en
Feedback
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ

Open in Telegram

👉 ሰሞነኛ ትኩስ መፅሐፍት ከነድስቱ እንገጮታለን። 👉 ዘርፈ ብዙ የሆነውን የኪነት ወሬ እስከነቃጭሉ ዱብ እናረጋለን። 👉 ነባርና አዳዲስ መፅሐፍትን መጠነኛ ዳሰሳ አድርገን እንጠቁሞታለን። ✴ ወሬ ጥሩ ስለሆነ በዚህ ቦይ ላኩልኝማ @a3b2ysm

Show more
1 955
Subscribers
-124 hours
-57 days
-2730 days
Posts Archive
ዓለማየሁ ገላጋይ፣ በወሪሳ አውድማ ላይ በምጸታዊ መንሽ ማኅበራዊ አዝዕርትን ንፋስ ላይ አበጥሯል። በታለ ማሰሮ ጦማራዊ ልቦለድን ንጧል። በኢህአዴግን እከስሳለሁ ሙቀጫ የጋዜጠኝነትን ዘነዘና ይዞ ምኩራ
ዓለማየሁ ገላጋይ፣ በወሪሳ አውድማ ላይ በምጸታዊ መንሽ ማኅበራዊ አዝዕርትን ንፋስ ላይ አበጥሯል። በታለ ማሰሮ ጦማራዊ ልቦለድን ንጧል። በኢህአዴግን እከስሳለሁ ሙቀጫ የጋዜጠኝነትን ዘነዘና ይዞ ምኩራብ ወጥቷል። በቅበላ ብራና የድህረ ዘመናዊ ልቦለድን ከትቧል። በመልክአ ስብሃት ሰፌድ ላይ ሰበዝም፣ አለላም፣ አክርማም ሆነ ስንደዶ ለመሆን የሚመች፥ የደቦ ከያኔ መሆኑን ተመልክተናል። በየፍልስፍና አጽናፍ ተርጓሚነቱን፣ በስብሃት ገ/እግዚአብሔር ሕይወትና ክሕሎት - ኀያሲነቱን አስመስክሯል። በየተጠላው እንዳልተጠላው አይነኬ ዕሳቤዎችን በመጠይቅ ወንፊት አንገዋሏል። በአጥቢያ የንስር ዓይናማነቱን፣ በመለያየት ሞት ነው ሊቀ-መጣጥፍነቱን፣ በፍቅር ስም ላይ ደግሞ experimental novelist-ነቱን ተመልክተናል። በኩርቢት መም ላይ የስሜት ጂምናስቲክ አሠርቶናል። በ18ኛው ደሞ 24 እንዳልሞላው ሊያስታውቀን ተከስቷል። እኔ በበኩሌ በጋሽ ወንድዬ ዓሊ ብሂል "የሥነ-ጽሑፍ ወዛደር" ብዬዋለሁ። what a ትጋት?!?! ቢኒያም አቡራ

#ካነበብኳቸው የ"ያ-ትወልድ" መጻሕፍት የኔ ምርጦች፦ ❤ማማ በሰማይ - ሕይወት ተፈራ 💙በአጭር የተቀጨ ረዥም ጉዞ - አንዳርጋቸው አሰግድ 💚እኛና አብዮቱ - ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ 💛የሻምላ
#ካነበብኳቸው የ"ያ-ትወልድ" መጻሕፍት የኔ ምርጦች፦ ❤ማማ በሰማይ - ሕይወት ተፈራ 💙በአጭር የተቀጨ ረዥም ጉዞ - አንዳርጋቸው አሰግድ 💚እኛና አብዮቱ - ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ 💛የሻምላው ትውልድ - ፋሲካ ሲደልል 🧡የጭድ እሳት - ፕሮፌሰር ጴጥሮስ ቶጃ 💜የሱፍ አበባ - ሀብታሙ አለባቸው ❤ያልታሰበው - ኮ/ል ብርሃኑ ባየህ 💚በሀገር ፍቅር ጉዞ - አብዩ ብርሌ 💜ዳኛው ማነው - ታደለች ኃ/ሚካኤል #የእናንተስ?

#የደራሲዎች ማስተርፒስ (በኔ የንባብ ደረጃና አቅም) ❤ ፍቅረማርቆስ ደስታ - ከቡስካ በስተጀርባ ❤ ሀብታሙ አለባቸው - ታላቁ ተቃርኖ ❤ ወንድዬ ዓሊ - ወፌ ቆመች ❤ አዳም ረታ - የስንብት ቀለማ
#የደራሲዎች ማስተርፒስ (በኔ የንባብ ደረጃና አቅም) ❤ ፍቅረማርቆስ ደስታ - ከቡስካ በስተጀርባ ❤ ሀብታሙ አለባቸው - ታላቁ ተቃርኖ ❤ ወንድዬ ዓሊ - ወፌ ቆመች ❤ አዳም ረታ - የስንብት ቀለማት ❤ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር - ሌቱም አይነጋልኝ ❤ በዓሉ ግርማ - ኦሮማይ ❤ ሀዲስ ዓለማየሁ - ፍቅር እስከ መቃብር ❤ ዳኛቸው ወርቁ - አደፍርስ ❤ አቤ ጉበኛ - አልወለድም ❤ እንዳለጌታ ከበደ (ዶ/ር) - በዓሉ ግርማ ሕይወቱና ሥራዎቹ ❤ ጸጋዬ ገብረመድህን (ሎሬት) - እሳት ወይ አበባ ❤ ዘነበ ወላ - ማስታወሻ / ልጅነት ❤ በዕውቀቱ ስዩም - ከአሜን ባሻገር ❤ ብርሃኑ ዘርይሁን - የታንጉት ሚስጥር ❤ ኃይለመለኮት መዋእል - ጉንጉን የእናንተስ????

ዛሬ ነው! ... 11:31 ይጀምራል። ወመዘክር እንገናኝ! ... መግቢያ በነጻ አድራሻ፦ ብሔራዊ አከባቢ ከሚገኘው ከድሮ የ etv ሕንጻ ጀርባ ወይም ከፌና ፊትለፊት (ወመዘክር-የኢትዮጵያ ቤተመጻሕፍት
ዛሬ ነው! ... 11:31 ይጀምራል። ወመዘክር እንገናኝ! ... መግቢያ በነጻ አድራሻ፦ ብሔራዊ አከባቢ ከሚገኘው ከድሮ የ etv ሕንጻ ጀርባ ወይም ከፌና ፊትለፊት (ወመዘክር-የኢትዮጵያ ቤተመጻሕፍትና ቤተመዛግብት)

የፊታችን አርብ 11:30 በወመዘክር አዳራሽ "የዓድዋ ስንኞች እና ንቡር ጠቃሽነታቸው" በተሰኘ ርዕስ የጂጂ፣ የቴዲ አፍሮ እና የዳኘ ዋለ አድዋን መሠረት ባደረጉ ሙዚቃዎች ላይ የውይይት ሐሳብ ይቀርባ
የፊታችን አርብ 11:30 በወመዘክር አዳራሽ "የዓድዋ ስንኞች እና ንቡር ጠቃሽነታቸው" በተሰኘ ርዕስ የጂጂ፣ የቴዲ አፍሮ እና የዳኘ ዋለ አድዋን መሠረት ባደረጉ ሙዚቃዎች ላይ የውይይት ሐሳብ ይቀርባል። የውይይት ጽሑፍ አቅራቢ - ቢኒያም አቡራ

ታላቅ ይቅርታ ========= የዛሬው የዐውደ ፋጎስ ፕሮግራማችን ተራዝሟል! ወመዘክር አዲሱን ሕንጻ ጨርሶ በትላንትናው ዕለት ማስመረቁ ይታወቃል ። ነገር ግን የሚመለከታቸው እንግዶች ዛሬም በወመዘክር
ታላቅ ይቅርታ ========= የዛሬው የዐውደ ፋጎስ  ፕሮግራማችን ተራዝሟል! ወመዘክር አዲሱን ሕንጻ ጨርሶ በትላንትናው ዕለት ማስመረቁ ይታወቃል ። ነገር ግን  የሚመለከታቸው እንግዶች ዛሬም በወመዘክር በመገኘት ስለሚመርቁና የምርቃቱ ሂደት በመቀጠሉ ከዘወትር ተባባሪዎቻችን የወመዘክር አመራሮች  አሁን  አሳውቀውናል ።  ውድ ጥሪ የተደረገላችሁ የዐውደ ፋጎስ የውይይት  ክበብ አባላትና ታዳሚዎች እንዲሁም ተጋባዥ የሚዲያ ተቋማት  ዛሬ ፕሮግራሙ እንደማይካሄድ ስናሳውቅ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው ።

እሁድ 8 ሰዓት በወመዘክር አዳራሽ "የዓድዋ ስንኞች እና ንቡር ጠቃሽነታቸው" በተሰኘ ርዕስ የጂጂ፣ የቴዲ አፍሮ እና የዳኘ ዋለ አድዋን መሠረት ባደረጉ ሙዚቃዎች ላይ የውይይት ሐሳብ ይቀርባል። የውይ
እሁድ 8 ሰዓት በወመዘክር አዳራሽ "የዓድዋ ስንኞች እና ንቡር ጠቃሽነታቸው" በተሰኘ ርዕስ የጂጂ፣ የቴዲ አፍሮ እና የዳኘ ዋለ አድዋን መሠረት ባደረጉ ሙዚቃዎች ላይ የውይይት ሐሳብ ይቀርባል። የውይይት ጽሑፍ አቅራቢ - ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 29 ጨዋታ ጦቢያ በየሩሳሌም የተሰኘው የተስፋ ስንታየሁ መጽሐፍ በተለምዶ ፈላሻ የምንላቸው የማኅበረሰባችን ክፍል ከጎንደር ተነስተው በገዳሪፍ አድርገው ሀገረ እሥራኤል የሚገቡበት
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 29 ጨዋታ ጦቢያ በየሩሳሌም የተሰኘው የተስፋ ስንታየሁ መጽሐፍ በተለምዶ ፈላሻ የምንላቸው የማኅበረሰባችን ክፍል ከጎንደር ተነስተው በገዳሪፍ አድርገው ሀገረ እሥራኤል የሚገቡበትን ጉዞ በታሪካዊ ልቦለድ የቀረበበት ድርሰት ነው። በዚህ ድንቅ መጽሐፍ ላይ አያ ተበጀ የሚባል ገጸባሕርይ አለ። ልክ አደፍርስ ላይ እንዳለችው ወይዘሮ አሰጋሽ በብሂል የተሞላ፣ ልክ ማዕበል ላይ እንዳለችው እንደ ወይዘሮ ዘርፈሸዋ ተንኳሽ አገላለጾችን የሚችል ቅመም የሆነ ገጸባሕርይ ነው። ከኢትዮጵያ ወጥቶ ገዳሪፍ ሲደርስ "ገዳሪፍ አለ ስም አውጭ፤ ባማረኛው፤ ቀጥታውን፤ ገደ-እርፍ (እንክልት የበዛበት) ቢሉት አይሻል ኑሯል?" ይላል። ልክ እሥራኤል ሲደርስና ሀገሩ ማርና ወተት የምታፈስ አለመሆኑን ሲያውቅ ደግሞ "ኢየሩሳሌም የቀረ ላሊበላ እኔ ያለሁ ሁመራ" ይላል። ይህ ድንቅ መጽሐፍ በቋንቋው ስሙርነት፣ በሐሳብ አይመጤነት፣ በገጸባሕርይ አሳሳል እና አሰፋፍ ረቀቅ ያለ ሥራ ቢሆንም እንዳለመታደል ሆኖ መጽሐፉ በሀገር ውስጥ አለመታተሙ እና አለመዳረሱ በኢትዮጵያ የሥነ ጽሑፍ አንባብያን ዘንድ እንዳይነግስ ትልቅ ተግዳሮት ሁኗል።  #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 28 የትውልድ አደራ የተሰኘውን የልዑል ራስ መንገሻ ሥዩምን መጽሐፍ ተጋበዙልኝማ! ልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም የዐፄ ዮሐንስ የልጅ ልጅ ልጅ ሲሆኑ በአሁኑ ሰዓት ዕድሜያቸው 97 ዓ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 28 የትውልድ አደራ የተሰኘውን የልዑል ራስ መንገሻ ሥዩምን መጽሐፍ ተጋበዙልኝማ! ልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም የዐፄ ዮሐንስ የልጅ ልጅ ልጅ ሲሆኑ በአሁኑ ሰዓት ዕድሜያቸው 97 ዓመት ደርሷል። መጽሐፋቸው በግለታሪክ ዘውግ የቀረበ ሲሆን በውስጡም የልጅነት ዘመናቸው መልክ፣ በፋሽስት ጣልያን ወረራ ወቅት ያሳለፉት የግዞት ዘመናቸው፣ የቀዳማዊ ወያኔ ኹናቴ፣ ከጅባትና ሜጫ አውራጃ ጀምሮ እስከ ሲዳሞ ጠቅላይ ግዛት አገረ ገዥነት ዘመናቸው የሠሯቸው ትላልቅ ሥራዎች፣ በሥራና መገናኛ ሚኒስቴር ቆይታቸው ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገኟቸው ድሎች፣ በትግራይ ጠቅላይ ግዛት አገረ ገዢ በነበሩባቸው ዘመናት የነበሩ የተረክ ጅረቶች ይፈስሱበታል። የልዑል ራስ መንገሻ ስም ከነጋሢ ዘር ይልቅ ከልማት ጋር ይጎዳኛል ቢባል እብለት አይሆንም። ከሠሯቸው ሥራዎች መካከል እጅግ በጣም በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል፦ በሐዋሳ ከተማ ምሥረታ እና ማስተር ፕላን፣ በአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ፣ በአፍሪካ ሕብረት ሕንጻ፣ በባሕር ዳር ከተማ ማስተር ፕላን፣ በሽሬ ከተማ እና በመቀሌ ከተማ ማስተር ፕላን፣ የሲዳማ ቡናን በማሻሻል፣ ቦይንግን በማስገባትና በሌሎች የአየር መንገድ ሥራዎች፣ በበጌምድር የገጠር መንገዶች፣ ከ75% በላይ በሚኾኑት በትግራይ ጥርጊያ መንገዶች፣ በአፋር ጂኦተርማል እና ተያያዥ ሥራዎች ስማቸው ከልማት ጋር ታትሟል። #የእኚህን ትልቅ አባት ግለታሪክ ለሕትመት ያበቃውን የኢትዮጵያ አካዳሚ ፕሬስን እናመሰግናለን 🙏 #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

"ሸክላ ሰውነታችን ከተሰበረ በኋላ፥ ሸክላ ሠሪው ክርስቶስ በውሃ ጠገነው!" ይላሉ ሊቃውንቱ፥ በጉባዔ ቃናቸው። ሰው ከአፈር የተፈጠረ ሰባራ ሸክላ መሆኑንና የተሰበረ ሸክላ በውሃ ተለንቁጦ እንደሚጠገን
"ሸክላ ሰውነታችን ከተሰበረ በኋላ፥ ሸክላ ሠሪው ክርስቶስ በውሃ ጠገነው!" ይላሉ ሊቃውንቱ፥ በጉባዔ ቃናቸው። ሰው ከአፈር የተፈጠረ ሰባራ ሸክላ መሆኑንና የተሰበረ ሸክላ በውሃ ተለንቁጦ እንደሚጠገን፥ ሰውም ከእግዚአብሔር ጋር የነበረውን ዝምድና በመለያየቱ፥ እንደገና በውሃ ተወለደ። እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ 🙏🙏🙏

#ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ #በአምባሳደር ዘውዴ ረታ የተሰናዳው "የኤርትራ ጉዳይ" በተሰኘው ዳጎስ ባለው ጥራዝ፥ ውስብስቡ የኤርትራ ጉዳይ ተፍተልትሎ ቀርቧል። በመረጃና በሰነድ የደለበው ይህ ድንቅ መጽሐ
#ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ #በአምባሳደር ዘውዴ ረታ የተሰናዳው "የኤርትራ ጉዳይ" በተሰኘው ዳጎስ ባለው ጥራዝ፥ ውስብስቡ የኤርትራ ጉዳይ ተፍተልትሎ ቀርቧል። በመረጃና በሰነድ የደለበው ይህ ድንቅ መጽሐፍ በማያታክት የቋንቋ አቀራረብ ለማሰናዳት ከሰባት አመት በላይ ጊዜ ወስዷል። ለታሪክ ተመራማሪዎች ሳይቀር በኤርትራ ጉዳይ ላይ አዳዲስ እንድምታን የጠቆመ መጽሐፍ ሲሆን በውስጡ የጸሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ምስል ግዘፍ ነስቶ ይታያል። ተደራሲው እንደ ልቦለድ ተመስጦ እንዲያነብ የሚያሰገድደው ይሄ ድንቅ መጽሐፍ የምዕራባውያንን ሴራ፣ የፓሪስ የሰላም ጉባዔ እና በኢትዮጵያ ላይ የተደረገ ሸፍጥ፣ በተመድ የኤርትራ ጉዳይ የታየበት ምስል፣ የመርማሪ ኮሚስዮን ሥራ እና ሴራ፣ የኮንፌዴሬሽን አመጣጥና መዘዝ ... በመጽሐፉ የተዳሰሱ አንኳር አንኳር ነጥቦች ናቸው። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጽሐፍ ግብዣ 26 የዶ/ር እጓለ ገ/ዮሐንስን፣ ዘመን አይሽሬውን "የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤን" ተጋበዙልኝማ! "ከግሪክ ፈላስፎች በኋላ ... የሌሎችን ሐሳብ መጥቀስ፥ መተንተን የመንፈስ ሞያ ሆ
ቢኒ የመጽሐፍ ግብዣ 26 የዶ/ር እጓለ ገ/ዮሐንስን፣ ዘመን አይሽሬውን "የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤን" ተጋበዙልኝማ! "ከግሪክ ፈላስፎች በኋላ ... የሌሎችን ሐሳብ መጥቀስ፥ መተንተን የመንፈስ ሞያ ሆነ። መንፈስ በገዛ ራሱ ውስጥ ያለውን ምንጭ ትቶ ወደ ሌላ እየሄደ እንደ ንብ በመቅሰም ዕውቀቱን ይቀምም ጀመር። የዚህ ዘመን ፍልስፍና 'ኤክሊስቲሲዝም' ይባላል። ከመቅሰም የተገኘ የሐሳብ ድርጅት ነው ..." በማለት በመጽሐፋቸው ያነበሩ ሲሆን፣ ይሄን ውሰት በማደርጀት እንዴት ባለ ሁናቴ ለከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ ማዋል እንዳለብን ጥቁምታ ይሰጡናል። በመጽሐፉ የትምህርትን ትርጓሜ በመዳሰስ፣ የሥልጣኔን ምንነት በማተት፣ የአውሮፓን የዕድገት መም በመፈተሽ፣ የኛን ሥልጣኔ በያሬዳዊ አስተማስሎ በመዘየብ፣ የከፍተኛ ትምህርት ትርጓሜን በተዋህዶ አክብረው ያቀርቡታል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 25 በርትራንድ ረስልን እሚያህል ጉምቱ ፈላስፋ ፊትለፊት የሞገቱትን የአብዬ መንግሥቱ ለማን የሕይወት ታሪክ "ደማሙ ብዕረኛ" በተሰኘ መጽሐፋቸው ማግኘታችን ምንኛ መታደል ነው?!
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 25 በርትራንድ ረስልን እሚያህል ጉምቱ ፈላስፋ ፊትለፊት የሞገቱትን የአብዬ መንግሥቱ ለማን የሕይወት ታሪክ "ደማሙ ብዕረኛ" በተሰኘ መጽሐፋቸው ማግኘታችን ምንኛ መታደል ነው?! ሐረር አደሬ ጢቆ ተወልደው፣ ከዜማ እስከ ጾመ ድጓ በልጅነታቸው ፉት ብለው፣ በግዕዝ ቅኔ ተጠምቀው፣ በጣልያን ወረራ ወቅት የነበረውን የልጅነታቸውን ዘመን ወሽኔ በሆነ ብዕራቸው ስለውታል። በለንደን ኢኮኖሚክስ ያጠኑ፣ በሕንድ የኢትዮጵያ አምባሰደር የነበሩ፣ በብሔራዊ ቋንቋ አካዳሚ ያገለገሉ፣ አያሌ ተውኔቶችን እና መጻሕፍትን ያበረከቱት አብዬ መንግሥቱ ለማ የሕይወት ታሪካቸውን ጽፈው ሳይጨርሱ በ1980 ዓ.ም ቢያርፉም ግለታሪካቸው እጅግ ውብና ሰው ሰው የሚሸት መሆኑን እንመሰክራለን። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 24 "ትዝታዬ ስለራሴ የማስታውሰው" የተሰኘው የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ መጽሐፍን ተጋበዙልኝማ! የብላታን ግለታሪክ የያዘው ይህ ድንቅ መጽሐፍ እንዴት ከእምቧጮ መግደላ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 24 "ትዝታዬ ስለራሴ የማስታውሰው" የተሰኘው የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ መጽሐፍን ተጋበዙልኝማ! የብላታን ግለታሪክ የያዘው ይህ ድንቅ መጽሐፍ እንዴት ከእምቧጮ መግደላዊት ተነስተው፣ በአራት ዓመታቸው የቀለም ትምህርት አሃዱ ብለው ... ጅሩ፣ ደብረ ብሥራት ዜና ማርቆስና፣ እንጦጦ ቅኔ ጠጥተው፣ የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ ራጉኤል በልተው፣ ጃንሆይ ለሚያሳትሟቸው መጻሕፍት አገልግሎት እንዲሰጡ የጽኅፈት ሥራን የተቀጠሩበትን ተረክ ያትታል። ብርሃንና ሰላም ሲከፈት በጋዜጠኝነት፣ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ሲጀመር በመምህርነት፣ እንዲሁም ለግማሽ ምዕተ ዓመት ለመማሪያነት ያገለገለውን የአማርኛ ሰዋሰው መጻሕፍን ያበረከቱልን የእኚህ ጉምቱ አባት ግለታሪካቸው ከታሪክ፣ ከባሕል፣ ከዘመን መንፈስ ጋር በውብ ቋንቡ ተዋዝቶ የተከተበ ነው። ጅጅጋ የራስ መኮንን ትምህርት ቤት በዳይሬክተርነት፣ ከእንግሊዝ ሱማሌላንድ ጋር የወሰን ክልል ኮሚሽን ውስጥ በዋና ጸሐፊነት፣ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኝነት ሀገራቸውን ያገለገሉትን የብላታ መርስዔ ኀዘንን ግለታሪክ ማንበብ የዚያን ዘመን የሀገርን ጅረት ከምንጩ እንደመጠጣት ነው። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

የምድራችን ጀግና በእውቁ ፕሮፌሰር ተወልደብርሃን ገ/እግዚአብሔር የሕይወት ታሪክ ላይ የተሰነደ የዘነበ ወላ መጽሐፍ ነው። በውስጡም የኔታ ተወልደ፦ ለ1.4 ቢልየን አርሶ አደር ሲል ከአሜሪካና ካናዳ
የምድራችን ጀግና በእውቁ ፕሮፌሰር ተወልደብርሃን ገ/እግዚአብሔር የሕይወት ታሪክ ላይ የተሰነደ የዘነበ ወላ መጽሐፍ ነው። በውስጡም የኔታ ተወልደ፦ ለ1.4 ቢልየን አርሶ አደር ሲል ከአሜሪካና ካናዳ አንገት ለአንገት የተናነቁ፣ ከረብጣ ዶላር ይልቅ ምስኪን ገበሬዎች የበለጡባቸው፣ በሀገረ እንግሊዝ ያለማስተርስ ፒኤችዲ የሠሩ፣ የኦልተርኔቲቭ ኖቤል ፕራይዝን የተቀዳጁ፣ የአስመራ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት የነበሩ፣ በደርግ ዘመነ መንግስት የባህል ሚኒስተርነት የተሾሙ፣ በጎልማሳነት ዘመን ተኩሶ ለመታቸው ምህረትን ያወረዱ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ሕይወት አባት፣ አፍቃሬ አከባቢ፣ በኢትዮጵያ አከባቢ ጥበቃ ቢሮ እና የብዝሃ ሕይወት ኢንስቲትዩት የመሠረቱ፣ ከሃምሳ በላይ ጥናትና ምርምር ያበረከቱ፣ ቻምፕዮንስ ኦፍ ዘ ኤርዝ ሽልማትን የተቀዳጁ፣ የሦስት ልጆች አባት፣ ከሃምሳ በላይ ሰዎችን በቤቱ እንደ ልጆቹ ያሳደጉ፣ ያስጠለሉ፣ የመገቡ፣ ለቁም ነገር ያበቁበት የሕይወት ተረኮቻቸው በመጽሐፍ ውስጥ ተሰድረዋል። በመጽሐፉ ውስጥ ስለ ዶ/ር ጌታቸው ቦሎዲያ፣ ስለታላቃቸው ስብሃት ገ/እግዚአብሔር፣ ስለፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ፣ ስለባለቤታቸው ዶ/ር ሱዛን ኤድዋርድስ እና መሰል ጉምቱ ሰዎችም በመጽሐፉ ውስጥ ከየኔታ ተወልደ ሕይወት ጋር ተሰናስሎ ቀርቧል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ - 22 የኢትዮጵያ ፍልስፍና የተሰኘው የብሩሕ አለምነህ መጽሐፍ በዘርዓያዕቆብ እና በወልደሕይወት መጻሕፍት ላይ በመመርኮዝ የኢትዮጵያ ፍልስፍናን የሚያትት መጽሐፍ ነው። በውስጡም
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ - 22 የኢትዮጵያ ፍልስፍና የተሰኘው የብሩሕ አለምነህ መጽሐፍ በዘርዓያዕቆብ እና በወልደሕይወት መጻሕፍት ላይ በመመርኮዝ የኢትዮጵያ ፍልስፍናን የሚያትት መጽሐፍ ነው። በውስጡም፦ የቅኔ እና የፍልስፍና ልዩነትን ለማሳየት የቀረበ የደራሲው ግለምልከታ፣ በዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ አክሱማዊነት እና ላሊበላዊነት ኀልዮት ተገን ያደረጉ ፍካሬዎች፣ በዶ/ር ክላውዶ ሰምነር ሐቲት ላይ የተደገፉ እና ዘርዓያዕቆብ ከምዕራባዊ ፈላስፎች ቀድሞ ያበረከታቸው እሳቤዎች ... ከአንኳሮቹ የመጽሐፉ ማጠንጠኛዎቹ ውስጥ ይገኛሉ። መጽሐፉ በብዙ ሕዳግ የተደገፈ፣ በማጣቀሻ መጻሕፍት የዳበረ ሲሆን የዘርዓያዕቆብና የወልደሕይወት ትሩፋቶችን የሚያወሳ፣ የሚፈክር እና ለሌላ መሰል ጥናቶች እንዲጠኑ የሚያነሳሳ ሆኖ አግንቼዋለሁ። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 21 የሕይወቴ ታሪክ የተሰኘውን የጋሽ ተክለጻድቅ መኩሪያ ግለታሪክን ተጋበዙልኝ! የኢትዮጵያ ታሪክ ሲነሳ ሁልጊዜ ስማቸው ይወሳል። እኚህ ጉምቱ አባት ሌላኛው የሕይወት ገጻቸው ግ
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 21 የሕይወቴ ታሪክ የተሰኘውን የጋሽ ተክለጻድቅ መኩሪያ ግለታሪክን ተጋበዙልኝ! የኢትዮጵያ ታሪክ ሲነሳ ሁልጊዜ ስማቸው ይወሳል። እኚህ ጉምቱ አባት ሌላኛው የሕይወት ገጻቸው ግን ይዘለላል። ጋሽ ተክለጻድቅ መኩሪያ! በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሰደር ሆነው የጻፏቸው ራፖር በዲፕሎማሲው ረገድ ያላቸውን ብስለት ያሳያል። የወመዘክር ዳይሬክተር በነበሩበት ጊዜ ተቋሙን ሊያዘምኑ የሞከሩበት መንገድ፣ በዘመነ ማርሻል ቲቶ በዩጎዝላቪያ የነበራቸው የአምባሳደርነት ዘመን፣ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ ሥርዓተ ትምህርቱ ላይ ለውጥ ለማምጣት ያደረጉት ሙከራ፣ የየካቲት 12 ገጠመኛቸው፣ ከክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል ጋር የነበራቸው አለመግባባት፣ በታሪክ አጻጻፍ ላይ ያላቸው ምልከታና መንገድ፣ የትዳር ሕይወታቸው፣ በጃንሆይ መንግሥት የነበራቸው ቅሬታ እና መሰል ተረኮች የሕይወቴ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው በስፋት ተዳስሷል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 20 አንድ መጽሐፍ በሥነ ጽሑፋችን ላይ ከሚጨምረው ነገር አንደኛው ሌሎች እንዲጽፉ በማነሳሳት ረገድ ነው። አዳም ሥነ ጽሑፋችን ላይ ከጨመረው ነገር አንደኛው እንደሱ በሕጽናዊነት
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 20 አንድ መጽሐፍ በሥነ ጽሑፋችን ላይ ከሚጨምረው ነገር አንደኛው ሌሎች እንዲጽፉ በማነሳሳት ረገድ ነው። አዳም ሥነ ጽሑፋችን ላይ ከጨመረው ነገር አንደኛው እንደሱ በሕጽናዊነት ወስፌ የሚሰፉ ጻሕፍት እንዲፈጠሩ በማድረጉ ረገድም አይደል? ሐምራዊ ተረኮች የተሰኘው የኤልሳ ሙልጌታ መጽሐፍ በሕጽናዊነት ቴክኒክ የዳበረ፣ ከጫጫ  ሰማይ ስር ያሉ  ትናንሽ የመንደሪን ጉሞችን በፍርፍር አስተሳስሮ የሚያካፋ አጃኢብ የሆነ ድርሰት ነው። #ሞት አባጨጓሬ የምትፈራዋን እናቴን ለምስጥ ሠራዊት ትተናት መጣን!  🔥 #ባይተዋርነት በሰው ቀዬ የተተከለ ችግኝ ካለሀገሩ አፈር ስሩ ይፀድቃል? እዚህ ከተማ በሰው ቀዬ የተተከልኩ ችግኝ ደግሞ እኔ ብቻ አይደለሁም። ቀለመማርያምም የኔው ብጤ ነች። ካለ ሀገሯ አፈር በሰው ምድር ላይ ካልፀደቅሽ ተብላ አጓጉል ያደገች ተክል። ... #ዘላለማዊነት የሰው ልጅ ተወልዶ ኖሮ ማርጀቱ፣ አሮጌ መሆኑ፣ አለፍ ሲልም መሞቱ ይቀራል? አየሽ ሁሉም ነገር አይቀርም። ይልቅ የእርጅናም ሆነ የሞት ማሸነፊያ መውለድ ነው። አሁን አንቺ ታድለሻል። አራት ጊዜ ነው ሞትን ያሸነፍሽው። ደጋግመሽ ነው የረታሽው። #ይነበብ #ቢኒያም አቡራ

ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 19 የእኛ ሰው በአሜሪካ የተሰኘው የጋሽ ነብይ መኮንን መጽሐፍ በአማርኛ ከተሰነዱልን የጉዞ ማስታወሻ መጻሕፍት ከመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚቀመጥ ሲሆን በውስጡ ... በአሜሪካ የአን
ቢኒ የመጻሕፍት ግብዣ 19 የእኛ ሰው በአሜሪካ የተሰኘው የጋሽ ነብይ መኮንን መጽሐፍ በአማርኛ ከተሰነዱልን የጉዞ ማስታወሻ መጻሕፍት ከመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚቀመጥ ሲሆን በውስጡ ... በአሜሪካ የአንደኛው ስቴት የትራፊክ ሥርዓት ስለዘረጋው ትውልደ ኢትዮጵያዊ፣ በጀርመን ሀገር ስላጋጠሙት አስቂኝ ተረኮች፣ እንደ ፕሮፌሰር አብይ ፎርድ ያሉ ታላላቆቻችን የሕይወት መንገድ፣ የአሜሪካ ተነባቢ መጽሔቶች አዘገጃጀት፣ ዝርወተ ኢትዮጵያ (ዲያስፖራ) የሚሠሩትን ሥራ ለመናገር ያላቸው ኅፍረት በአንጻሩ በማያዘባንን ጉዳይ ስላላቸው አላቅም ተቧቃሽነት፣ ጋሽ አሰፋ ጫቦ ሆቴሉን ካልከሰስኩ ብለው ስለደነፉበት የክስ ጉዳይ እና መሰል ውብ ማስታወሻዎች ተካተውበታል። ጋሽ ነብይ አሜሪካን ውስጥ ለተወለደ ልጅ እትብት የሚለውን ቃል እንዴት ባለ አውድ እንደሚነግረው እዩልኝማ፦ እትብት ... ከተወለድክበት ካደግክበት ቤት ጋር የሚያስተሳስርህ ክር፣ Roots(ሥረ-መሠረትህ) ደጅህ፣ ጓሮህ፣ አፈርህ ከአንተ ጋር ትርታ ለትርታ፣ ሽታ ለሽታ የተቆራኘ ነው። በዓይንህ ላይ ይሄዳል። ከልብህ ጋር አብሮ ይመታል። ከሙቅ ህዋስህ ጋር ሰምሮ ይነዝራል። የእናትህ ጠረንና ሙቀት ፣ የአባትህ ተግሳጻዊ ፍቅር፣ የወንድም የእህቶችህ ጫጫታና ሳቅ፣ ሁሉ ከአፈሩ ጋር አብረው ይሸትቱሃል። ... እትብት በዕድንባ የታሰረ ረቂቅ አገር ነው። በዚህ ላይ እንግዲህ በሆስፒታል ሳይሆን በጥንቱ ወግ፣ በሰፈር አዋላጅ እናት አባት ቤት ተወልደህ፣ አባትህ ጓሮ ተቀብሮ ከሆነ፣ ለአፈሩ የዘር ሀረግ ይጨምርለታል። የማይበጠስ ፍቅር ይቋጥርለታል። #ይነበብ #ቢኒያም አቡሬ

የእንጀራ ቤት የሚል ትርጉም ከያዘችው ቤተልሔም የሕይወት እንጀራ በበረት ተጋገረ። ከዚህ በረት የተገኘውን እንጀራ የበሉ በጎች ሁሉ ዳግመኛ ረኀብ እንዳያገኛቸው። እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረ
የእንጀራ ቤት የሚል ትርጉም ከያዘችው ቤተልሔም የሕይወት እንጀራ በበረት ተጋገረ። ከዚህ በረት የተገኘውን እንጀራ የበሉ በጎች ሁሉ ዳግመኛ ረኀብ እንዳያገኛቸው። እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ ቢኒያም አቡራ