en
Feedback
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

Open in Telegram

👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን። 👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። 👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ✴ ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm

Show more
1 955
Subscribers
-124 hours
-57 days
-2730 days
Posts Archive
ታድያ እንግዲህ አንቺ ኢትዮጵያ፥ እኛስ ልጆችሽ ምንድነን አመንኩሽ ማለት የማንችል፥ ፍቅራችን የሚያስነውረን ዕዳችን የሚያስፎክረን ግፋችን የሚያስከብረን ቅንነት የሚያሳፍረን፥ ቂማችን የሚያስደስተን ኧ
ታድያ እንግዲህ አንቺ ኢትዮጵያ፥ እኛስ ልጆችሽ ምንድነን አመንኩሽ ማለት የማንችል፥ ፍቅራችን የሚያስነውረን ዕዳችን የሚያስፎክረን ግፋችን የሚያስከብረን ቅንነት የሚያሳፍረን፥ ቂማችን የሚያስደስተን ኧረ ምንድነን? ምንድነን? አሜከላ እሚያብብብን ፍግ እሚስመልምብን፥ ከአረም ጋር ያፈራን ጊንጦች፥ ከእንክርዳድ ያልተለየን ዘር ግርዱ ከምርቱ ተማጥቆ፥ ከቶ ያልተበራየን መከር ምንድነን? ምንድነን እኮ? አረጋዊውን ባንቀልባ፥ ከምንሸከም እንኮኮ ጐልማሳውን ከወኔ ጣር፥ ካልፈታን ከፍርሃት ምርኮ እንደወዶ ገባ ወደል፥ መጠለሉን ከሴት ታኮ ካቃተን፥ ምንድነን እኮ? … አየሽ አንቺ እማማ ኢትዮጵያ፥ አየሽ አንቺ እናት ዓለም ቃል የእምነት ዕዳ ነው እንጂ፥ ያባት የናት እኮ አደለም። #አባት ዓለም ጸጋዬ ገ/መድኅን #እሳት ወይ አበባ 🎨 Ras Habte

#በሰው ልጅ ተስፋ እንዳንቆርጥ ፈጣሪ አንዳንዶቹን ነስነስ ያደርግልናል። #ዓለም ላይ የልብ ሐኪም በባትሪ (ኧረ እንደውም በባውዛ) በሚፈለግበት ዘመን፥ አንዲት ደሃ አገር ላይ በፔሮል ለመታጠር መምረ
+3
#በሰው ልጅ ተስፋ እንዳንቆርጥ ፈጣሪ አንዳንዶቹን ነስነስ ያደርግልናል። #ዓለም ላይ የልብ ሐኪም በባትሪ (ኧረ እንደውም በባውዛ) በሚፈለግበት ዘመን፥ አንዲት ደሃ አገር ላይ በፔሮል ለመታጠር መምረጥን ምን ልንለው እንችላለን? #አንድ ካርድዮሎጂስት ከሁለት መቶ ሺህ እስከ አንድ ሚልየን ዶላር የሚከፈልባቸው ሀገራት በአንዲት የስልክ ጥሪ መሄድ እየቻለ፥ በሀገራችን ያሉ አቅመ ደካሞችን በነጻ ለማከም ይታትራል። ከ 400 በላይ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረገ መሆኑ ይሰመርበት! ዶ/ር ፈቀደ አግዋር የክፋታችንን ጥግ ለማሳየት ፈጣሪ ያስቀመጠልን ማነጻጸሪያ ይሆንን? "እንዲህ መሆን እየቻላችሁ ነው የከረፋችሁት" ሊለን። #የልብ ጠጋኙ ማስታወሻን እያነበባችሁ ...

ተዛ . . . ተዛ እስተዚ ጀበና ተደርድሮ፡፡ ጆሮ ያለው ጀበና፥ ጆሮ የሌለው ጀበና፥ ጋን 'ሚያህል ጀበና፥ ሙጥቅላ ጀበና፥ ቀይ ጀበና፥ ጥቁር ጀበና፥ ቀይ ጥቁር ቡራቡሬ ጀበና፥ ግማሽ ጎኑ እርጥብ ጀ
ተዛ . . . ተዛ እስተዚ ጀበና ተደርድሮ፡፡ ጆሮ ያለው ጀበና፥ ጆሮ የሌለው ጀበና፥ ጋን 'ሚያህል ጀበና፥ ሙጥቅላ ጀበና፥ ቀይ ጀበና፥ ጥቁር ጀበና፥ ቀይ ጥቁር ቡራቡሬ ጀበና፥ ግማሽ ጎኑ እርጥብ ጀበና፥ ተዛ እስተዚ ጀበና. . . ተሰርቶ ሳይሆን በቅሎ! የጀበና እርሻ እጓሯችን ውስጥ:: ሁሉንም ሁሉንም ትቸ ጀበና ወደድኩ፡፡ የሰር የጀበና ፈጣሪ ናት᎓᎓ የሰርንም አብልጨ ወደድኩ። የየሰር ወዳጅ፥ የየሰር ተከታይ ሆንኩ፡፡ ገጣባ ተራራ ምኑ ያምራል የጀበና አፈር እውስጡ ባይኖር? ያን የመሰለ አፈር ለምን “የሸክላ አፈር” ብለው ይጠራሉ? የጀበና አፈር አይሉም? ተራራ መውጣት ለጀበና አፈር! የጀበና አፈር መቆፈር! የጀበና አፈር መሸከም! የጀበና አፈር ማቡካት! የሰር ተጭቃው ጋር ስትጫወት ቀናለሁ፡፡ “የሰር እባክሽ ጀበና መስራት አለማምጅኝ?” ለመንኳት። “ኋላ እማማ ይቆጡና” እናቴን ተማጠንኩ:: ... #በተለይ አሥራ አንደኛው #ይፍቱሥራ ምትኩ

" ...እንደው ለማንም ልብሽ እሽ አላለም?” “ይልቃልን ወድጄዋለሁ!” የጎረሰችው ምግብ ሊወጣ ታገላት። በላብ ተዘፈቀች። ዐይኗ ተስለመለመ። አባቢ፣ ጠባቂዎቻችን፣ የጓዳው ሠራተኞች ሁሉም እናቴን ለማ
+2
" ...እንደው ለማንም ልብሽ እሽ አላለም?” “ይልቃልን ወድጄዋለሁ!” የጎረሰችው ምግብ ሊወጣ ታገላት። በላብ ተዘፈቀች። ዐይኗ ተስለመለመ። አባቢ፣ ጠባቂዎቻችን፣ የጓዳው ሠራተኞች ሁሉም እናቴን ለማዳን ተሯሯጠ። የገበታው ሥርዓት ተናጋ። እውነት ለመናገር በእናቴ ሁኔታ ምንም አልደነገጥኹም። ውኃ እንኳን ለማቀበል ከተቀመጥሁበት ብድግ አላልኹም። ብቻ ጠረጴዛው መሃል ላይ ካለው ወይን አንድ ዘለላ ይዤ ለዐይኔ ያማረችን ፍሬ ብጥስ እያደረግኹ ወደ አፌ እልካለሁ። በሁኔታዋ የተደናገጠው አባቢ ከማማ ጋር መኝታ ክፍል ቆይቶ፣ ስለ ተፈጠረው ችግር ሲጠይቅ የእኔን ጉድ አረዳችው። #የነፍስ_እኩያሞች (በ11 ደራስያን የተሰናዳ) አዲስ አበባ ሮማናት መጽሐፍ መደብር (ለገሃር) ጃዕፋር መጽሐፍ መደብር (ለገሃር) ኮሜርስ መጽሐፍ መደብር (ሜክሲኮ) ጌታቸው መጽሐፍ መደብር (ጊዮርጊስ - ፒያሳ) እነሆ መጽሐፍ መደብር (አራት ኪሎ) ዓይናለም መጻሕፍት መጽሐፍ መደብር (ብሔራዊ) ሻሸመኔ ሐዊ መጽሐፍ መደብር (+251935531626) ሐዋሳ (+251939177091) ነጌሌ አርሲ (+251928828448)

ማክሰኞ፥ ፒያሳ ሀገር ፍቅር ቲያትር ጋ ጠብቂኝ! ደገፍ ብለን ከ11 ሰዓት ጀምሮ የዓለማየሁ ገላጋይን ኬክ በረድኤት ተረፈ ሻይ እናወራርዳለን። በእምዬ የዝና ወርቁ ምኩራብ walk አድርገን በቴዎድሮስ
+1
ማክሰኞ፥ ፒያሳ ሀገር ፍቅር ቲያትር ጋ ጠብቂኝ! ደገፍ ብለን ከ11 ሰዓት ጀምሮ የዓለማየሁ ገላጋይን ኬክ በረድኤት ተረፈ ሻይ እናወራርዳለን። በእምዬ የዝና ወርቁ ምኩራብ walk አድርገን በቴዎድሮስ አጥላው ጎዳና ኩርባ እንመታለን። በጋሽ መሠረት አበጀ ሕንጻ ሠርገን የኪሩ፣ የአበባን የዘቢደርን ሱቆች እንሾፋለን። የኔ ድምጽ ካልሞደሽ ደግሞ ከዛፍ በተሠራ ጊታር ይቀየርልሻል። አቦ በቃ አታካብጂ! ነገ (ማክሰኞ) "የነፍስ እኩያሞች" ትመረቃለች፤ በጥቁር ጋዎን ተጀቡና። 11 ደራስያን፥ 1 መጽሐፍ፥ በዕለተ ማክሰኞ፥ በ 11 ሰዓት፥ በሀገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ! መግቢያ - በነጻ

ወታደሮች የሚያምር ወታደራዊ ልብስ ከመሣሪያ ጋር አንግበው በከተማ ውስጥ ለፀጥታ ጥበቃ ተሠማርተው ሲታዩ ኑሯቸውም ከዛው ጋር የተመጣጠነ ሊመስል ይችላል፡፡ በተለይ እንደኛ አይነት ሕዝብ የሚጠላው መን
ወታደሮች የሚያምር ወታደራዊ ልብስ ከመሣሪያ ጋር አንግበው በከተማ ውስጥ ለፀጥታ ጥበቃ ተሠማርተው ሲታዩ ኑሯቸውም ከዛው ጋር የተመጣጠነ ሊመስል ይችላል፡፡ በተለይ እንደኛ አይነት ሕዝብ የሚጠላው መንግሥት በሚፈራረቅበት ሃገር ወታደሮቹም በመንግሥት ዓይን ስለሚታዩ የተመቻቸውና የናጠጡ እንጂ ወጥቶ አደሮች መሆናቸው የሚረዳላቸው የለም፡፡ ይህም በመሆኑ እነዛ የለበሷትን ልብስና ትጥቃቸውን እንደያዙ በቀን አንድ ጊዜም ይሁን ሁለት ጊዜ የምትወረወርላቸውን እዚህ ግባ የማይባል ነገር እየተቃመሱ የቀን ፀሐይ፤ የሌሊት ቁርና ዝናብ ቸነፈር ሳይል ሲፈራረቅባቸው የሚውሉና የሚያድሩ ወታደሮች የሚደርስባቸውን ችግር በትክክል የሚያውቁትና የሚረዱት እነሱ ራሳቸው ብቻ ናቸው:: በሃገራችን የተፈራረቁት አንባገነን መንግሥታትም የግፍ አገዛዛቸው ዋና መሣሪያ አድርገው የሚጠቀሙበት ወታደሩን በሕገ ወጥ መንገድ በማይገባው ግዳጅ ላይ እያሠማሩ ሕዝብን እንዲያስፈራራና እንዲጎዳ እያደረጉ በመሆኑ ወታደሩን ከሕዝቡ በማቃረን ተግባራቸው ተሳክቶላቸው ነበር ማለት ይቻላል። በእኛ ጊዜ የኋላ ደጀኑን ጨምሮ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጋ የሠራዊት ቁጥር ነበር። ከዚህ ውስጥ በከተማ አካባቢ ተመድበው በቀይና በነጭ ሽብሩም ሆነ ከዛ ቀጥሉ በሕዝብ ላይ በሚደረግ የመንግሥት ግድያ የሚሳተፉ የጦር ክፍሎች ሲበዙ ቢዉሉ ከአንድ ብርጌድ ይብዛ ከተባለም ከአንድ ክፍለ ጦር አይበልጡም ነበር᎓᎓ ከዚህ ውጭ ያለው 98% የሚሆነው የሠራዊቱ አባል ግን ከላይ እንደተገለፀው የኢትዮጵያን አንድነት ዳር ድንበሯንና ሉዓላዊነቷን ለማስከበር ወጥቶ አደር በመሆን ከትውልድ ቦታውና ከቤተ ሰቡ ተነጥሎ ጦር ሜዳ ዘምቶ አፈር ድንጋይና አሸዋ ላይ እየተኛ በየዕለቱ እየሞተና እየቆሰለ ላብና ደሙን እያፈሰሰ የሚኖር ነበር፡፡ #የወገን ጦር #ሻለቃ ማሞ ለማ

#በ1967 የአዲስ አበባ ከተማ ሁኔታ ሲጠና 5% የሆኑት ኗሪዎች የከተማውን 90% መሬት መያዛቸውን፣ 15% የሆኑ ቤተሰቦች አዲስ አበባን ግማሹን መያዛቸውን ጥናቶች አሳዩ። የገጠር መሬት አዋጅ ተግባ
#በ1967 የአዲስ አበባ ከተማ ሁኔታ ሲጠና 5% የሆኑት ኗሪዎች የከተማውን 90% መሬት መያዛቸውን፣ 15% የሆኑ ቤተሰቦች አዲስ አበባን ግማሹን መያዛቸውን ጥናቶች አሳዩ። የገጠር መሬት አዋጅ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በሕብረተሰቡ ዘንድ በተለይ ከአዲስ አበባ ነዋሪ ሕዝብ የተነሳው ጥያቄ፣ የከተማውስ የመሬት ይዞታ እንዴት ይታያል? የሚል ነበር፡፡ በእርግጥ የከተማው መሬት በአብዛኛው የተያዘው በጥቂት የፊውዳል ባላባቶች ሲሆን የተወሰኑ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ነጋዴዎችና ግለሰቦች የመሬት ባለቤቶች ነበሩ:: ከፍተኛ ቁጥር ያለው የከተማው ሕዝብ ግን የሚኖረው በኪራይ ቤት ወይንም ከመሬት ባለቤቶች ላይ በጭሰኝነት በወሰደው መሬት ላይ መለስተኛ ጐጆ በመቀለስ ነበር፡፡ ስለሆነም ሰፊው የከተማ ኗሪ ሕዝብም ከአብዮቱ መጠቀም እንዳለበት የብዙዎቹ የደርግ አባላት እምነት ነበር᎓᎓ #በገጠመኞች የታጀበ የሕይወት ጉዞ #ሌጀነራል አዲስ ተድላ

#የሌ/ኮሎኔል አጥናፉ ሞትና ትንቢት "ሰው እንዴት በገዛ አንገቱ ገመድ ያጠልቃል?! ደርግን እያወቀው! ከደርግ ጋር አራት ዓመት የኖረ ሰው፣ በሆነ ባልሆነው ግደለው! ቁረጠው!› ሲል የነበረ ሰው! ም
#የሌ/ኮሎኔል አጥናፉ ሞትና ትንቢት "ሰው እንዴት በገዛ አንገቱ ገመድ ያጠልቃል?! ደርግን እያወቀው! ከደርግ ጋር አራት ዓመት የኖረ ሰው፣ በሆነ ባልሆነው ግደለው! ቁረጠው!› ሲል የነበረ ሰው! ምን ያለ መሰለህ፤ ‹ሶሻሊዝም ሶሻሊዝም እየተባለ፤ አጉል ሕዝቡን አሠቃየነው፣ ፈጀነው፣ አስጨፈጨፍነው፣ ጨፈጨፍነው! አማራውና ክርስቲያኑ ነፍጠኛ እየተባለ አለቀ! ሶሻሊዝም ለኢትዮጵያ አይሠራም። ለኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ቅይጥ ኢኮኖሚ ነው! ሶሻሊዝም በገባበት ሁሉ ዕልቂት ነው የሚከተለው! ሶሻሊዝም ኢትዮጵያ ውስጥ እንኳን በእኔ ዕድሜ በልጅ ልጆቼም ዕድሜ ተግባራዊ አይሆንም!› ምን ያላለው ነገር አለ! አለ፡፡ “እውነትም በጤናው አይደለም፤ ይኽን ካለ፣” አልኩ። “ደርግ እንደሆነ ቀልድ አያውቅም፤ ለጥብሰ አደረሰው! ጅል! እንዴ ሰው በገዛጁ _ግደሉን ብሎ ይሞታል! ከመሞቱ ደግሞ ውርደቱ! ተራ ወታደሩ ሁሉ እየተነሣ ወረደበት! እነዚህ ከእኛ ጋር ሞስኮ ተምረው የመጡትማ፣ አቤት ሳይንቲፊክ በሆነ መንገድ እየተነተኑ ነው ያዋረዱት!” አለ። #ያልታሰበው (የሕይወቴ ፈታኝ ጉዞ እና የኢትዮጵያ አብዮት ተሳትፎዬ) #ብርሃኑ ባይህ (ሌ/ኮሎኔል)

ስርዝ ድልዝ ያለበት ሥዕል ወይም መጽሐፍ አይተን አናውቅም። ይህም የሚሆነው ሠዓሊ ወይም ደራሲ ቢሮው ውስጥ ሰርዞ ደልዞ በመጨረሻ የደረሰበትን የተቀሸረ የሥራ ውጤት ለተመልካች ወይም ለአንባቢ ስለሚያ
+2
ስርዝ ድልዝ ያለበት ሥዕል ወይም መጽሐፍ አይተን አናውቅም። ይህም የሚሆነው ሠዓሊ ወይም ደራሲ ቢሮው ውስጥ ሰርዞ ደልዞ በመጨረሻ የደረሰበትን የተቀሸረ የሥራ ውጤት ለተመልካች ወይም ለአንባቢ ስለሚያቀርብ ነው። በፖለቲካ ትግል ውስጥ ያለ ድርጅት ግን ይህን ማድረግ አይችልም፡፡ ተዘጋጅቶ የሚወጣበት ላቦራቶሪ ስለሌለ እንኳን ተመልካችን ተሳታፊውንም «ዞር በሉ ሙከራ ላይ ነኝ» ማለት አይችልም፡፡ መሰረዝ መደለዝ የሚችለው የፖለቲካ መድረክ ላይ በአደባባይ ነው፡፡ እያንዳንዱ ስርዝ ድልዝ ደግሞ ከመሥዋዕትነት ጋር፣ ከወደኋላ መወርወር ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህ ዓይነት እየሰረዘ፣ እየደለዘ የአደባባይ ትርምስ ውስጥ ማለፍ ከነበረበት ድርጅት (ያውም ጀማሪ ከነበረ) ሙዚየም ለመቀመጥ የበቃ «የተቀሸረ» የሥራ ውጤት መጠበቅ አይቻልም፡፡ #በአጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ #አንዳርጋቸው አሰግድ

በሕይወት እያሉ ግለታሪካቸው ተጽፎ ባነብ ደስ የሚለኝ የሀገራችን እንቁዎቻችን፦ ❤️ነብይ መኮንን 🔥 ዶ/ር አሉላ ፓንክረስ 1️⃣መዓዛ ብሩ 🎬 ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ 🔷 ፍቅረማርቆስ ደስታ 🎤 እጅ
በሕይወት እያሉ ግለታሪካቸው ተጽፎ ባነብ ደስ የሚለኝ የሀገራችን እንቁዎቻችን፦ ❤️ነብይ መኮንን 🔥 ዶ/ር አሉላ ፓንክረስ 1️⃣መዓዛ ብሩ 🎬 ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ 🔷 ፍቅረማርቆስ ደስታ 🎤 እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) 🔥 ዳንኤል ጎበና (ሰርቅ ዳንኤል) 🎭 ጌትነት እንየው 🏅ዘነበ ወላ 🦋 ወንድዬ ዓሊ 🙆‍♂️በኃይሉ ገ/መድኅን 🔴 አያልነህ ሙላቱ 💙 ሀብታሙ አለባቸው ⭐️ ስዩም ተፈራ 🎼 ሙላቱ አስታጥቄ 🔶 አስፋው ዳምጤ 🤦‍♂️ ንጉሴ አክሊሉ (ጋዜጠኛ) 🦋 ደረጀ ኃይሌ (ጋዜጠኛ) 💚 ፕሮፌሰር አታላይ ዓለም 🥇ሣህለሥላሴ ብርሃነ ማርያም 🇪🇹 ኃይለመለኮት መዋዕል 🙆‍♀️ ኃይሌ ገ/ሥላሴ 🎹 ጋሽ መሃሙድ አህመድ 🏆 ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌ. ድሌቦ 📝 ዓለማየሁ ገላጋይ 💔 ረ/ፕሮፌሰር አደም ካሚል ⓵ ሃማ ቱማ (እያሱ ዓለማየሁ) 💛 ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ 👌 እንዳለጌታ ከበደ 🎤 ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ 💥 ጌታቸው በለጠ 💜 ይልማ ገብረአብ ➊ ቴዎድሮስ ገብሬ 🔧 አበበ ባልቻ 🧡 ተፈሪ ዓለሙ 💫 ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ 🔶 ኃይሉ ጸጋዬ 🖤 ላሌ ለቡኮ 🇪🇹 ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) 🔥 ደሳለኝ ራህመቶ ❤️ ዶ/ር በላይ አበጋዝ (የረሳኋቸውን እናንተ ጨምሩበት)

ሰው ከአፈር ነው የሚሰራው ካሉኝ ጊዜ አንስቶ፥ ዝናብ በዘነበ ቁጥር በጎርፍ ተሸርሽሬ የማልቅ እየመሰለኝ እሰጋ ነበር - በልጅነቴ። #አለማወቅ #ዳዊት ወንድማገኝ (ዶ/ር)
ሰው ከአፈር ነው የሚሰራው ካሉኝ ጊዜ አንስቶ፥ ዝናብ በዘነበ ቁጥር በጎርፍ ተሸርሽሬ የማልቅ እየመሰለኝ እሰጋ ነበር - በልጅነቴ። #አለማወቅ #ዳዊት ወንድማገኝ (ዶ/ር)

... ጸሐይን በምእራብ አስወጥቶ በምስራቅ ካላጠለቃት፣ በምድር ላይ ያለውን የሞት ሰቆቃ ሞትን አሸንፎ ዘላለማዊነትን ካላስገኘ ምንድነው ፉከራው? ... እኔ ደግሞ ይህንን ማድረግ ካልቻልኩና ለመለወጥ
... ጸሐይን በምእራብ አስወጥቶ በምስራቅ ካላጠለቃት፣ በምድር ላይ ያለውን የሞት ሰቆቃ ሞትን አሸንፎ ዘላለማዊነትን ካላስገኘ ምንድነው ፉከራው? ... እኔ ደግሞ ይህንን ማድረግ ካልቻልኩና ለመለወጥ ካልቻልኩ ብተኛም ዋጋ የለውም። ... ሰማይን ባህር ውስጥ ለመጨመር፣ አስቀያሚነትን በውበት ለማጥፋት ሰቆቃ የተባለውን ሁሉ በደስታ ለመቀየር ወስኛለሁ። ... የእኛን እድሜ ዘላለማዊ አደርገዋለሁ። ሰማይ ባህር ላይ ሲነጥፍ ጨረቃም በእጄ ስትገባ ... ከዚያ በኋላ ሰዎችም መሞት ያቆማሉ። ለዘላለም በደስታ ይኖራሉ። #ካሊጉላ #አልበርት ካሙ #ትርጉም - ጌታቸው ታረቀኝ

አሲምባ ላይ በነበርንበት ጊዜ አንድ ከኛ ጎራ ያለ ቄስ መረጃ እንደሚያቃብል ደረስንበት። መሣሪያዬን ወድሬበት "እውነቱን አውጣ" ብዬ ሳስፈራራው ቄሱ ፍንክች አልልም አለ። "እንግዲያውስ ልገድልህ ነው
+3
አሲምባ ላይ በነበርንበት ጊዜ አንድ ከኛ ጎራ ያለ ቄስ መረጃ እንደሚያቃብል ደረስንበት። መሣሪያዬን ወድሬበት "እውነቱን አውጣ" ብዬ ሳስፈራራው ቄሱ ፍንክች አልልም አለ። "እንግዲያውስ ልገድልህ ነውና መቃብርህን ቆፍር!" ብዬ መቃብሩን በልኩ አስማስኩት። መሣሪያዬን አቀባብዬ 'ኑዛዜ ካለህ ተናገር!' ስለው ... "ከመኝታ ቦታዬ ራስጌ የቀበርኩት ገንዘብ አለ፤ እሱን ልጆቼ ይጠቀሙበት። አንድ መንታ መንታ የምትወልድ ፍየል አለች። ፍየሏን ከአቶ እከሌ የሰረቅኳት ናትና መልሱለት። ይኸው ነው! አሁን ልትገድለኝ ትችላለህ!" አለኝ። መረጃ ማቃበሉን ባለማመኑ ብበሽቅም ሴትና ቄስን ገድሎ በማኅበረሰቡ ዘንድ ቅቡልነትን ማግኘት አዳጋች ስለሆነ ተውኩት። ይህ ከሆነ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ከተማ ቆይቼ ወደ ምሽጋችን ስመጣ ቄሱ እርሻ ሲያርስ ተመለከትኩ። በማሳዎቹ ድንበር መኃል ባለችው የጉብታ መስመር ስጓዝ ቄሱ አይቶኝ ኖሮ "አያ ጓዱ!" ብሎ ተጣራኝ። መልስም አልሰጠሁት። ማረሱን ሳያቆም "ምነው የደከመህ ትመስላለህ ..." አለኝ። መንገዴን ስቀጥል "ወደ ቤት ጎራ በልና ቡና እንጠጣ!" ሲለኝ "መርዝ ልትግተኝ ነው!" አልኩ በሆዴ። እርሻውን ተወውና ወደ እኔ ፈጠን ብሎ መጣ። ከመንገዴ ላይ ቆሞ "ባለፈው የወነጀልከኝ በሙሉ ትክክል ነው! አዎ መረጃ አቃብያለሁ! እኔን እንደማርከኝ አንድዬም እንዲምርህ፥ የማገለግላት ማርያም እንድትለመንህ እየፀለይኩልህ ነው!" አለኝ። መሣሪያ ወድሬበት ትንፍሽ ያላለው ሰውዬ አርጩሜ እንኳ በእጄ ሳልጨብጥ እውነታውን ነገረኝ። በሞቱ አፋፍ ላይ ቆሞ እንኳ አሻፈረኝ ያለው ሰው ያለአንዳች ጫና ግን እውነቱን አፈረጠው። ይሄ ሕዝብ ምንድነው የሚገዛው? ምንድን ነው የሚያሸንፈው? ማንን ነው የሚፈራው? ሕዝቡን አናውቀውም። እውነትም ሐበሻ ቅኔ ነው። #አስማማው ኃይሉ #አያ ሻረው

#በዚህ ዘመን ወደ ሲኒማ መሄድ ወደ አምልኮ ሥፍራ የመሄድን ያህል ነው። #በ21ኛ ክፍለ-ዘመን የሚትን ዕጣ ፈንታ ከሚወስኑ ጉዳዮች መሃል የሲኒማ ኪን ዓቢይ መሆኑን ይጠቁማል። በዚህ ዘመን ወደ ሲኒማ
#በዚህ ዘመን ወደ ሲኒማ መሄድ ወደ አምልኮ ሥፍራ የመሄድን ያህል ነው። #በ21ኛ ክፍለ-ዘመን የሚትን ዕጣ ፈንታ ከሚወስኑ ጉዳዮች መሃል የሲኒማ ኪን ዓቢይ መሆኑን ይጠቁማል። በዚህ ዘመን ወደ ሲኒማ መሄድ ወደ አምልኮ ሥፍራ የመሄድን ያህል ነው። (ሮበርት ሴጋል፣ 2004፣ Myth: A Very Short Introduction) #በይነ-ዲሲፕሊናዊ የሥነ ጽሑፍ ንባብ #ቴዎድሮስ ገብሬ

#ጂጂ ሳትሆን ሙዚቃ ዛሬ ተከበረች! ሙዚቃ ሰው ብትሆን ጂጂን ከመምሰል ምን ያግዳታል? መርፌ "ምን እጠቅም?" ብላ ነው ጨርቅ የምትበሳው፤ ከኋላዋ ግን ክር ይከተላታል። ባለቅኔዋ ሶሪት የኢትዮጵያን
+5
#ጂጂ ሳትሆን ሙዚቃ ዛሬ ተከበረች! ሙዚቃ ሰው ብትሆን ጂጂን ከመምሰል ምን ያግዳታል? መርፌ "ምን እጠቅም?" ብላ ነው ጨርቅ የምትበሳው፤ ከኋላዋ ግን ክር ይከተላታል። ባለቅኔዋ ሶሪት የኢትዮጵያን ሙዚቃ አንድ እርከን ከፍ አደርገዋለሁ ብላ መድረክ ላይ አልወጣችም። ግና እንኳን ለሀገራችን ቀርቶ ለወርልድ ሚዩዚክ ዠነር ተርፋለች። በችክችካ ሙዚቃ ብቻ የታጠረውን ጆሮ እነድለዋለሁ ብላ ማይክ አልጨበጠችም፤ ዳሩ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ቅንብቡን እጅግ በማስፋት ሙዚቃችን እንዲናኝ አስችላለች። በዘመኑ እንደ ጸያፍ የነበረውን "አዝማሪ" የሚለውን ስም ለመሸክም ሳታመቻምች፥ ትምህርቷን ሰውታ፥ በስደት ኬንያ ተንከራታ፥ ለሴት ልጅ እጅግ አስቸጋሪ በሆኑ በምሽት ክበቦች ሰርጥ አልፋለች። ፀሐይ የተሰኘው የመጀመሪያ አልበሟ በሕዝብ ዘንድ ቅቡልነትን ባለማግኘቱ በቀቢጸ-ተስፋ ከመዋጥ አምልጣ የለመለመች እንጂ በአንዲት ሌሊት ሽቅብ የወጣች ሸንበቆ አይደለችም። የሙዚቃዎቹ ግጥሞቿ ከማር ከንፈር የተቀዱ ብቻ ሳይሆን ከሚደማው ቁስል የመሆኑ ምስጢር የወጣችው አቀበት እጅጉን የተገደገደ መሆኑን ማሳያ ነው። ይህ የክብር ዶክትሬት ለኔ የሚሰጠኝ ትርጉም፦ #የምታደንቋት ሴት ልትደነቅ የሚገባት ናት የሚል confirmation ነው። #ለሀገራችን የሰጠሽው አበርክቶት እስከ Phd ከተማሩት ምሁራን ጋር እሚተካከል ነው እንደማለት ነው። #ሞዴል ልታደርጓት ይገባል እንደማለት ነው። #ነገ በሷ ዓይነት ደረጃ ለሚመጣ ሰው "እንዲህ ይከበራል!" የሚል ቀብድ ነው። #ሌላም ሌላም #በመጨረሻም ጂጂዬ እንኳንም ዩኒቨርስቲ ገብተሽ አዕምሮሽን ያላሳጠብሽ! ቢኒያም አቡራ

#ጂጂ ሳትሆን ሙዚቃ ዛሬ ተከበረች! ሙዚቃ ሰው ብትሆን ጂጂን ከመምሰል ምን ያግዳታል? መርፌ "ምን እጠቅም?" ብላ ነው ጨርቅ የምትበሳው፤ ከኋላዋ ግን ክር ይከተላታል። ባለቅኔዋ ሶሪት የኢትዮጵያን
#ጂጂ ሳትሆን ሙዚቃ ዛሬ ተከበረች! ሙዚቃ ሰው ብትሆን ጂጂን ከመምሰል ምን ያግዳታል? መርፌ "ምን እጠቅም?" ብላ ነው ጨርቅ የምትበሳው፤ ከኋላዋ ግን ክር ይከተላታል። ባለቅኔዋ ሶሪት የኢትዮጵያን ሙዚቃ አንድ እርከን ከፍ አደርገዋለሁ ብላ መድረክ ላይ አልወጣችም። ግና እንኳን ለሀገራችን ቀርቶ ለወርልድ ሚዩዚክ ዠነር ተርፋለች። በችክችካ ሙዚቃ ብቻ የታጠረውን ጆሮ እነድለዋለሁ ብላ ማይክ አልጨበጠችም፤ ዳሩ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ቅንብቡን እጅግ በማስፋት ሙዚቃችን እንዲናኝ አስችላለች። በዘመኑ እንደ ጸያፍ የነበረውን "አዝማሪ" የሚለውን ስም ለመሸክም ሳታመቻምች፥ ትምህርቷን ሰውታ፥ በስደት ኬንያ ተንከራታ፥ ለሴት ልጅ እጅግ አስቸጋሪ በሆኑ በምሽት ክበቦች ሰርጥ አልፋለች። ፀሐይ የተሰኘው የመጀመሪያ አልበሟ በሕዝብ ዘንድ ቅቡልነትን ባለማግኘቱ በቀቢጸ-ተስፋ ከመዋጥ አምልጣ የለመለመች እንጂ በአንዲት ሌሊት ሽቅብ የወጣች ሸንበቆ አይደለችም። የሙዚቃዎቹ ግጥሞቿ ከማር ከንፈር የተቀዱ ብቻ ሳይሆን ከሚደማው ቁስል የመሆኑ ምስጢር የወጣችው አቀበት እጅጉን የተገደገደ መሆኑን ማሳያ ነው። ይህ የክብር ዶክትሬት ለኔ የሚሰጠኝ ትርጉም፦ #የምታደንቋት ሴት ልትደነቅ የሚገባት ናት የሚል confirmation ነው። #ለሀገራችን የሰጠሽው አበርክቶት እስከ Phd ከተማሩት ምሁራን ጋር እሚተካከል ነው እንደማለት ነው። #ሞዴል ልታደርጓት ይገባል እንደማለት ነው። #ነገ በሷ ዓይነት ደረጃ ለሚመጣ ሰው "እንዲህ ይከበራል!" የሚል ቀብድ ነው። #ሌላም ሌላም #በመጨረሻም ጂጂዬ እንኳንም ዩኒቨርስቲ ገብተሽ አዕምሮሽን ያላሳጠብሽ!

ስለ-ፕሮፌሰር ተወልደብርሃን ገ/እግዚአብሔር ሕይወትና ሥራዎች የሚያትት ዶክመንተሪ ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ፣ ፕሮፌሰር ማስረሻ ፈጠነ፣ ሮማን ተወልደ፣ ለምለም ተወልደ፣ ፕሮፌሰር ሰብስቤ ... በየኔታ ተወልደ ማንነትና ሥራዎች ላይ ሐሳባቸውን አካፍለዋል። መልካም ቆይታ ሊንኩን እነሆ ፦ https://youtu.be/kIRzoKXnmOY

"እኔ ምልህ አክሊሉ፤ ስለፍልስጤማውያን፣ ስለቱፖማሮስ፣ ስለደቡብ አሜሪካ በሰፊው በማጥናት እነዚህን አገሮች የምንወቅሳቸው ለምንድን ነበር? የከተማ የትጥቅ ትግልን እንደስልት ስለሚያካሄዱ አልነበረምን
"እኔ ምልህ አክሊሉ፤ ስለፍልስጤማውያን፣ ስለቱፖማሮስ፣ ስለደቡብ አሜሪካ በሰፊው በማጥናት እነዚህን አገሮች የምንወቅሳቸው ለምንድን ነበር? የከተማ የትጥቅ ትግልን እንደስልት ስለሚያካሄዱ አልነበረምን? አሁን እዚህ ምን እየተደረገ ነው? #ዳኛው ማነው? #ታደለች ኃይለሚካኤል

አብርሀም ድንኳኑን በየቦታው ተክሎ፣ ዕድሜውን ሲፈጀው፤ በቀበሌ ዘመን፣ አለመኖር በጀው ዳዊትም ወንጭፉን ያለ እግዜር ይሁንታ፣ ቢያስወነጭፍ እንኳን፤ እጁ ይዛል እንጂ … አይደለም ጎልያድን፣ አይጥልም
አብርሀም ድንኳኑን በየቦታው ተክሎ፣ ዕድሜውን ሲፈጀው፤ በቀበሌ ዘመን፣ አለመኖር በጀው ዳዊትም ወንጭፉን ያለ እግዜር ይሁንታ፣ ቢያስወነጭፍ እንኳን፤ እጁ ይዛል እንጂ … አይደለም ጎልያድን፣ አይጥልም ብርትኳን እኔም በዘመኔ ማመስገን ተስኖኝ፣ እንዲሁ ስፈጠር ድንኳኔን በሳለሁ፣ በተሰጠኝ ጠጠር። አስታወሰኝ ረጋሳ (ASTU ... አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ብላችሁ የምታነቡ ሰዎች ግን እረፉ 😋)

#እሳቱ ይነዳል፤ ጭሱ ወደ ሰማይ ይወጣና ከደመና ጋር ይቀላቀላል፤ የቱ ጭስ፣ የቱ ደመና እንደሆነ መለየት ያስቸግራል! #ኃይል ከበደ #ኦደሲ (በዲፕሬሽን ሸለቆ ውስጥ ረጅሙ ጉዞ)
#እሳቱ ይነዳል፤ ጭሱ ወደ ሰማይ ይወጣና ከደመና ጋር ይቀላቀላል፤ የቱ ጭስ፣ የቱ ደመና እንደሆነ መለየት ያስቸግራል! #ኃይል ከበደ #ኦደሲ (በዲፕሬሽን ሸለቆ ውስጥ ረጅሙ ጉዞ)