ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ
Open in Telegram
👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን። 👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። 👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ✴ ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm
Show more1 955
Subscribers
-124 hours
-57 days
-2730 days
Posts Archive
1 955
በሳሪያን ኮት ላይ፥ ያንን ቀጭን ኩታ፥ ጣል አድርጌ
በመኮንን ድልድይ፥ ልምጣ በደረጃው፥ በፒያሳ አድርጌ
ለቀጠሮው፥ በሳሪያን ኮት ላይ ቀጭን ኩታ ጣል አድርጓል። ሳሪያን ኮትን የነደፈው ማርቲሮስ ሳርያን የተሰኘ ሶቭየት አርሜኒያዊ ሲሆን የአርመኖች ዘመናዊ የስዕል ትምህርት ቤት መስራችም ነበር። ደንበኛ ሶሻሊስት እንደሆነም ይነገርለታል። ቁልፍ የሚበዛው የሳሪያን ኮት የወታደሮች ሁነኛ ምርጫ ነው። የቀጠራት አመሻሹን ስለሆነ ብርድ ከሰውነቱ እንዳይዘልቅ በማድረግ ረገድ ኮቱ ሁነኛ መድኅን ነው። በተጨማሪም፥ በሳሪያን ኮት ላይ ቀጭን ኩታ ማዋዛቱ ሳቢ ገጽታን ይደርብለታል።
የቀጠራት ከሰፈሯ አቅራቢያ ነው። የፍቅር ክራሩን ሲከረክር በፍጥነት ሰምታ ምላሽ እንድትሰጠው፥ በመንደሯ ነው የቀጠራት። ፍቅሩን በቶሎ በሚገልጸው ዶሮ ተመስሏል። የፍቅር አኩኩሉው እንዳይታነቅበት ሰግቷል። ዶሮ ማነቂያ፥ ድሮ ማነቂያም አልነበር? ፍቅሩ ከወንጀለኛነት አስቆጥሮት እንደቀደመው ዘመን እንዳይሰቀል ሰግቶ ይሆን? የፍቅር እሪታው በከንቱ እንዳይባክን ውስጡ ጥርጣሬ ሰርጓል። የናፍቆቱ ጩኸቱ፥ ድምጸ-ከልብ እንዳይሆን ሰግቷል። "እሪ በከንቱ ማን ሊሰማው ነው ጩኸቱን?" አይደለ ብሂሉ?! በዶሮ ማነቂያና በእሪ በከንቱ መንደር አሳብሮ ስጋቱን አመሳጥሯል። ይኼን ስጋቱን ተገንዝባ በፍጥነት ብቅ እንድትል ያስገነዝባታል።
ጥሪውም የክራር ድምጽ ነው። ክራር ውስጥ የሷ ስምን የያዘ ድምጽ አለ። ስም ያለው ሞኝም አይደል? እቤቷ በር ላይ ቆሞ የከተም በሩን በማንኳኳት ከሚወጣው ድምጽ በላይ ክራሩ ያስተጋባል።
በፍቅር ማነቂያው፥ ዶሮ እንዳይል በከንቱ፥ እሪ አንችን ወዶ
ክራሩን ስትሰሚ፥ ብቅ በይ ቆሜያለሁ፥ ከበርሽ ማዶ።
#ወደ ፍቅር ጉዞ ...
#ቢኒያም አቡራ
1 955
የዮቶር ልጅ ርሰቱ
ዜግነቴን ሳሰላስለው
ዓባይ ሆኖ ጣና ዳር ቤቱ፤
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እንደ “ታቲሆያ” ናት። “ታቲሆያ” በደቡብ ምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ዘማሪ ወፍም አይደለች? በአፍሪካ ደራሲያን ዘንድ እንደ ነጻነት ተምሳሌት ተደርጋ ትሳልም የለ? ከሰው መጀመሪያ የነቃንስ እኛ አልነበርን? ለወንዛችን ባዳ ሆነን በዓባይ ላይ ከተኛን፥ ቆንጆዎቹ እንዴት ይወለዳሉ? ቆንጆዎቹ ተወልደውስ ቢሆን ማን ያውቃል? የተኛ ሰው መወለዳቸውን በምንስ ይገለጥለታል?
የቴዲ ገጸሰብም የዮቶር ልጅ ነው። ጥበብ ለመቅዳት ከወንዙ ርቋል። ዘመናዊ በተሰኘው ትምህርት ሰበብ ባህር ማዶ አቋርጧል። ከቀዬው መራቁ ከሌሎች ምክንያቶች ጋር ተዳብሎ ለወንዙ ባዳ አድርጎታል። ግዮንን የሚያህል ጅረት ታቅፎ በጥም እንደተኛም ይነግረናል። ሌሎቹም እንዳሸለቡት። ታንዛንያ፥ 36 ሚሊዮን አዉንስ የሚሆን (ወደ አንድ ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ) የወርቅ ክምችት እንደታቀፈችው። ከሁለት ቢልየን ቶን በላይ የከሰል ድንጋይን ለአርባ አመታት ቢወጣ እንኳን የማይነጥፍ የድንጋይ ከሰል ክምችት በሆዷ የያዘችው ሞዛምቢክ፥ ሕዝቧን በድህነት እንደምታስፈጀው። በመኪና ምርት ኢንዱስትሪ እጅግ ተፈላጊ የሆነውን ቦክሳይት፥ የዓለምን ሁለት ሶስተኛውን በእጇ የያዘችው ጊኒ-ኮናክሪ በእንቅልፍ እንደደነዘችው። 366 ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት አንጎላ፥ 40 በመቶው ሕዝቧ በቀን ከአንድ ዶላር በታች ገቢን እንደሚያገኘው። ግዮንን የሚያህል ጅረት ታቅፈን በጥም እንደምናልቀው። ከሰው መጀመሪያ ነቅተን እንዳንቀላፋነው።
ጥበብ ርቄ ስቀዳ
ዜግነቴን ሳሰላስለው
እንዴት ልሁን ለወንዜ ባዳ?
ዜግነቴን ሳሰላስለው
ጠምቶኝ ተኛው በዓባይ ዙሪያ
ከሰው መጀመሪያ ነቅቼ።
#ወደ ፍቅር ጉዞ
#ቢኒያም አቡራ
1 955
በመዝናኛና በቁም ነገር የዳበረ ምርጥ ቻናል ይዘንላችሁ መጥተናል።
ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን
https://youtu.be/KgZxmxbNkU0?si=2s8nCVaRMz2zRoP_
1 955
መስቀል ተ ሠላጢን ከመጽሐፍ ጠቅሳ
"እመነኝ" አለችኝ፥ ልትቀብረኝ ምሳ፥
በኦቴሎ ቲያትር ላይ ደንበኛ የሆነ የመስቀል ተሠላጢን ምሳሌ እናገኛለን። እንደሚታወቀው ቃስዮ እና ኦቴሎ በኢያጎ እና በሮድሪጎ ሴራ አማካኝነት ተቀያይመዋል። ይህንን ኦቴሎም ሆነ ቃስዮ ጨርሶውኑ አያውቁም። መሰሪው ኢያጎ መስቀሉን በምላሱ፥ ጉድጓዱን በልቡ ምሶ፥ ቃስዮን ያማክራል። በሠላጢኑ ጎኑን ሊሰብቀው የመስቀሉን መንገድ ይጠቁማል። ከኦቴሎ ዘንድ ይቅርታን የሚያስገኘውን ትክክለኛ ሰርጥ ያሳየዋል። እርቅ የሚፈጸምበትን የመስቀል ምርኩዝ ለቃስዮ ይሰጠዋል። የኦቴሎ የቅያሜ ጥሩር በዴዝዴሞና ለስላሳ አንደበት እንደሚወልቅ አሻግሮ ያሳየዋል። ቅሉ፥ የመስቀሉ ምርኩዝ ስሩ ደንበኛ አንካሴ ነው። የኢያጎ ግብር መስቀል ተሠላጢን መሆኑን ራሱ እንዲህ በማለት ያጸናልናል፦ "በገሃነም ግብረ-ገብ ውስጥ አጋንንት የመጨረሻውን ጭለማ ሲጎናጸፉ እንኳ እንደ አሁኑ እንደኔ አያያዝ አስቀድመው የጽድቅን መግቢያ ትርዕይት ያሳያሉ አሉ።"
መስቀል ተሠላጢን እርስ በራስ የሚጻረሩ የሁለት ቃላት ድማሮሽ ነው። ጽድቅ ተ ኩነኔ። ሟች ተ ገዳይ። ምርኩዝ ተ አንካሴ። የሁለቱ ጽንፍ ትስስሮሽ ግን ውስብስቡን የእጓለ-መህያው ሥነ-ልቦናን የሚፈክር እርሾ ሆኗል። ከውጭ መስቀል፥ ከውስጥ ጸብ የጨበጠ ንጉሥ፥ ከሥር ጉድጓድ ምሶ፥ ከላይ ድግስ እንዳበላው እሷም ወጥናለች። የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር ልትፈጽም። ከቤልሆር መቅደስ ምስጢር አይታ የኩነኔ ዲቁና ተካነች። የክሕደት ሠላጢን ጨብጣ የእምነት መስቀሉን ልታሳልመው ዳከረች። ግና ቀድሞውኑ መዘጋጀቱ በጀው። ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ እንደማይለቅ ተገንዝቦ፥ ቀድሟት ከቀሳውስቱ ጎራ ተሰልፎ ጠበቃት።
ተምራ ተክና ላሳር ለኩነኔ፤
ደቁና ስትመጣ ቄስ ሆንኩባት እኔ።
ከወደ ፍቅር ጉዞ መጽሐፍ የወሰደ
1 955
ሲመሽ ወደማታ ሁሉ ዘግቶ በሩን
ታም ታራም ሳረገው ብቅ በይ ክራሩን።
በዐፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት አዲስ አበባን የሚጠብቁት ዘበኞች ከሐረርጌ የመጡ ሱማሌዎች ነበሩ። ሕዝቡ ደወሪያ ይላቸዋል። ምሽት ሦስት ሰዓት ላይ የጩኸት ድምጽ ሲያሰሙ ሕዝቡ ሁሉ በየግቢው ይከተታል። ከዚያ በኋላ መንገድ ላይ ያገኙትን ያስሩትና ያሳድሩታል። ሲነጋም አንድ ሩብ ከፍሎ ይወጣል። አሁን ግን መቼቱ ከኮሪያ ዘመቻ ወዲህ ስለሆነ ደወሪያዎች እንደሌሉ እሙን ነው። ስለዚህ በምሽት ቢቀጥራት ችግር የለውም። ናፍቆቱን ሳይወጣ የደወሪያዎች ጩኸት አያለያያቸውም። የእሱ ክራር እንደ ደወሪያ ሰውን ወደ ቤቱ ባያስገባም። እሷን ግን ከቤቷ ያስወጣል። ሁሉም በሩን ዘግቶ እቤት መስረጉን የእሱ የክራር ድምጽ ሲያሳብቅ ለእሷ ደግሞ የጥሪውን መልዕክት ያደርሳል። ለዚያች ዘበናይ የክራሩ ድምጽ የዘማቹን ናፍቆት ይመልክላታል። ለዚያች ዘበናይ። ጠጉሯን እንደ ሜሪ አርምዴ ለተተኮሰችው ዘበናይ። ሜሪማ ዶሮ ማነቂያም አልነበር የተወለደችው? ልክ እንደ ዘማቹ ተፈቃሪ። በፋሽስት ጥልያን ላይ ከዘመቱ አርበኞች መሐል አንዷም አይደለች? በዘመናዊ የልብስ ስፌት እና በዘመናዊ ዳንስ ማን ይስተካከላታል? የፀጉር ተኩስ ሙያን “ያኸዘበችው” እሷም አይደለች? ከክራር ድምጽ ጀርባ እንደ ማርታ አሻጋሪ ባለው ወፍራም ድምፇ ስታንጎራጉር የማይመሰጥ ማን አለ? የዘማቹ ተናፋቂ ጠጉሯን እንደ ሜሪማ ተተኩሳ፥ ፍቅሯን በክራር የምትገልጽ ዘበናይ ናት። እብድና ዘበናይ የልቡን ይናገርም የለ?!
#ወደ ፍቅር ጉዞ መጽሐፍ መገኛ
ሮማናት መጻሕፍት መደብር - ለገሃር
ጃዕፋር መጻሕፍት መደብር - ለገሃር
ክብሩ መጽሐፍ መደብር - ቸርችል ጎዳና
እነሆ መጻሕፍት መደብር - 4 ኪሎ
ኮሜርስ መጻሕፍት መደብር
1 955
ድር አስተርታሪ ጥልፍ የጠለፈው
አስዋብኩሽ ብሎ ምን አስጎበረው?
አንድ ሁነኛ የአርሲ ኦሮሞ ዋሰዲ አለ። የፍየል ወጠጤ ሦስት ነገሮችን ይመስላል፤ በጺሙ ሽማግሌን፥ በጩኸቱ እብድን፥ በጭራው ውሻን። በጺሙ ሽማግሌን ይመስላል እንጂ በዕድሜ አኮፋዳ የቋጠረው ተቃርኖዎችን የማረቅ ልቡና የለውም። ጭራ አለው ግን ገበናን የመሸፈኛ ግብር የለውም። ድር አስተርታሪውም እንዲያ ነው። ድር አስተርታሪው ጥልፍ መጥለፍ የሚችል ይመስላል። ግን ይጎብራል። የቱ ጋር ማጠጣት እንዳለበት አያውቅም። ያዛንፋል። አስጌጥኳት ብሎ ያጠለሻታል። ሁሉም ነገር ተነባቢ ነው ባዩ የዲኮንስትራክሽን ኀልዮት የድር አስተርታሪው ጭምብል ናት። ነባሩን ሚት እንፈትሸው በሚል ቀና መሰል መንፈስ ነባሩን ከማስጌጥ ይልቅ የሚያስጎብር አካሄድ የተጠናወተው የፍየል ወጠጤ ነው። እስማለሁ ብሎ ንፍጥ እንደለቀለቀው። እኩላታለሁ ብሎ እንዳጠለሻት።
#ወደ ፍቅር ጉዞ መጽሐፍ መገኛ
ሮማናት መጻሕፍት መደብር
ጃዕፋር መጻሕፍት መደብር
ክብሩ መጽሐፍ መደብር
እነሆ መጻሕፍት መደብር
ኮሜርስ መጻሕፍት መደብር
ሻሸመኔ - ሐዊ መጽሐፍ መደብር
ሆሳዕና - +251925608804
ሐረር - +251925079835
አርባምንጭ - 0989826060
ሐዋሳ - 093 071 4458
1 955
ኡኡ ባልል ባፌ ውጣ ከተራራ፥
ድምጹ ሳይገጫጭ አንዱ ካንዱ ጋራ፤
ጥቀርሻዋ እሥሩ እየተዝለገለገች ነው። ከሲታ ሕጸጽ ለመወፈር ብሌኑ ሥር እያደባች ነው። የክፋት እንቦጭ፥ የገዛ የሕይወት ባሕሩ ውስጥ ሰርጋ፥ እንዘጭ ልታደርገው እያሟሟቀች ነው። ኋላ እምቢኝ እምትል አሜኬላ በገዛ ሜዳው ልታብብ ሽታለች። ከሰጋርነት የራቀች ባዝራ ልትሆን ከጮሌነት አቅጣጫ ይልቅ ወደ መጋዣነት ቀዬ የሚያደርሳትን ኩርባ መርጣለች።
'ስሕተቷ ዕድሜ ካገኘ ሕግ ይሆናልና' ኋላ የመሰናከያው ድንጋይ እንዳትሆን፥ ከሕግ አርቃቂው እስከ ሕግ አስፈጻሚው ሸንጎ ድረስ ቅቡልነት እንዳታገኝ “ኡኡታውን” ማሰማት አለበት። ድምጹ እንዳይገጫጭ አንዱ ከአንዱ ጋራ። ጊዜ የእሱ ድንጋይ የምትነርትበትን ወረፋ ለቅሏ ሳይቸራት፥ የቅልነቷን ውስንነት ቀድሞውኑ ማጽናት ይኖርበታል። ዛሬ በሰዓቱ፥ አንደበቱ ኡኡታውን ማሰማቱ ግድ ነው። አለዚያ ወቅቱ ካለፈ በኋላ መጮህ፥ ሰሚ የሌለ አፍ ነው የሚያደርግ! የክረምት ዝናብ ካለፈ በኋላ በበጋ እንደሚዘራ አዝእርት ያለ። ትንሿ ጠብታ ኋላ ጎርፍ ሆና ገንድሳ እንዳትጥል ከአሁኑ በአንደበት ሁነኛ ቦይ መቅደድ ያሻል። በጎርፍ የተወሰዱ ጊዜ ኡኡታው ለምንም አይበጅም። ልሳን ምን ቢከፈት ከደራሽ ውሃ አያስመልጥ። እሪታውንም ሆነ ቃላቱን ከማባከን ውጭ። ለዚህ ነው በጊዜ እሪታውን የሚያቀልጥ። ለዚህ ነው ሕጸጿን ለመንቀስ የፈጠነው። በኢትዮጵያ ላይ የተደቀኑ እባጮች ሳይወሯት የሚጮኸው። ኋላ ሰሚ ለሌለህ አፍ እንዳይሆን። ወደ ፍቅር ጉዞው እንዳይታጎል።
ኡኡ ሳትል አፌ ዛሬ በሰዓቱ፥
'ጅብ ከሄደ ውሻ' ይሆናል ጩኸቱ፤
ኡኡታዬ ላይሰማ ያኔ
ነይ ብላትም አስኪነቃ ልሣኔ
#ወደ ፍቅር ጉዞ
©ቢኒያም አቡራ
#የመጽሐፉ መገኛ
ሮማናት መጻሕፍት መደብር
ጃዕፋር መደብር
እነሆ መጻሕፍት መደብር
ኮሜርስ መደብር
1 955
ማ ዘንድ ይደር ሄዶ ጎኔ
ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ
ዘመኑ በሼክስፔር ብእር እንደተቀረጸው ኢያጎያዊ ኀልዮት የረበበት ነው። 'ማ ዘንድ ይደር ሄዶ ጎኔ፥ ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ" ለኢያጎያውያን ፉርሽ ነው። ከሮድሪጎ ጅላጅልነት የሚያስቆጥር እዬዬ ነው። "ኑሮ ሰቀቀን ስትሆን አዎን ጅል ነው የሚኖር ሰው፥ ሐኪማችንም ሞት ሲሆን መድኃኒታችንም ሞት ነው" ከማለት የማይተናነስ ተራ እንቶፈንቶ ነው፤ ለኢያጎያውያን። ኢያጎ "እንኳን ለዚህች ላንዲት ዶሮ ከምል ራሴን አጠፋለው - ነፍሴን ለጅንጀሮ ኑሮ ለውጬ መኖር እመርጣለው" ባይም አይደል?
ልክ ቻይናዊው ባለቅኔ ሊ ፖ ለጨረቃ እንዳለው ፍቅር ጋር በሚገዳደር ሁናቴ “ነበልባላዊ መፍቅድ” በቴዲ ገጸሰብ ላይም ጎጆውን ቀልሷል። (ሊ ፖ ጨረቃን ሊስማት በሚያደርገው መውተርተርም አይደል ሕይወቱን የገበረው?) ፍቅር መልከ ማክዳ ላይ ጥሎታል። በፍቅሯ ከንፏል። ሊ ፖ ጨረቃን ባፈቀራት መጠን።
እንኳን ሰው ይቅርና ዕቃ ራሱ የሚያድረው ታማኝ ሰው ጋር ነው። እምነት ነው የመተሳሰሪያው ውሉ። አለዚያ ዕቃው ስለመሰንበቱ አንዳች ዋስትና የለም። ዕቃው ላለመጉደሉ እርግጠኝነት የለም። ጎኑን 'ማ ጋር ካላሳደረም እንዲያ ነው። ጎኑን እሷ ጋር የማያሳድር ከሆነ አይከርምም። ጤፉ ጎተራ ውስጥ ካላደረ የአልፎ ሂያጅ መጫወቻ ይሆናል። የቴዲ ገጸሰብም ሆነ መሰሎቹ ከሰውነት ላለመጉደላቸው መያዣ የለም። ያለፍቅር የእምነት ቆጥ ላይ አይወጣም። የእምነት መሠረት ፍቅር ነውና። መልከ ማክዳዋ ፍቅር ነች። ካለፍቅር ሰውነት የለምና 'ሰው አልሆንም ካላንቺ እኔ' ይላል።
#ወደ ፍቅር ጉዞ
ቢኒያም አቡራ
የመጽሐፉ መገኛ
እሸቱ እና ሮማናት መጻሕፍት መደብር
ጃፋር መጻሕፍት መደብር
እነሆ መጻሕፍት መደብር
ኮሜርስ መጻሕፍት መደብር
1 955
ነይ ወደ ፍቅር ጉዞ እንሂድ! ... ከነገ ወዲያ አርብ 11 ሰዓት ወመዘክር አዳራሽ ጋ ጠብቂኝ። በጋሽ አያልነህ ሙላቱ የዘመን ሰርጥ ተምመን፣ ከዛሬ 18 ዓመት በፊት በሶልያና የግጥም ሲዲው የተዋወቅነው ኤፍሬም ስዩም ጎዳና እንደርሳለን።
በናቲ ማናዬ የአጋፋሪነት ኩርባ መትተን፥ የይነገር ጌታቸውን የመጽሐፍ ዳሰሳ እንኮሞኩማለን። በዶ/ር ፌቤን ፋንጮ የታከሙ ስንኞችን ቃርመን፥ በወሎዬው ሙሀመድ ሙፍቲ የግጥም ሁዳድ እንጋልባለን።
በጨዋታ አዋቂው ዮናታን ጌታቸው ዓረፍተ ስንኞች ፈግገን ከሮማን ተወልደብርሃን አትሮኖስ እንደርሳለን። ከሮማን ሼልፍ ደግሞ ምን ይታጣል? ለነገሩ አቶ ስስት የሷ መደርደሪያ ላይ አይገኙም። በየአብቃል እና በኪሩቤል ሙዚቃ ነፍስያችንን አረስርሰን፥ ከጌታቸው መንጉዳይ ዘንድ ቁምነገር እናፍሳለን። ብቻ ወመዘክር አዳራሽ ጋር ደገፍ ብለሽ ጠብቂኝ!
ወመዘክር ከጠፋሽ ብሔራዊ አከባቢ ከሚገኘው የ etv ሕንጻ ጀርባ የኢትዮጵያ ቤተመጻሕፍትና ቤተመዛግብት የሚለው ሰፊ ግቢ ነው። አትፍሪ የአባባ ቤት ነው። የኛ ነው! 😛
ድንገቴ ፈንጠዝያ እንግዳ ...
1 955
ሁለተኛው መጽሐፌ ...
በዜማ እና ግጥም ደራሲው፣ በክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን የዘፈን ግጥም ይዘት ላይ ያሰናዳሁት የፍካሬ(review) መጽሐፍ፣ ከጥቂት ቀናት በኋላ ለንባብ ይቀርባል።
ጥፊም ይደገማል!
1 955
#የጠበቅነው ቀርቶ ያልጠበቅነው መጣ
እባቡን ብንቀብረው ከስር ጊንጡ ወጣ
________________
የደርጉ መኪና ሸራ የለበሰው
ያን ሁሉ መኳንንት ወዴት አደረሰው?
--------------------------
#ባህያ ቆዳ የተሰራ ቤት
ብትንትን ይላል ጅብ የጮኸ'ለት
-------------------------
#አስበን እንስራ ለነገም እንዲሆን
ይሁን ይሁን ብለን የማይሆን እንዳይሆን
--------------------------
#አልሆን ብሎ ብሎ ነገሩ ሲጠጥር
ውጥረቱ እንዲላላ የላላውን ወጥር
--------------------------
#የወያኔ ጥይት ጨሞጋ ቢያጓራ
ማርቆስ ላይ ቀረ ደሐና ባንዲራ
#ቅሌት
#አንዳርጌ መስፍን
1 955
#ሀብታሙ_አለባቸው የኔ ዘመን ብርሃኑ ዘርይሁን ነው (ለኔ)
#አንፋሮ ፦ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ እና የልጅ እያሱን ፍጥጫ፥ ብሎም የዘመኑን የፖለቲካ ጥልፍልፎሽ በተባ ብዕሩ የከተበበት መፅሐፉ ነው።
#የቄሳር_እምባ ፦ መንግሥቱ ኃይለማርያምንና የዘመን ጓዶቹን ትምምታ፥ ወሽኔ በሆነ ብዕሩ የሳለበት ድንቅ ጥራዙ ነው።
#አውሮራ ፦ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጦርነት መባቻን በታሪካዊ ልቦለድ ዘውግ የተጠበበት ሥራው ነው።
#የሱፍ አበባ ፦ በያ ትውልድ፥ በተለይም በኢህአፓ የነበሩ ተረኮችን ምስል ከሳች በሆነ ሁኔታ ያቀረበበት ድንቅ ፈጠራ ነው።
1 955
እኛ የጂጂ አድናቂዎች ... ሰኞ ዕለት፣ ጥቅምት 12 የጂጂን ልደት ምክንያት በማድረግ ተስፋ አዲስ የሕጻናት ካንሰር ሕሙማንን ለመጠየቅ ከቀኑ 10:00 ላይ እንሄዳለን ። ለልጆቹ እራት እና የተለያዩ ነገሮችን ለማበርከት ፒያሳ ሰባ ደረጃ እንሰባሰባለን። የዕለቱ የክብር እንግዳ ጋሽ ብርሃኑ ሽብሩ ናቸው። ጂጂ በ1989 ዓ.ም የሠራቻቸውን ሁለት ፊልሞች ዳይሬክተር የነበሩት ጋሽ ብርሃኑ ሲሆኑ ጂጂን ከማንም በላይ በደንብ ያውቋታል። በተጨማሪም ጋሽ ብርሃኑ የኢትዮጵያ ፊልም ኮርፖሬሽን የመሠረቱና በዳይሬክተርነት የመሩ ሰው ናቸው።
መርኃግብራችን
1. የካንሰር ሕሙማን ሕጻናት በምግብና በአንዳንድ ነገር በጂጂ ስም ይረዳሉ።
2. የጂጂን ልደት እናከብራለን፤ ከብላቴናዎቹ ጋር።
3. ጋሽ ብርሃኑ ሽብሩ ጂጂ ፊልሞቹን በሠራችባቸው ወቅቶች የነበሩ ተረኮችን ያቀጉናል።
4. በማግስቱ ማክሰኞ (ጥቅምት 13) በጂጂ ስም የደም መለገስ መርኃግብርም አለን። 10 ሰዓት፣ ቀይ መስቀል።
በእነዚህ ሁለት ቀናት የጂጂ ወዳጅ እና አድናቂ የሆነ ሰው ቢመጣ በደስታ እንቀበላለን።
ለሕጻናቱ ለሚወጡ ወጪዎች መተባበር የሚፈልግ ታች ባለው አካውንት ማስገባት ይችላል!
1000515382643 (ዘነበወርቅ ስዒድ፣ ኤልሳ ዳግማዊ)
እናመሰግናለን 🙏🙏🙏
ለተጨማሪ መረጃ +251923609126
1 955
እጄ ላይ የቀረ የባለቅኔዋ ሶሪት መጽሐፍ 7 Copy አለ። የአምስቱን Copy ገቢ የጂጂ የልደት ቀንን ምክንያት በማድረግ በተስፋ አዲስ የሕጻናት የካንሰር ሕሙማንን ለመጠየቅ ለሚካሄደው program ልናውለው አቅደናል።
ምንም እንኳ የአንዱ መጽሐፍ ዋጋ 150 ብር ቢሆንም ለተስፋ አዲስ ገቢ ማሰባሰቢያ እንዲሆን አንዱን copy በ 500 ብር እንዲገዙ አምስት ሰው እንፈልጋለን።
ስለዚህ ከታች ባለው አካውንት ቁጥር 500 ብር በማስገባት የዚህ የተቀደሰ መርሐግብር አካል እንዲሆኑ በአክብሮት እንጋብዛለን!
1000515382643
ዘነበወርቅ ስዒድ፣ ኤልሳ ዳግማዊ
የጂጂን ለጂጂ!!!
እናመሰግናለን
1 955
ይናፍቀኝ ነበር . . .
የመንደር ጭስ ማታ . . .
ይናፍቀኝ ነበር የሣር ቤት ጥቀርሻዉ
መደቡ ምሰሶዉ፤
ማገሩ ግድግዳዉ፤ አጥሩና ጥሻዉ፡፡
የፈራረሰ ካብ . . .
ቀጭን ጠባብ መንገድ በመንደር የሚሮጥ
ቅጠል የሸፈነዉ፤
ሣር ያለባበሰዉ፤
እነዚህ፤ እነዚህ፤ ይናፍቁኝ ነበር፡፡
የተቆላ ቡና፤
የሚወቀጥ ቡና፤
የጎረቤት ቡና አቦል ሁለተኛ፤
የተረጨ ቆሎ የሚያርቅ መጋኛ፤
የሚጨሰዉ ዕጣን . . .
እንጀራ በመሶብ ወጥ የፈሰሰበት
ያገልግል እንጀራ የሚቧጠጥ ፍትፍት፤
የክክ ወጥ የሽሮ፤
የሥጋ የዶሮ፡፡
ይናፍቀኝ ነበር ቅራሪ ጉሽ ጠላ
ይናፍቀኝ ነበር ፊልትር ዞማ ኮላ፡፡
ያገራችን ድግስ . . .
ከበሮ ጭፈራዉ፤
ዝላዩ እስክስታዉ፣ ስካሩ ሁካታዉ፡፡
ትርክምክሙ ነበር ግፊያዉ ትንቅንቁ
ኳኳታዉ እርግጫዉ ዘፈን ድብልቅልቁ፡፡
#የኔታ ገብረ ክርስቶስ ደስታ
#መንገድ ስጡኝ ሰፊ
