ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ
Open in Telegram
👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን። 👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። 👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ✴ ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm
Show more1 955
Subscribers
-124 hours
-57 days
-2730 days
Posts Archive
1 955
#ሎሬት ጸጋዬ ሼክስፒርን ለማግኘት ጥሮ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሼክስፒርን አልፎታል።
ወፌ ላ አጋግም ብዬ
ግግም ብዬ
ከግዞተኛ ስጫወት ውዬ
አላለም ሼክስፒር
#ጋሽ ነብይ መኮንን በሸገር ኤፍኤም ከመዓዛ ብሩ ጋር ባደረገው ቃለመጠየቅ ከተናገረው።
1 955
#ምነው መቀነቴን ስትወስድ የሚታሰረውን ወገብ ረሳህ የእኔ ልጅ? ወገብ ከሌለ'ኮ መቀነት ገመድ ነው። ብትፈልግ ልብስ ታሰጣበታለህ። ... ስትፈልግ ትታነቅበታለህ። ግን የተፈጠረው እኮ ለወገብ ነበር! ወገቡን ደግሞ አንተ አሳጥተኸዋል። ... የተገኘበትን ምክንያት ካስወገድክ ለፈለከው ምክንያት ልታውለው ትችላለህ። ... "የእናቴ መቀነት" ያልከው፥ 'ወገቤን ለማሰር ጠቅሞኛል!' ለማለት ሳይሆን 'እንዳልሻገር ተብትቦኛል' ለማለት ነው። አንተ ግን መዝለሉ ሲያቅትህ"የእናቴ መቀነት ጠልፎኝ ነው" አልክ። ይሄኔ በገዛህ እጅህ አንገትህ ላይ አስገብተኸው ትንፋሽ ቢያጥርህ ኖሮ "እናቴ ያልኳት ሴት ስጦታ ነው ብላ በሰጠችኝ መቀነት አንቃ ልትገለኝ" ብለህ ነበር የምታወራው። ተዋናይ ነሃ! ማን ዋሸህ ይልሃል?
#ፍቅር እና እምነት
#ወንጌል አግአዚ
1 955
#ባለስልጣናት መንግሥትን ራሱን ነው እንደ ታላቅ ጠንቋይ የሚቆጥሩት። ተራው ሰው መናፍስትን ለማስደሰት በግ ያርዳል። መንግሥት ሥልጣን ለሚባል ሰይጣን በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይሰዋል።
#የሶሻሊስቱ ጠንቋይ ጉዳይ
#ሐማ ቱማ
#ትርጉም ሕይወት ታደሰ
1 955
#ሳጥናኤልም ... የሰው ልጅም አምላክ መሆን ነው የፈለጉት። ፈጣሪ ግን ሳጥናኤልን እስከመጨረሻው ቀጥቶት አዳምን የመመለስ እድል ሰጠው። ህግ ለአንድ ወንጀል ሁለት የተለያየ ቅጣት አይቀጣም። ፍቅር ነው እንደዚህ ፍርድን የሚያንሻፍፈው።
#ማሙሽ
#ማይክል አዝመራው
1 955
እድሜው መገስገሱን ከቶ ሰው ዘንግቶት
ነገ አልፎልኝ ይላል ማለፉን ረስቶት
አይቀር መንፈራገጥ ያ ሆድ እስኪሞላ
ወድቃ እስክትሰበር ህይወት እንደሸክላ”
ሒሩት በቀለ
1 955
#የነብይ_መኮንን ብዕር፦
➊ክፉ ሰዉ ሞተ አሉ፣ ኑ እናልቅስ እንቅበር
ደሞ ከደጎቹ፣ ክፉ እንዳይፈጠር
➋ተመለስኩ አገሬ
ከአያቴ ሽበት ዉስጥ ታሪኬን ልፈልግ
እንደዶቅማ ልልቀም የህይወቴን ፈለግ ::
ቅቤ አይወጣዉ፣ በስሜት አልባ ወግ
➌ባዶ ስንኝ ቅቤ አይወጣዉ፣ በስሜት አልባ ወግ ቢናጥ
ከዉበት ጋር ካልተቃኘ፣ ልብን ነዉ የሚሰቀጥጥ
➍ጊዜ አራቀዉና
ቦታ ለየዉና
እትብትሽ ሰዉ አገር ተቀበረም ቢባል
የእኔ እትብት አለልሽ ለሁለት ይበቃል !
ባገር የበቀለ
ባገር ላይ ያበበ እልፍ ይዘረዝራል::
➎ያኔማ ልጅ ነበርኩ እድሜዬ ገራገር
ያኔማ ልጅ ነበርኩ ህይወቴ ግርግር
ሳድግ ነዉ የገባኝ የከበደ ነገር::
https://telegram.me/binibook
1 955
"ልጄን ወሰድክብኝ አይደል? ... ፍጡርን ማምለጫ ማሳጣት ምን የሚሉት ጥበብ ነው? ... እንኳን በሕልውናህ የሚያምን ቀርቶ የካደህስ ቢሆን እንዲህ ይደረጋል? ...እንኳንስ ፈጣሪ በዚህ መጠን ፍጡርስ የወደቀን ለመጣል ይታገላል? ... አንተ ግን ማሰቃየት፣ ምርኩዜን መስበር አይደክምህም?"
#አዎ እሱ ጋ ያመኛል
#አድኃኖም ምትኩ
