en
Feedback
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

Open in Telegram

👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን። 👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። 👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ✴ ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm

Show more
1 955
Subscribers
-124 hours
-57 days
-2730 days
Posts Archive
ቢኒ የመጽሐፍ ግብዣ 18 ምስጢረኛው ባለቅኔ በአባት ዓለም ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድኅን ሥራዎች ላይ ትንታኔ የሚሰጥ የሚካኤል ሽፈራው መጽሐፍ ነው። የተመረጡ የሎሬት ጸጋዬ ግጥሞች እና ቲያትሮች ተፈክረውበ
ቢኒ የመጽሐፍ ግብዣ 18 ምስጢረኛው ባለቅኔ በአባት ዓለም ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድኅን ሥራዎች ላይ ትንታኔ የሚሰጥ የሚካኤል ሽፈራው መጽሐፍ ነው። የተመረጡ የሎሬት ጸጋዬ ግጥሞች እና ቲያትሮች ተፈክረውበታል። ጋሽ ጸጋዬን ለመረዳት ቀላል የማይባል አስተዋጽዖ የሚለግስ መጽሐፍ ነው። አርክቴክት ሚካኤል ሽፈራው በመጽሐፉ ገጽ 74 ላይ ጋሽ ጸጋዬንና አዋሽ የተሰኘ ቅኔያቸውን አሰተማስሎ እንዲህ ይለናል፦ ጸጋዬንና አዋሽን የሚያመሳስላቸው ራሳቸውን በራሳቸው የመዋጥ አሳዛኝ ታሪካቸው ነው። እስከዛሬ ከተዋወቅኳቸው የአገር ውስጥና የውጭ ሐገር አርቲስቶች የገሀድ ሕይወቱ አርቲስቲክ ህይወቱን ሸፍኖ መልሶ ራሱን ሲውጠው ያየሁት ይኸው የኛውን ጸጋዬን ብቻ ነው። ... እና ጸጋዬ ስለአዋሽ ሲቀኝ ስለራሱ አርቲስቲክ ህልውና ሲቀኝ በሥነ ጥበቡም መልሶ ሲፈጥረው ራሱን ስለፈጠረው የሀገራችን ባህል ስፒሪት መቀኘቱ ነው። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 17 አዝማሪው ልቤ የተሰኘው የጌታነህ ደጉ ድርሰት አንድ ለቤሳ ልቦለድነት የቀረበ ሥራ እና ዘጠኝ ወግ እና አጫጭር ልቦለዶችን ያካተተ ጥራዝ ነው። አይረሴ ገጸባሕርያት፣ ወሽኔ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 17 አዝማሪው ልቤ የተሰኘው የጌታነህ ደጉ ድርሰት አንድ ለቤሳ ልቦለድነት የቀረበ ሥራ እና ዘጠኝ ወግ እና አጫጭር ልቦለዶችን ያካተተ ጥራዝ ነው። አይረሴ ገጸባሕርያት፣ ወሽኔ ሊያስብል የሚችል ምስል ክሰታ፣ አንዳች ረብ የሚፈይድ ማሰሪያ አንቀጽ የመጽሐፉ ጠንካራ ጎኖቹ ናቸው። አዝማሪ ... ያዝልኝ ብለው የሰጡትን ግጥም አስተጋብቶ በውብ ድምጽ እንደሚያሰማው  ... እኔም ይህን ከገሃዱ ዓለም በዓይንና በጆሮዬ የተቀበልኩትን ልብ-ወለዳዊ ነጸብራቅ አሳምሬ ለመጻፍ ሞክሬአለሁ። ይለናል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 16 አውቶ ሜካኒኮች "Troubleshooter" የሚሉት የመኪና ሕመም የት እንደሆነ የሚያገኙበት መሣሪያ አላቸው። “የፈረንጅ ሚስት” የተሰኘው የእስከዳር ግርማይ መጽሐፍ በኢትዮ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 16 አውቶ ሜካኒኮች "Troubleshooter" የሚሉት የመኪና ሕመም የት እንደሆነ የሚያገኙበት መሣሪያ አላቸው። “የፈረንጅ ሚስት” የተሰኘው የእስከዳር ግርማይ መጽሐፍ በኢትዮጵያ መኪና ላይ ካሉ ሕመሞች አንደኛውን የሚጠቁም ባለ 119 ገጽ መጽሐፍ ነው፡፡ የመኪና አንዱ ብልሽት መኪናውን በሂደት ከጥቅም ውጭ እንደሚያደርገው ሁሉ በሀገር ላይ የተሰነቀረ አንድ ሳንካም ጉዞን ለመግታት አቅም ማደርጀቱ አይቀሬ ነው፡፡ እስከዳር ግርማይ የራሷን የሕይወት ሽንቁሯን ለማሳየት ምኩራብ ላይ ተሰይማለች፡፡ በዚህ የሕይወት ሽንቁር ስናጮልቅ በሀገራችን ካሉ ደዌዎች አንደኛውን እናገኝበታለን፡፡ ምን ይሆን ይህ ሳንካ? #ይነበብ! #ቢኒያም አቡራ

አሌፍ ቤት የተሰኘው የወንድሙ ገዳ መጽሐፍ "ድንቢጮ" በተሰኘ ገጸሰብ በኩል ታሪክን፣ ሃይማኖትን፣ ባሕልን የሚሞግት፣ በልቦለድ ዘውግ የቀረበ ፍልስፍናዊ መጠይቅ ነው። የወሎ ዘዬ በተጫነው ቋንቋ፣ ለአ
አሌፍ ቤት የተሰኘው የወንድሙ ገዳ መጽሐፍ "ድንቢጮ" በተሰኘ ገጸሰብ በኩል ታሪክን፣ ሃይማኖትን፣ ባሕልን የሚሞግት፣ በልቦለድ ዘውግ የቀረበ ፍልስፍናዊ መጠይቅ ነው። የወሎ ዘዬ በተጫነው ቋንቋ፣ ለአውዱ ስምሙ የሆኑ አስደናቂ ብሂሎች ታጭቀውበታል። ደራሲው ቋንቋውን የማዘዝ አቅሙ ላቅ ያለ ሲሆን በወል የተቀበልናቸውን ነገሮች በመጥያቄያዊ ዓረፍተነገር እንደ አዲስ እንድንመለከት ሸንቆጥ ያደርገናል። ለቅምሻ ታህል ከመጽሐፉ ውስጥ ያገኘኋቸውን አንድ አራት ብሂሎች ጀባ ልበላችሁማ 1. ወሬ ሲደራ እናቴ ቡዳ ነች ይመጣል 2. ልክ እንደ ጆሮ ጭገር ተደብቆ ያድጋል 3. ሥራ ያጣ ጢስ ይሞቃል 4. ሾላው ቢረግፍ ከዛፍ አይርቅም #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አስራ ሦስት "ማማ በሰማይ" ግለ-ታሪክ ነው፤ ሀገራዊ ታሪክም ነው። የግለሰብም፥ የጋርዮሽም፥ የህቡዕ ድርጅትም ተረክ አለው። ከሐረር የተማሪነት ሕይወቷ ልቧን ያነሆለለው የተማሪ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አስራ ሦስት "ማማ በሰማይ" ግለ-ታሪክ ነው፤ ሀገራዊ ታሪክም ነው። የግለሰብም፥ የጋርዮሽም፥ የህቡዕ ድርጅትም ተረክ አለው። ከሐረር የተማሪነት ሕይወቷ ልቧን ያነሆለለው የተማሪዎች እንቅስቃሴ፥ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አሳብሮ፥ በጌታቸው ማሩ ወጌሻ ኩርባ መትቶ፥ የኢህአፓን አላማ አንግቦ፥ በደም በተለወሰ ታሪክ ተጀቡኖ፥ ኁልቆ-መሳፍርት በሌለው አሳር ተፈትኖ፥ የወኅኒ ቤት አለምን አካሎ ወሽኔ በሚባል ቋንቋ ያህል ተሰድሯል። #ሕይወት_ተፈራ የያን ዘመን ክስተት በመተረክ ረገድ ቀላል የማይባል መዋጮ ካዋጡቱ ዋናዋ ትመስለኛለች። ማማ_በሰማይ የስልሳዎቹ ትውልድን ለማጤን ትልቁን መዋጮ ያበረከተ መፅሐፍ ነው (በኔ እምነት)። ጋሽ ጌታነህ አንተነህ ውብ አድርገው ተርጉመውታል! #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ከአገሬው የኪን ፍልስፍና ተነስቶ፥ በ40ዎቹ አርመናውያን አመጣጥ ጎዳና ተምሞ፥ ማርሽ ኢትዮጵያ እና ማርሽ ተፈሪን ተዝቶ፥ የኬቦርክ ናልባንዲያን እና የየኔታ ዮፍታሄ ንጉሴን ፍጥጫ አውስቶ፥ በፋቼታ ኔ
ከአገሬው የኪን ፍልስፍና ተነስቶ፥ በ40ዎቹ አርመናውያን አመጣጥ ጎዳና ተምሞ፥ ማርሽ ኢትዮጵያ እና ማርሽ ተፈሪን ተዝቶ፥ የኬቦርክ ናልባንዲያን እና የየኔታ ዮፍታሄ ንጉሴን ፍጥጫ አውስቶ፥ በፋቼታ ኔራ ኩርባ ታጥፎ፥ መሰንቆ እንደ ጦር መሣሪያ የተቆጠረበትን አውድ አውግቶን ይነጉዳል። ጠመንጃና ሙዚቃ - በይነገር ጌታቸው ብዕር። የሀገር ፍቅር ማኅበርን ከአመሠራረቱ ጀምሮ የነበረውን ታሪክ ለመሰነድ የሄደበት ርቀት እሚደንቅ ነው። የቀብር ቀኑን በገዛ ሙዚቃው ከታጀበለት አሰፋ አባተ፥ እስከ ሙዚቃ የዋጠው ፖለቲካ (አሊ ቢራ)፥ ከሜሪ አርምዴ ታሪክ አንስቶ፥ የአበበ ፍቅር እስካናወዛት አስናቀች ወርቁ ድረስ ያሉ  የሕይወት ታሪክ መድብል ብዙ የተለፋበት ሥራ መሆኑን ያሳብቃል። የተለያዩ የሙዚቃ ባንድ ታሪኮችን ማካተቱ ሲገርመን፥ ዓይነስውራን ሙዚቀኞችን ማውሳቱ ደግሞ እጅግ ያስደንቃል። የ700 ሙዚቃዎች "ካታሎግ" ደግሞ ሌላ ታሪክ ነው። ደራሲውን እጅ ነስተናል! በኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበር፥ በሀገር ፍቅር ማኅበር፥ የሙዚቃ ባንዶች ማኅበር ... ተጋግዘው መሥራት የነበረባቸውን የቤት ሥራ በአንድ ሰው ትከሻ ብቻ መሞከሩ አጃኢብ እንድንል አሰኝቶናል። #ጠመንጃና_ሙዚቃን ጋብዘናል #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 12 #የዶ/ር ኃይሉ አርዓያ "ኢትዮጵያና 5ቱ ሕልመኞች" የተሰኘው መጽሐፍ የፖለቲካ ሀዲዳችን ዝንፈቱን ከአምስቱ ሕልመኛ ትውልድ ጋር አቆራኝተው አስቀምጠዋል። #የጎህ_ሕልመኞች
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 12 #የዶ/ር ኃይሉ አርዓያ "ኢትዮጵያና 5ቱ ሕልመኞች" የተሰኘው መጽሐፍ የፖለቲካ ሀዲዳችን ዝንፈቱን ከአምስቱ ሕልመኛ ትውልድ ጋር አቆራኝተው አስቀምጠዋል። #የጎህ_ሕልመኞች - በአፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት በውጭ ሐገራት የተማሩ ባለራዕዮች #የታህሳስ_ሕልመኞች - የእነ መንግሥቱ እና ግርማሜ ንዋይ ሕልም #የደርግ_ሕልመኞች - ደርግ #የአስኳላ ሕልመኞች - የተማሪዎች ሕልም .... ኢሕአፓ፥ መኢሶን፥ ወዝሊግ ... #የበረሃ ሕልመኞች ... የሕወሓት ... #መፅሐፉ ላይ የእያንዳንዱ የዘመኑና የትውልዱ ታሪክ የተካተተ ሲሆን፥ የሕልማቸው መንስዔም ተወስቷል። የሕልማቸው ጠንካራና ደካማ ጎንም ተከትቧል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አስራ አንድ ክርስቲ ብራውን ይሰኛል። አይሪሻዊ የዊልቸር ጥገኛ ነው። ለ49 አመታት ሲኖር፥ እጆቹ ከእንቅስቃሴ ውጭ ነበሩ። ከግራ እግሩ በተቀረ መላ ሰውነቱን መቆጣጠር አይችልም
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አስራ አንድ ክርስቲ ብራውን ይሰኛል። አይሪሻዊ የዊልቸር ጥገኛ ነው። ለ49 አመታት ሲኖር፥ እጆቹ ከእንቅስቃሴ ውጭ ነበሩ። ከግራ እግሩ በተቀረ መላ ሰውነቱን መቆጣጠር አይችልም። በግራ እግሩ በከተበው ድርሰቱ ከ40 በላይ ቋንቋዎች ተተርጉመው የተነበበለት ድንቅ ጸሐፊ ነው። ይሄ ተዓምረኛ ግለሰብ በዚሁ ግራ እግር በቀለም የሚራቀቅ ሰዓሊም ጭምር ነው። አይገርምም? አንዳንድ ሰው አለ- ልቦለድ መሰል ተረክ አንግቦ እሚወለድ! የሕይወት ዘመን ሌጋሲው የስንፍናችንን ጥግ እንደ መስታወት አንጸባርቆ፥ በኩነኔ በትር ሸንቆጥ የሚያደርግ! እስቲ የዚህን ሰው "My Left Foot" የተሰኘውን የግለታሪክ መጽሐፍ ተጋበዙልኝ!

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አስር "በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራሮች ቆይታዬ" በጉዞ ማስታወሻነት ምጣድ ላይ የተጋገረ የታሪክ እንጀራ ነው። ባለብዙ ዓይናማ። የመፅሐፉ ደራሲ ፈረንሳዊው አርኖ ዳባዲ ከ180 ዓመታ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አስር "በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራሮች ቆይታዬ" በጉዞ ማስታወሻነት ምጣድ ላይ የተጋገረ የታሪክ እንጀራ ነው። ባለብዙ ዓይናማ። የመፅሐፉ ደራሲ ፈረንሳዊው አርኖ ዳባዲ ከ180 ዓመታት በፊት ወደ ሀገራችን የመጣ ሲሆን "የያኔይቱን ኢትዮጵያ" ቅልብጭ አድርጎ ጽፏታል ማለት ይቻላል። ዘመነ-መሳፍንትን ከራስ ፀጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ ድረስ ያሳየናል። ከምጽዋ አንስቶ፥ ትግራይን አሳብሮ፥ ጎንደርን ሰንጥቆ፥ ጎጃምን አካልሎ፥ የኦሮሚያ አውራጃዎችን ባካተተው የሕይወት ገጠመኙ የተሰደሩ ትርክቶቹ አጀብ የሚያሰኙ ናቸው። ፈረንሳዊው ዳባዲ የሀገራችንን ታሪክ ከመዘገቡም በላይ የዘርዓያዕቆብ እና የወልደ-ሕይወትን ፍልስፍና ያዘሉ ብራናዎች እንዲሰነብቱ ትልቁን ሚና የተጫወተ ግለሰብ ነው። ይሄን መጽሐፍ ከፈረንሳይኛ ቋንቋ ወደ አማርኛ ለተረጎመችው ገነት አየለ እጅ ነስተናል!

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ዘጠኝ አደፍርስ የርእይ መነጠቅ የረበበት ልቦለድ ነው። በሚት ውስጥ እንዳለ ተጋዳላይ። በአደፍርስ መጽሐፍ ውስጥ ሁለት ጸጉር ለማውጣት ያለ ሰዓሊ ገጸሰብ አለ። ሰዓሊው ዘንድ ለመሳል የሚመጡ ሰዎች ከፊቱ ይደቀናሉ። እሱም በብሩሹ ቀለም ይዘግንና ሸራው ላይ እፍ ይልበታል። ስእልም ሁን ይለዋል። ይሆንለታል። ይስላቸዋል። ስእላቸው አልቆ መልካቸውን ሊመለከቱ ሲመጡ ፈጽሞ እነሱን ከማይመስል ሶዬ ጋር ይፋጠጣሉ። "የእኔን መልክ አይመስልም" ብለው ይበሽቃሉ። የሰዓሊው ምላሽ ግን "የምስለው አንተን ሳስብ የሚመጣልኝ ማንነትህን እንጂ ውጫዊ ገጽታህን አይደለም። ፊትህን ሸራዬ ላይ ከደገምኩህማ ምኑን ሳልኩት?" የሚል ምላሽ ይሆናል። የአደፍርስ መጽሐፍ ፍካሬም እንዲያ ይመስለኛል። ከአደፍርስ፥ ከፂዮኔ፥ ከሮማን፥ ከጎርፉ ፊት የተሻገረ ምስል ስንከስት ይመስለኛል፥ ይበልጡን ስሜት እሚሰጠው። ፈረንሳዊው ፈላስፋ ፒየር ማሽሬ "ስነጽሑፍ ለተጻፈበት ዘመን ጥበባዊ አንደበት ነው" ይላል። አደፍርስም የዘመኑን ምስል እሚከስት፥ በጋሽ ዳኛቸው ብሩሽ የተቀነበበ፥ የዘመን መስታየት ነው። ጺዎኔ እና ሮማን የኢትዮጵያ ውክል ናቸው። የሁለቱን ስብእና በአንድ ሰርጥ ውስጥ ማጎር paradox ነው። ለነገሩ ጃንሆይ ራሱ ኢትዮጵያዊነትን በኩራትና በትህትና ባለ ሳንዱች ዘይበውትም የለ?! ጺዎኔ እና ሮማንም እሚጣረስ ስብእና አላቸው። ግን በአንድነት የተሰፉ የሐገራችን ውክል ናቸው። እንቀጥል! ጎርፉ ወጠምሻ የሆነ ፍቅር አንገዳግዶታል። አብሮ አደጉ ከሆነችው ጺዎኔ ጋር የለየለት ፍቅር ይዞታል። ጺዎኔን የግሉ ለማድረግ ግን አዳጋች ሆነበት። አደፍርስ የተባለ የተማረ ከተሜ ተጋረጠበት። ነገርየውን በጎርፉ ሳያጠራው አጅሬው ይበልጥ አደፈረሰበት። ጎርፉ ምን ያህል ግብስብስ ነገርን እየቃረመ እንደሚነጉድ "የእኛ ድንቁርና የተሻለ ነው!" ለሚለው ፈሊጥ ያለው ተገዥነት ሁነኛ ማሳያ ነው። በአንጻሩ አደፍርስ ለአከባቢው መጤ ቢሆንም ከዘልማዳዊው መንገድ እጅግ ያፈነገጠ ነው። ከሮማን ጋር መሆን ውስጡ ነው(በቃና አገላለጽ)። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን ከጸጥታ ኃይሎች ጋር ያለውን አተካሮ ለማርገብ ሲዳክር ቁስልን አትርፏል። በጎርፉ እጅ ሕይወቱን አጥቷል። ጎርፉ የሞትን ደራሽ ውሃ አዝሎ አደፍርስን ጠርጎት ወሰደው። በጎርፍነት ድፍርሱ እሚጠራ መስሎት። ግን ጎርፉ ጺዎኔን ማግባት አልቻለም። ምክንያቱም ጺዎኔ መነኩሴነትን መርጣለችና። ሮማንም የሴተኛ አዳሪነት ሕይወት ውስጥ ትዘፈቃለች። እዚህ ጋር ... የድምዳሜውን ፍካሬ በራሴ ከምንዘባዘብ ረዳት ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ገብሬ ከጻፉት "Period, History, and the Literary Art: Historicizing Amharic Novels" ከተሰኘ "አርቲክል" ላይ ለመዋስ እገደዳለሁ። ጽዮኔ እና ሮማን በኢትዮጵያ ይመሰላሉ ካልን፥  ኢትዮጵያ በተመሳሳይ ሰዓት ገዳም እና ቡና ቤት(brothel) ትሆናለች እሚል ትንቢት ይሆንም የለ? ይህም የሐገራችን የወደፊት እጣፈንታ ፈለካዊ ምጸት ነው። አደፍርስ የ60ዎቹ ትውልድ ውክል ሲሆን፥ የአደፍርስ ሞት ደግሞ የዚያ ዘመን ትውልድ ከማህበረሰቡ የመነጠላቸው ተምሳሌት ነው። #ይሄን ድንቅ መጽሐፍ ተጋበዙልኝ #ቢኒያም አቡራ

#ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ስምንት "መጽሐፈ ትዝታ - ዘአለቃ ለማ"ን ተጋበዙልኝ። አብዬ መንግሥቱ ለማ የአባታቸውን የአለቃ ለማ ኃይሉን ትዝታዎች በፊደላት የሰነዱበት ግለ-ታሪክ ነው። የአለቃ ለማ የንግ
#ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ስምንት "መጽሐፈ ትዝታ - ዘአለቃ ለማ"ን ተጋበዙልኝ። አብዬ መንግሥቱ ለማ የአባታቸውን የአለቃ ለማ ኃይሉን  ትዝታዎች በፊደላት የሰነዱበት ግለ-ታሪክ ነው። የአለቃ ለማ የንግግር ዘዬ በመጽሐፉ ውስጥ ጎላ ብሎ ይስተዋላል። ከአለቃ የግል ተረኮች በተጨማሪነት የአብነት ትምሕርት ቤት መልኮች፣ የታላላቅ ምሑራኖቻችን መንገድ፣ የንጉሠነገሥት አመጣጥ እንዲሁም የታሪክና የባሕል  ሰበዞች የታጨቁበት መጽሐፍ ነው። እንደ ታሪክ ሰነድነትም የሚወሰድ ይህ ድንቅ ጥራዝ በተገኘበት ታድኖ ቢነበብ አጥጋቢ ስንቅ ነው ባይ ነኝ። መጽሐፉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ውጤት ሲሆን ዩኒቨርስቲው በዚሁ "ደማሙ ብዕረኛ"ንም በድጋሚ ሕትመት ጀባ ቢለን ሸጋ ነው። #ይነበብ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ሰባት የገዛ አጎቱ ተዋነይ የሚል ታሪካዊ ስም ስላሸከመው ነው መሰል በነጭ ገደል መንደር የብላቴናነቱ ዘመኑ እንዳይሰክን ይወዘውዘዋል። የሕይወት ጥሪውን ለማግኘት በአብነት ትምሕ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ሰባት የገዛ አጎቱ ተዋነይ የሚል ታሪካዊ ስም ስላሸከመው ነው መሰል በነጭ ገደል መንደር የብላቴናነቱ ዘመኑ እንዳይሰክን ይወዘውዘዋል። የሕይወት ጥሪውን ለማግኘት በአብነት ትምሕርት ቤት ሊማስን እናትና አባቱ በተኙበት ጥሏቸው ይነጉዳል። ደብረ ገነት ኤልያስ ወጥኖ ከደብረ ወርቅ ማርያም አሃዱ ብሎ፣ ደበሎ ለብሶ፣ ከውሻ ጋር ተናጥቆ፣ ከተስቦ ጋር ግብግብ ገጥሞ፣ በቤተሰብ ናፍቆት ናውዞ፣ ከወበረተኞቹ ጋር ቁሩንም ወበቁንም ተቋድሶ፣ ወደ ሕልሙ ውቂያኖስ ሊገባ እንደ ዥረት ይተምማል። "ኀሠሣ" የተሰኘው የሕይወት ተፈራ መጽሐፍ ለነባር ሀገር በቀል የትምሕርት ሥርዓታችን ትዕምርት የሆነውን የአብነት ትምሕርት ቤት ሕይወትና አጠቃላይ ገጽታ  ተዋነይ በተሰኘ ገጸሰብ ተረክ ውስጥ የቀነበበ እጹብ ድንቅ ድርሰት ነው። የሕይወት ተፈራን "Mine to Win" በአውዳዊው ትርጉም ወደ አማርኛ የመለሰችው ሕይወት ታደሰ ስትሆን፤ የአማርኛው ትርጉም (ቋንቋው) ... ውብዬ (ቀሽትዬ 👌👌👌) መሆኑን እንመሰክራለን። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ስድስት በአስራ አምስት ዓመታችን የእናታችን ምድጃ አጠገብ ሆነን ይሆን? "Night" የተሰኘው ድንቅ መጽሐፍ አይሁዳዊው ኤሊ ዊዝል በአስራ አምስት ዓመቱ ወገኖቹ የሚቃጠሉበት የ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ስድስት በአስራ አምስት ዓመታችን የእናታችን ምድጃ አጠገብ ሆነን ይሆን? "Night" የተሰኘው ድንቅ መጽሐፍ አይሁዳዊው ኤሊ ዊዝል በአስራ አምስት ዓመቱ ወገኖቹ የሚቃጠሉበት የኦሽዊትዝ የሞት ምድጃዎች አጠገብ እንደነበር ያስነብበናል። አይሁዳውያን ከናዚ ማጎሪያ ወደ ሌላኛው ማጎሩያ እንዴት ባለ አሰቃቂ ኹናቴ እንደሚያጓጉዟቸው ያወሳል። ወገኖቹ ቀቢጸ-ተስፋ ሳይጎበኛቸው ለሟቾች ካዲሽ (ፍታት) እንደሚያደርጉም ጥቁምታ ይሰጠናል። የማጎሪያ ካምፑን ጠባቂዎችን ግብር በወጉ ያትታል።  በናዚ ማጎሪያ ካምፑ ውስጥ ያሉ ተረኮችንም ሰንዷል። አንድ ወጣት ወደ ራባዩ (የይሁዲ መምህር) ዘንድ ቀረብ ብሎ "ራባይ ... ኦሽዊትዝን ካዩ ኋላ አሁንም በእግዚአብሔር ያምናሉ?" ብሎ ጠየቃቸው። "እንዴት በእግዚአብሔር አላምን? ዓለም ያለእግዚአብሔር ምን እንደምትመስል ማሳያው እኮ ኦሽዊትዝ ነው!" ብለው መለሱለት። ኤሊ ዊዝል ተዓምር በሚባል ደረጃ ከናዚ የማጎርያ ካምፕ ተርፎ፣ 57 መጻሕፍትን ጽፎ፣ የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸልሞ ከሰባት ዓመት በፊት በ87 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። የዛሬው የመጽሐፍ ግብዣዬ Night ይሰኛል። ጳውሎስ ፍቃዱ "ሌሊት" ብሎ ወደ አማርኛ በጥሩ ሁኔታ ተርጉሞታል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አምስት በ19 50ዎቹ በልጅነቱ በእናቱ ጉያ ተሸሽጎ ደንቢያ ውስጥ ያደገን ኢትዮጵያዊ ብላቴና አስቡ። ይህ ብላቴና አድጎ በወጣትነት ዘመኑ በ1970ዎቹ መጀመሪያ አሜሪካን ሄደ እ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አምስት በ19 50ዎቹ በልጅነቱ በእናቱ ጉያ ተሸሽጎ ደንቢያ ውስጥ ያደገን ኢትዮጵያዊ ብላቴና አስቡ። ይህ ብላቴና አድጎ በወጣትነት ዘመኑ በ1970ዎቹ መጀመሪያ አሜሪካን ሄደ እንበል። ማደጎ በሚመስል ኹናቴ በዕድሜ የገፉ አሜሪካዊ እናትና አባት አገኘ። እኚህ አሜሪካዊ አዛውንቶች አደንዛዥ ዕጽ የምትጠቀም ሴት ልጅ አለቻቸው። በኢትዮጵያዊ ወላጆቹ እና በአሜሪካዊ ቤተሰቦቹ መካከል ያለውን የባሕል፣ የአስተሳሰብ ልዩነት እንዴት ሊያስታርቅ የሚችል ይመስላችኋል? በዚያ ላይ ይህ ሰው አሲምባ ላይ የጋንታ መሪ የነበረ የ"ኢህአፓ" አባል ነው። አሜሪካዊ ቤተሰቦቹን ከማግኘቱ በፊት ሱዳን ላይ በስደተኝነት ናውዟል። ብዙ ሰቆቃ የተመለከተው ይህ ግለሰብ አሜሪካን ውስጥ የሚኖረው የፍቅር ሕይወቱ ምን ሊመስል የሚችል ይመስላችኋል? ከደንቢያ ጎንደር እስከ ዋሽንግተን ዲሲ ከላይ የቀረቡ ተረኮችን እጅግ ውብ በሆነ ሥነጽሑፍ ያነበረ ታሪካዊ ልቦለድ ነው። ደራሲው አስማማው ኃይሉ አሁን በሕይወት ባይኖርም ከዚህ መጽሐፍ በተጨማሪ ኢሕአሠ (ቅጽ 1 እና 2)፣ ብዥታ(የግጥም መደብል) የተሰኙ ሕያው መጻሕፍትን ጀባ ያለን ብዕረኛ ነው። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አራት ቤተክርስቲያን ውስጥ አገልጋይ ብትሆኑ፣ የገዛ ልጃችሁ በሕመም ጻማ ቢሰቃይ፣ ይባስ ብሎም ልጃችሁ ራሱን ቢያጠፋ በምን ዓይነት ድብታ ውስጥ የምትወድቁ ይመስላችኋል? ይህ መ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ አራት ቤተክርስቲያን ውስጥ አገልጋይ ብትሆኑ፣ የገዛ ልጃችሁ በሕመም ጻማ ቢሰቃይ፣ ይባስ ብሎም ልጃችሁ ራሱን ቢያጠፋ በምን ዓይነት ድብታ ውስጥ የምትወድቁ ይመስላችኋል? ይህ መጽሐፍ የሚወደው ልጁ ራሱን በራሱ በማጥፋቱ በታላቅ ድብታ ውስጥ ስለወደቀ ሮናልድ ደን የተሰኘ የቤተክርስቲያን አገልጋይ የሕይወት ተሞክሮ የሚያትት መጽሐፍ ነው። በብዙ ዓይነት የሕይወት ፈተና ውስጥ ላሉ ሰዎች የሚያላቅስ መጽሐፍ ነው። የሕይወትን ጥያቄ ዐብሮ በማጣየቅ መልሱን ዐብሮ የሚያፋልግ ቆንጆ መጽሐፍ ነው። #ይህን When Heaven Is Silent የተሰኘውን የሮናልድ ደንን መጽሐፍ ጳውሎስ ፍቃዱ ወደ አማርኛ "ሰማይ ዝም ሲል" በማለት በጥሩ ኹኔታ ተርጉሞታል። #ይነበብ

ጸሐፊ ተውኔት ፤ጋዜጠኛና ገጣሚ ሰዓዳ መሐመድን ‹‹እሾሃማ ወርቅ›› በተሰኘ የረዥም ልቦለድ መጽሐፏ ብዙዎች ያውቋታል። በእፍታ መጻሕፍት ተከታታይ እትሞች ላይ የእሷ አጫጭር ልቦለዶች እና ግጥሞች ይገኛሉ። ፖፕሌሽን ሚዲያ ሴንተር ባሳተማቸው የአጭር ልብ ወለድ ስብስብ መጻሕፍት ወንዞች አስኪሞሉ እና ያልተነበቡ ልቦች”ውስጥም ድርሰቶቿ ታትመዋል፡፡ ‹‹ዕለታዊ አዲስ››፣ ‹‹ሩሕ››፣ ‹‹አልነጃሺ››፣ ‹‹አልዋህዳ››... በተሰኙ ጋዜጦች ላይ ሪፖርተር ሆና ሠርታለች። በአንድ ወቅት ደግሞ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ እንዲሁም በእፎይታ መጽሔት እና ጋዜጣ ላይ በርካታ ጽሑፎችን አስነብባናለች፡፡ በ1990ዎቹ መጀመሪያ፣ ለኢትዮጵያ ሬዲዮ የቅዳሜ መዝናኛና ለወጣቶች ፕሮግራም አጫጭር ድራማዎችን በመጻፍ የጀመረችው ይህች ብርቱ ሴት በርካታ የሬዲዮ ድራማዎችን ጽፋለች። በኢትዮጵያ ሬዲዮ በብሔራዊው ጣቢያ፣ ‹‹ያበቃ ሕልም››፤ ‹‹ሦስቱ መስኮቶች››፤ ‹‹ጥልፍልፎሽ››፤ ‹‹ያልተደፈነ ጉድጓድ››፤ ‹‹መክሊት›› እና ‹‹የባቡ እግሮች›› የተሰኙ ተከታታይ ድራማዎችን ስትጽፍ፣ በሬዲዮ ፋና ደግሞ ‹‹የወንዝ ድንጋይ›› የተሰኘ ባለሰባት ክፍል ድራማ ጽፋ አየር ላይ ውሎላታል፡፡ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በሬዲዮ ድራማ ጸሐፊነት በቆየችበት ፖፑሌሽን ሚዲያ ሴንተር በዛ ያሉ ድራማዎችን ጽፋ ነበር፡፡ ከጻፈቻቸው ተከታታይ ድራማዎች መካከል ባለ 226 ክፍሉ ‹‹ስብራት›› በዋናነት ይጠቀሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም፣ ‹‹የረገፉ ፈትሎች›› (ባለ 130 ክፍል)፤ ‹‹የብርሃን አፅናፋት›› (ባለ 190 ክፍል) ‹‹ምዕራፍ››፤ (ባለ 180 ክፍል - ይህ የሬዲዮ ድራማ በኢንተርናሽናል ግሎባል አዋርድ አሸናፊ የሆነ ነው፡፡) የተሰኙ ድራማዎችም ሕዝብ ዘንድ ደርሰውላታል፡፡ ሰዓዳ መሐመድ ከሌሎች ጻሕፍት ጋር በመሆን ‹‹የቤት ሥራ›› እና ‹‹ዘመን›› የተሰኙ የቴሌቪዥን ድራማዎችን ጽፋ እየታዩላት ነበር፡፡ ወደ ሬዲዮ ሥራዎቿ ስንመለስ፣ ‹‹በየኛ›› የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ የሚቀርበው 120 ክፍል ድራማም የተጻፈው በእርሷው ነበር፡፡ ከጌታቸው ዓለሙ ገጽ የተወሰደ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ሦስት እሾሃማ ወርቅ ከሃያ አምስት ዓመት በፊት የታተመ ረጅም ልቦለድ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ኑሮን ለማሸነፍ ብለው በሀረብ ሀገር እንዴት ባለ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደሚያሳልፉ የሚያት
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ሦስት እሾሃማ ወርቅ ከሃያ አምስት ዓመት በፊት የታተመ ረጅም ልቦለድ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ኑሮን ለማሸነፍ ብለው በሀረብ ሀገር እንዴት ባለ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደሚያሳልፉ የሚያትት መጽሐፍ ነው። ደራሲዋ (ሰዓዳ መሃመድ) ስሙር የሆነ ቋንቋ በመጠቀሟ፣ በተደራሲያን ዘንድ ኹነቶችን በዕዝነ ልቦና የመከሰት አቅሟ ላቅ ያለ ነው። የገጸባሕርይ አሳሳል፣ የታሪክ ፍሰት፣ ጡዘት፣ ልቀት ... ሸጋ በሆነ ኹናቴ አንብረዋለች። መጽሐፉ እጅግ መሳጭ ከመሆኑ የተነሳ ካነሱት ኋላ ለማስቀመጥ ይቸግራል። #ይነበብ #ስለደራሲዋ (ሰዓዳ መሃመድ) ታላላቅ ሥራዎች ማወቅ ለምትሹ ከጌታቸው ዓለሙ ገጽ የወሰድኳትን ከታች አስቀምጥላችኋለሁ።

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ሁለት "ኦደሲ" የተሰኘውን የኃይል ከበደን መጽሐፍ ተጋበዙልኝ። "እጅጉን ግላዊ የሆነ ነገር እጅጉን ዓለም-አቀፋዊ ነው" ይባልም የለ?! ጋሽ ኃይል በሕመም እና በሰቆቃ ውስጥ ሁ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ ሁለት "ኦደሲ" የተሰኘውን የኃይል ከበደን መጽሐፍ ተጋበዙልኝ። "እጅጉን ግላዊ የሆነ ነገር እጅጉን ዓለም-አቀፋዊ ነው" ይባልም የለ?! ጋሽ ኃይል በሕመም እና በሰቆቃ ውስጥ ሁኖ ያሳለፈውን እጅጉን ግላዊ የሆኑ የሕይወቱን ውጣውረድ በመጽሐፉ አንብሮታል። በዲፕሬሽን ሸለቆ ውስጥ ለምንናውዝ ሰዎች ሁነኛ አስታማሚ ጥራዝ ነው። “እሳቱ ይነዳል፤ ጭሱ ወደ ሰማይ ይወጣና ከደመና ጋር ይቀላቀላል፤ የቱ ጭስ፣ የቱ ደመና እንደሆነ መለየት ያስቸግራል!” #ይነበብ

ተስፋዬን ፍለጋ ወጥቼ ማርቆስ ጋር አገኘሁት። (ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 1) በ1960ዎቹ ተስፋዬ ገብሬ የሚባል ኢትዮጵያዊ ሙዚቀኛ በአውሮጳ የጃዝ ሙዚቃ ነግሦ ነበር ቢባል የኔ ዘመን ትውልድ ያምን ይሆ
ተስፋዬን ፍለጋ ወጥቼ ማርቆስ ጋር አገኘሁት። (ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 1) በ1960ዎቹ ተስፋዬ ገብሬ የሚባል ኢትዮጵያዊ ሙዚቀኛ በአውሮጳ የጃዝ ሙዚቃ ነግሦ ነበር ቢባል የኔ ዘመን ትውልድ ያምን ይሆን? "ተስፋዬን ፍለጋ" የተሰኘው የማርቆስ መጽሐፍ ስለዚህ ታላቅ ሙዚቀኛ የሕይወት ውጣ ውረድ የሚተርክ ነው። የሺ ከረሜሎን አስተዝቶን፣ በአራት ኪሎ ሰርጥ አስተምሞን ሃገር ፍቅር ይከተናል። ኢዩኤል ዮሐንስን አስቃኝቶን ሳንጠግብ በጂቡቲ መርከብ ያሳፍረናል። ከናፖሊ እስከ ቬሮና ከተስፋዬ ገብሬ ጋር ያዟዙረናል። አሜሪካ ወስዶ ይመልሰናል። ከቴስ ጋር በስደት አናውዞን፣ በሀገር ፍቅር አቃጥሎን፣ በጃዝ ሙዚቃ አስመድርኮን፣ በታፕ ዳንስ ይንጠናል። አጃኢብ ነው! ሰው እንዴት ሥራውን ትቶ፣ ከአሜሪካ ጣልያን ይሄዳል? ያን ሁሉ ፍራንክ እንዴት ላልተጨበጠ ነገር ሆጭ አድርጎ ለማውጣት ይሞኛል? በዕድሜ የገፋች አንዲት ነጭ፣ ከ40 ዓመት በኋላ ስለነበረው ተረክ ልትነግረኝ ትችላለች ተብሎ ያ ሁሉ ዋጋ እንዴት ይከፈላል? ደራሲው ግን ይሄን መጽሐፍ ለመጻፍ ሳይሆን የቴስን ማንነት ለማወቅ ይሄን ሁሉ ዋጋ ከፍሏል። ለኔ ተዓምር ነው። እውነትም ኢንካርኔሽን! መጽሐፉን ካነበብኩ በኋላ ጆሮዬ ከቴስ ሙዚቃዎች ላይ አልነሳ ብሏል። "በአብዮት"ን ስሰማ ፈገግ፣ በ"ስፖርት" ነቃ ነቃ እያልኩ ነው። "ፒጌራ"ን ስሰማ ዜማው እንባዬን እያመጣሁ ተቸገርኩ። "ላቬራቶሪ"ን አልሰማሁትም። "ሮማና"ን ስሰማ የቴስን ብቃት እና ማንነት ከእንቅብ በታች ሆኖ እስከ ማርቆስ መጽሐፍ ድረስ መክረሙ ያብከነክነኛል። "መጋቢት 28" ይነሽጠኛል። Dear Ethiopia በቃ Dear Ethiopia ነው። ዛሬም ስሰማው የልጅነት ዘመኔ፣ ሀገሬ፣ ቤተሰቤ ትዝ ትዝ ይሉኛል። "ሰላም ለኢትዮጵያ ውቢቷ ሀገሬ" ያንሰፈስፈኝ ጀምሯል። ይነበብ! ©ቢኒያም አቡራ