ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ
Open in Telegram
👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን። 👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። 👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ✴ ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm
Show more1 955
Subscribers
-124 hours
-57 days
-2730 days
Posts Archive
1 955
ቋንቋ የሐሳብ እግር-ብረት ይሆን ዘንድ እማይፈቅዱ ቃል የሸክላ ጭቃ ነው ይላሉ። እንደየእሾት ተላውሶና ተለንቁጦ ወይ ጣባ ወይ ጥዋ፣ ወይ እንስራ ወይ ግርግራ፣ ... እሚደረግ። በመጀመርያም እንዲህ ነበር፤ እንዲህም ሆኖ ይኖራል። ካመረና ከሰመረ ይጠቀሙበታል፣ ያጌጡበታል። ውሃ ካልያዘ፣ ሐሳብ ካልያዘ፣ ምኞት ካልያዘ፣ ሕልም ካላረገዘ ናቅ አርገው ይተውታል ወይም ሰባብረው አሽቀንጥረው ይጥሉታል፤ "አፈር ነህና ወዳፈር ትመለሳለህ፤" እያሉ። ቢያንስ ሌላ ሸክላ ሰሪ ፍራሹን ዳግም እስከሚሰበስብ፣ ዳግም ትንሳኤ እስከሚሆነው።
#ኬክሮስና ኬንትሮስ
#ስንቅነህ እሸቱ (ኦታም ፑልቶ)
1 955
ሐመር ውስጥ ከነጮች ጋር ፊልም እየሠራን የሐመሩ አባቴ የሆነው በርቲ ራቅ ብሎ እንደ አንበሳ ተቀምጦ ይጠብቀናል። ወደ አባቴ ሄድኩና "ከእኔ ጋር ፊልም የሚሠሩት ቆዳቸው ነጭ በመሆኑ ምን ይሰማሃል?" አልኩት። ዝም አለኝ። አልገባውም እንዳልል ዓይን ዓይኔን እየተመለከተ ነበር፤ ሰምቷል እንዳልል ምላሽ አልሰጠኝም። በሁለተኛው ይሁን በሦስተኛው ቀን አስጠራኝና ከብቶቹ እተሰማሩበት መስክ ወሰደኝ። "ያ ጥቁሩ ከብት የማን ነው?" ሲል ጠየቀኝ። "ያንተ ነዋ!" አልኩት። "ነጩስ?"
"እሱም ያንተ ነው"
"እዚህ ውስጥ በመልኩ ምክንያት የኔ ያልሆነ አለ?"
"ኧረ የለም?'
"ታዲያ ነጭ ስታይ ምን ይሰማሃል ያልከኝ ነጭ ሰው አይደለም ወይ? እኔ እንደ ሰው ነው የማየው!" አለኝ። በጣም ተገረምኩ።
ያኔ አባት እና ልጅ የሆንን ጊዜ እንዲህ ብሎኝ ነበር፦ "አንተ ከብት ብትሆን ኖሮ ወደ ከብት በረት እወስድህ ነበር። ፍየል ብትሆን ወደ ፍየል ጋጥ እወስድሃለሁ። አንተ ሰው ነህ። ስለዚህም ወደ ቤቴ ነው የማስገባህ።"
በሰውነቴ አባት ሆነኝ። በሰውነቴ ወደ ቤቱ ወሰደኝ። በሰውነቱ አባቴ አደረግኩት። በሰውነቱ ልጁ ሆንኩ።
#ፍቅረማርቆስ ደስታ፥ በሸገር ኤፍኤም ላይ ከመዓዛ ብሩ ጋር ካደረገው ቃለመጠየቅ የተወሰደ
1 955
#ኮርማ መቼም ቢሆን አንድን ሰው በቀንዱ ወግቶ አይገድልም፤ ያ ሰው ኮርማው በቀንዱ ወግቶ እንዲገድለው ካልጋበዘ በቀር! እናም፣ በእርግጥም፣ ሰውየው ለሞቱ ከኮርማው ይልቅ ተጠያቂ ነው።
#መጽሐፈ ሚርዳድ
#ሚካኤል ኔይሚ
#ግሩም ተበጀ (ትርጉም)
1 955
አንድ አባት ገዳም ውስጥ በጽድቅ እየኖሩ ሳለ አንድ ሐሳብ ወደ አዕምሯቸው ይመጣል። "ይህን ሁሉ ዓመት በጽድቅ ኖሬ ሳበቃ ከሞት በኋላ ሕይወት ባይኖርስ? ፈጣሪ ባይኖርስ? መና መቅረቴም አይደል?" ብለው አሰቡ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ሞቱና ሰማይ ቤት ሄዱ። መልኣክት በሥራ ተወጥረው ሳለ ነው የደረሱት። መልኣክቱ ይራወጣሉ። አንድ መልኣክ ይመጣና "እዚህ ምን እየሠራህ ነው? ምን ታደርጋለህ?" ብሎ ጠየቃቸው። "በቅርቡ ሞቼ ለፍርድ መጥቼ ነው!" ብለው መለሱለት። መልኣኩ በአንክሮ አስተዋላቸውና "ማን ነው የምትባለው? ከየትስ ነው የመጣኸው" ሲላቸው፥ "ሰው ነኝ! መሬት ከምትባል ፕላኔት ነው የመጣሁት" ብለው መለሱለት። መልኣኩ እጅግ ተገርሞ "መሬት የሚባል ፕላኔት እና ሰው የሚባል ፍጡር አላውቅም!" አላቸው። መልኣኩ ትንሽ አሰበና ከሱ ከፍ ላለው መልኣክ ነገሩን አሳወቀ። መልኣክቱ ግራ ሲገባቸው የባሕር መዝገቡን አገላብጠው ቢመለከቱት መሬትና ሰው የሚባል ነገር ጨርሶውኑ አጡ። ግራ ሲገባቸው ሽማግሌውን ይዘው እግዚአብሔር ጋር ወሰዱት። እግዚአብሔርን እጅግ በሥራ ተወጥሮ ያገኙታል። እግዜሩም እጅግ ተቆጥቶ "ምንድነው በተዋረድ ወስኑ አላልኳችሁም?! ለምን ሥራ ታስፈቱኛላችሁ?" አላቸው። መልአኩም "መሬት ከሚባል ፕላኔት ሰው የሚባል ፍጡር እግዚአብሔር ፈጥሮኛል ብሎ መጥቶ ነው" አለው። እግዜሩ ቢያስብ ቢያስብ ሰውን ስለመፍጠሩ ሊያስታውስ አልቻለም። "ለመሆኑ ባሕር መዝገቡ ላይ አለ?" ብሎ ጠየቃቸው። "የባሕር መዝገቡ ላይ መሬት የሚባል ፕላኔትም ሆነ ሰው የሚባል ፍጡር ጨርሶውኑ የለም" አሉት። እግዜሩም "በቃ ምናልባት ከመጀመሪያዎቹ ሥራዎቼ አንዱ ሊሆኑ ስለሚችሉ Others የሚባል Folder ክፈቱና እዚያ ላይ መዝግቧቸው" አለ።
#ዓለማየሁ ገላጋይ ሸገር ኤፍኤም ላይ ከተናገረው የተወሰደ
1 955
#በ1988 ዓ.ም እንደ ኮንፈደሬሽን በመሰለ ውህደት ከኢትዮጵያ ጋር መጣመር የኤርትራ መንግሥት እንደሚፈልግ ኢሳያስ አፈወርቂ እና ኃይሌ መርቆሪዎስ (በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኤርትራ አምባሳደር) በመጠቆሙ ሁለቱ ሐገራት እንደገና ወደ ሕብረት የማምራት ዝንባሌ አሳይተው ነበር።
#የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግጭት መንስዔ እና መፍትሔ
#ዶ/ር ደጃዝማች ዘውዴ ገብረ ሥላሴ
1 955
#ያ ትውልድ በአንዳንድ ነገሮች ዕድለኛ ነበር። ለጣልያን ጦርነት ጀብድ በጣም ቅርብ የሆኑ ወላጆች ነበሯቸው። እነሱን ዓይተው "እምቢ ለነጻነቴ!" ማለት ቻሉ። ጭቆናን፣ ኢ-ፍትሐዊነትን ለመታገል የሞራል ትጥቅና ስንቃቸው ይኸው ማኅበረሰብ ነበር። እኛ ማንን ዓይተን ደፋር እንሁን? ከአባቶቻችን ያየነው ልጆቻቸውን ሲሸጉጡ ነው። የኛ እናትና አባት ያስተማሩን መደበቅን ነው፤ ዝም ማለትን ነው። ስለዚህም ብልጥ ማለት ግፍንና ጭቆናን ዝቅ ብሎ ማሳለፍ ሆነ።
#ንሥር እና ምስር
#ቴዎድሮስ መብራቱ
#የሙሴ ደረጀ ሐሳብ
1 955
ለሀዲስ ዓለማየሁ የመጀመሪያ መጽሐፌን "ከቡስካ በርተጀርባ"ን እንዲገመግሙልኝ ስሰጣቸው እንዲህ አሉኝ፦ "እኔ ደራሲ ነኝ። አንተ ደሞ ይዘህ የመጣኸልኝ የድርሰት ጽሑፍ ነው። ደራሲ የደራሲን ጽሑፍ ሲገመግም እኔን ሁን ማለቱ አይቀሬ ነው። ስለዚህ በሥርዓት ደራሲን የሚዳኘው ሐያሲ ስለሆነ ለዘሪሁን አስፋው ማስታወሻ እጽፍለታለሁ። ሄደህ ስጠው!" አሉኝ። ለረዳት ፕሮፌሰር ዘሪሁን የመጽሐፉን ረቂቅ ስሰጠው ቢሮው ውስጥ የተቆለሉትን የተማሪዎች ጽሑፍ እና ገና ያልተገመገሙ የመጽሐፍ ረቂቅ ጥራዞችን አሳየኝና "አልችልም" አለኝ። አዲስ አበባ እስክደርስ ድረስ ያሳለፍኩት ስቃይ ትዝ ብሎኝ ይሁን በሌላ ምክንያት እዚያው ጋሽ ዘሪሁን ቢሮ ውስጥ አለቀስኩ። ጋሽ ዘሪሁን ደነገጡ። አባበሉኝ። የመጽሐፌን ረቂቅ ተቀብለው ሸኙኝ። ጠዋት ላይ ከጎረቤት ስልክ እንደሚፈልገኝ ሲነገረኝ ተረበሽኩ። የስልኩን እጀታ እንደያዝኩ "እንዴት አደርህ ፍቅረማርቆስ? ዘሪሁን ነኝ!" ሲሉኝ ደንግጬ የስልኩን እጀታ ለቀቅኩ። እንደገና ተረጋግቼ ሳወራቸው ቢሯቸው እንድመጣ ነገሩኝ። ቢሯቸው ስገባ ከወንበራቸው ቆመው ተቀበሉኝ። "ትላንት ስላሳዘንከኝ ረቂቁን እቤት ወስጄ ከእራት በፊት አንድ ገጽ ላነብ ሙከራ ባደርግ መጽሐፉ ይዞኝ ሄደ። ትልቅ መጽሐፍ ነው!" አሉኝ። በደስታ ሰከርኩ። ከቢሯቸው ልወጣ ስል "ምን ልታደርግ አሰብከው?" አሉኝ። "እኔ ችሎታ እንዳለኝ ለማረጋገጥ ነበር እርስዎ ዘንድ የመጣሁት። እርሱን ደግሞ አሁን ነገሩኝ!" አልኳቸው። እሳቸው ግን ተቃወሙኝ። "የለም የለም ... ይሄ በጣም ትልቅ ጥናት ነው። መታተም አለበት። Ethiopian studies የሚመራው ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ስለሆነ ሄደህ ለሱ ስጠው! እኔ የጻፍኩልህን ሒስም ጨምረህ ስጠው!" አሉኝ። አመስግኜ ከቢሯቸው ወጣሁና ለፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ ሰጠኋቸው። መጽሐፏም ታተመች።
1 955
#በመንግሥት የተወሰነ ሞት ቅጣት ነው። አንተ መኖር ትፈልጋለህ፤ መንግሥት አይቻልም ይልሃል። በዚህ ተቃርኖ ውስጥ ሞት የቅጣት ዋጋ ይኖረዋል። ሞትን በደስታ የምትቀበል ከሆነ መንግሥትን እያጭበረበርክ ነው ማለት ነው። ለዚህም ነው በመንግሥት እጅ ሞትን ከመቅመስ ይልቅ ራሳቸውን የሚገድሉ አናርኪስቶች እጥፍ ወንጀል ሠርተዋል የምንለው።
#የሶሻሊስቱ ጠንቋይ ጉዳይ
#ሐማ ቱማ
#ትርጉም ሕይወት ታደሰ
1 955
#የኢትዮጵያ ታሪክ የሚያስረዳን ነገር ቢኖር የኢትዮጵያ ታሪክ በሦስት ሺህ ሆነ በመቶ ዓመት የሚለካ አለመሆኑን ነው። የሦስት ሺ ዓመቱ አኃዝ በተረት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ያህል የመቶ ዓመቱም ታሪክ ከመፈክርነት ያላለፈ መሆኑን እናገኘዋለን። እውነተኛው የኢትዮጵያ ታሪክ በስፋት ሲታይ [ማለትም የሕዝቦች አሰፋፈርን፣ የቋንቋዎች ስርጭትን እና የኢኮኖሚያዊና ማኀበራዊ ኑሮ አወቃቀርን ሲጨምር] እስከ ስድስት ሺህ ዓመት የሚደርስ፣ በጠባቡ (ከመንግሥት ምስረታ አንጻር ሲታይ ደግሞ ከሁለት ሺ እስከ ሁለት ሺ ዓመት ተኩል የሚሆን ነው።
#ኅብር ሕይወቴ
#ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ
#ይነበብ!
1 955
በአማርኛ ልቦለድ ውስጥ አይረሴ የሆኑ ገጸባህሪያትን በዋልታ ቲቪ ላይ ቀባጥረናል። (አሁን ከቀባጥረናል ይልቅ አውስተናል የሚለው ቃል አይሻልም? አይ ቢኒ!) ሮማን ተወልደብርሃን ፣ ይፍቱሥራ ምትኩ፣ እሱባለው አበራ ንጉሴ እና ቢኒያም አቡራ ተሳትፈውበታል። እና ምን ይጠበስ? በሊንኩ በኩል የዘንጋዳ ገንፎ በግመል ወተት ሲጠበስ ሾፍ ሾፍ አድርጉልኝማ!
ሊንኩን እነሆ፦
1 955
ብዙ ሠዎች የፀሀይን መውጣት ቤታቸው ውስጥ ሆነው ይጠብቃሉ፡፡ በአልጋዎቻቸው አፎት ውስጥ እንደ ሰይፍ ተወሽቀው ዐይኖቻቸውን የንጋት ውጋገን ውስጥ በልጥጠው በሙቀት የሙዋሙዋ ቆዳቸውን እየዳበሱ፣ ወይም የሚስለመለሙ አይኖቻቸውን ጨምድደው ገላቸውን በእርካታ እያከኩ፣ በእነሱ እምነት በመኖር ፍትወት ታስረው … የእንቅልፍ ሰንሰለታቸውን ሰብረው ለመነሳት በሰመመን ሲንደፋደፉ፡፡
‹‹እኔ እጅግ በጠዋት አንድ እድሜ ያነገላት የካኪ ጃኬቴን ደርቤ ከተማዬ መሃል ካለች አንዲት ትንሽ ጉብታ ላይ እተተከለች የስልክ እንጨት ስር ሄጄ እቀመጣለሁ፡፡
‹‹ግራና ቀኝ አይኖቼ ብብት አተር የሚያካክሉ ዓይን አሮች፣ ከአንደኛው የአፌ ጥግ ምናልባት የቀኜ (ፊቴን ወደ መስኮት አዙሬ በቀኝ ጎኔ ስለምተኛ) ወደተዘጋው … ብዙ ነገር መስማት ወዳላማረው ጆሮዬ የሚቃጣ የልጋግ ሰንበር፡፡ ሰፍሳፋ የጠዋት እግሮቼ ሁሉን ነገር በቀስታና በፍርሀት ይረግጣሉ፡፡
‹‹አልጋዬ ውስጥ በቡልኮ የተሟሟቀችውም ቂጤ እዚያ እርጥብ ቀዝቃዛ ሳርና አፈር ላይ ስታርፍ ጮቄው የሚፈጥረው ውጋት በአሰርሳሪዬ አልፎ ማጅራቴን ይሰማኛል፡፡ ግድ ሰጥቶኝ ግን አያውቅም፡፡ መጠበቅ እፈልጋለሁ፡፡ ፀሃይ ስትወጣ ፀዳልዋን ማየት እፈልጋለሁ፡
#ግራጫ ቃጭሎች
#አዳም ረታ
1 955
“ዕጣ ፋንታ ልክ እንደ ካርታ ጨዋታ ነው፤ የሚታደሉሽን ካርታዎች አስቀድመሽ ማወቅ አትችይም፣ ግን በተሰጠሽ ካርታዎች አጨዋወትሽን ግን መምረጥ እና መምራት ይቻላል።”
“እናማ ዕጣ ፈንታው ለኔ ሲታደለኝ፣ እድለኛ ሁን ብሎ ነው የተሰጠኝ፣ ይህ ደግሞ እድሌ ነው፣ ምንም እና ማንም አይቀይረውም።”
#ጋሽ ስብሃት
#ከሮማን ተወልደ ገጽ የተወሰደ
1 955
#የዶ/ር ኃይሉ አርዓያ "ኢትዮጵያና 5ቱ ሕልመኞች" የተሰኘው መጽሐፍ የፖለቲካ ሀዲዳችን ዝንፈቱን ከአምስቱ ሕልመኛ ትውልድ ጋር አቆራኝተው አስቀምጠዋል።
#የጎህ_ሕልመኞች - በአፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት በውጭ ሐገራት የተማሩ ባለራዕዮች
#የታህሳስ_ሕልመኞች - የእነ መንግሥቱ እና ግርማሜ ንዋይ ሕልም
#የደርግ_ሕልመኞች - ደርግ
#የአስኳላ ሕልመኞች - የተማሪዎች ሕልም .... ኢሕአፓ፥ መኢሶን፥ ወዝሊግ ...
#የበረሃ ሕልመኞች ... የሕወሓት ...
#መፅሐፉ ላይ የእያንዳንዱ የዘመኑና የትውልዱ ታሪክ የተካተተ ሲሆን፥ የሕልማቸው መንስዔም ተወስቷል። የሕልማቸው ጠንካራና ደካማ ጎንም ተከትቧል።
#ይነበብ
1 955
#የማኅበራችን አቋም የተሠራበት ሥራት፣ ልማዱ፣ ወጉ፣ እንደ ሕይወታዊ ሥራት ማኅበር ሳይሆን ሕይወት እንደ ሌለው የድንጋይ ካብ አንዱ ባንዱ ላይ ተደራርቦ የታችኛው የላይኛውን ተሸክሞ እንዲኖር ሆኖ የተሠራ በመሆኑ ከጊዜ ብዛት የታችኛው ማፈንገጡ ስለማይቀርና ይህ ሲሆን ሕንጻው በሙሉ እንዳይፈርስ እንደገና ተሻሽሎ፣ ሰውን ከድንጋይ በተሻለ መልክ የሚያሳይ የሕያዋን አቁዋመ ማኅበር እንዲሠራ ያስፈልጋል።
#ጉዱ ካሳ
#ፍቅር
እስከ መቃብር
#ሀዲስ ዓለማየሁ
1 955
#በሰው ቀዬ የተተከለ ችግኝ ካለሀገሩ አፈር ስሩ ይፀድቃል? እዚህ ከተማ በሰው ቀዬ የተተከልኩ ችግኝ ደግሞ እኔ ብቻ አይደለሁም። ቀለመማርያምም የኔው ብጤ ነች። ካለ ሀገሯ አፈር በሰው ምድር ላይ ካልፀደቅሽ ተብላ አጓጉል ያደገች ተክል። ...
#ሐምራዊ ተረኮች
#ኤልሳ ሙሉጌታ
