en
Feedback
Gamo Zone Government Communication

Gamo Zone Government Communication

Open in Telegram

Gamo Zone Government Communication Affairs Department የጋሞ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

Show more
1 840
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+1630 days
Posts Archive
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማካሄድ ይጀምራል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከዛሬ የካቲት 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማካሄድ ይጀምራል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከዛሬ የካቲት 7 እስከ 9/2017 ዓ.ም ድረስ በአርባምንጭ ከተማ እንደሚያካሄድ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል ። ጉባኤው የ3ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ በማጽደቅ የክልሉን መንግስት የግማሽ ዓመት አፈጻጸም ይገመግማል። ምክር ቤቱ በኢንቨስትመንት፣ በግብርና ኮሌጅ ማቋቋሚያ፣ በከተሞች ደረጃ ማሻሻያና በበጎ አድራጎት ሥራ ላይ ያተኮሩ አዋጆችንና የተለያዩ ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል ።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid02DWLb273SmumxccMePD3PDfDf94RMdqAJKaihQSPuPEUhsaNHSF946gvck4ureuyUl/?app=fbl

"ወንድማማችነትን እና አንድነታችንን በማጠናከር ክልላችንን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ መስራት ይገባል" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በቦረዳ ወረዳ በዛሬው ዕለት ከ86 ሚሊየን ብር የተገነቡ የተ
+4
"ወንድማማችነትን እና አንድነታችንን በማጠናከር ክልላችንን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ መስራት ይገባል" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በቦረዳ ወረዳ በዛሬው ዕለት ከ86 ሚሊየን ብር የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል። በርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራው ሉዑክ በቦረዳ ወረዳ ያደረጉትን የልማት ስራ ጉብኝት አጠናቀዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ከልማት ጉብኝቱ ማጠቃለያ በኃላ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ በርካታ ፀጋ ያላት ውብና ሀብታም ሀገር መሆኗን ማሳያ ከሆኑት መካከል አንዱ በጋሞ ዞን የሚገኘው የቦረዳ ወረዳ ፀጋዎችን መጥቀስ በቂ እንደሆነ ገልፀዋል። ዛሬ የተመረቀው ፕሮጀክት አበረታች መሆኑን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጋር ያለውን አንድነት አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። በተለይ የትምህርት ቤት ግንባታ ትውልድ የሚታነጽበት ሀገር የሚገነባበት መሆኑን በመግለፅ መምህራንና ባለ ድርሻ አካላት ትኩረት ሊሰጡበት ይገባል ብለዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ የቦረዳ የመንገድ መሰረተ ልማት ለሟሟላት ለፌደራል መንግስት ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ እየተጠበቀ እንደሚገኝ ገልፀው የክልሉ መንግስት ትኩረት እንደሚሰጥ ተናግረዋል ። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ በበኩላቸው በቦረዳ ወረዳ በዛሬው ዕለት ከ86 ሚሊየን ወንድማማችነትና ፍቅርን በማጠንከር መገፋፋትን በማራቅ ልዩነት ቢኖር እንኳን በንግግር የመፍታት ልምዳችን በማዳበር የአካባቢን ሰላም በመጠበቅ https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0P6mKsvKLFTH3AsnUf9JjKuxi1zfugkn1oVYv5tqnU75JndetAJ252S2Y8fxseCqjl/?app=fbl

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በቦረዳ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ ልማቶችን በይፋ መርቀው ከፍተዋል። አርባምንጭ፦ የካቲት 6/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን) ፦ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በሰ
+3
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በቦረዳ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ ልማቶችን በይፋ መርቀው ከፍተዋል። አርባምንጭ፦ የካቲት 6/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን) ፦ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ዛፋኖ ህዳሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የቦንጌ ተንጠልጣይ ድልድይን በይፋ መርቀውዋል። ተንጠልጣይ ድልድዩ በክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የተገነባ ሲሆን ለእግእረኛ፣ ለእንስሳት እና ለሞተር ተሽከርካሪ እንዲውል ታስቦ የተሰራ መሆኑም ተመላክቷል። ርዕሰ መስተዳድሩ ትምህርት ቤቱ በጭቃ ከተሰራበት ዛሬ በዘመናዊ መንግድ ምቹ በሆነ ሁኔታ ተገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑ ለተማሪዎች ትልቅ እድል ነዉ ብለዋል። ይሄን ዘመናዊ ህንፃ ገንብቶ ለትውልድ ላስተላለፉ የሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት በክልሉ መንግስት ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የትምህርት ተቋማት ላይ መስራት ለተሻለ ትውልደ ቀረጻ አሻራ ማኖር በመሆኑ ሌሎች ግብረሰናይ ድርጀቶችም በትምህርት ዘርፍ ከክልሉ መንግስት ጋር በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። የዛፋኖ ህዳሴ ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ቤት ግንባታው 12 የመማሪያ ክፍሎችንና አንድ የአስተዳደር ህንፃን በውስጡ የያዘ ሲሆን ከ500 በላይ ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑን ተገልጿል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid036NyddnUKTnQmNfQbwsWccJ8GeQGAu7VP6t7vEoRYAZTBnWQwKwKNn94GjvN2auySl/?app=fbl

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በክልል መንግስ ፣ በዞን እና በወረዳው ድጋፍ የተገነቡ ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች ተመረቁ አርባምንጭ፦ የካቲት 6/2017ዓ.
+4
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በክልል መንግስ ፣ በዞን እና በወረዳው ድጋፍ የተገነቡ ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች ተመረቁ አርባምንጭ፦ የካቲት 6/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን) ፦በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በክብር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራው ልዑክ ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረደ ጋጋ ጎቾ ጤና አጠባበቅ ጣብያ የእናቶች መለስተኛ ቀዶ ጥገና ህንፃ እና የዞንጋ ዋጫ ቀበሌ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላን አስመርቀዋል። በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ በክልል መንግስት፣ በዞን እና በወረዳው ድጋፍ የተገነባውን ጋጋ ጎቾ ጤና አጠባበቅ ጣብያ የእናቶች መለስተኛ ቀዶ ጥገና ህንፃ እና በወረዳው መንግስት የተገነባውን የዞንጋ ዋጫ ቀበሌ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላን አስመርቀዋል ። የ ጋጋ ጎቾ ጤና አጠባበቅ ጣብያ የእናቶች መለስተኛ ቀዶ ጥገና ህንፃ እና የዞንጋ ዋጫ ቀበሌ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ 11 ሚሊየን 7 መቶ 53ሺህ 998 ብር በሆነ ወጪ መገንባቱም ተመላክቷል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid02oNvGHtyDDGos6yoYWwJFsUsNN9WHFUs9MLFPedeC19TKM9YbJ59NKoB3Ta4YDVAKl/?app=fbl

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በክብር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረደ ገቡ። አርባምንጭ፦ የካቲት 6/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን) ፦በክ
+3
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በክብር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረደ ገቡ። አርባምንጭ፦ የካቲት 6/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን) ፦በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በክብር አቶ ጥላሁን ከበደ የተመራው ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ገብተዋል። እንግዶቹ በቆይታቸው የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጉብኝትና የጤና ተቋማትን ያስመርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0rgoVMCwPnoMAzGdk5Ra4MBnH9gR84anLmYiZFvE6M5AuogD4vbtDmvWKxNt88HEjl/?app=fbl

ውድድሩ ሀገራችን በሌሎች ዘርፎች እያስመዘገበች ያለውን ውጤት በስፖርትም ለመድገም ዕድል የፈጠረ ነው :-የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሀገር አቀፉ የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት ምዘና ውድድር ተጠናቀቀ "የታ
+3
ውድድሩ ሀገራችን በሌሎች ዘርፎች እያስመዘገበች ያለውን ውጤት በስፖርትም ለመድገም ዕድል የፈጠረ ነው :-የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሀገር አቀፉ የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት ምዘና ውድድር ተጠናቀቀ "የታዳጊ ስፖርተኞች ልማት ለአሸናፊ ሀገር" በሚል መሪ ቃል በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ላለፉት ቀናት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የቆየዉ ሀገር አቀፉ የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት ምዘና ውድድር ተጠናቋል። በማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ መኪዪ መሀመድ ላለፉት 6 ዓመታት ተቋርጦ የነበረው ውድድሩ መጀመሩ በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ተተኪ የሆነ ወጣቶችን ለመመልመል ዕድል የፈጠረ እንደሆነ ተናግረዋል። ውድድሩ ሀገራችን በሌሎች ዘርፎች እያስመዘገበች ያለውን ውጤት በስፖርትም ለመድገም ዕድል የፈጠረ እንደሆነ የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው አብሮነትን በማጎልበት በክልሎች መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠናከረ መሆኑንም አክለዋል። በደማቅና ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ውድድሩን በማዘጋጀቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልንና የወላይታ ሶዶ ከተማ እንዲሁም ውድድሩ ግቡን እንዲመታ የድርሻቸውን አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላት ሁሉ ሚኒስቴር ዴኤታው አቶ መኪዩ ምስጋናን አቅርበዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ በበኩላቸው ውድድሩ የሀገራችንን የስፖርት ስብራት የሚጠግኑ ታዳጊ https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0DUGGnExnjBsAamCsh32C5ZDvg7ar7F8NYGfJNUgYuyUKZHZYBAEV3GhxFc242nWul/?app=fbl

በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የቆየው ሀገር አቀፋ የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ምዘና ውድድር የመዝጊያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል በፍፃሜው የወንዶች እግር ኳስ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና ከሶማሊያ ክ
+2
በወላይታ ሶዶ ከተማ ሲካሄድ የቆየው ሀገር አቀፋ የታዳጊ ወጣቶች ስፖርት ምዘና ውድድር የመዝጊያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል በፍፃሜው የወንዶች እግር ኳስ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና ከሶማሊያ ክልል ለዋንጫ ይጫወታሉ።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid02GE39nkt1LiiXncu31USn6ebcsn5UZRctAVg59KdQLGJQLA2zDbQRRior7argfeBel/?app=fbl

ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ በጋሞ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። አርባምንጭ፦ የካቲት 5
+2
ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ በጋሞ ዞን በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። አርባምንጭ፦ የካቲት 5/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን) ፦"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተላለፉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ በዞኑ ሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የአመራር ውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0gJQ7oHpYuUBj7FEsbtQAn4D2rEjpFk4XAHDzv41jxBQyj8en8GrgKzbXoRnkQpQVl/?app=fbl

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የዞኖችን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ አመት እቅድ አፈጻጸም በጽ/ቤታቸው እየገመገሙ ነው ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች ጋር የ2017 በጀ
+1
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የዞኖችን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ አመት እቅድ አፈጻጸም በጽ/ቤታቸው እየገመገሙ ነው ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት አጠቃላይ ስራዎች አፈጻጸምን በጽህፈት ቤታቸው እየገመገሙ ነው። ርዕሰ መስተዳድሩ በግምገማው ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ስድስት ወራት አፈፃፀምን ከፍ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች በግብገማው ትኩረት እንደሚደረግባቸው ገልፀዋል። ብልፅግና ፓርቲ ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ለህዝብ ቃል መግባት ብቻ ሳይሆን ቃልን በተግባር የምናሳይበት ለኢትዮጵያ የመንሰራራት ዘመን እንዲሆን የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ከመግባባት ላይ መደረሱን ገልፀዋል። በጉባኤው የተቀመጡ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማሳካት የዞን አስተዳዳሪዎች ወሳኝ ናቸው ብለዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በግምገማው የተጀመሩ ኢንሼቴቮችን ከማሳካት አንፃር የተሰሩ ስራዎች፤ በተለይ ከስራ ዕድል ፈጠራ ፣ ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት ከመላቀቅ አኳያ፤ እንዲሁም በኮሪደር ልማት የተሰሩ ስራዎች ትኩረት እንደሚደረግባቸው አብራርተዋል። ክልሉን የሰላም የመቻቻልና የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይን እውን ለማድረግ ክልሉ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ከማስጠበቅ አኳያ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ስራዎችን ማጠናከር፣ በህዝቡ https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid025sbo8VM7AWSgmGpxJ9udvd7B7iVQnT2LScoiChMVs8r5GUwnDFgCsnbYEZWhHP2nl/?app=fbl

ጋሞ ቴሌቪዥንን በአገሪቱ ካሉ ተወዳዳሪ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንዱ ለማድረግ ተቋማዊ ግንባታን ከወዲሁ ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ። አርባምንጭ፦ የካቲት 04/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)የ
+2
ጋሞ ቴሌቪዥንን በአገሪቱ ካሉ ተወዳዳሪ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንዱ ለማድረግ ተቋማዊ ግንባታን ከወዲሁ ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ። አርባምንጭ፦ የካቲት 04/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)የጋሞ ቴሌቪዥን ቦርድ አባላት በቴሌቪዥን ጣቢያው የግማሽ ዓመት አፈጻጸም ላይ ተወያይተዋል። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የቴሌቪዥን ጣቢያው ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አባይነህ አበራ ጋሞ ቴሌቪዥንን በቀጣይ በአገሪቱ ካሉ ምርጥ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንዱ የማድረግ ዓላማ መያዙን ገልፀው ለዚህም ተቋማዊ ግንባታ ከአሁኑ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል። ተቋማዊ ግንባታ እንዲጠናከር ቴለቪዥን ጣቢያው የራሱ ህንፃ እንዲኖረው ማድረግ፣ የሰው ኃይልንና ቁሳቁስን ማሟላት ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች እንደሆኑም አስተዳዳሪው ጠቁመዋል። የጋሞ ቴለቪዥን ሥራ አስኪያጅ ዶክተር አዲሱ አዳሙ ለቦርዱ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት ጣቢያው በግማሽ ዓመቱ 2 ሺህ 372 ዜናዎችን በመደበኛና በትንታኔ በአራቱ ቋንቋዎች ማለትም በጋሞኛ፣ በአማርኛ፣ በዜይሰኛና በጊዲቾኛ ማስተላለፉን ገልጸዋል። ቴለቪዥን ጣቢያው በግማሽ ዓመቱ ከማስታወቂያ፣ ከስፖንሰር፣ ከአየር ሰዓት ሽያጭና መሰል ስራዎች 2 ሚሊዮን 3 መቶ ሺህ ብር ገቢ መሰብሰቡንም ዶክተር አዲሱ አክለው በሪፖርታቸው አመላክተዋል። የቦርድ አባላትም ጣቢያው ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቅቆ ወደ መደበኛ ተግባር ገብቶ ያከናወናቸው አፈጻጸሞች ጥንካሬውን የሚያጎሉ መሆናቸው የተቋሙ አመራርና ባለሙያዎቹ ያላቸውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid02D152RnmqyJfiQTJc1kcuPP3cnHupfbnGEzNXRxjcevHBbbVxAfzPPAHR7QoK4zL3l/?app=fbl

ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ብቃት ያለዉ አመራርና አባል መፍጠር ወሳኝ ነዉ" አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ ጉባኤው ከጥር 23 እከ 25 መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ጠንካራ ፓርቲ የመገንባት ስራ አጠናክሮ ማስቀጠ
+2
ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ብቃት ያለዉ አመራርና አባል መፍጠር ወሳኝ ነዉ" አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ ጉባኤው ከጥር 23 እከ 25 መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ጠንካራ ፓርቲ የመገንባት ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል ብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛ ጉባኤው ካሳለፋቸዉ ዉሳኔዎች አንደኛው መሆኑም ተመላክቷል። አርባምንጭ፦ የካቲት 4/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን)፦በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ብቃት ያለዉ አመራርና አባል መፍጠር ወሳኝ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኙ የፓርቲው አደረጃጀቶችን ማጠናከርና ተልዕኮ የመፈፀም አቅማቸውን ማሳደግ ይገባል ብለዋል። ብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤው የፓርቲ ግንባታ ስራዎችን በጥልቀት በመገምገም አቅጣጫ ማስቀመጡን አስታውሰው አመራሩ ይሄንኑ አቋም ተግባራዊ በማድረግ ለፓርቲው ስኬታማ ጉዞ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም አቶ ኃይለማርያም አሳስበዋል ። እንደ ሀገር፣ እንደክልልም ሆነ በዞን ደረጃ የሰላም፣ የልማት እና የብልጽግና ተምሳሌት ማድረግ የፓርቲ እና መንግስት ተቀዳሚ አጀንዳዎች መሆናቸውንም አስታውቀዋል። ባለፉት ጊዜያት ፓርቲው ለአመራሩ የጋራ አረዳድ ለመፍጠር ሰፋፊ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መስጠቱን አስታውሰው ፓርቲው ከጊዜ ወደ ጊዜ በሁሉም ዘርፍ ብልፅግናን እያረጋገጠ መሆኑን ገልፀዋል። የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ በበኩላቸው ፖርቲው ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ፣ጥራት ያለው ትምህርትን ለትውልhttps://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0bWEwo6WaLzYJXKosj9J6mG88gimrV566mpi6wMzvF7sz8DMjMR8bpCnM1qMUaCiyl/?app=fbl

ለዉጥ የማይቆም ተፈጥሯዊ ሂደት መሆኑን ተገንዝቦ ወደ ተግባር የሚገባ ቁርጠኛ አመራር ያስፈልጋል- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ
+2
ለዉጥ የማይቆም ተፈጥሯዊ ሂደት መሆኑን ተገንዝቦ ወደ ተግባር የሚገባ ቁርጠኛ አመራር ያስፈልጋል- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ዉሳኔዎች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ በወላይታ ሶዶ ከተማ ዉይይት እያካሄዱ ይገኛል። በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ብልጽግና ፓርቲ ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ከጉባኤ እስከ ጉባዔ የተፈፀሙ ጉዳዮች በዝርዝር ቀርበዉ መገምገማቸውን ገልፀዋል። በጉባኤዉ አጠቃላይ አሁናዊ ሀገራዊና ዓለምአቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታ ትንተና ቀርቦ በጥልቀት ምክክር መደረጉን ጠቅሰው አመራሩ ዉስጥ ያለው የዉስጥ ጥንካሬ ሊሻሻል እንደሚገባም ተመላክቷል ብለዋል። ለዉጥ የማይቆም ተፈጥሯዊ ሂደት መሆኑን ተገንዝቦ የጋራ ራዕይ በመያዝ ወደ ተግባር የሚገባ ቁርጠኛ አመራር አስፈላጊ መሆኑ በጉባኤዉ አፅንኦት የተሰጠዉ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል። "ከቃል እስከ ባህል" የሚለውን መነሻ በማድረግ ስራዎቻችንን ባህል በማድረግ የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በማለፍ ፓርቲው በጉባኤው ያሳለፋቸውን ዉሳኔዎች ተፈፃሚ ማድረግ ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል። አመራሩ በ 2018 ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ብርሃን፣ በ 2023 የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን የተቀመጠውን ዕቅድ የማሳካት ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለበት ተገንዝቦ እንዲንቀሳቀስ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋልhttps://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid02g21vufiCDa7eDHzTwgSsYYouPb6eifm1xHWnvfVgTFTVN1R8Ep2Cq1rKY7kTmQgol/?app=fbl

የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል አርባምንጭ፦ የካቲት 4/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲ
+2
የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል አርባምንጭ፦ የካቲት 4/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ በተላለፉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ ዞናዊ የአመራር ውይይት መድረክ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ እና የብልፅግና ምክር ቤት አባል አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ ፓርቲው ከምስረታው ጀምሮ ያጋጠሙ ችግሮችን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር የፈፀማቸውን ተግባራት እንደመነሻ አቅርበዋል። ፓርቲው በ2ኛ መደበኛ ጉባኤው ሊከናወኑ በሚገባቸው አንኳር ተግባራት ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥና የተለያዩ ውሳኔዎችን መወሰኑን ተክትሎ የሚካሄድ የአመራር ውይይት መድረክ መሆኑንም ገልፀዋል። አመራሩ የፓርቲው አቅጣጫዎችንና ውሳኔዎችን በተሟላ መልኩ ለመፈጸምና ለማስፈጸም እንዲሁም ጥልቅ ግንዛቤ እና የጋራ አረዳድ እንዲኖረው ለማድረግ ያለመ መድረክ መሆኑም ተመላክቷል። ፓርቲው 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች በሚገባ አመራሩ በማወቅ እና ለፓርቲው ጥንካሬና ለሀገራችን ብልፅግና ወሳኝ የሆኑ ትልሞቻችን አፈፃፀም ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ የሚያስችል መድረክ በመሆኑም ተገልጿል። በመድረኩ የፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ለአመራሩ እየቀረበ ይገኛል። በመድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ እና የብልፅግና ምክhttps://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid02JEtjPcSrh93zYivraLCX9iRGYnLqghB1BApb2KvavVRwxVBanCgsppJLZRwUAqLdl/?app=fbl

የሴቶችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማስቀጠል የምክር ቤት የሴት ተመራጮች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የሴት ተመራጮች የኮከስ አባላት የ2017
+2
የሴቶችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማስቀጠል የምክር ቤት የሴት ተመራጮች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የሴት ተመራጮች የኮከስ አባላት የ2017 ዓ.ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ ተካሂዷል። አርባ ምንጭ፦ የካቲት 03/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን) የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ክብርት ወ/ሪት አለሚቱ ዮሴፍ የሴቶችን ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ እምርታዊ ለውጦች እየመጡ መሆኑን ተናግረዋል። ይህን በየዘርፉ እየመጣ የሚገኘውን የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጠናከርና ለማስቀጠል የምክር ቤት የሴት ተመራጮች የኮከስ አባላት ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ገለፀዋል። በዞኑም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመሩ የልማት ኢኒሼቲቮች እንዲሳኩና ለቀጣይነቱም የምክር ቤት የሴት ተመራጮች የኮከስ አባላት እየተወጡት የሚገኘው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት ክብርት አፈ ጉባዔዋ ይህን ከፍተኛ ሚናቸውን ለማስቀጠል በልዩ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል። የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ ክብርት ወ/ሮ አቢዮት አባይነህ በበኩላቸው የምክር ቤት ሴት ተመራጭ የኮከስ አባላት የሴቶችን ተጠቃሚነት ከማረገጥና ልማታዊ ተግባራትን ከማስቀጠል በተጨማሪ በበጎ ተግባራትና ቁጠባን ባህል ከማድረግ አኳያ ግንባር ቀደም ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን አንስhttps://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0GpsnwPuB5gKxgstCr7Wjpp7k8mKA3Xr6b2Us8DaXBxD5VW8F4Aw3gAQ5rGbSpDoLl/?app=fbl

ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማጠናቀቂያ በጋሞ ዞን እየተካሄደ የሚገኘው የቦንድ ግዢ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል አርባምንጭ፦ የካቲት 3/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦ የጋሞ ዞን ባህልና
+2
ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማጠናቀቂያ በጋሞ ዞን እየተካሄደ የሚገኘው የቦንድ ግዢ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል አርባምንጭ፦ የካቲት 3/2017ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦ የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አመራሮችና ሠረተኞች ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማጠናቀቂያ የ73 ሺህ ብር የቦንድ ግዢ ፈፅመዋል። የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙናዬ ሞሶሌ ባስተላለፉት መልዕክት የአባይ ግድብ የኢትዮጵያን በጋራ መቻልን ያሳየ ታላቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። አያይዘውም ይህ የአንድነት ማሳያ የሆነው ግድባችን እስኪጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0MLSCC28WNErJKKdA8Tav85Dpe2gk1L5AC6HrNyxQemAJBKecV3chhC2s4UzS7zEdl/?app=fbl

የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የኦዲት ግኝት ክትትልና እርምጃ አወሳሰድ ላይ ከአብይና ቴክንክ ኮሚቴዎች ጋር ምክክር አካሄደ ግብረ ሀይሉ የኦዲት ግኝት እርምት እርምጃ አወሳሰድ ላይ ቅንጂታዊ አሰራርን
+2
የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት የኦዲት ግኝት ክትትልና እርምጃ አወሳሰድ ላይ ከአብይና ቴክንክ ኮሚቴዎች ጋር ምክክር አካሄደ ግብረ ሀይሉ የኦዲት ግኝት እርምት እርምጃ አወሳሰድ ላይ ቅንጂታዊ አሰራርን ማጠናከር እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑም ተመላክቷል። አርባምንጭ ፣ የካቲት 3/2017 ዓ.ም(ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)፦ የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት አለሚቱ ዮሴፍ በምክክር መድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት የመንግስትን ውስን በጀት ለታለመለት አላማ በማዋል የህብረተሰቡን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ኦዲት ግኝት አስመላሽ ኮሚቴው ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል። አክለውም የግብረ-ሀይሉን አቅም በመጠቀምና አፈፃፀሙን የተሻለ በማድረግ የተጠቃሚነትን ስርዐት ማጠናከር በህብረተሰቡ ልማት ተጠቃሚነት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያበረክት መሆኑን በማመን የአሰራር ሥርዐት ማስፈፀሚያ ሰነዶች ላይ መግባባት አስፈላጊ ነው ብለዋል። በየደረጃው ያለው ግብረ ሃይል የክትትል እና ድጋፍ አግባቡን በማጠናከር ፣ ውሳኔ በማሰጠት፣ ክስ በመመስረት መደበኛ ኦዲት ግኝት ታክስ፣ ከግብር ወለድ እና መቀጮ ፣ የአፈር ማዳበሪያ ፣ በኦሞ ኤጀንት እጅ በሚኖር፣በኦሞ ባንክ እና በማጤመ የተገኙ የኦዲት ግኝቶችን ግብረሃይሉ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚራም ዋና አፈ ጉባኤዎ አሳስበዋል።https://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid0338bAJBZ62N4xEzp1b7hCZq8bkqkZq1H18bJfps2cYhPeBtPMUTPn5zFaR72imj5Pl/?app=fbl

የአርባምንጭ እፀዋት ክሊኒክ ጂ.አይ.ዜድ ከተሰኘ ግብረ-ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የተቀናጀ የነብሳት ተባይ አወጋገድ ዜዴ ዙሪያ ለዘርፉ ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ተጠናቀቀ። ስልጠናው የ
+2
የአርባምንጭ እፀዋት ክሊኒክ ጂ.አይ.ዜድ ከተሰኘ ግብረ-ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የተቀናጀ የነብሳት ተባይ አወጋገድ ዜዴ ዙሪያ ለዘርፉ ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ተጠናቀቀ። ስልጠናው የተቀናጀ የነብሳት ተባይ አወጋገድ ዜዴ እና ለአርሶ አደሮች የመስክ ትምህርት ቤት ጠቀሜታ ላይ የዘርፉን ባለሞያዎች ዕውቀት ለማዳበር ያለመ መሆኑም ተመላክቷል። አርባምንጭ ፣ የካቲት 3/2017ዓ.ም(ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)፦ የአርባ ምንጭ እፀዋት ክሊኒክ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙላለም መርሻ እፀዋት ክሊኒኩ በግብርናው ዘርፍ አከባቢውን እና አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በየጊዜው ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት በርካታ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የተቀናጀ የነብሳት ተባይ አወጋገድ ዜዴ እና የአርሶደሮች የመስክ ትምህርት ቤትን በመመስረት አርሶ አደሩ በስፍራ ሆኖ ከተግባሩ ሳይነጠል ከችግኝ ተከላው እስከ ፅድቀቱ ያለውን ሂደት በዕውቀት እንዲመራ ባለሙያዎች ኃላፊነት እንዳለባቸውም አቶ ሙላለም አሳስበዋል። አክለውም የአግሮ ፎረስትሪ ተግባራትን ማሳለጥ ለብዝሃ ህይወት ፣ ለአፈር ጥበቃና በግብርናው ዘርፍ ለምርትና ምርታማነትም የጎላ ሚና እንዳለውም ስራ አስኪያጅ ጠቁመዋል። በጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የተፈጥሮ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ ግርማ ተግባራትን ለማከናወን ተነሳሽነት እና ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ገልፀውhttps://www.facebook.com/100069415860348/posts/pfbid021reycCVpx6w4mAYKfcnvPLCEGTzjQrpdHFfLkXj8i82MZ9gd1GKVrdoxFQQGHnQ7l/?app=fbl

የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ እያካሄደ ይገኛል አርባ ምንጭ፦ የካቲት 03/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን) የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሀ ግብር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባኤ በማካሄድ ላይ ይገኛል። ምክር ቤቱ በአስቸኳይ ጉባኤው የአርባምንጭ ከተማ ፈርጅ ለውጥ ወይም ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማነት ለውጥ በተመለከተ እየቀረበ ባለው ሰነድ ዙሪያ ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ እያካሄደ ይገኛል አርባ ምንጭ፦ የካቲት 03/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን) የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሀ ግብር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ ዙር አስቸኳይ ጉባ ካሄድ ላይ ይገኛል። ምክር ቤቱ በአስቸኳይ ጉባኤው የአርባምንጭ ከተማ ፈርጅ ለውጥ ወይም ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማነት ለውጥ በተመለከተ እየቀረበ ባለው ሰነድ ዙሪያ ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።