2 948
Subscribers
No data24 hours
-27 days
+430 days
Posts Archive
2 948
ዘጠነኛው የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት ተከፍቷል፡፡
ህዳር 21/2015 ዓ.ም
‘‘ሚሊዮን ተግዳራቶች፣ ሚሊዮን ዕድሎች’’ በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የኢንተርፕርነርሺፕ ሳምንት በርካታ አማራጮችን ይዞ ዛሬ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ግቢ ተከፍቷል፡፡
ሳምንቱን ሪቫን በመቁረጥ የከፈቱት የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ይህ አጋጣሚ ለኢትዮጵያ ብዙ መልካም ዕድሎችን ይዞ እንደመጣ ገልጸዋል፡፡
የስራ ፈጣሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት አንድ ላይ የሚገናኙበት መድረክ በመሆኑ ትስስር እንዲፈጠርና የስራ ዕድሎች እንድስፋፉ ያደርጋል ብለዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት እና ዩኒቨርሲቲዎች የሚያሰሯቸው ፈጠራዎች ህብረተሰቡን የሚጠቅሙ እንዲሆኑ ለማስቻል የፋይናንስ ተቋማትና ስራ ፈጣሪዎች በትብብር መስራት እንዳሉበቸው ክብርት ሚኒስትር አሳስበዋል፡፡
ክብርት ሚኒስትርና ለሎች እንግዶች የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን ጉብኝት አደርገዋል፡፡
በኢንተርፕርነርሽፕ ሳምንቱ ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሃንስ አያለውን ጨምሮ የተለያዩ ሚንስትር ዲኤታዎች እና ዋና ዳይሬክተሮች ተገኝተዋል፡፡
2 948
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ተግዳሮቶች ጠንክረን ከሰራንባቸዉ እድሎች ናቸዉ"፡፡
ክብርት ሙፈሪሃት ካሚል
የሥራና ክህሎት ሚንስትር
ዓለም አቀፍ የኢንርፕሪነርሺፕ ሳምንት ፕሮግራም ሚሊዮን ፈተናዎች፤ ሚሊዮን እድሎች በሚል መሪ ቃል በይፋ ተጀመረ፡፡
በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት በተጀመረዉ እና በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ዉጤቶች ለጉብኝትና ልምድ ልዉዉጥ በቀረቡበት በዚህ መድረክ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
በመድረኩ መዕክት ያስተላለፉት የሥራና ክህሎት ሚንስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተግዳሮቶችና ችግሮች ጠንክረን ከሰራንባቸዉ እድሎች ናቸዉ ሲሉ ገልጸዋል፡፡
የአለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት በአንድ ሳምንት ተከብሮ የሚያልቅ አለመሆኑ ጠቁመዉ ይልቁንም አመቱ ሙሉ ለምንሰራቸዉ ስራዎች ሃሳብ የምንለዋወጥበት እና ባለድርሻ አካላትን የምናገኝበት መድረክ ነዉ ብለዋል፡፡
የኢንተርፕሪነር አስተሳሰብ ባህል አድርጎ ለመገንባት ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት ሚንስትሯ እንደ ሀገር ለተጀመረዉ ለዉጥ እንዲሁም ለቴክኖሎጂ ሽግግር ትልቅ አስተዋጽዎ እንደሚኖረዉም አብራርተዋል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት በየጊዜ የሚያፈልቋቸዉ ሀሳቦች ሼልፍ ላይ የሚቀመጡ ሳይ ወደ ተግባር ተቀይረዉ ችግር የሚፈቱ፣ ስራ እና ሀብት የሚፈጥሩ ለማድረግ ከሚመለከታቸዉ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች በጋራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በበኩላቸዉ በዚህ የኢንርፐሪነርሺፕ ሳምንት የቴክኖሎጂ ዉድድር፣ የጀማሪ ኢንርፕራይዞች ዉድድር፣ ኤግዚቢሽንና ልምድ ልዉዉጥ ፣ የቴክኒክና ሙያ እና ዩኒቨርስቲዎች የትምህርት አሰጣጥ እና ኢንተርፕረነረሺፕ እና የፐብሊክ አንተርፐሪነርሺ ላይ የሚመክር አወደ ጥናት እና ሌሎችም በርካታ ስራዎች ማስጀመሪያ ፕሮግራም ነዉ ብለዋል፡፡
በዕለቱ የተለያዩ የፈጠራ ስራ ዉጤቶች ተጎብኝተዋል፡፡
2 948
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ዓለም አቀፍ የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት የመክፈቻ ስነ-ስርዓት
#Live
https://youtu.be/hiEnwBCo8F0
2 948
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
እንዲገኙ ተጋበዘዋል!
ዓለም አቀፍ የኢንተርፕሪነርሺፕ ሳምንት በኢትዮጵያ ሚሊዮን ፈተናዎች፤ ሚሊዮን ዕድሎች በሚል መሪ ቃል ከህዳር 20 እስከ ሕዳር 25 /2015 ይካሄዳል፡፡
ኢንተርፕሪነርሺፕ እና ኢኖቬሽን ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ እና ለፈጠራ ሥራና ሥራ ፈጣሪዎች ምቹ ምህዳር መፍጠርን ዓላማው ባደረገው በዚህ መድረክ ችግሮችን ወደ መልካም አጋጣሚ ቀይረው ስኬታማ የሆኑ ስራ ፈጣሪዎች ልምዳቸውን ያካፍላሉ፤
የኢንተርፕሪነርሽፕ ትምህርት፤ ስነ- ምህዳር፤ ፖሊሲ እና አካታችነት ላይ ውይይቶች ይደረጋሉ፡፡
በኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሺፕ እንዲስፋፋና ለስራ ፈጣሪነት አስተሳሰብ ማደግ የበኩላቸው አስተዋጸጽኦ ላበረከቱ ዕውቅና ይሰጣቸዋል፡፡
ከሕዳር እስከ ሕዳር የሚካሄዱና የሚያሸልሙ ውድድሮች ይፋ ይደረጋሉ፡፡
ከተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የተወጣጡ የፈጠራ ሰዎች በፈጠራ ስራዎቻቸውና ሀሳቦቻቸው ይወዳደራሉ፡፡ የሰሯቸው የፈጠራ ስራዎችም ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናሉ፡፡
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሲደገፉ የቆዩ አንተርፕረነሮች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት መርሃ ግብርም ተሰናድቷል፡፡
እርሶም ሕዳር 21/2015 ዓ.ም ጀምሮ በሚኖሩ መርሃ ግብሮች ላም በረት በሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ኢንቲትዩትዩት ተገኝተው በአንድ በኩል የፈጠራ ስራዎችን እየጎበኙ የፈጠራ ባለሙያዎችን እንዲያበረታቱ በሌላ በኩል ችግሮች እንዴት ወደ መልካም አጋጣሚነት እንደሚቀየሩ ልምዶችን እንዲወስዱ ተጋብዘዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
2 948
Original certificate has been ready to be given to 9500 graduates.
29 Nov. 2022
A number of graduates were asking the Register to give them original certificate sealed by the Institute.
As Yonas Akele, officer at Registrar and Alumina Directorate, confirmed original certificate for 9500 graduates, both undergraduate and graduate completes has been ready.
The officer added that students graduated since 2007 EC (2014 GC) can get their original certificate now onwards.
Students gradated in regular, extension, weekend and summer programs can get the original certificate after returning their temporary one and pay 200 birr. Graduates who cannot come to Addis Ababa can get through their legal representatives, told the officer.
The Institute has graduated bachelor degree students about eight times and graduate students five times.
2 948
በስልጠናው የተለያዩ አገራት ተሞክሮ በመውሠድ ከአገራችን ጋር በማነጻጸር ክፍተቶቻችን ለመቀነስ እንዴት መስራት እንደሚቻል ግንዛቤ አግኝተንበታል ብለዋል። የሁለትዮሽ እና የትብብር ስልጠና እንዴት ውጤታማ መድረግ እንደሚቻል ትምህርት የተገኘበት እንደሆነም ተናግረዋል።
#የጎንደር_ፖሊቴክኒክ_ኮሌጅ_ዲን የሆኑት አቶ #ጋሻው_ያለዉ በስልጠናው የሥነ አመራር ጥበብ፣ ተቋማዊ ለውጥ፣ የግጭት አፈታት እና ተያያዥ ያሉ ክህሎቶችን እውቀት ጨብጠናል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ችግሮች ያሉበት ቢሆንም ብዙ መልካም ጎኖች ያሉት በመሆኑ ጠንካራ ጎኖችን ልናሠፋው ይገባል የሚሉት አቶ ጋሻው በዚህ ስልጠና የተለያዩ አገራትን ልምድ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ተቋማት መካከል ልምድ መለዋወጥ የተቻለበት ነበር ብለዋል።
ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አቶ #ጴጥሮስ_ሌጋሞ #የዲላ_ፖሊቴክኒክ_ኮሌጅ_ምክትል_ዲን ከተለምዷዊ አሠራር በመውጣት ከኢንዱስትሪ ጋር በትብብር በመስራት ተቋማቸውን ለመለወጥ የሚያስችል ዘመናዊ አሠራርን ከስልጠናው እንዳገኙ ገልጸዋል።
ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት መምህርት የሆኑት #ሰሎሜ_ፋንታሁን በበኩላቸው
ያለንበት ዘመን በፍጥነት እየተለወጠ ያለ ዘመን በመሆኑ አመራሮች ዘመኑን የሚመጥን ክህሎት መጨበጥ ይገባቸዋል ይህ ስልጠና እነዚህን ክልሎቶች ያስጨበጠ በመሆኑ በጣም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከስልጠናልው የተገኘው እውቀት በግለሰብ ህይወትም ተተግብሮ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል በመሆኑ በስፋት ተደራሽ የሚሆንበት ሁኔታ ቢመቻች መልካም ነው ብለዋል።
እንደ ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ኤደን ገለጻ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በቀጣይ በፍላጎት ዳሰሳ የሚለዩ ክፍተቶችን ለመሙላት የተለያዩ ስልጠናዎች መዘጋጀታየቸው ይቀጥላል።
2 948
ኢንስቲትዩቱ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አመራርና መምህራንን ክህሎት ለማሳደግ በፍላጎት ላይ የተመሠረቱ ተከታታይ ስልጠናዎችን ማዘጋጀቱን እንደሚቀጥል ተገለጸ
******ሕዳር 16/2015*****
ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ከGIZ STEP3 ጋር በመተባበር ያዘጋጁት እና ለፖሊቴክኒክ ዲኖች እና አካዳሚክ ምክትል ዲኖች በአዲስ አበባ ሲስጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ።
ወ/ሮ #ኤደን_ከበደ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት #የሌደርሽፕ_ስልጠና_ማዕከል_ዳይሬክተር ናቸው በስልጠናው መጠናቀቂያ ላይ እንደተናገሩት
ለደርሺፕ ስልጠና ማዕከልም ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የያዘውን የተቋማት አመራር እና መምህራን አቅም ግንባታ ተልዕኮ ለማሣካት የተቋቋመ ሲሆን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በአጫጭር ስልጠና አቅም እየገነባ ይገኛል ብለዋል።
ላለፉት አምስት ቀናት ሲስጥ የቆየው ስልጠና በዋናነት ሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን የመጀመሪያው #የ21ኛው_ክፍለ_ዘመን_የአመራር_ክህሎቶች ሲሆን ሁለተኛው #ቴክኒክና_ሙያ_ስልጠና_ተቋማት_ከግሉ_ዘርፍ_ጋር_ስለሚኖራቸው_ትብብር ያተኮሩ ናቸው::
ስልጠናዎቹ የአገራችንን የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለመለውጥ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
በስልጠናው ላይ ተሳታፊ የሆኑ ዲኖች እና ምክትል ዲኖች በስልጠናው ሠፊ እውቀት እንደጨበጡ ተናግረዋል።
አቶ #ጫላ_ግርማ #የአዳማ_ፖሊቴክኒክ_ኮሌጅ_ዲን ሲሆኑ
"በ21ኛው ከፍለ ዘመን የሚገኙ አመራር ከሚመራው አካል ቀድሞ መግኘት አለበት። ስልጠናው ለዚህ የሚያዘጋጅ ነው" ብለዋል።
2 948
በኢንስቲትዩቱ ለመማር የተመዘገቡ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተናቸውን ወስደዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ የሚሰጣቸውን የሁለተኛ ዲግሪ መርሐ-ግብሮች በእጥፍ ማሳደጉም ተገለፀ፡፡
********ህዳር 9/2015***********
ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ2015 የትምህርት ዘመን ከሲ (C) ደረጃ ወደ ቢ (B) ደረጃ እንዲሁም ከቢ (B) ደረጃ ወደ ኤ (A) ደረጃቸውን ለማሳደግ የሚያስችል ትምህርት ለመማር የተመዘገቡ ከቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት የመጡ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት የመግቢያ ፈተናቸውን ወስደዋል፡፡
የኢንስቲትዩቱ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር #ሀፍቶም_ገ/እግዚአብሔር ለተፈታኞች ተቋማዊ ሁኔታዎች እና አካዳሚክ ካሌንደር ላይ አጭር ማስገንዘቢያ ሰጥተዋል፡፡
ም/ዋና ዳይሬክተሩ በማብራሪያቸው እንደገለፁት ኢንስቲትዩቱ በአምስት ዓመት እቅዱ መሰረት በ2015 ዓመት ሁሉም የሲ (C) ደረጃ ሰልጣኞች ወደ ቢ (B) ደረጃ የሚያሳድጋቸውን ትምህርት እንዲከታተሉ ይደረጋል፡፡ ለዚህም ከዋናው ካምፓስ በተጨማሪ በኢንስቲትዩቱ ሳተላይት ተቋማት የሚማሩበት ሁኔታ ተመቻችቷል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም በአገራዊ የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ላይ በተጠቀሰው መሰረት ኢንስቲትዩቱ የሦስተኛ ዲግሪ ደረጃ አቻ የሆነውን ደረጃ ስምንት ትምህርት ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቅቋል ብለዋል፡፡
ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት እስከ 2014 ትምህርት ዘመን በሁለተኛ ዲግሪ አስር የት/ት መርሐግብሮች የነበሩት ሲሆን በዚህ ትምህርት ዘመን በእጥፍ በመጨመር ወደ ሀያ ማሳደጉን ሐፍቶም ገ/እግዚአብሔር (ረዳት ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡
2 948
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እንየው ጌትነት ከዓለም አቀፍ ብየዳ ኢንስቲትዩት ተወካይና የደቡብ አፍሪካ ብየዳ ኢንስቲትዩት ሃላፊ የእውቅና ወረቀት ተቀብለዋል፡፡
ጥራት ያላቸውን ባለሙያዎችን ከማፍራት ባሻገር የውጭ ስራ ዕድል የሚፈጥር ተቋም በመሆኑ ባለሙያተኞች በርትታችሁ ልትሰሩ ይገባል ሲሉ ዶ/ር ተሻለ አሳባቸውን አጠናክረዋል፡፡
ክብርት ሚ/ር ሙፈሪሃት ካሚልም በበኩላቸው በዚህ ሙያ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያገኙ ባለሙያዎች ተጨማሪ የሰው ሃይልን በጥራት ከማፍራት ባሻገር ያለብን አገራዊ ክፍተት መሙላት ከባለሙያዎች ይጠበቃል ሲሉ የዕለቱን መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
አያይዘውም በአውሮፓና መካከለኛው ምስራቅ የዚህ ሙያ ባለበቶች ተፈላጊ መሆናቸውን በማስታወስ ይህንን ገበያ ለመሻማት የሚስችል ሰው ሃይል ከአጋሮች ጋር በመሆን ማፍራት እንደሚቀጥሉበት ተናግረዋል፡፡
የብየዳ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ማዕከል የአፍሪካ ብየዳ ማህበር መስራች አባልም ነው፡፡
2 948
ኢትዮጵያ በብየዳ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማሰልጠን የሚያስችል ዓለም አቀፍ ዕውቅና አገኘች፡፡
ጥራት ያላቸውን በያጆችን ማፍራት የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችን ከመደገፍ ባሻገር ወደውጭ ባለሙያዎችን ልኮ ተጨማሪ የስራ ዕድል ለመፍጠር ከፍተኛ እገዛ አለው፡፡
ጥቅምት 29 2015 ዓ.ም
የብየዳ ቴክኖሎጂ ብዙ መቶ ብሊየን ዶላሮች የሚንቀሳቀስበት የቴክኖሎጂ ዘርፍ ሲሆን ከቀላል የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ እስከህዋ ሳይንስ ድረስ በተለያዩ አግባቦች ይጠቀሙታል፡፡
የህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ ከዓመታት በፊት ገጥሞን የነበረው ችግር የብየዳ ችግር እንደሆነ ባለሙያዎች አረጋግጠዋል፡፡
ይህንን ችግር ለመፍታት (የባለሙያ ክፍተት ለመሙላት) ብዙ የውጭ ምንዛሪ እየወጣ ባለሙያዎች ከውጭ እየመጡ ይሰራሉ፡፡
በአንጻሩ በርካታ ኢትዮጵዊያን ስራ ፍለጋ ላይ ታች ሲሉ ይስተዋላል፡፡
እየተስፋፋ ያለውን ኢንዱስትሪ ለመደገፍና የብየዳ ባለሙያዎችን በብዛት ለማፍራት የበቃ እንደሆነ የተመሰከረለት የብየዳ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ማዕከል ዓለም አቀፍ ዕውቅናን አግኝቷል፡፡
በዚህም የዓለም አቀፍ ብየዳ ኢንስቲትዩት አባል መሆን ችሏል፡፡ ይህ እንዲሆን የተለያዩ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና አጋሮች ሚናቸው የላቀ ነበር፡፡
የደቡብ አፍሪካ ብየዳ ኢንስቲትዩት ( SAIW)፣ የጀርመን ዓለም አቀፍ ተራዲኦ ድርጅት (GIZ) እና የቴክንክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ባለሙያዎችና አመራሮች (TVT Institute- WTTC) ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ለእነዚህ ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል ሲሉ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልና ሚኒስትር ዲኤታው ዶ/ር ተሻለ በሬቻ አድናቆታቸውን አበርክተዋል፡፡
2 948
ለቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት መደበኛ፣ የማታ፣ ቅዳሜና እሁድ ነባር እና አዲስ እንዲሁም ለክረምት ተማሪዎች የወጣ ማስታዎቂያ
2 948
በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መማር ለምትፈልጉ አመልካቾች።
*******
ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2015 ትምህርት ዘመን በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ በቅዳሜና እሁድ እና በማታ ፕሮግራም ማሰልጠን ይፈልጋል።
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በአካል በመገኘት ወይም በበይነመረብ http://apply.etu.edu.et/onlineapplication/applications መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን።
በአካል መምጣት ለምትፈልጉ ከላምበረት አውቶብስተራ ወደ ወሠን በሚወስደው መንገድ 500 ሜትር ላይ እንገኛለን
2 948
የስራ ርክክብ አደረጉ
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት እና ከጥቅምት 10/2015 ዓ/ም ጀምሮ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው የተሾሙት ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ቀድሞ ከነበሩት ክቡር ዶ/ር በከር ሻሌ የስራ ርክክብ አድርገዋል።
ሁለቱም አመራሮች በየተመደቡባቸው ዘርፎች ውጤታማ ጊዜን እንመኝላቸዋለን።
መረጃው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ነው
2 948
እንኳን ደስ አለዎት!
የኢንስቲትዩታችን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር #ተሻለ_በሬቻ ከጥቅምት 10/2015ዓ/ም ጀምሮ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ በኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ተሹመዋል፡፡
ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በኢንስቲትዩታን በነበረዎ ውጤታማ የስራ ዓመታት በኢንስቲትዩታች ላስመዘገቧቸው ስኬታማ ተግባራት ሁሉ እናመሰግንዎታለን፡፡
በተመደቡበት የሥራ መስክ ሁሉ ውጤታማ ጊዜ እንዲኖርዎት የኢንስቲትዩቱ ማህበረሰብ መልካም ምኞቱን ይገልጽልዎታል፡፡
በድጋሚ እንኳን ደስ አለዎት!
2 948
በኢንስቲትዩቱ የተመደቡ 12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የፈተና ጊዜያቸውን በበጎ ተግባር ደመደሙ፡፡
*********ጥቅምት 11/2015ዓ/ም *********
በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተመደቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዛሬው እለት ፈተናቸውን ሲያጠናቅቁ በጎ ተግባር በመፈፀም አርኣያነታቸውን አሳይተዋል፡፡
ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን በተሳካ ሁኔታ ካጠናቀቁ በኋላ ለፈ ተና የተገለገሉባቸውን እርሳስ፣ ላጲስ እና የእርሳስ መቅረጫ በመሰብሰብ ለበጎአድራጎት ድርጅት እንዲበረከትላቸው ለኢንስቲትዩቱ አስረክበዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የማህበረሰብ አገልግሎት አስተባባሪ የሆኑት መምህር ንጉሴ ኦሎሎ ተማሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት ይህንን ድጋፍ ማሰባሰባቸውን አድንቀው ለሌሎች ተማሪዎች ትልቅ ትምህርት የሚሆን ተግባር ነው ብለዋል፡፡
ተማሪዎች በቀጣይም በሚሄዱባቸው አካባቢዎች ሁሉ በጎ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
ድጋፉን ካሰባሰቡት ተማሪዎች መካከል ከእድገት ጮራ ትምህርት ቤት የመጡት ተማሪ በረከት ንጉሴ እና ተማሪ ሠላም አብዲሳ ተማሪዎች በጎ ተግባር መሰማራታቸው ለወገኖቻቸው አለኝታነታቸውን ማሳያ መሆኑን በመገንዘባቸው ቁሳቁሶች እንዲሰባሰቡ ሀሳብ ሲቀርብ ሁሉም ተማሪዎች በቅንነት ተግባሩን እንደፈፀሙት ተናግረዋል፡፡
መምህር ንጉሴ በመጨረሻም ቁሳቁሶቹ በቀጣይ ከሌሎች ተጨማሪ ድጋፎች ጋር ተጨምረው ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንደሚበረከቱ ተናግረዋል፡፡
2 948
ጥቅምት 11/2015
በኢንስቲትዮታችን የተመደቡ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፈተናቸውን በሠላም አጠናቅቀው ወደ የቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንሰቲትዩት የተመደቡ የሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን በሰላም አጠናቅቀው ወደ የቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል፡፡
