ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት - ሐረር
ይህ በኢት/ኦ/ተ/ቤ/ክ የምሥ/ሐ/ሀ/ስ ጥንተ አድባራት ወገዳማት አቦከር ደብረ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ እና ሐኪም ጋራ ደብረ አድኅኖ ቅ/ገብርኤል አብያተ ክርስቲያናት ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ገጽ ነው። ፨ ለመቀላቀል፡ 👉https://t.me/frehaymano ሀሳብ እንዲሁም አስተያየት ካሎት : 👉 @Frehaymanot1923 ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ "አገልግሎት ሕይወቴ ካልሆነ ፤ መኖር ለእኔ ሞቴ ነው"
Show more554Subscribers
+324 hours
+97 days
+1930 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
❗#በግብረ_ሕማማት_ውስጥ❗
በተደጋጋሚ የምንሰማቸው_ቃላት
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ። የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
🔵#ኪርያላይሶን
👉ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን» ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል አለበት፡፡
🔴👉 ትርጉሙም «አቤቱ ማረን» ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
🔵#ናይናን
👉 የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔵#እብኖዲ
👉 የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ ሆይ ማረን» ማለቱ ነው።
🔵#ታኦስ
👉 የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
🔵#ማስያስ
👉 የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም «መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው።
🔵#ትስቡጣ
👉 «ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው።
👉 አምንስቲቲ = አስበን
👉 ሙኪርያ = አቤቱ ጌታ ሆይ
👉 አንቲ ፋሲልያሱ = በመንግሥትህ
👉 ሙአግያ = ቅዱስ
👉 ሙዳሱጣ = ቸር ጌታ
🔴👉 አምነስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲ ፋሲልያሱ ። የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡
🔵👉 አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ። የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ - ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው።
👉 አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው።
።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
🙏🙏🙏 አሜን 🙏🙏🙏
👍 4
ዛሬ በሆሳዕና እለት በፍሬ/ሃ/ሰ/ትቤት
በበጎ አድራጎት ክፍል ለምዕመናን ነፃ የጤና ምርመራ ማድረግ ተችሏል ። በዚህም ነፃ የጤና ምርመራ መርሀ ግብር ላይ ከሥልሳ በላይ እናቶች እና አባቶች ነፃ የጤና ምርመራ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ።
በዚህም ለመርሀ ግብሩ መሳካት በአገልግሎቱ አብራችሁን ለነበራችሁ እህት ወንድሞቼ ። እግዚአብሔር አገልግሎታችሁን አይቶ የልባችሁን መሻት ይፈጽምላችሁ አሜን !
የፊታችን ባለው በዓል በበጎ አድራጎት ክፍል ደግሞ ላቅ ያለ የነዳያን ምገባ ስላዘጋጀን በዚህም መርሀ ግብር ላይ ደግሞ የምናገለግልበትን ቁሳ ቁስ በማምጣት ።
በጎ አድራጎት ክፍሉን መደገፍ ፣ ማገዝ ስላለብን ። 👇👇
0953409521
0920892776
0923957184
እግዚአብሔር የልባችሁን ይስጣችሁ ።
👍 3
ውድ🤚 ሰላም ውድ የፍሬ ሃይማኖት ቤተሰብ
ለፋሲካ በዓል ለነዳያን ምገባ ስለምናደርግ እርስዎም በዚህ መርሀ ግብር ላይ የአቅምዎትን እንዲያደርጉ ፤ ተጋብዘዋል ።
ለምገባው የሚያስፈልጉን ዝርዝር ።
1 ሽንኩርት ፥ ለብቻ ወይንም ለሁለት ወይም ለሦስት እየሆናችሁ ።
2 ዶሮ ፥ ለብቻ ወይንም ለሁለት ወይም ለሦስት እየሆናችሁ።
3 ዘይት ፥ ለብቻ ወይንም ለሁለት ወይም ለሦስት እየሆናችሁ
4 በርበሬ ፥ ለብቻ ወይንም ለሁለት ወይም ለሦስት እየሆናችሁ
5 ሥጋ ፥ ለብቻ ወይንም ለሁለት ወይም ለሦስት እየሆናችሁ ።
ለበለጠ አገልግሎት ይጠቅም ዘንድ ፥
0953409521
0920892776
በፍሬ/ሃ/ሰ/ቤት ከበጎ አድራጎት ክፍል ።
ምድር ላይ ቁጭ ብለህ ከእግዚአብሔር ጋር የምትታረቅበት በደልህም የሚፋቅበት መፋቂያ ፣ ጸሎትህም የሚሰምርበት መሣሪያ ፣ ከወደቅክበትም የምትነሣበት መሣሪያ ፣ ስትደክምም ጥንካሬን የሚሰጥህ መሣሪያን ማግኘት ከፈለክ መስጠትን ገንዘብ አድርጋት ።
👍 1