥ ይልቅ ሌሎች እንደፈለጉት ይጠመዝዙታል። ትምህርት ለሁሉ ነገር መሠረት ነው። ሀገርን ለማበልፀግ በአስተሳሰብ በተግባር ለሀገር ብልፅግና የሚሰራ ትውልድ ያስፈልጋል። "የተገነባ ጭንቅላት የፈረሰ ከተማን ይገነባል" እንዲሉ የተገነባ ትውልድ ለመፍጠር ትምህርት ላይ ማተኮር ይፈልጋል። ፓርቲያችን ብልፅግና ጠንካራ የትምህርት ስርዓት ለመገንባት በሙህራን በማሳትፍ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል። ለትምህርት ተደራሽነት የሚያግዙ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ስራ ተሰርቷል። በክ/ከተማችን እንኳን በአጭር ጊዜ ውስጥ በትምህርት ማስፋፋት ላይ የተሰሩትን ስራዎች ብናይ በጣም በርካታ ናቸው። ማስፋፋቱ ላይ ሳለን የትምህርት ጥራት ላይ በርካታ ሪፎርም ተካሂዷል። የተጠና የትምህርት ካርኩለም ተቀርፆ ወደ ተግባር ማስገባት ተችሏል።  ለትምህርት ጥራት ካርኩለም ብቻ በቂ ስላልሆነ ተማሪዎች የክፍል ጥምርታ በስታንዳርዱ ለማድረግ በርካታ የማስፋፊያ ስራ ተሰርቷል። የመምህራንን ብቃት ማሳደግ ለጥራት አስፈላጊ በመሆኑ ብቃታቸውን ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል። ትምህርት ቤቶችን ውብና ፅዱ በማድረግ ተማሪዎች ትኩረታቸው ትምህርት ላይ እንዲሆን ለአእምሮ እረፍትና መነሳሳት የሚፈጥር የትምህርት ቤት አካባቢ መፍጠር እየተቻለ ነው። መንግስት ትውልድ ላይ ኢንቬስት በማድረግ ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን ታሳቢ አድርጎ የሚሰራ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል። የትምህርት ቤት ምገባ ትውልድ ላይ ኢንቬስት የማድረግ ትልቅ ተግባር ነው። የተማሪዎች ደብተር፣ እስኪርብቶ፣ ዩኒፎርም የመሳሰሉትን በማሟላት ተማሪ ብቻ ሳይሆን ወላጅ እፎይ ብሎ ትምህርት ላይ ብቻ እንዳተኩሩ የመስራት ስራ ነው። ለትውልድ እንሰራለን የምንለው በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ነው የምንለው የነገዋ ኢትዮጵያ ስለምታሳስበን ነው። የነገዋን ኢትዮጵያ ዛሬ ካልገነባናት ነገ የልጆቻችን እዳ ነው የምናወርሰው።  ለትውልድ እዳን ሳይሆን ምንዳን ለማውረስ መስራት ደግሞ ከእኛ ይጠበቃል። ዛሬ ትውልዱ ላይ በመስራት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በጋራ እንትጋ! #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !

photo content

ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር እንደመሆኗ የሚመጥናት ታላቅነት ላይ እንዲትሆን መስራት ይጠይቃል። ኢትዮጵያ ከእዳ ወደ ምንድ እየተጓዘች ያለች ሀገር ነች። በእርግጥ ከእዳ ወደ ምንዳ ለመሸጋገር ትርክትን ማስተካከል ይጠይቃል። ከብሔርተኝነት ወጥቶ ብሔራዊነትን መላበስ ይሻል። የእኔ ብቻ ከሚል ተሻግሮ የእኛ ማለት አለብን። ያለንን ወረትና ሀብት ብሎም እምቅ አቅም አውቆ መስራት አለብን። በእውቀትና በእውነት መምራት የሚለውን በተግባር መግለጥ የእኛ ድርሻ ነው። ኢትዮጵያዊያን ልዩነቶች ቢኖረንም በርካታ የወል (የጋራ) ማንነት የገነባን ህዝብ ነን። ኢትዮጵያዊያን የጋራ ማንነት ብቻ ሳይሆን የጋራ ድል እና ታሪክም አለን። በእርግጥ ኢትዮጵያዊነት የበርካታ ማንነቶች ድምር ውጤት ነን። በማንነትታችን ወስጥ የወል እና  የነጠላ እውነት አለ። የራስን ማንነት ብቻ ነጠላ እውነትን በመለጠጥ እና ያለ አግባብ በማስፋት የግል ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ የሚሰሩ ጥቂት ግለሰቦች አሉ። ጠቃሚው ጉዳይ ነጠላ እውነታ እንዳለን ሁሉ እኛ ኢትዮጵያዊያን የወል ማንነት ገንብተናል። ነጠላ እውነትም የወል እውነትም አለ። ነጠላ እውነት ያለው የሌላውን አውነት ለመስማት እስከተዘጋጀ እውነታው ጠቃሚ ይሆናል። ሀገራችን ኢትዮጵያ የኢትዮጵያዊያን የወል እውነት ነች። ሀገር እውነት ከመሆኗ ተጨማሪ የወል (የጋራ) ነች። የወል እውነትን ለሁላችንም በሚጠቅም በሚያግዝ መንገድ መገንባት ለሁላችንም ይጠቅማል። እኛ ኢትዮጵያዊያን ከእኔነት ይልቅ እኛነት ያገዘፈን በብሔር፣ በጎጥ፣ በሰፈርና በጎሳ ከማሰብ ተሻግረን ስለ የጋራ ቤታችን ኢትዮጵያ ግንባታ እድገትና ብልፅግና የምንተጋ ህዝብ ነን። ይህንን ስናደርግ ደግሞ ከብሔርተኝነት ወጥተን ብሔራዊነት ደረጃ ላይ መድረስን የሚያሳይ ነው። ከሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ፣ ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ያለው ህዝቤ ተጠቃሚነት መረጋገጥ የእኔ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ነው ብሎ ማሰብ ሲቻል ብሔራዊነትን መኖር እንችላለን። የትርክታችን ማጠንጠኛ ቢያንስ ብሔራዊነት ከቻልን አርበኝነት ነው። አርበኝነት ለኢትዮጵያዊያን በአባቶቻችን በተግባር የተኖረ ማንነት ነው። በአድዋ ተራራ ላይ በጋራ የተሰውት የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ከማስጠበቅ በማንም አለመገዛትን ከማስቀረት የተሻገረ ለሰው ልጅ የማሰብ የሰውን ልጅ እኩልነት በተግባር የማረጋገጥ ጉዳይ ነው። ቅድመ አያቶቻችን ለመላው የሰው ልጅ ነፃነት እኩልነት ሲሉ ተዋድቀዋል፣ ተሰውተዋል። አርበኝነት በየትኛውም የአለም ጫፍ ስለሚኖር የሰው ልጅ ብሎ መስራት ማለት ነው። ቅድመ አያቶቻችን በአድዋ ተራራ ላይ ለሰው ልጅ እኩልነት ሲሉ የበላይ የበታች የሚለውን የጭቆና ቀንበር ከአለም ላይ እንድነሳ ሲሉ ከተዋደቁ የአርበኝነት በወረትነት አለን ማለት ነው። ፓርቲያችኝ ብልፅግና ደግሞ ወረቶችን ጠብቆ በማከማቸትና በማካበት ለትውልድ ጥቅም እንድውሉ የሚሰራ ፓርቲ ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን ብሔራዊነትን መላበስ ግዴታችን ከቻልን ደግሞ የቅድመ አያቶቻችን ወረት ይዘን አርበኞች መሆን ይጠይቀናል። ሁላችንም ለሰው ልጅ በሙሉ የሚጠቅም በመስራት አርበኞች እንሁን። #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !

photo content

ብልፅግና ፓርቲ የትርክቱ ዋነኛ ማጠንጠኛ ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ነው። ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ስር ሲሰድ የሰው ልጆች ስጋዊ ዝምድና አካባቢያዊ ማንነት ወይም በሌሎች መገለጫዎች አጥር ውስጥ ሳይገደቡ እርስ በእርስ የሚደጋገፉበት፣ አንዱ የሌላኛውን ችግር ለመቅረፍ የሚተጋበት እሴት ነው። የእኩልነት እና የነፃነትን ጥያቄዎች በዴሞክሬሲያዊ መንገድ ለመፍታት የወንድማማችነት እሴት መዳበር በእጅጉ ወሳኝ ነው። ወንድማማችነት/ እህትማማችነት ሲዳብር በመርህ ላይ ተመስርቶ የእኩልነት እና የነፃነትን ጥያቄዎች በቀላሉ መፍታት ይቻላል። በአንድ ሀገር ውስጥ የሚኖርን የህዝቦች የእርስ በእራስ መተማመን፣ አንዱ ለሌላው አለኝታነቱ እየጨመረ በወንድማማችነት/ እህትማማችነት እሴት እያደገ ሲመጣ ሀገራዊ ብልፅግና እውን ይሆናል። ነገ ብቸገር የሚረዳኝ፣ አደጋ ቢገጥመኝ የሚደርስልኝ፣ ብታመም የሚያክመኝ ዘመድ አዝማድ፣ ወዳጅ ጎረቤት፣ ሀገር ወገን አለኝ ብሎ የሚያምን ሰው ለራሱም ሆነ ለማህበረሰቡ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ የላቀ ነው። ይህንን ስሜት እንዲዳብር የሚያደርገው ደግሞ የወንድማማችነት/ እህትማማችነት እሴት ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን የተጋመድን፣ የተዛመድን፣ የተዋለድን፣ ለሀገር ክብር አንድ ላይ ተዋድቀን በአንድነት መስዕዋትነት የከፈልን የጋራ ማንነት ያለን ህዝብ ነን። በአድዋ ተራራ ላይ ነፃነትን ለማስጠበቅ አንድ ጉድጓድ የተቀበረው በርካታ ማንነት በኢትዮጵያዊነት ነው። ኢትዮጵያዊያን የአድዋን ድል ያበሰርነው የሀገራችንን አልገዛም ባይነት ብቻ ሳይሆን የሰውን ልጅ እኩልነት የመላው አለም ጭቁን ህዝቦችን ነፃነት ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን ከራስ የተሻገረ ለሰው ልጅ በሙሉ እኩልነትና ነፃነት የመታገል ልምድ ያለን አርበኛ ህዝብ ነን። አርበኝነታችንን በወንድማማችነት/ እህትማማችነት እሴታችን አበርትተን  የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ። #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

photo content

ፓርቲያችን ብልፅግና ሰው ተኮር ፓርቲ ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና መነሻውም መዳረሻውም ሰው ተኮርነት ነው። የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬት ለኢትዮጵያ ህዝቦች ምቾትና ድሎት መፍጠር ነው። በሰው
ፓርቲያችን ብልፅግና ሰው ተኮር ፓርቲ ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና መነሻውም መዳረሻውም ሰው ተኮርነት ነው። የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬት ለኢትዮጵያ ህዝቦች ምቾትና ድሎት መፍጠር ነው።  በሰው ተኮር ተግባራችን የአቅመ ደካማ እናቶች ቤት ከዝናብ፣ ብር፣ ፀሀይ እያፈራረቀ ከማሳቀቅ ወጥቶ ሲያዩት የሚያምር ቅንጡ ቤት ገንብቶ መስጠት እውን የሆነ ተግባር ነው። የሰው ተኮር ተግባራችን በርካታ የሰውን ህይወት መቀየር የቻሉ ሰፋፊ ስራዎች ተሰርተዋል። በቀን አንድ ጊዜ መመገብ የማይችሉ የመመገቢያ ማዕከላት ተገንብተው አገልግሎት እንድሰጡ ማድረግ ተችሏል። በሰው ተኮር ተግባራችን "ምግባችንን ከደጃችን" በሚል ሀሳብ በሌማት ትሩፋት ብዙ ምርት ማገኘት ብቻ ሳይሆን የአመለካከት ለውጥ ማምጣትም ችሏል። ቦታ የለኝም፣ ከተማ ላይ የግብርና ስራ አያዋጣም የሚሉት ምክንያቶችን ያሸነፈ በትንሽ ቦታ በቂ ምርት ያስገኘ ስራ ተሰቷል። ተመግበው የማያድሩ ወገኖቻችንን ማዕድ በማጋራት ጓዳቸውን በወንድማማችነት/ በእህትማማችነት ስሜት መሙላት የተቻለበት ስራን እውን አድርጓል። የትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ የነገውን ትውልድ ለማነፅ ከሚሰሩት ስራዎች መካከል ከመሆኑ ባሻገር የሰው ተኮርነት ተግባርም ነው። በርካታ ተግባራት በሰው ተኮርነት ተፈፅመዋል። የሰው ተኮር ተግባራችን ተጠናክሮ በመቀጠል የምናልማትን የበለፀገች ሀገር እውን እናደርጋለን። #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

የመደመር ትውልድ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እያደረገ ያለ ትውልድ ነው። በመደመር ትውልድ የነበረንን ጥሩ ስራ ወረቶች አድርጎ የሚያስቀጥል የሚያሳድግ እና የሚያከማች ትውልድ ነው። የመደመር ትውልድ
የመደመር ትውልድ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እያደረገ ያለ ትውልድ ነው። በመደመር ትውልድ የነበረንን ጥሩ ስራ ወረቶች አድርጎ የሚያስቀጥል የሚያሳድግ እና የሚያከማች ትውልድ ነው። የመደመር ትውልድ ትናንት የተሰሩ ስተቶች፣ ሳይሰሩ የቀሩ ስራዎች በስራው ወቅት የነበሩ ድክመቶች እዳ ናቸውና ልንከፍላቸው ይገባል ብለው ያምናሉ። ከማመን የተሻገረ የትናንት እዳን እየከፈለ የነበረውን ወረት እያካበቱ ከእዳ ወደ ምንዳ ሀገራችንን እያሻገረ ይገኛል። የመደመር ትውልድ የኢትዮጵያ የትናንት ችግር የሚፈታው በወንድማማችነት/ እህትማማችነት እሴት ነው ብሎ የሚያምን ነው። የመደመር ትውልድ ትናንትን በዛሬ የበለጠ አሳምሮ የሚገነባ ለነገ መሠረቱን በጠንካራ እና ዘመን ተሻጋሪ አድርጎ የሚገነባ ትውልድ ነው። በመደመር እሳቤ ተመርተን የበለፀገች ኢትዮጵያን በጋራ እውን እናድርግ! #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን ኢትዮጵያን ውብ ጠንካራ አንድ አድርገው የገነቧት ብዙ ማንነቶች ማሳያ መድረክ ነው። ኢትዮጵያ ብዙ ማንነቶች፣ ባህሎች፣ ወጎች እንደ ቀስተ ደመና ቀለም ተዋህደው ልዩ ውበት ከጠንካራ አንድነት ጋር አላብሰዋታል። ሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ለኢትዮጵያ ጠንካራ መሆን በአንድነት እና በጋራ በርካታ ታሪኮችን ሰርቷል። በጋራ አንድ ሆኖ የጋራ ማንነትን ሰርቷል። ከሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት የማይለያይ እጣ ፋንታ ያላቸው በመከባበር ላይ የተመሰረተ አንድነትን አጠናክረው ቀጥለዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ውብ ባህሎቿ አንዱን ሌላኛው ለማወቅ እድል የሰጠ ከመሆኑ ባሻገር ጠንካራ ትስስር እንድኖር አድርጓል። አንዱ የአንዱን ወግ፣ ባህል፣ ስርዓት ሀብቱ እና ውበቱ አድርጓል። በአንዱ አካባቢ የሚገኘው ተፈጥሮ ለሌላኛው አካባቢ አስፈላጊ በመሆኑ አንዱ ለአንዱ የሚፈላለግና የሚዋደድ እንድሆን አድርጎታል። ኢኛ ኢትዮጵያዊያን እጣ ፋንታችንን በጋራ እየወሰንን ሉዓላዊነታችንን አስከብረን ትልልቅ ገድሎች እና ታሪክ እየሰራን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሻገር የቻልንበት ታሪክ አለን። ኢትዮጵያውያን የራሳችንን እኩልነት፣ ነፃነትና መብት ከማክበር ተሻግረን የሰው ልጅ እኩልነትን አንዱ ከሌላው የማይበልጥ መሆኑን በአድዋ ተራሮች ላይ እኩል አስፈላጊውን መስዋዕትነት በመክፈል ለአለም አስተምረናል። ለአፍሪካ የእንችላለን መንፈስን ለአለም የሰው ልጅ ሁሉ እኩልነትን ያስተማርንበት የትናንት ወረታችን ነው። ዛሬ ላይ ፍትሃዊነት መከበር አለበት የራስን ጉዳይ በራስ የመፍታት መብትን አሳልፈን አንሰጥም የሚለውን ትምህርት የመደመር ትውልድ ከዳር እስከዳር አንድ ላይ ሆኖ ያሳየበት የህዳሴ ግድባችን አንዱ ለትውልድ የተሰራ ታሪክ ነው። ኢትዮጵያ ልጆቿ እንችላለን ብለው የጀመሩት ሁሉ ችለው አሳክተው አሳይተዋል። እንችላለን ብለው ጀምረው ያሳኩት ደግሞ በብዙ ማንነት ውስጥ ትልቁን ኢትዮጵያዊ የጋራ ማንነትን በተላበሰ መንገድ ነው። ስንዴ ከመለመን ወጥተን ወደ ውጭ የሚላክ መጠን ማምረት የቻልነው በጋራ በአንድነት በተባበረ ክንድ መስራት በመቻላችን ነው። አረንጓዴ አሻራ ለአለም የእንችላለን መንፈስን ያሳየው ሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ዳር እስከዳር በእኩል መንፈስ መስራት በመቻሉ ነው። ኢትዮጵያ የተሟላች ኢትዮጵያ፣ ትልቋ እና ሀያሏ ኢትዮጵያ መሆን የምትችለው በሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ህዝቧ አንድነት ላይ ተመስርታ ነው። የጥንካሬዋ፣ የውበቷ፣ የተስፋዋ፣ የትናንት ገድሏ ምንጭ የሁሉም ብሔር ብሔረሰብ የጋራ የተዋሃደ አንድነት ነው። የገነባነውን የጋራ ማንነት አጠናክረን ሁሉንም ማንነቶች በእኩል አክብረን የተሰናሰለ የማይለያይ የጋራ እጣ ፋንታችንን የበለጠ አጠናክረን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ይገባናል። አንዱ ለአንዱ አስፈላጊነቱን የሚረዳው አንዱ ሌላኛውን ባወቀው ልክ ነው። የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ደግሞ አንዱ የሌላኛውን ወግ፣ ባህል፣ ስርዓት እንዳውቅ በማድረግ የባህል የወግና ስርዓት ውርርስን በመፍጠር የበለጠ ውብ ጠንካራ አንድነትን በመፍጠር የጋራ ማንነታችንን ያጠናክራል። አንተ ለእኔ እኔ ለአንተ በእጅጉ አስፈላጊ ነኝ የሚለውን በመረዳት በፍቅር የተሳሰረ እና የሚተሳሰብ ማንነትን ይፈጥራል። በመከባበር፣ በመፈቃቀር፣ በመተሳሰብ ላይ የተመሠረት ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን አጠናክረን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የመደመር ትውልድ ኃላፊነትና አደራ ነው።  ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ። እንኳን ለኢትዮጵያ 18ኛው የብሔር ብሔረሰበቦች ቀን አደረሳችሁ። #መልካም_ቀን_ይሁንለዎ ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

እንኳን ለብሔር ብሔረሰቦች ቀን በሰላም አደረሰን/ አደረሳቹ!! ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ብዙ ሆነን አንድ፣ አንድ ሆነን ብዙ የምንሆንበት፣ ለጋራ ግብና አላማ የምንደመርበት ቀመር ነው። በብዙሃነታችን ደምቀን፣ በአንድነታችን በርትተን ወደፊት የምንራመድበት የውበትና የጥንካሬያችን ምንጭ ነው። kolfe prosperity party

በምግብ ራስን መቻል የሀገር ክብርን መጠበቅ ሉዓላዊነትን ማስከበር መቻል ነው። በምግብ ራስን መቻል በቂና የተመጣጠነ ምግብ ከማግኘት ባሻገር ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋርም በቀጥታ የተቆራኘ ነው።
በምግብ ራስን መቻል የሀገር ክብርን መጠበቅ ሉዓላዊነትን ማስከበር መቻል ነው። በምግብ ራስን መቻል በቂና የተመጣጠነ ምግብ ከማግኘት ባሻገር ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋርም በቀጥታ የተቆራኘ ነው። እንደ ሀገር በምግብ ራስን መቻል በኢኮኖሚያዊ ረገድ ፈጣን እና አስተማማኝ ውጤቶችን ከማስመዝገብ ባሻገር በፖለቲካዊ ጉዳዮችም መረጋጋትና ሰላምን በቀላሉ ለማስፈን ሚናው በእጅጉ የጎላ ነው፡፡ በተግባር ሲታይ በምግብ ራስን መቻል በተለያዩ መንገዶች የሚገለጽ እና የሚለካ ቢሆንም ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመከተል የሀገር ውስጥ የምግብ ምርትን በመጨመር በቤተሰብ ደረጃ ማሳካት መቻል መሆኑንም ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡ እንደ ኢትዮጵያ በዚህ ጽንሰ-ሃሳብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሃሳብ አመንጪነት “የሌማት ቱሩፋት” የተሰኘ መርኃ ግብር ይፋ ሆኗል፡፡ በምግብ ራስን መቻል በቂ የሆነ እና የተመጣጠነ ምግብ ከማግኘት ባሻገር ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋርም በቀጥታ የተቆራኘ መሆኑን ተከትሎ የሌማት ቱርፋት ዘመቻ በፍጥነት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እየተተገበረ ይገኛል፡፡ የሌማት ትሩፋት የምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የወጪ ንግድን ገቢ ማሳደግ እንዲሁም ከውጭ የሚገባ ምርትን በሀገር ውስጥ መተካት ላይ ትኩረቱ የሚያደርግ ልማታዊ ዘመቻ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የሌማት ቱርፋት መርኃ ግብርን ባስጀመሩበት ወቅት በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ራስን መቻል ጉዳይ ኢትዮጵያ ካረጋገጠች በሀገር ደረጃ ያለው በምግብ ራስን የመቻል ሩጫ በቀላሉ የሚሳካ ሲሆን ለቀጣዮች አራት ዓመታት ይህንን በማሳካት ዶሮ፣ ስጋ፣ ወተት፣ ማር እና አሳን ማትረፍረፍ እንችላለን ብለዋል፡፡ ውጤት እያመጣም ይገኛል።

የሀገር ብልፅግናን ከሚገቱት ጉዳዮች አንዱና ትልቁ ሌብነት ነው። ሌብነት የሀገር ብልፅግና ዋነኛ ፀር ነው። ሌብነት የትውልድ ሰርቶ የመለወጠ ተስፋን የሚያጨልም በአቋራጭ መክበርን የሚመኝ ትውልድ በመፍጠር ሀገርን ከትውልድ ጋር ሊያጠፋ የሚችል አደገኛ የነቀርሳ በሽታ ነው። ሌብነት እንደምናውቀው ከኢኮኖሚያዊ ምዝበራው እና የትውልድ ሰርቶ የመለወጥ እሳቤን ከመግደል ባሻገር የሀገር መረጋጋት እንዳይኖር ሰላም እንዳይሰፍን በከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል። ሌባ ስራው ሀብት መዝረፍ ብቻ አይደለም። ይልቁንም ሰላም እና ሀገራዊ መረጋጋት ከመጣ ተጠያቂነት ይሰፍናል። ሌብነታቸው ተጋልጦ ተጠያቂ እንሆናለን ብለው ስለሚያስቡ በቻሉት መጠን አለመረጋጋት እንዲኖር ሰላም እንዳይሰፍን አጥብቀው ይሰራሉ። በሌብነት ውስጥ ተቀባዩ ዋና ሌባ እና የሀገር ጠላት ቢሆንም ሰጭውም ሌብነት እንድንሰራፋ የራሱን አስተዋፅኦ ያበረክታል። ሰጭ በሌለበት ተቀባይ አይኖርም። የማይገባውን ያልጠየቀ ለማይገባው አካል የማይገባውን ክፍያ ለመፈፀም አያስብም። በተገቢው ህጋዊ መብቱን አሳልፎ በገንዘብ የሚገዛ ደግሞ ከባርነት የተሻለ አስተሳሰብ አይኖረውም። የሚገባውን መብቱን በገንዘብ የሚገዛ ከሆነ የዜግነት ግደታውን አልተወጣም። የማይገባውን ለማገኘት ገንዘብ ከከፈለ ከፋዩ ዋና ሌባ ነው። ትግላችን ተቀባዩ ጋር ብቻ መሆን የለበትም ሰጭውም ጭምር እንጂ። ዜጋ ማሰብ ያለበት መብቱ የሆነውን አገልግሎት ለማገኘት ገንዘብ ከከፈለ ሰላሙን የሀገሩን መረጋጋት የሚረብሽ አካል በገንዘቡ እየገዛ ነው። የማይገባውን ለማገኘት ገንዘብ ከከፈለ ሌባ ነው ሌላኛው ሌባ ጋር ጥምረት ፈጥሮ ሀገር ለማጥፋት ትውልድ ለማምከን እየሰራ ነው። ሀገር ወዳድነት በቡዙ ይገለጣል። ሀገር ወዳድ መሆናችንን እራሳችንን ከሌብነት የፀዳ በማድረግ ሌቦችን በማጋለጥና በመታገል እናሳይ። የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ከሌብነት የፀዳ አገልግሎት እውን እናድርግ። እራሳችንን ከሌብነት ነፃ አድርገን ሌቦችን በማጋለጥና በመታገል በስነ ምግባሩ የሚመሰገን ዜጋ እንፍጠር። መልካም ቀን ይሁንለዎ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ኃላፊነት አለበት። ሀገር የምትገነባው በሁሉም ሰው ኃላፊነቱን የመወጣት ሂደት ውስጥ ነው። ኃላፊነት ትልቅ አደራ ነው። የማይወጡትን ኃላፊነ
የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ኃላፊነት አለበት። ሀገር የምትገነባው በሁሉም ሰው ኃላፊነቱን የመወጣት ሂደት ውስጥ ነው። ኃላፊነት ትልቅ አደራ ነው። የማይወጡትን ኃላፊነት መውሰድ የተሰጠን አደራ እንደመብላት የማይገባውን እንደመውሰድ ይቆጠራል። ኃላፊነትን በቅጡ ጠንቅቆ ማወቅና ለምን እንደሚሰራ መልስ መስጠት ወሳኙ ጉዳይ ነው። አንዳንድ ጊዜ የምንሰራው ኃላፊነታችንን ለመወጣት ሳይሆን አዩኝ አለዩኝ ብለን የግለሰቦችን ሙገሳ እና ምስጋና ፈልገን ከሆነ ኃላፊነት መወጣት ይሳነናል። ምክንያቱም ምስጋናቸውን በቸሩን ጊዜ በተቆጣጠሩን ወቅት የበለጠ እንሰራ እና ቁጥጥርና ምስጋና ሲቀር ኃላፊነት መወጣትን እንተዋለን። ከዚህ ከፍ ብለን የተሰጠንን ኃላፊነት መወጣት ለኢትዮጵያ ብልፅግና ስኬት የበኩላችንን ድርሻ ማበርከት ነው። ለነገ ለልጆቼ ምቹ ሀያል የበለፀገች ሀገር እየገነባን ነው። በግንባታው ውስጥ እኔም ድርሻ አለኝ። ድርሻዬ ደግሞ የተሰጠኝን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት ሙሉ ሰዓቴን በአስፈላጊ ስራ ውስጥ ማሳለፍ ነው ብለን ስንሰራ ኃላፊነታችንን መወጣት ይቻለናል። የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የድርሻችንን ማበርከት እንችላለን። በተሰማራንበት ሁሉ ኃላፊነታችንን በአግባቡ እንወጣ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ። መልካም ቀን ይሁንለዎ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

ኢትዮጵያ የሚገጥሟትን ፈተናዎች በድል የማለፍ ልምድ ያላት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ በየዘመናቱ በርካታ ችግሮች ገጥመውናል። ችግሮቹ ከውጭ ያሉ ጠላቶቻችን ከውስ ያሉ ባንዳዎች ተቀናጅተተው ሲፈጥሯቸው የነ
ኢትዮጵያ የሚገጥሟትን ፈተናዎች በድል የማለፍ ልምድ ያላት ሀገር ናት። ኢትዮጵያ በየዘመናቱ በርካታ ችግሮች ገጥመውናል። ችግሮቹ ከውጭ ያሉ ጠላቶቻችን ከውስ ያሉ ባንዳዎች ተቀናጅተተው ሲፈጥሯቸው የነበሩ ናቸው። ነገር ግን እኛ ኢትዮጵያውያን ፈተናን በድል ችግርን በብልሃት ወደ እድል እየቀየርን የሀገራችንን ክብር አስጠብቀን ቀጥለናል። የሚገጥሙንን ፈተኔዎች ያለፍነው በጀግንነት ነው። ፍትህን የሚያጓድሉ ፍትህ እንዳይጓደል በመታገል፣ ለሰው ልጅ ክብር የሌላቸው ለሰው ልጅ ክብር እንድሰጡ በማድረግ አሸናፊ ሆነን ቀጥለናል። ትግላችን ለእውነት እና ለፍትህ ነው። መዋደቃችን ለሀገር ክብርና ሉዓላዊነት ነው። ኢትዮጵያ በርካታ ጀግኖች ልጆች አሏት። በተቃራኒው ደግሞ የእናት ጡት ነካሽ ሆነው ከጥቅሟ ተቃራኒ የሚቆሙ ትንሾች አይጠፉም። ሀገር ለመሸጥ የሚያስማሙ ትንሾችን እያሸነፍን ጠላቶቻችንን በየጊዜው እያሸነፍን የገጠሙንን ፈተናዎች በድል ማለፋችንን እንቀጥላለን። ኢትዮጵያ በልጆቿ ታፍራ ተከብራ በአለም አደባባይ አሸናፊ ሆና ትቀጥላለች። ለዚህ ደግሞ ሁላችንም በተሰማራንበት ኃላፊነታችንን በመወጣት የበለፀገች ሀያል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ይገባናል። መልካም ቀን ይሁንለዎ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

የመደመር ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ አሻራውን አሳርፎ የሚያልፍ ትውልድ ነው። ትናንት በርካቶች አሻራቸውን አሳርፈው በማለፋቸው ለዛሬዎቹ መነሻ ሆኖናል። በተቃራኒው አሻራ ማሳርፍ ሳይችሉ የቀሩባቸው የትው
የመደመር ትውልድ ለቀጣዩ ትውልድ አሻራውን አሳርፎ የሚያልፍ ትውልድ ነው። ትናንት በርካቶች አሻራቸውን አሳርፈው በማለፋቸው ለዛሬዎቹ መነሻ ሆኖናል። በተቃራኒው አሻራ ማሳርፍ ሳይችሉ የቀሩባቸው የትውልዱ እዳ ሆነው እናያቸዋለን። አሻራ ማሳረፍ የሁሉም ዜጋ ተግባር ነው። አሻራ ስናሳርፍ ዘመን ይሻገራል ምንዳ ሆኖ ለትውልድ ይተርፋል። በተሰለፍንበት ስራ ሁሉ አሻራችንን በማሳረፍ የበለፀገች ኢትዮጵያን በጋራ እንገንባ። መልካም ቀን ይሁንለዎ! #kolfe Prosperity Party - ብልፅግና

ነገን ዛሬ እንሰራዋለን። የትኛውም ነገ በትናንቶች የተሰራ መሠረት አለው። ዛሬ ያልጀመርከው ግንባታ ነገ ፎቅ ሆኖ አታየውም። ዛሬ ያልተተከለ ችግኝ ነገ ዛፍ ሆኖ ጥላ መሆን ምግብ መሆን የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም አይችልም። ዛሬ ላይ ሆነን ያልዘራነው ፍቅር ነገ በፅኑ መሠረት ላይ የተገነባ አንድነትን ሊወልድ አይችልም። መከባበር፣ ወንድማማችነት/ እህትማማችነትን በተግባር እንዲኖሩ ያላስተማርናቸው ልጆች ነገ በመከባበር አንተ ለእኔ አስፈላጊ ነህ ብለው ተፋቅረው መኖር ይከብዳቸዋል። ዛሬ በህዝብ ይሁንታ በምርጫ አሸንፎ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ባያሸንፉም ሀሳብ አላቸው የሚወክሉት አካል አላቸው የእኛው ወንድም እህቶች ናቸው አንድት ሀገር ነው ያለችን ብለህ ያልሰራህበት ተግባር ሀሳብ ልዮነትን እንደ ፀጋ ተቀብሎ ከሁሉም ሀሳብ የሚጠቅማቸውን የሚወስዱ ትውልዶችን ማፍራት አትችልም። ዛሬን ስንሰራ ዛሬን ብቻ አይደለም እየሰራን ያለነው። በዛሬ ውስጥ ነገ አለ። በዛሬ ግንባታ ውስጥ ነገ ይገነባል። ዛሬ የዛሬውን ብቻ ሰርተን የምናሳልፍበት አይደለም፤ ይልቁንም በዛሬ ውስጥ የምንመኘው ነገ አለ። ብልፅግና ፓርቲ ዛሬ የሚሰራቸው ስራዎች ውስጥ ለዛሬው ትውልድ ብቻ አስቦ የሚሰራ ፓርቲ አይደለም። ብልፅግና የትልቅ ራዕይ ባለቤት ፓርቲ ነው። ብልፅግና ትናንት ከሰማናቸው፣ ካነብናቸው፣ ከታሪክ ውስጥና በተግባር ካየናቸው የአለም ተሞክሮዎች ከመማር ባለፈ ነገ ምን ሊፈጠር ነገ ምን ሊያስፈልገን እንደሚችል ተንብዮ የሚሰራ ፓርቲ ነው። አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ያስፈልገናል ተብሎ ሲሰራበት ብዙዎቻችን የቅንጥ ስራ፣ አላስፈላጊ መስሎን ይሆናል። ነገር ግን ሳይውል ሳያድር አለም በፈጣን ተቀያያሪ ሁኔታ ውስጥ ሆና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ምናልባትም የሰው ልጅ ሊከውነው እየቻለው ካለው ጉዳይ በላይ መከወን የሚችል አድርጎ እየፈጠረው ነው። ኢትዮጵያም አለም በሚሮጠው ሩጫ ፍጥነት ልክ ለመሮጥ እየሰራች ነው። በአንዳንድ ጉዳይ ደግሞ በሩጫው ላይ መሪነቱን ይዛ እናያታለን። ከመሪነቱ ሚናዋ ውስጥ አረንጓዴ አሻራን ማየት እንችላለን። የአረንጓዴ አሻራ ውጤቱ ሳይውል ሳያድር እየታየ ያ፣ ከቆረጥን ማሳካት እንችላለን የሚል መንፈስን ያላበሰ ተግባር ነው። ዛሬ ላይ በምንሰራው ስራ ሁሉ ነገን ታሳቢ ያደረገ ተሻጋሪ ስራ መስራት ከሁላችንም ይጠበቃል፤ ይገባናልም። ብልፅግና የነገ ተውልድ ፓርቲ ጭምር ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና የሀሳብ ብዝሃነትን፣ የማንነት ብዝሃነትን፣ የእምነት ብዝሃነትን ሌሎችም ብዝሃነት እዳ ሳይሆኑ ምንዳ ናቸው። መከራ ሳይሆኑ እድል ናቸው ብሎ ከማመን ባሻገር በተጨባጭ እድልና ምንዳ መሆናቸውን እያሳየ ያለ ፓርቲ ነው። ያሉብንን እዳዎች ወደ ምንዳ ቀይረን፣ በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን አድርገን ለትውልድ ማሻገር አለብን። እዳችንን ወደ ምንዳ ለመቀየር ያሉንን እድሎች በአግባቡ ለመጠቀም ለትውልድ ምንዳን ለማውረስ ሁላችንም ኃላፊነታችንን በአግባቡ እንወጣ። መልካም ቀን ይሁንለዎ! #Kolfe Prosperity Party - ብልፅግና