1 671
Subscribers
No data24 hours
-177 days
-8030 days
Posts Archive
1 671
የኢትዮጵን ክብር ማስጠበቅና ኢትዮጵያን ማበልፀግ የሁሉም ሰው ኃላፊነት ነው!
ኢትዮጵያ በቅድመ አያቶቻችንና በአባቶቻችን ነፃነቷንና ክብሯን አስጠብቀው ለእኛ አድርሰዋታል ። የአሁኑ ትውልድ ደግሞ በርካታ ኃላፊነት አለበት አንዱ የበለፀገች ማድረግ ነው። አሁን በቀጥታ ቅኝ የሚገዛ አካል የለም። ነገር ግን እጅ ጠምዝዞ ፍላጎታቸውን ለማስፈፀም የሚታትሩት በርካቶች ናቸው። እጅ የሚጠመዘዘው ደግሞ የራስን የቤት ስራ መወጣት አለመቻል ነው።
በተሟላ ሁኔታ የሀገር ክብር ልክ እንዳባቶቻችን አስጠብቀን ለልጆቻችን ማስተላለፍ ከፈለግን በተሰማራንበት ሁሉ መፍጠር መፍጠን ያስፈልገናል። የቴክኖሎጂ ክፍተት እንዳይገጥመን መፍጠር አስፈላጊ ነው። አሁን ትልቁ ሀብት ያለው ፈጠራ ላይ ነው። በፈጠራ መስራት የዘመኑን ፈተና ለማለፍ ወሳኝ ነው።
ፈጠራ ብቻውን በቂ አይደለም መፍጠን ይጠይቃል። ዘመኑ አለም በከፍተኛ ሁኔታ ውድዶር ውስጥ መግባቷ ብቻ ሳይሆን ጥሎ የማለፍ ሩጫም ውስጥ ገብታለች። እንደዚህ አይነት ፍጥጫ ባለበት ቀድሞ ለመገኘት ፍጥነት ወሳኝ ነው። በመፍጠር እና በመፍጠን ለበለፀገች ኢትዮጵያ እንትጋ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !!
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
አድዋ የኢትዮጵያውያን የድል ታሪክ፤ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት አርማ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
የነገ ትውልድ ላይ ዛሬ መስራት ለሀገር ብልፅግና የማይነቃነቅ መሠረት ማስቀመጥ ነው።
ዛሬ የምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ ነገን ይወስናሉ። ዛሬ መልካም ስራችንን ባበራከትን ቁጥር ነገ ብርሃን ማድረግ ይቻለናል። ፓርቲያችን ብልፅግና የትናንት ስብራታችንን ጠግኖ ዛሬን በማሳመር ነገን ብሩህ ለማድረግ እየሰራ ነው።
ከነገ ስራዎቻችን መካከል ደግሞ ትውልድ ላይ እየተደረገ ያለው ኢንቬስትመንት ትልቁን ቦታ ይዟል። የትምህርት ቤት ምገባ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ ግንባታ፣ የቀዳማዊ ልጅነት ላይ እየተደረገ ያለው ስራ ለነገው የምናደርገው ኢንቬስትመንት ትልቅጨመሆኑን ያሳያል።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ የበለፀገች በአየር ንብረቷ የታደለች ሀገር ነች። የመበልፀግ ተስፋዋ በእኛ በልጆቿ እጅ ላይ አለ። ተቀናጅተን ተናበን በመስራት ነገን ከዛሬ የተሻለ ለማድረግ የጀመርነውን ተግባር በማጠናከር የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና
1 671
መደመር በለውጥ መንገድ ላይ የተወለደ የአተያይ ፓራዳይም ነው።
መደመር በለውጥ መንገድ ላይ የተወለደ የአተያይ ፓራዳይም ነው፤ ቁስሎች እንዲጠገኑ፣ ሕመሞች እንዲድኑ፣ ችግሮች እንዲፈቱ፣ ፈተናዎች እንዲታለፉ፣ ያለፈውን ጉዟችንን መመልከቻና የቀጣይ ጉዟችን ጠቋሚ፤ አዲስ የእሳቤ ማዕቀፍ ነው፡፡
ከመደመር ትውልድ መጽሀፍ ገጽ v የተወሰደ
1 671
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረትና ልፋት በአለም አደባባይ ከፍ ትላለች።
የውስጥ አንድነትን ማረጋገጥ የሀገር ከፍታን ማረጋገጥ ነው። ኢትዮጵያ የውስጥ አንድነቷ በተጠበቁ ወቅቶች የሰራቻቸው ታሪኮች አለም ደግመው ለመስራት እንኳን የሚከብዱ ናቸው። በዛን ዘመን አለም ያላሰባቸው ኢትዮጵያ ግን ቀድማ ያሰበችውን እውን አድርጋ እስካሁንም የትውልድ ኩራት ሆኖ ቀጥሏል። አሁንም ለአለም የሚተርፍ ምስራቅ አፍሪካን የጥቅሙ ተቋዳሽ የሚያደርግ ስራ ለመስራት የሚደረገውን ጥረት የውስጣዊ አንድነትን ጠብቀን ማፍጠን ይገባናል።
የተረጋጋ አካታች ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርዓት መገንባት ያስፈልጋል። ፓርቲያችን ብልፅግና ህብረ - ብሔራዊ እውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓትን በመገንባት አካታችነት መሠረት እንዲይዝ አድርጓል። ፓርቲያችን ብልፅግና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ስር እንዲሰድ በአጭር ጊዜ ተነግሮ የማያልቅ ታሪክ ፅፏል። ፓርቲያችን ብልፅግና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በተሸነፉበት ምርጫ ላይ ሀገር መምራት፣ ማገልገል፣ ለሀገር ክብርና ብልፅግና አብሮ መስራት ይቻላል በሚል ማሳያ ስልጣንን በመስጠት አብሮ መስራት እንደሚቻል አሳይቷል። በምንለያይበት ጉዳይ መነጋገር፣ በሚያግባባን ጉዳይ አብሮ መስራት፣ በማያግባባን ጉዳይ ልዩነትን ማክበር እንደሚቻል በተግባር እውን ሆኗል። የተረጋጋ ፖለቲካ ስርዓት የሌላት ሀገር ደፋሪዋ ብዙ ነው። ለዚህም ነው የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት እንዲኖር መሠረት ተጥሎ ውጤቱ እየታየ ያለው።
የመጡ ውጤቶችን ማስፋትና ማሳደግ ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ ነው። በውስጥ ጉዳያችን እንኳን የማያግባቡን ቢኖሩ በብሔራዊ ጥቅማችን ላይ መደራደር ግን ታሪካዊ ስህተት መስራት ነው። የሀገር ፍቅር ስሜት መገለጫው አንዱ ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ፀንቶ መቆም ነው። የእኔ ካልሆነ በሚል በብሔራዊ ጥቅማችን ላይ ጉዳት የሚያደርስ ስራ መስራት የማይሽር የታሪክ ጠባሳ ማሳረፍ ነው። በነገውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት ላይ መፍረድ በአሁኑ ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት ላይ መቀለድ ነው።
እኛ ኢትዮጵያውያን ሰብሰብ ማለት መነጋገር እና መወያየት ልዩነትን በሀሳብ የበላይነት መፍታት መለማመድ ይኖርብናል። የሀገርን ጥቅም በሚያሳጣ ጉዳይ ላይ እየተደራደሩ ለሀገር አስባለሁ ማለት አይቻልም። በሀገር ጥቅም ላይ የኢትዮጵያን ማደግ መበልፀግ መለወጥ በፍፁም በማይፈልጉ በእኛ መቸገር እነሱ ለመጥገብ ከሚሰሩ ጋር አብሮ ሀሳብ ማዋጣት ሀገርን ከጠላት ጋር አብሮ ከመውጋት በምንም የተለየ አይደለም። ሁላችንም በሀገራችን ጥቅም ላይ አንድ መሆን የውስጥ ጉዳያችንን በምክክር በድርድር መፍታት ይኖርብናል። ለዚህ ደግሞ ሁላችንም በተሰማራንበት ሁሉ ኃላፊነታችንን እንወጣ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ጠንካራ የመከላከያ ሀይል ለዘላቂ ሰላምና ለኢትዮጵያ ክብር አስፈላጊ ነው።
ኢትዮጵያ ልጆቿ በየዘመናቱ ታሪክ የማይሽረው ደማቅ አሻራ አስቀምጠዋል። በተለይ በኢትዮጵያ ክብር እና የግዛት አንድነት መጠበቅ ያለድካም የሰሩ በርካቶች ናቸው። ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር ነች። ትልቅነቷን የሚመጥን ቀድሞ ውጊያን ማስቀረት የሚችል ሀይል መገንባት ያስልጋታል። ሀገራዊ ክብር የሚጠበቀው በሁለንተናዊ ረገድ መበልፀግ ማደግ ሲቻል ነው። በኢኮኖሚው የዳበረ ኢኮኖሚ ብንገነባ ዳር ድንበር የሚያስጠብቅ ለቀጠናው እና ለአለም ሰላም መጠበቅ የሚተጋ መከላከያ ሀይል ከሌለ ሀገራዊ ክብር ማስጠበቅ ያዳግታል።
የሀገር ክብር የሚያስጠብቀው ጠንካራ የመከላከያ ኃይል መገንባት ነው። ለሀገር ክብር ገር ኃይልና ጠጣር ሀይል በእጅጉ ያስፈልጋል። ኢትዮጵያ የምድር ኃይል፣ የአየር ኃይል፣ የባህር ኃይል ብሎም በሳይበር ላይ ያላት ኃይል ክብሯን የሚያስጠብቅ እንዲሆን እየሰራች ነው። አንዳንድ ሰዎች የባህር ኃይል ስንገነባ ከፊል እውነታ የያዘ ግን የተሟላ እውነት የሌለው አያስፈልግም የሚል ሀሳብ ነበራቸው። እውነታው ግን የባህር ኃይልም ሆነ የአየር ኃይል፣ የምድር ኃይልም ሆነ ሳይበር ላይ የምንገነባው ኃይል ለሀገር ክብር ወሳኝ ነው።
ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው መከላከያ ኃይል ብሔራዊ ኩራት የሚሆን ኃይል ነው። በአራቱም አውድ ላይ የሚገነባው ኃይላችን ግጭትን ቀድሞ ማስቀረት የሚችል ጠንካራ ኃይል ነው። ኢትዮጵያ ጠንካራ የጦር ኃይል በመገንባት የአካባቢውን ሰላም የማስከበር ብሎም ለተለያዩ ሀገራት ሰላም አስከባሪ ኃይል በማሰማራት ሰላምን የማስከበር የካበተ ልምድ አላት። ኢትዮጵያ ሰላምን በማስከበር ረገድ የሚያስመሰግን ውጤት በማስመዝገብ በርካታ ተልዕኮ በብቃት መፈፀም ችላለች። የነበረንን የዳበረ ልምድ በወረትነት በመያዝ ዘመኑን የዋጀ አዳዲስ አሰራሮችን እና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የኢትዮጵያ ክብር ማስጠበቅ ይገባናል።
ለሀገራዊ ክብር መጠበቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት አለበት። ኃላፊነቱም በተሰማራበት ውጤት ማምጣት ነው። ሀገራዊ ክብር በምኞት አይጠበቅም በስራ እንጂ። ሁሉም በተሰማራበት ውጤታማ ከሆነ የበለፀገች የተከበረች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ እንችላለን። ሁላችንም የተሰጠንን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ።
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳቹ። በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብና የአብሮነት በዓል ይሁንላችሁ።
#መልካም በዓል!
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና
1 671
ሀገራዊ ክብርን ማስጠበቅ የመደመር ትውልድ ኃላፊነት ነው።
ሀገራዊ ክብርን ያስጠበቀ ኢትዮጵያን በአለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ ስራ መስራት የአሁኑ ትውልድ ኃላፊነት ነው። ሀገራዊ ክብር ፅኑ መሠረት የሚኖረው በኢኮኖሚያዊ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊ እንዲሁም በወታደራዊ አቅም የዳበረና የተደራጀ አቅም መፍጠር ሲቻል ነው።
በኢኮኖሚው ረገድ ሀብት ያፈራች ሀገር መገንባት ካልቻልን ሀገራዊ ክብር ሊኖር አይችልም። ለልመና እጅ የሚዘረጋ ሀገር ሀገራዊ ክብሩን ማስጠበቅ ይሳነዋል። ኢኮኖሚ የሁሉ ነገር መሠረት ነው። የሀገር ክብርን ለማስጠበቅ የዳበረ ኢኮኖሚን እውን ማድረግ ያስፈልጋል። በኢኮኖሚው ብቻ የዳበረ ሀብት ስላለ ግን ሀገራዊ ክብርን ማስጠበቅ ይቻላል ማለት አይደለም። ..... ሌሎች ስራዎችም መስራት ይፈልጋል።
ለሀገራዊ ክብር መጠበቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት አለበት። ኃላፊነቱም በተሰማራበት ውጤት ማምጣት ነው። ሀገራዊ ክብር በምኞት አይጠበቅም በስራ እንጂ። አንድ የጤና ባለሞያ አክሞ ለማዳን ከሰራ፣ አንድ መምህር ጥራቱን የጠበቀ ትምህርተት ለትውልድ ከዘራ፣ አንድ ፖለቲከኛ በመርህ እና በስርዓት ለህዝብ ጥቅም ከቆመ፣ አንድ የመንግስት ሰራተኛ በተሰጠው ስታንዳርድ ካገለገለ፣ አንድ አርሶ አደር ምርታማነትን ለማሳደግ ከተጋ፣ .... ሁሉም በተሰማራበት ውጤታማ ከሆነ ሁሉም ሲደመር የበለፀገች የተከበረች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ያስችለናን። ሁላችንም የተሰጠንን ኃላፊነት በቃት በመወጣት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ።
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ኢትዮጵያውያን ጠንካራ ፌደራላዊት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ላይ ነን።
የፓርቲያችን ብልፅግና ዋና አላማ በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው። በሁለንተናዊ ረገድ የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ስትሆን ለሁሉም ዜጎቿ ምቹና ተስማሚ መሆን አለባት ማለታችን ነው። ምቹ ተስማሚዋ ኢትዮጵያ እውን እንዲትሆን ደግሞ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን የምትመስል ሆና እንድትገነባ መስራት ግድ ይለናል።
ኢትዮጵያ ብዝሃ ማንነት ያለባት የቡድን መብት ጠያቂዎች የሚበዙባት ሀገር ነች። ስለሆነም የቡድን መብት የሚያከብር ዲሞክራሲ እውን መሆን አለበት። የቡድን መብት ብቻ ብናከብር የግለሰብ መብት በሙሉ ይከበራል ማለት አይደለም። የቡድን መብትና የግለሰብ መብት በማክበር መካከል ሚዛን የጠበቀ እና ሁለቱንም መብት በእኩል የሚያከብር ስርዓት ግድ ይለናል። አሁን ፓርቲያችን ብልፅግና እውን ያደረገው ስርዓት የቡድን እና የግለሰብ መብት ላይ ሚዛን የጠበቀ ስርዓት እየገነባን ነው።
ብዝሃነት ባለበት ዲሞክራሲ መሰረት ሊኖረው ይገባል። ዲሞክራሲ ስርዓት ብቻውን በቂ አይሆንም። በብዝሃ ሀገር ጠንካራ ህብረ ብሔራዊ ፌደራል ስርአት መትከል ያስፈልጋል። አሁን ላይ ጠንካራ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን እውን በማድረግ ለሁሉም ዜጎቿ ምቹ ኢትዮጵያን በመገንባት ላይ ነን።
ባለፉት ጊዚያት የተመዘገቡ ድሎች አሁን እየተገነባ ላለው ስርዓትም ሆነ ለሁለንተናዊ ብልፅግና መሠረት ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና ስርዓት በተቀየረ ቁጥር ከዜሮ የመጀመርን እሳቤ አስቀርቶ ባለው በተጀመረው ላይ እየገነቡ የመሄድን ሀገራዊ ልምድ አምጥቷል። አዎ ትናንት ወረት ነበር ከዜሮ እያፈረሱ መሄድ ተቋም እና ስርዓት አይገነባም እና ነው።
ከትናንት የወረስነው ድል እና ስኬት ብቻም አይደለም። በርካታ ስህተቶች እና እዳዎችም ጭምር እንጂ። ታዲያ የትናንት እዳ ተከማችቶ ለነገ መሻገር የለበትም ዛሬ ተከፍሎ ሊጠናቀቅ ይገባል። ለዚህም ነው ለትውልድ ምንዳ እንጂ እዳ ማውረስ የለብንም ብለን የምንተጋው። ከትናንት እዳችን አንዱ ሀገርን ወደብ አልባ የሆነችበት አጋጣሚ ነው። ስለዚህም በሰጥቶ መቀበል በሰላማዊ መንገድ በአጭር ጊዜ ኢትዮጵያን የወደብ ባለቤት ማድረግ ተችሏል።
የወደብ ጥያቄ ሲነሳ በርካቶች አስፈላጊነቱን በመረዳት ወደብ ማገኘት ግድ ይላል የሚል አቋም ይዘዋል። ከሌላ አሀጉር መጥተው የመጠቀሚያ ቦታ የሚገነቡ ከሆነ ጎረቤት ሆነን ከ30 ኪሎ ሜትር ባልበለጠ ተቀምጠን መጠቀም አለመቻል ኢፍትሃዊነት ነው የሚለው ሀሳብ ፍትሃዊ ጥያቄ ነበር። በርግጥ የኢትዮጵያን ብልፅግና የማይፈልጉ፣ በጉስቁልና እንዲንቆይ ፍላጎት ያላቸው የወደብ ጥያቄውን ስጋት የሚፈጥር አድርገው ለመሳል ሞክረዋል።
የወደብ ጥያቄው ግን በነበረን ሰጥቶ የመቀበል መርህ፣ በነበረን በሰላማዊ መንገድ በፍትሃዊነት የመጠቀም አቋም በአጭር ጊዜ የወደብ ባለቤት ሆነናል። የወደብ ጥያቂያችን ምላሽ ማገኘት የድፕሎማሲ ስራችን ውጤታማነት የታየበት ያለሙትን በአጭር ጊዜ የማሳካት ብቃት እውን የሆነበት ለጎረቤት ሀገር ቅድሚያ በመስጠት አብሮ የመበልፀግ እሳቤ የታየበት ተግባር ነው። ሁላችንም አንድ ሆነን ስንሰራ የበለፀገች ኢትዮጵያን በአጭር ጊዜ እውን ማድረግ ይቻለናል። ባለንበት ቦታ ሁሉ፣ በተሰማራንበት የስራ መስክ ሁሉ ለኢትዮጵያ ብልፅግና፣ ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ለሀገር ክብር እንትጋ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የሰጠ የኢትዮጵያን ክብር እና ጥቅም ያስከበረ የውጭ ግንኙነት እየተገበረች ያለች ሀገር ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ ስመ ገናና ትልቅ ገድል የመፈፀም ታሪክ ያላት ሀገር ናት፡፡ በአሀጉራችን አፍሪካ አፍሪካን አንድ በማድረግ ለአፍሪካዊ ብልፅግና በጋራ በመትጋት ላይ ነን፡፡ ኢትዮጵያ ጎረቤቶቿን ቅድሚያ ሰጥታ ለጎረቤቶቿ ተጠቃሚነትም የምትሰራ ነች፡፡ ስራችን በትብብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ መሰረት ያደረገ ስርዓትን እውን በማድረግ በጋራ የምትሰራ ትርፍን እያሳየ ነው፡፡ ጎረቤቶቿን ደግፋ እና አግዛ አብራ ለመበልፀግ የምትሰራ በመሆኑ ድፕሎማሲያዊ ድል አምጥቷል፡፡ ትብብር ያስፈልጋል፤ አንዱ ለአንዱ በእጅጉ ያስፈልጋል ብሎ መስራት ውጤቱ የካበተ አቅም ማገኘት ነው፡፡ ታላቅነቷን እና ለጎረቤት የሚተርፍ አቅም እንዳላት የተረዱ ሀገራት ደግሞ ፈጥነው አብረው ይሰራሉ፡፡
ኢትዮጵያ በየዘመናቱ ለአፍሪካ የሚተርፍ በርካታ አኩሪ ታሪክ ፈፅማለች። አፍሪካን አንድ የሚያደርጋት ታሪክ ከመስራት ጀምሮ ያለንን ተፈጥሯዊ አቅም በራስ የመጠቀም መብትን እውን በማድረግም ላይ ነን፡፡ አፍሪካ አይኑን ገልጦ ማየት እንድችል በር ከፋች መሆን ይፈልጋል።
ኢትዮጵያ ጥቅሟን የምታስከብረው የሌሎች ተጠቃሚነትን ሳትነካ በሰጥቶ መቀበል መርህ በፍትሃዊነት ነው፡፡ ፍትህ ሲጓደል ለፍትሃዊነት የምትቆም ሀገር ሆና ሳለ በፍፁም በኢፍትሃዊነት ጥቅም ለማስከበርም ሰርታ አታውቅም፡፡ ኢትዮጵያ በትብብር የምታምን ለትብብርና ለጋራ ተጠቃሚነት ትኩረት በመስጠት አጋሮቻችንን በማስፋት በርካታ ስኬት እያስመዘገበች ነው፡፡
በፕሮግራማችን ግብ ላይ በግልፅ እንደተቀመጠው የብዙዮሽ ትብብርን በቀጠናው እያሳደግን ተቋማት ተስሚነትን በመጨመር የሀገርን ጥቅም ከፍ በማድረግ ላይ እየተሰራ ነው፡፡ የፖሊሲያዊ ነጻነታችንን ያስከበረ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ የውጭ ግንኙነት እውን ሆኗል፡፡
ያለ ጎረቤቶቻችን ያለምነውን ማሳካት አንችልም። ለጎረቤት ሀገራት ትኩረት በመስጠት ዘርፈ ብዙ የጋራ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ላይ ነን፡፡ እየመጣ ባለው ሀገራዊ እድገት ብቻ ሳይሆ እየተገነባ ባለው የውጭ ግንኙነት የጎረቤት ሀገር ቅድሚያ መስጠት ትኩረታችን ነው።
የኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በሀገራቸው ሁለንተናዊ ብልፅግና ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግም እየተሰራ ነው፡፡ በሀገር ሁለንተናዊ ብልፅግና ላይ በድፕሎማሲው ስራ ላይ የኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ያገባኛል የሚል ተሳትፎ ማረጋገጥ ለእድገታችን ወሳኝ ይሆናል።
እውን የሆነው የውጭ ግንኙነት ሀገራዊ ክብርን እና ሀገራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቅ ከመሆኑ ተጨማሪ የመፈጸም ዐቅም በመገንባት ለይ መሠረት አድርጓል፡፡ በርካታ ሀገራዊ ክብርን የሚያረጋግጡ የውጭ ግንኙነት ተግባራትም ተፈፅመዋል። ሁላችንም ኃላፊነታችንን በመወጣት የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ለማድረግ እንስራ።
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ኢትዮጵያ በመልከ ብዙ ልጆቿ ጠንካራ አንድነት ህብረ ቀለም ያማረች ውብ ጠንካራ ሀገር ነች።
ኢትዮጵያ በማንነት ብዝሃ ያለባት አንዱ ለአንዱ ውብትን ጥንካሬን እና አንድነትን ያላበሰ ማንነት ያላት ሀገር ነች። ብዝሃነት ሲኖር ብዝሃነትን ለአንድነትና ለጥንካሬ መጠቀም በሚያስችል መንገድ ማስተናገድ ግድ ይላል።
ህብረ ብሔራዊነትን በቃላት ከመመስከር ያለፈ በተግባር መግለጥ ያስፈልጋል። የአንድነት ጥንካሬ የሚመጣው ከመተዋወቅ ነው። በደንብ በተዋወቅን ቁጥር አንድነታችን የበለጠ ይጠነክራል።
ፓርቲያችን ብልፅግና ህብረ ብሔራዊ ፌደራሊዝም መሠረት ይዞ የህዝባችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንድረጋገጥ በርካታ ስራ እየተሰራ ነው። ብዝሃ ብሔር ባለበት ሀገር ውስጥ የቋንቋ ብዝሃነትን የማስተናገድ ልምድ አንድነትን የማጠናከሪያ መንገድ ነው።
ከአንድ ቋንቋ በላይ ተናጋሪ ልጆች እንድኖሩን ማድረጋችን የበለጠ እንድተዋወቁ የበለጠ አንዱ ሌላኛውን እንድረዳው እድል ይፈጥራል።
ብዝሃነታችን ከፈጣሪ የተሰጠን ወርቃማ ፀጋ ነው። የተሰጠንን ፀጋ በአግባቡ መጠቀም የእኛ ድርሻ ነው። አሁን ላይ ብዝሃ ቋንቋን ለመተግበር መስራታችን የተሰጠንን ተፈጥሯዊ ፀጋ መጠቀም መቻላችን መጀመሪያ ነው። ፓርቲያችን ብልፅግና በምርጫ ቃል ቂዳን ሰነዱ ላይ ያስቀመጠውን ብዝሃ ቋንቋ እውን ማድረግ በተግባር የፓርቲው የስራ ቋንቋ እንደሆኑ ሁሉ የመንግስት የስራ ቋንቋን የማበራከት ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ብዝሃነታችንን አክብረን ወደን እና ወደ ተግባር በመቀየር የበለፀገች ጠንካራ ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ለዜጎች ተጠቃሚነት መትጋት የፓርቲያችን ብልፅግና መገለጫ ነው።
ሁላችንም እንደምናውቀው አለም በተለያዩ ምክንያቶች የኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ውስጥ የገባችበት ወቅት ነው። በተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በየጊዜው የሰው ህይወት ሲቀጠፍ የኑሮ ውድነት ሲከሰት የዋጋ ንረቱ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ሲያናውጥ ቆይቷል። ይህ ሁኔታ የአለምዓቀፍ እውነታ ነው። ችግሩ አለምዓቀፋዊ በመሆኑ ምንም እንኳን ውስብስብ ቢያደርገውም በሀገራችን ችግሩን ለማቃለል በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።
የዋጋ ንረቱ የማቃለል ዘላቂ መፍትሄ የሚሆነው ምርት እና ምርታማነትን መጨመር በአለም አቀፍ ደረጃ ሰው ሰራሽ የሆኑ ችግሮች እንዲቀረፉ የመፍትሄ አካል መሆን ነው። ለዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
የተማሪዎች ምገባ አንዱ እና ዋናው ትውልድ ላይ መስራት የሀገርን መሠረት ማጠናከር በመሆኑ እየተሰራ ያለ ነው። በሌላ በኩል ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ወላጆች ለልጅ የትምህርት ቁሳቁስ እና ለምግብ የሚያወጡትን ወጭ እንድቀንስላቸው በማድረግ የኑሮ ውድነቱን የማቃለል ተግባር ነው።
የተማሪዎች ምገባ ኢትዮጵያ ለአለም አቀፍ ማህበረሰቡ ትምህርት የሰጠችበት ዜጎቿን ጠንክረው እድማሩ መሠረት እየጣለችበት ያለ ትልቅ ፕሮጀክት ነው። ወላጆች ከመሳቀቅ ያወጣ ባዶ ምሳ እቃ ለልጅ ቋጥሮ ሰጥቶ የአእምሮ እረፍት ከማጣት የገላገለ ትልቅ ስራ ነው።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ምንም ገቢ የሌላቸውን ለመደጎም ከተሰሩ ወርቃማ ስራዎች ውስጥ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከላት ናቸው። አዲስ አበባ ውስጥ በቀን አንድ ጊዜ ተመግቦ ማደር የማይችል ዜጋ ሊኖረን አይገባም የሚለው ቁርጠኝነት ለዜጎች የሚሰራ ፓርቲ ከመሰረተው መንግስት የሚጠበቅ ተግባር ነው። ለሰው ልጆች ጥቅምና ፍላጎት ስኬት የምሰራ መሆናችን ከሚያሳዩ ተግባራት ትልቁ የምገባ ማዕከል ነው። በቀን አንድ ጊዜ መመገብ የማይችሉትን መመገብ ብቻ ሳይሆን ነገ ሰርቶ ከራስ አልፎ ሌሎችን ማገዝ የሚቻልበት መነሳሳት የሚፈጥር ነው።
የእሁድ ገበያ፣ የሌማት ትሩፋት ተግባር፣ የማዕድ ማጋራት፣ የቤት እድሳት፣ የነዳጅ ድጎማ የመሳሰሉት ተግባራት በአለምአቀፋዊው የኑሮ ውድነት ጫና የተነሳ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎቻችን እንዳይጎዱ መንግስት ለመደጎም ያደረገው ጥረት ነው።
ምርትና ምርታማነትን በመጨመር ከውጭ የሚገቡ እቃዎችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅም በመፍጠር ከውጭ ሀገር ከምንገዛው ይልቅ ለውጭ ሀገር የምንሸጠውን በማሳደግ ዘላቂ የሆነውን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ማድረግ ይገባናል። ይህ ተግባር ደግሞ በሁላችንም ሁለንተናዊ ተሳትፎ የሚሳካ ነው።
ሁላችንም በተሰማራንበት ያለንን አቅም አሟጠን ለሀገራዊ ብልፅግና እናውለው። በመተባበር እንስራ፤ የፈጠራ ችሎታችንን እናሳድግ፤ የፈጠርነውን ጠቃሚ ጉዳይ በመፍጠን እናባዛው፤ በተሰጠን ኃላፊነት፣ በተሰማራንበት የስራ መስክ ሁሉ የሚጠበቅብንን እንወጣ። በጋራ ወንድማማችነትን/ እህትማማችነትን አጠናክረን በትብብር ሰርተን የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ችግሮችን መቋቋም የቻለ አይበገሬ የኢኮኖሚ ስርዓት በመገንባት የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጣሉ መሠረቶች ወሳኝ ናቸው።
ጊዜው አለም በተለያዩ ፈተናዎች እየተፈተነች ያለችበት ነው። አለም በኮረና ቫይረስ ስትታመስ በቆየች ማግስት የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት አለምን መልሶ ችግር ውስጥ አስገብቷል።
በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ኢትዮጵያ ግን ኢኮኖሚያዊ እድገቷ በአለም እየተመሠከረላት ያለች ሀገር ማድረግ ተችሏል። ችግሮችን ወደ እድል ለመቀየር ባለ ራዕይ መሪ ያስፈልጋል። መፈፀም የሚችል ጠንካራ ተቋም መፍጠርም ግድ ይላል።
አካታች ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት በተደረገው ስራ ውስጥ የሚታይ መሠረት እየተጣለ ነው። የድጅታል ኢኮኖሚ ስርዓት ግንባታችን በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚታይ ውጤት መጥቷል። ለዘመናት የሰራንበት ግብርና ውጤት ማምጣት የቻለው በኢኮኖሚያዊ ለውጡ ነው። ሳንጠቀምበት የቆየው ቱሪዝም የኢትዮጵያ ትናንት ዛሬ እና ነገ በሚያስተሳስር መንገድ እየተሰራበት ውጤት መጥቷል። ማዕድን ኢኮኖሚው ላይ ድርሻውን በመወጣት ላይነው። የግሪን ኢኮኖሚ ግንባታ ስኬት ሁሉም የማያውቀው ነው። በፍትሃዊነት ረገድም ከጫፍ ጫፍ ሁሉንም ማስተሳሰር የቻለ ስራ በመሠራት ላይ እንድሆን አድርጎታል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የመጣው ስኬት አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል። አጠናክሮ ማስቀጠል የሚቻለው እየመጣ ያለውን ለውጥ በቅጡ ተረድተን የግል ኃላፊነትን መወጣት ስንችል ነው። ሁላችም በተሰማራንበት ውጤት በማስመዝገብ የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
1 671
ለሀገራዊ ብልፅግና ስኬት ሜጋ ፕሮጀክቶች ዘርፈ ብዙ ሚና አላቸው።
ሜጋ ፕሮጀክት ጀምሮ በተያዘለት ጊዜና ገንዘብ ማጠናቀቅ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከፍተኛ ነው። ፕሮጀክቱ በሚሰራበት ወቅት ለዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ዜጎችን ገና በግንባታው ተጠቃሚ ማድረግ ይችላል። ግንባታው ላይ በመሳተፍ በአጭር ጊዜ ሰርቶ የማጠናቀቅ ልምድ በማካበት ሞያዊ ልምድ ይገኝበታል።
ተሰርቶ ሲጠናቀቅ ለዜጎች ስራ እድል ይፈጥራል። የሀገር ገፅታን ይገነባል። የውጭም የውስጥም የጉብኝት ማዕከል በመሆን የቱሪስት ፍሰትን ያሳድጋል። የውጭ ቱሪስት የውጭ ምንዛሬን እንዳስገኙ በማድረግ የምንዛሬ እጥረትን ይቅርፋል።
ኢትዮጵያ አሁን እየሰራች ያለችው ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እድገት በእጅጉ የሚያፋጥኑ ናቸው። የእንጦጦ ፓርክ፣ የአንድነት ፓርክ፣ የወንድማማችነት ፓርክ የከተማችንን ገፅታ ውብ አድርገው ከመቀየር ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸው ከፍተኛ ነው። የጫካ ፕሮጀክት ሌላው ግዙፍ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት ነው።
ሀላላ ኬላ፣ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ፣ የጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ የመሳሰሉት ለሀገር የሚጠቅሙ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ናቸው። የመንግስት በጀት ሳይያዝላቸው ህዝብን በገበታ ለሀገር በሚል በልማቱ ተሳታፊ በማድረግ ኢትዮጵያን የማበልፀጉ ግስጋሴ ማሳያ ፕሮጀክቶች ናቸው። በሀይል ማመንጫው ዘርፍ ህዳሴን ገንብቶ ማጠናቀቅ ትልቁ የኢትዮጵያ ኩራት ነው። የኮይሻ ሀይል ማመንጫ ግድብ ያልተነገረለት ያልተዘመረለት በአፍሪካ ግን ከህዳሴ ግድብ ውጪ የሚበልጠው አንድ ግድብ ብቻ ነው። ይህ ግድብ ግንባታው 62% ተጠናቋል። ሁላችንም የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ኃላፊነታችንን እንወጣ።
#መልካም_ቀን_ይሁንለዎ !
#Kolfe_Prosperity_Party_ብልፅግና !
