cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

መዝሙር ግጥሞች ቤት

ይህ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ሥርዓትን የምንማማርበት Channel ነው !  ወደ ቻናላችን በመቀላቀል 👇 ➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መፅሐፍትን በPDF ➲ስንክሳር ትምህርቶች ➲ መዝሙራትን በግጥሞች ➲ ኪነ-ጥበብ ➲ ጥያቄዎችን በሐይማኖት ብትኖሩ እራሳችሁን መርምሩ"   ( 2ኛቆሮ -13 ፥ 5)👇 Group ገጽ👇👇 https://t.me/Orthodoxs_Tewahdo_menfeswi_group

Show more
Advertising posts
16 336
Subscribers
+14124 hours
+8387 days
+2 51130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailableShow in Telegram
ንብ ዲኮር ለየት ያሉና ሳቢ ዲኮር * ለሠርግ                                *ለመልስ                                *ለልደት                                *ለምርቃት                                *ለሽምግልና                                *ለአጥር ወፍ አትስማሽ                                *ለክርስትና እንዲሁም ለሚፈልጉት ፕሮግራም ማዘዝ ከፈለጉ እንግድያውስ አሃዱ ብለው በ 0927334801 ላይ ይደውሉ በተጨማሪ በቴሌግራም @kingo8 በለው ይዘዙን በጥራት እና በውበት ፕሮግራሞን እናሳምራለን ንብ ዲኮር:: የተለያዩ የዲኮር ስራዎችን ለማየት JOIN ይበሉ::
Show all...
ንብ ዲኮር
[ ስንክሳር ሰኔ - ፳ - ] .mp33.11 MB
🕊 [ †  እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንጸተ ቤታ [ ሕንጸታ ] በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ] †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🕊   †   በዓለ ሕንጸታ    †   🕊 †  በዚሕች ቀን : በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በአምላክ እናት ስም ታንጻለች:: ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን "ሑሩ ወመሐሩ ኩሎ አሕዛበ" [አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ] [ማቴ.፳፰፥፲፱] (28:19) ባላቸው ቃል መሠረት ዓለምን በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና [ዮሐ.፮፥፶፮] (6:56) አበው ሐዋርያት ቁርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን: ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲሕ ይከናወን ነበር:: ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኩራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቁጥር እጅጉን በዛ:: በተለይ ቅዱስ ጳውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ:: በዚሕ ምክንያት መምሕራን ሕዝቡን "ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?" ቢሏቸው "እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት እንደሆን የለን" ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ጳውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች "ለምን አናንጽም" ብለው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ግን "ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም" አለ:: [ለዚሕ ነው ዛሬም ሊቀ ጳጳስ ካልፈቀደ ቤተ ክርስቲያን የማይታነጸው::] ከዚያ ቅዱሳን ጳውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ጴጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱም "የጌታችን ፈቃዱ መሆኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ" ብሎ አዋጅ ነገረ:: በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔአቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ:: ሁሉንም ሐዋርያት በደመና ጭኖ ፊልጵስዩስ አደረሳቸው:: ከከተማ ወጣ ብሎ ባለ መሬት ላይም "ቤተ ክርስቲያንን በእናቴ ስም አንጹ" ብሎ አዘዛቸው:: ለቅዱስ ጴጥሮስም ሦስት ዓለቶችን ሰጠው:: እነዚያን መሬት ላይ ተክሎ : ጌታችን ቆሞለት : ሐዋርያቱ እየተራዱት : ግርምት የምትሆን ሦስት ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን በ52 ዓ/ም በዚህች ቀን አንጿል:: ቤተ ክርስቲያኗን ነገ ጌታችን ቀደሳት የምንል ነንና ይቆየን:: † አምላካችን የድንግል እናቱን ፍቅር : የተቀደሰች ቤቱን ጸጋ : የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን:: 🕊 [ † ሰኔ ፳ [ 20 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፫. ቅዱሳን ሐዋርያት ፬. ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ [ ዕረፍቱ ] [ † ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት [ሰማዕት] ፪. ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር ፫. ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ ፬. ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ [ ንጉሠ ኢትዮጵያ ] ፭. አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና ፮. ቅድስት ሳድዥ የዋሒት † " በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር : አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት : ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . . የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው:: " † [፪ቆሮ. ፲፩፥፳፫-፳፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
Show all...
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስንቱ አመቱ ነው የተጠመቀው?
Show all...
በአርባ
በሰላሳ
በሀያ
በተወለደ እለት
አብርሃም ከሌላ ሴት(ከባርያው)የወለደው ልጅ ስሙ ማን ነው?
Show all...
ይስሐቅ
ያዕቆብ
እስማኤል
ሙሴ
አዳም በምድር ላይ የኖረው ስንት ዘመን ነው?
Show all...
64
98
999
930
5. በቀን ውስጥ የታወቁት የጸሎት ጊዚያት ስንት ናቸው?
Show all...
1
3
5
7
በጉባኤ ኬልቄዶት የተነሳው ምንፍቅና ምን ነበረ?
Show all...
አንድ አካል አንድ ባህሪ
ሁለት አካል ሁለት በህሪ
አንድ አካል ሁለት ባህሪ
አንድ ባህሪ ሁለት አካል
4. የጌታችን ዐበይት በዓላት ስንት ናቸው?
Show all...
5
9
2
7
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.