Christian Mindset
Open in Telegram
We explore faith, personal growth, and spiritual development through a Christian lens. We offer inspiring devotionals, practical tips for spiritual growth, and a supportive community to help you live out your faith authentically. 😎ቤተሰብ + @cms_help_me
Show more1 382
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-1430 days
Posts Archive
1 382
☺️እስቲ አንድ ያልተለመደ መዝሙር
እናድምጥ (🧎♂➡️ደግሞ እየሰማን ትንሽ አብረን በፀሎት እንተንፍስበት)
😌እኔ ወድጄዋለሁ
1 382
😞ፍለጋ 😌
😕እኔን ብሎ ፎቶግራፈር 😎😎
🤔ይህን ፎቶ ያነሳሁት ከ 7 ዓመት በፊት በ2010 ሚያዝያ ወር ጎንደር ከተማ በሚገኝ አንድ ገዳም ውስጥ ነው። ታድያ ሁሌም ሳየው ብዙ ነገር እማርበታለሁ በሀዘን ልብስ ምን አልባትም ባዘነ ተስፋ በቆረጠ ልብ ውስጥ ተስፋ ፍለጋ ፣ ደግሞ የማያቋርጥ ፍለጋ ፣ የወስጥ ደግሞ የልብ ህመም ፣ ደግሞ ሌላ የሚመጣ የሚያቆጠቁጥ እውነት ፣ ናፍቆት ፣ ደግሞ ጥበቃ የዘገየ ቀጠሮ ብቻ ብዙ ትርጉም እየሰጠኝ ደግሜ ደጋግሜ አየዋለሁ ለአመታትም ከስለኬ ላይ አልጠፋም። ሁሌም ግን ፎቶውን ካየሁ በኃላ የሚመጣብኝ ይህ ቃል ነው ……
1ኛ ዜና መዋዕል 16፥11 “እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። “
🎵🎵ፈልግሀለው
🎶🎶ፈልግሀለው …….
😐በጣም ብዙዎቻችን ብዙ ግዜ በየእምነታችን ፀሎት አድርገን እናውቃለን ይህም በጣም ጥሩ እና ትክክለኛ ነገር ነው። ግን ስንቶቻችን ፊቱን ብቻ እንፈልግ ይሆን ?? እግዚአብሔር ሁሌም ቢሆን በምንም አይነት ፀሎቶቻችነእ ይደሰታል ይሰማናልም አባት አይደል? እኛስ ልጆች አይደለን ? የልጅነት መንፈስስ ተቀብለን አይደል ?? ወደ ገላትያ 4፤6 “ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።” ልክ አንድ አባት በልጁ ኮልታፋ እና ያልተሰደረ ቃላት እንደሚደሰተው እርሱም ይደሰታል።
🎶🎶ፊትህ ደስታን ይናገራል ……….
መዝሙረኛው እንዳለ
መዝሙረ ዳዊት 27 ፥ 8 “አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።”
ልባችን ፊቱን ቢፈልግ በርግጥም ከኰልታፋው ይልቅ ያደጉት ልጆቹ እንሆናለን። ምክንያቱም እኔ ሲገባኝ እግዚአብሔር ፊቱ ሁለንተናው ነውና
ፊቱ ውበቱ ነው
ፊቱ ደስታችን ነው “መዝሙር 16፥ 11”
ፊቱ ክብሩ ነው
ፊቱ ማፅናናቱም መፅኛውም ነው
ፊቱን የፈለገ ሁሉን ያገኛል እጁን የፈለገ ግን በምድረ በዳ ጠግቦ ይሞታል።
ፊቱን የፈለገ ዘላለም ናፋቂ እንጂ ከምድር የተጋባ አይሆንም።
ፊቱን የፈለገ ተስፋን ያያል ……ወዘተ
😕ብዙ የምትሉት ሊኖራችሁ እንደሚችል በደንብ አውቃለሁ እኔ ግን ልላቹህ የፈለኩት ልክ እንደዚህ ፎቶ መንፈስ ቅዱስ ሁሉን እረስተን ዓለምን እና ምኞትዋንም ክደን ፊቱን ናፋቂዎች ያድርገን። ምናልባትም መዝሙር 27፥4 እንደሚለው የአንዲት ነገር ለማኞች እንሁን “የፊቱ” 🫀
🙏ዘመናችሁ ፀሎታችሁም ሁሉ ፊቱን በመናፈቅ ይሞላ መልካም ሳምንት።
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_se
1 382
😞ፍለጋ 😌
😕እኔን ብሎ ፎቶግራፈር 😎😎
🤔ይህን ፎቶ ያነሳሁት ከ 5 ዓመት በፊት በ2010 ሚያዝያ ወር ጎንደር ከተማ በሚገኝ አንድ ገዳም ውስጥ ነው። ታድያ ሁሌም ሳየው ብዙ ነገር እማርበታለሁ በሀዘን ልብስ ምን አልባትም ባዘነ ተስፋ በቆረጠ ልብ ውስጥ ተስፋ ፍለጋ ፣ ደግሞ የማያቋርጥ ፍለጋ ፣ የወስጥ ደግሞ የልብ ህመም ፣ ደግሞ ሌላ የሚመጣ የሚያቆጠቁጥ እውነት ፣ ናፍቆት ፣ ደግሞ ጥበቃ የዘገየ ቀጠሮ ብቻ ብዙ ትርጉም እየሰጠኝ ደግሜ ደጋግሜ አየዋለሁ ለአመታትም ከስለኬ ላይ አልጠፋም። ሁሌም ግን ፎቶውን ካየሁ በኃላ የሚመጣብኝ ይህ ቃል ነው ……
1ኛ ዜና መዋዕል 16፥11 “እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። “
🎵🎵ፈልግሀለው
🎶🎶ፈልግሀለው …….
😐በጣም ብዙዎቻችን ብዙ ግዜ በየእምነታችን ፀሎት አድርገን እናውቃለን ይህም በጣም ጥሩ እና ትክክለኛ ነገር ነው። ግን ስንቶቻችን ፊቱን ብቻ እንፈልግ ይሆን ?? እግዚአብሔር ሁሌም ቢሆን በምንም አይነት ፀሎቶቻችነእ ይደሰታል ይሰማናልም አባት አይደል? እኛስ ልጆች አይደለን ? የልጅነት መንፈስስ ተቀብለን አይደል ?? ወደ ገላትያ 4፤6 “ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።” ልክ አንድ አባት በልጁ ኮልታፋ እና ያልተሰደረ ቃላት እንደሚደሰተው እርሱም ይደሰታል።
🎶🎶ፊትህ ደስታን ይናገራል ……….
መዝሙረኛው እንዳለ
መዝሙረ ዳዊት 27 ፥ 8 “አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ።”
ልባችን ፊቱን ቢፈልግ በርግጥም ከኰልታፋው ይልቅ ያደጉት ልጆቹ እንሆናለን። ምክንያቱም እኔ ሲገባኝ እግዚአብሔር ፊቱ ሁለንተናው ነውና
ፊቱ ውበቱ ነው
ፊቱ ደስታችን ነው “መዝሙር 16፥ 11”
ፊቱ ክብሩ ነው
ፊቱ ማፅናናቱም መፅኛውም ነው
ፊቱን የፈለገ ሁሉን ያገኛል እጁን የፈለገ ግን በምድረ በዳ ጠግቦ ይሞታል።
ፊቱን የፈለገ ዘላለም ናፋቂ እንጂ ከምድር የተጋባ አይሆንም።
ፊቱን የፈለገ ተስፋን ያያል ……ወዘተ
😕ብዙ የምትሉት ሊኖራችሁ እንደሚችል በደንብ አውቃለሁ እኔ ግን ልላቹህ የፈለኩት ልክ እንደዚህ ፎቶ መንፈስ ቅዱስ ሁሉን እረስተን ዓለምን እና ምኞትዋንም ክደን ፊቱን ናፋቂዎች ያድርገን። ምናልባትም መዝሙር 27፥4 እንደሚለው የአንዲት ነገር ለማኞች እንሁን “የፊቱ”
ተስፋ አለው ፊትህን ሳየው 🎵🎵🎵🎶🎶
🙏ዘመናችሁ ፀሎታችሁም ሁሉ ፊቱን በመናፈቅ ይሞላ መልካም ሳምንት።
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_se
1 382
Repost from Maranatha Digital Network
ኔፍሊም እነማን ናቸው? በዚህ ቪዲዮ ቀርቧል
👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻👇🏻
https://youtu.be/3B3jiPqp_OQ?si=Zp83pnqUqW18O2dR
〽️aranatha Digital Network
@Maranatha_MDN
@Maranatha_MDN2
1 382
#ጠኔ_ይያዛችሁ
ሰው የሚጠጣው የጠማውን ያህል ነው። የሚበላውም የራበውን ያህል ነው። አንድ አንድ ሰው በጁ ውሀ ስለያዘ ብቻ በየደቂቃው ጎንጨት ይላል። ጉሮሮውን ለማራስ ያህል እንጂ እውነት ተጠምቶ አይደለም እርካታውም ቢሆን የዚያን ያህል ነው። ረሀብም እንደዛው ነው ስለቀረበ ብቻ የምንበላው እና ከቀናት ምግብ ፍለጋ በኃላ የምንበላው በመጠኑም ሆነ በርካታው ይለያያል። እኔ ሁለቱም አጋጥሞኝ ያውቃል የጠኔ ያህል እርቦኝ ያውቃል ምግብ መብላት ፈልጌ አጥቼ አውቃለሁ እሱ ሰዓት ታድያ እንዴት ከባድ መሰላችሁ ውሃ እንኳ ለተወሰነ ሰዓታት ካልሆነ አጥቼ አላውቅም።
ምን ልላችሁ ነው ታድያ ውፍረት እየቀነስኩ እና ግዴታ ሆኖብኝ የምበላው ምግብ እና በረሀብ ግዜ የምበላው አጎራረሱ እራሱ ይለያል ልክ እንደዛው መንፈሳዊ እረሀብም ይለያያል። መንፈስ ቅዱስን የምንፈልገው የራበንን ያህል ነው የምንፀልየው የፍለጋችንን ጥግ ነው። የናፈቀንን ሰው ለማየት ረጅም መንገድ የምንሄደው ቀጠሮው ሁሉ የማይደርስ የሚመስለን የናፍቆታችን ሙላት ስለሚበልጥ ነው። የሆነ አገር ተጉዘን ይሄ ነው የማይባል ተራራ እና ገደል አይተን ፎቶ አንስተን ተነስተን ሞኝ ይመስል ስቀን ወድቀን ተሰባብረን የምንመለሰው የአይናችንን ረሀብ ለመሙላት ነው። በተይ በበረሀ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች እንዳወሩኝ ውሀ ጥማት እጅግ ከባድ ነገር ነው። ጌታ እየሱስም እኮ እንደዚህ አለ።
#ማንም_የተጠማ
የዮሐንስ ወንጌል 7
37፤ ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ እንዲህ ብሎ ጮኸ፦ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።
አንድን ሰው ጠምቶሀል ብላችሁ በግድ ልታጠጡት እንደማትችሉ እንደዛው በርግጥ የተጠማን ሰው ደሞ ፍለጋውን ልታቋርጡበት አትችሉም። ሳይጠጣ አይረካምና።
በርግጥ እኔም ሆንኩ ከላይ የተጠቀሰው ቃል በስጋ ምድር ላይ ስለምናገኘው ውሀ አናወራም በርሱ ሊያምኑ ስላሉት ስለ መንፈስ ቅዱስ እንጂ።
ይሄን ፅሁፍ ከመፃፌ ከተወሱ ሰዓታት በፊት Daniel Tebebu የሚባል ጓደኛዬ ስለ እያሱ ቤተ መቅደስ ደጃፍ ላይ መቆየት በቪድዮ በጣም ጥሩ መልእክት ሲያስተላልፍ ነበር። እያሱም መንፈሳዊ ረሀብ በድንኳን ደጅ እንደሚያሳድረው አስቤ አላውቅም ነበር።
መንፈሳዊ ረሀብ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። ጌታም በተራራው ስብከት ላይ እንደተናገረው በመንፈስ ድሆች የሆኑ እነሱ መንግስተ ሰማያትን እንደሚወርሱ እንዲሁም ፅድቅን የሚራቡ እንደሚጠግቡ ይናገራል።
የማቴዎስ ወንጌል 5
3፤ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥
መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
…………….
6፤ ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥
ይጠግባሉና።
ድህነት ሰውን ፍለጋ ውስጥ ይከተዋል ሰው ሁሌም የሚፈልገው የሌለውን ነውና።
በዚህ ፅሁፍ ላይ ማለት የምፈልገው አንድ ነገር ነው መፀሀፉ እንደሚነግረን
- እያሱ ከመቅደስ አይለይም ነበር
- ሳሙኤል በመቅደስ ውስጥ ያድር ነበር
- እግዚያብሔር ደሞ ለሚፈልጉት ይገኛል
- በመንፈስ ድሆች የሆኑቱ የተጠሙቱ ተሰብስበው እንደጠበቁት ሐዋርያቶች ይሞሉታል ይቀምሱታል
#ምን_ይሆን_የራበን ??
ታድያ የዛሬ ጥያቄዬ ለኔም ለትውልዴም ይሄ ነው። ምን ይሆን በጣም የጠማን ? ምን ይሆን የጠኔ ያህል የራበን እርሱን የተራብነውን እናገኘዋለን። መፈለጋችን እና እረሀባችን ላመል ያህል ብቻ አለመሆኑን እርግጠኛ እንሁን እንጂ ከውስጥ የወጣ የምድረ በዳ አይነት ጥማት ይሁን እነጂ ከምንጩ ሊያጠጣን ዛሬም መንፈስ ቅዱስ ህያው ነው ረሀባችን ይጥና እንጂ ቤታችንን ሊያጠግብ ሙላታችን ሊሆን ቃሉ በደጃችን አለ። ብቻ ይራባችሁ።
#የማያረካ_ውሃ
በጣም የሚገርመኝ ነገር ሁላችንም እንደምናውቀው በጣም የራበን ቀን የምንፈልገው ምግብ እንደኔ ከሆናችሁ ሞላ እና ጠቅለል ያለ በአፍ ሲበላ ጠንከር ያለ ምናምን ሊሆን ይችላል ግን በዚህ ዘመን እንደዛ አይደለም እዚህ ግባ የማትሉት የማይረቡ ምግቦች አሉን እንደ ፋንዲሻ ትሪውን ሞልተውት ምግብ መሰል መሸወጃዎች እንበላቸው ?? ብዙዎቻችን የራበንን ስለማናውቀው እነዛን መሰል ምግቦች እናግበሰብሰና ረሀባችን ከደቂቃዎች በኃላ ደሞ ይቀጥላል። መዝናኛው፣ ፊልሙ፣ የተደላደሉ ቀጠሮዎቻችን፣ አጠር ያሉ ስብከቶቻችን፣ የደህና እደር ያህል ፀሎታችን፣ የምንሰራቸው እንቅስቃሴዎች እና ሌሎችም መሰል ነገሮቻችን ተደማምረው ግዜያዊ ጥጋብ እየሰጡ ከትክክለለኛው ምንጭ እያራቁን ነው። እስኪ እዚህ ጋር ምንባባችሁን ገታ አድርጉት እና ስለራሳችሁ ትንሽ አስቡ
- የውነት ምግብ ከበላችሁ ስንት ቀን ሆናችሁ ?
- የእውነት ምንጭ ስር ሄዳችሁ እንደ ሰማሪያዊትዋ ሴት ከቀዳችሁ ስንት ግዜ አስቆጠራችሁ ??
- መች ነበር ከድምፁ የጠገባችሁት መች ነበር ተሞልታችሁ እርፍ ያላችሁት።
እንደሚመስለኝ ሁላችንም እንደ ማርያም እና ዮሴፍ የፌስቲቫል ጋጋታ እየሱስን አስረስቶ አስጉዞን ሳይሆን አይቀርም ወይም ደግሞ ፊታችን እየጠወለገ እንደ ኤማአኦስ መንገደኞች ጥቂት ምእራፍ ገሰገስን ??
እነዚህ የኔ ጥያቄዎች ናቸው መልሶቹ ደሞ ለናንተ።
#እኔ_ግን_ልንፀልይላቹ
የርሀብ ጠኔ ልክ ስጋ የሚያከሳ ምንፈስ የሚያወፍር ያግኛችሁ ብዬ
የሚያቅበዘብዝ ጥማት ከምንጩ የሚተክል ድንኳን የሚያስቀር ፍቅር መቅደስ የሚያሳድር ይያዛችሁ ብዬ
እናንተ አሜን በሉ።
#ጥላ_ጥላውን_ታድያ
1 382
አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። #ቅድሚያ #የእግዚአብሔርመንግሥት #አስቀድሞመፈለግ
Seek first the kingdom of God and all these things will be added to you. #Priorities #GodsKingdom #SeekFirst
1 382
🥹 #ባንድ_ሌሊት_ዳንኩኝ ።🥰
🎵 🎶 በምን አይነት ፍቅር እንደነካኸኝ እኔንጃ ….)2x by Yidnekachew Teka
☺️እድገቴ ብዙ ነፃነት ስለነበረው የፈለኩትን የማድረግ የማሰብ ፣ የመሆንም መብት ነበረኝ ለምን የሄን አነበብክ ለምን እንደዚህ አደረክ የሚሉ ክሶች ብዙም አልነበሩብኝም፥ አባቴ በጣም እራሴን እንድፈልግ እና በመረጥኩት መንገድ እንድሄድ ረድቶኛል በጣም አመስግነዋለሁ። በተለይ ስለ Existence of God and thinking logical lifestyle ያወራነውን መቼም አልረሳውም። የእናቴ ፀሎት ደግሞ መሬት ጠብ የማይል ነው። በዚህ አስቸጋሪ ዘመን ስለተሸከምሽኝ አመሰግናለሁ።
👉🏾 ብዙ የልጅነት ጥያቄዎች እና የማያጠግቡ መልሶች
🤔እግዚያብሔር የለም ወይም ቢኖር ኖሮ የሄ እና ያ ለምን ሆነ ?
ሰው መሆን ማለት ምንድን ነው ?
ሞት የመጨረሻችን ነው ?
እኔ እራሴ ሁሉን ለምን አላውቅም ?
ሃይማኖት ምን ድረስ ያስኬደናል ?
ሀይማኖት አምላክ ሰራሽ ነው ወይስ ሰው ሰራሽ ?
እነዚህን እና መሰል ጥያቄዎች ከ13 አመቴ ጀምሮ እጠይቅ ነበር። እንደውም ከልጅነት ጏደኞቼ ጋር ወጣ ባለ መልኩ የማይረሱ አይነት ውይይቶችን እናደርግ ነበር። ለዚህም ደግሞ አንድ አንድ ግዜ ለማሸነፍ ሌላ ግዜ ለማወቅ ካለን ጉጉት የተነሳ የማናነባችው መፀሃፎች አልነበሩም።
👉🏾 ቀልድ የሚመስል ጉብኝት
🥺በፈረንጆቹ የጥቅምት ወር መጀመርያ ላይ ነበር ልክ የዛሬ 16 አመት ለመጀመርያ ግዜ ሙሉ ባዶ በሆነ ማንነት በአንድ በተባረከ አርብ ቀን በቤተስብ ውስጥ በሌለ ባልተለምደ ቤተእምነት (you go city church ) ውስጥ የተገኘሁት፥
ስባኪው( ፓስተር ሞ) ስብከቱን ሲጀምር እንደዚህ አለ
“እግዚያብሄር አለ“ ቀጥታ ወደ እኔ ለእኔ በሚምስል መልኩ በልቤ ውስጥ ያለው ጥያቄ ሁሉ ተዳሰሰ ስባኪውም ቀጠለ
“ ሰዎች በጣም ሰነፎች ነን አምላክን መፈለግ ሲያቅተን የለም እንላለን እሱ ግን አለ በተለያየ መንገድም እራሱን ሲያሳይ ኖርዋል ሰነፍ ግን በልቡ ሰነፍ ስለሆነ የለም ይላል እርሱ ግን ለሚፈልጉት ይገኛል” …….
እያለ በሰፊው አስተማረ ታድያ በዚህ መሃል ነበር ምን እንደነካኝ ሳላውቅ አንዳች የሆነ መረዳት በልቤ ውስጥ የገባው። ለመጀመርያ ግዜ መፀሃፍ ቅዱስም ያነበብኩት በዚያን ቀን ነበር።
👉🏾 “ በምን አይነት ፍቅር እንደነካኸኝ እኔንጃ ..”
😭ያን ቀን በምን እና ምን እንደነካኝ ሳላውቅ ሰው እጁን ሳይጭንብኝ ፣ ማንም ይሄን በል ያንን ሳይለኝ ፍቅሩ በልቤ መፍሰስ ጀመረ…….. ያላየሁት አምላክ እንደሚወደኝ እንድሚፈልገኝ ተሰማኝ……. አለቀስኩ ደግሜ አለቀስኩ ለሊቱን ሙሉ ግን ሊወጣልኝ አልቻለም ……. ድንገት በረደኝ ደሞ ሞቀኝ ደስታ እና ለቅሶ ተቀላቀሉብኝ …….. ደሞ መስቀል ታየኝ መኖር ፈለኩ……..ለምን እንደሆነ ሳላውቀው ደሞ ወዲያው ይቅርታ ጠየኩት….. የቆሸሽኩ ተሰማኝ ልጅነቴ ጥፋቶቼ ሁሉ ታዩኝ…….. ደሞ ውዲያው ይቅር ያለኝ መሰለኝ በውሃ ሳይሆን በደም አጠበኝ ……ብቻ ምኑ ቅጡ አንዳንዱን ስሜት የሚያውቅ ያውቀዋል …….. ባንድ ሌሊት ዳንኩኝ ።
👉🏾 ማን የለየኛል ???
🤗ይህው ድፍን 16 አመት ያ ስሜት ያ እንባ ያ ፍቅር አልበረደም ዛሬም እግዚያብሄር ለኔ ሩቅ አይደለም በክርስቶስ ቅርቤ ሆኖልኛል። በመንፈሱ የእስትንፋሴ ያህል እሰማዋለሁ። “እናንተ ርቃችሁ የነበራችሁ … “ ኤፌሶን 2:13 እንድሚል ቃሉ በፊቱ፣ በቤቱ ዛሬም አለሁ። ፍቅሩ መልካምነቱ አባትነቱ እንክብካቤው እያደገ እንጂ ሲቅንስ አላየሁትም። እርግጥ ነው ሮሜ 8፥39 “ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ:: “ ዛሬም በተለያየ ነገር ውስጥ እናልፋለን ከዚህ ፍቅር ግን ፀሃፊው እንዳለው አንዳች ሊለየኝ(ን) እንዳይችል ተረድቼያለሁ።
🥰ብዙ መፃፍ ባስብም ብዙ ማለት ግን አልቻልኩም አንዳንዴ እኮ ቃላቶች እጅግ ትንሽ ናቸው።
👉🏾 ይሄን ሁሉ ለምን አልከን ??
🤲አንድም ጌታ እየሱስን ስለወደደኝ ላመሰግነው
ሁለትም ምን አልባት በኔ አይነት የተሰላቸ ፍለጋ እና የስንፍና መንገድ ውስጥ ካላችሁ እግዚያብሔር ዛሬም እንደሚወዳችሁ ለማስታወስ እንዲሁም እርሱን በማወቅ እንድበረታ ያደረጉኝን ለማመስገን ነው።
😍ወንድማችሁ
አንተነህ ነኝ
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
😍አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ።| Do not keep talking so proudly or let your mouth speak such arrogance, for the Lord is a God who knows, and by him deeds are weighed.
📖 1 Samuel 2:3 (NIV) | 1ኛ ሳሙኤል 2:3
J
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
Repost from Maranatha Digital Network
ያልተሰጠን ለበጎ ነው
የጠየቅነውን ሁሉ እግዚአብሔር ሰጥቶን ቢሆንስ??
✨ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር በየእለቱ በጸሎት ሕብረት ያደርጋል። እናም በዚህ ሕብረቱ በህይወቱ ያሉበትን ጥያቄዎች በእግዚአብሔር ፊት ያቀርባል፣ ለውሳኔዎቹ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይጠይቃል። እግዚአብሔር አምላክም እንደ አባትነቱ የሚያስፈልገውን ሁሉ ያደርግለታል። ነገር ግን ጥያቄው የጠየቀውን ሁሉ ይሰጠዋል ወይ ነው። በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምናምን ዮሐንስ በመልእክቱ እንዲህ ይለናል
Digital Network
@Maranatha_MDN
@Maranatha_MDN2
ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ!!!
በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል።” 1ዮሐንስ 5፥14⚡️እግዚአብሔር አብ አምላክ እና አባቱ እንደሆነለት ሰው ህይወታችን የተመሰረተው በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ ነው።የጸሎታችንን መልስ ወሳኙ ጥያቄው(ጸሎታችን) በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ መመስረቱ ነው። እንደፈቃዱ ለሆነ ጸሎት ከእግዚአብሔር ዘንድ መልስ አለ።
እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው? ማቴዎስ 7:11⚡️ጌታ ኢየሱስ በዚህ ክፍል የስጋ አባቶች እንኳ ለልጆቻቸው መልካምን መርጠው ማድረግ ያውቃሉ በማለት የሰማይ አባታቸው አብልጦ እየመረጠ የሚበጃቸውን እንደሚሰጣቸው ይነግራቸዋል።መከልከልን እንዳለመወደድ እና እንዳለመሰማት ከመቁጠራችን በፊት ለእኛ መልካም መስሎ የታየን በእግዚአብሔር በጊዜ አለመወሰን እና ገደብ የለሽ እውቀት ውስጥ መልካም እንዳልሆነ መገንዘብ አስፈላጊ ነው።
“እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።” ሮሜ 8፥28⚡️ጳውሎስ በመልእክቱ እግዚአብሔር ለሚወዱት ነገር ሁሉ ለበጎ ነው ይለናል ።በስራው ትክክል የማይሳሳት ሁሉን ቻይና ጻድቅ ፈራጅ አምላክ እንዳለን በመረዳት አይሆንም ማለቱ ለኛ ካለው ጥልቅ ፍቅር እና አሳቢነት በመነሳት እንደሆነ ያልሰጠን ለበጎ እንደሆነ እና በእኛ ላይ ያለው ሀሳብ መልካም እንደሆነ ማወቅ እና መቀበል ተገቢ ነው። 💥አይሆንም በተባልነው ነገር 'ለምን' ከማለት እና ከመቆዘም የሚሰራውን የሚመዝን አምላክ የልቡን ሀሳብ እንዲያስረዳን መጸለይ መፍትሔ ነው። የበረከት አምላክ ልጆቹን አጥፊ ከሆነ መሻታቸው መጠበቁ የአባትነት መገለጫው እና የበጎነቱ ክፍል ነው። ✍ በጸሎት ዘሪሁን 〽️aranata
1 382
😒ሁሌ ከእራሴ ጋር የምሟገትበትን እውነት ልሞግታችሁ
🤔እስቲ ከራሳችሁ ህይወት አስተያዪት እድሜችሁ በጨመር ልክ የቱ እየበለጠባቹ የመጣ ይመስላችኋል ?
👆 ከላይ ያለው ምስል የሰው ልጅ በዘመናት መካከል ትኩረት ስለሚሰጣቸው በልብ እየነገሱ እና እየተቆጣጠሩት ያሉ ጉዳዮችን 1923 - 2024 ያለውን ጥናት በአሀዝ አቀረብኩላቹ ‼️ እናንተ ግን በቀን ውሏችሁ አስተያዪት
😎 መልካም ምሽት
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
😊ከእኔ ተማሩ የቀጠለ ............
😐ከብዙ ቀናት ሙከራ እና ውትወታ በኋላ ከዚያም በአክስቱ ልጅ በኩል እንዲያገኘኝ እናም ምን እንደተፈጠረ እንዲነግረኝ ስራ ቦታቸው አከባቢ የነበረው ካፌ ላይ እንድንገናኝ መልዕክት ላኩኝ የማይደርስ የለምና የቀጠሯችን ሰዓት ደረሰ እና ሄድኩኝ ትንሽ አርፍዶም ቢሆን ደረስ (ከዚህ በፊት በነበረን ግዜ አርፍዶ አያውቅም) ከዛም ከወትሮው ለየት ያለ ሰላምታ እጁን ዘርግቶ አቀረበልኝ ግራ ስለተጋባው ዝም ብዪ አየውት ቁጭ ብሎም እጄን ይዞ እየተርበተበተ አይኖቹ እንባ ቆጥረው ማውራት ጀመረ
ሰሉ አሁን በህይወቴ የማልቋቋመው ጭንቀት ውስጥ ነኝ ብዙ ጥያቄ እንድትጠይቂኝ አልፈልግም ግን ቤተሰቦቼ በእኔና በአንቺ ግንኙነት ደስተኛ አይደሉም አለኝ ምን አጠፍው ብዪ
ለምን ብዪ ጠየኩት ?
እርሱ፦ ቤተሰቦቼ ከእንናንተ ዘር(ጎሳ) ጋር መጋባት አይፈልጉም ንቀት አለባቸው አባቴ እና እናቴ ዘራችን አሰድበህ የዘመድ አዝማድ መሳለቂያ ታደርገን እና ልጅነትህ የዛን እለት ያበቃል ብለውኛል ብዙ ላስረዳቸው ሞከርኩ በጣም ለብዙ ቀናት ለመንኳቸው ግን ምንም ርህራሄ አልነበራቸውም ይባሱኑ ዘመድ ሰብስበው ሁሉም ወይ እርሷን ወይ እኛን ምረጥ ብለው ነብሴን አስጨነቋት የልጅነት ፍቅሬን አንቺን እንድተው ነገሩኝ አለኝ
እኔም፦ በከባድ ግራ መጋባት ውስጥ ሆኜ እና ምን ወሰንክ አልኩት
😔መልሶም ብዙ ለማውራት አቅም የለኝም ግን በጣም እወድሻለሁ ግን ካንቺ በላይ ለቤተሰቦቼ አስፈልጋለሁ ሳምንት ሙሉ ለብቻዪ አስቢያለሁ ተጋብተን ብንኖሮ የቤተሰቦቼ ሀዘን ብሎም መገለል በህይወት አያቆየኝም ልጆችንም ባይተዋር ሆነው እንዲያድጉ አልፍም በሰቆቃ የተሞላ ኑሮ እንድንኖር አልፈልግም ስለዚህ አለሜ ያሳለፍናቸው እነዛ አመታት ሁሌም ልቤ ላይ ይኖራሉ እወድሻለሁ አሁን አቅም የለኝም የምትይኝ ነገር ካለ በይኝ እና ልሂድ አለኝ
"ልብህ ወዳለህ ሂድ " አልኩት ከዛን ተነስቶ ሄደ (የሚገርመው የዘላለም ቤተሰቦች ክርስቲያኖች አልፎም አገልጋዮች ናቸው😏)
😔 ለብዙ ወራት በህመም እና በለቅሶ በቤቴ ከረምኩ አያሌ ቀናት ተሰቃየው ወደዛ ወደጠላትውት ዝምታዪ ከአመታት በኋላ ተመለስኩ ብዙ ግዜ ምግብ አልበላም እነጫነጫለሁ ዝም ብዪ አለቅሳለሁ እራሴንም ለማጥፍት አስብ ነበር ህመሜን እና ጉዳቴን ካብራራው ቀናት አይበቁኝም ነገር ግን በዚህ ሁሉ አዝነው ልባቸው የወረደው ወላጆቼ ነበሩ አላለቀሱም እንጂ ደምተዋል .....ብቻ ሆድ ይፍጀው ከዛም ሳሳጥረው ጌታ አበረታኝ እንደገና በረታሁ የማያልፍ የመሰለኝ ያ ግዜ ብዙ ትውስታዎችን አሸክሞኝ አለፈ ብዙ ልነግራችሁ የምፈልገው ነገር ቢኖረኝም በዚህ ልቋጭ አሁን በህይወቴ ደስተኛ ነኝ ጌታ ትሁት በሆነ ባል ክሶኛል ደግሞም አንድ ቆንጅዪ ወንድ ልጅ ወልደናል ቁስሌን ከነ አካቴው እረሳ ዘንድ በልጅ ባርኮኛል ሁሉም ለትምህርት ሆኗል....
እስቲ ልጠይቃቹ ?
ማን ነው መርጦ የተፈጠረ ? ማንስ ነው ተሽሎ የተወለደው?* ሁሉም አፈር አይደል?
😏 ከእኔ እንድትማሩ የምፈልገው የእግዘብሔርን ቃል እንደሚለው
“ነገር ግን፦ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው
— 1ኛ ቆሮንቶስ 1፥30-31
እባካችሁ ሰዎችን በተወለዱበት ዘር ብሄር ጎሳ እየከፋፈላችሁ አትመልከቱ እንዲህ የሚያስብ ሰው ክርስቶስ አልበራለትም እኝደገና ወንጌል ሊመሰከርለት ይገባል አልዳነም ምክንያቱም ከክርስቶስ በላይ የጎሳ ትምክህት በልብ አለና
🤔ሌላው በአስተሳሰብ ማነስ ምክንያት በወረዱ ሰዎች ህይወታችሁን አታስገምቱ ሁላችንም ስንሞት አፈር ነን + እንደ ክርስቲያን ኢየሱስ ከነገድ ከቋንቋ ከዘር ዋጀን እንጂ የጎሳ ተከራካሪ አላደረገንም ስለዚህ ለግንኙነታቹ ድንበር አበጁለት ለቤተሰቡ + ለባህል + ለጎደኛ .... ሁሉም በእናንተ ህይወት ገደብ ይኑራቸው ይህን ካረጋችሁ ጥሩ የሆነ ግንኙነት ይኖራችኋል የቀድሞ ህይወቴን ያፈረሰው ቤተሰብ ነውና
2, ለነገ ህይወታችሁ ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ሁኑ🫡
3, የሚታይ ማታስነኩት አቋም ይኑራችሁ (ከመጣው ጋር ሁሉ አትሂዱ😒 )
4, ጭንቀታችሁን ለጌታ ንገሩት 😔
ሁሉን ካወሩ ሆድ ባዶ ይቀራል ይባላል አይደል ስለዚህ ብዙ ምላችሁ ነገር ቢኖረኝም .... በዚሁ ልሰናበታችሁ በርቱልኝ 🙏
"ሁሉም ለትምህርታችን ሆነ"
እህታችሁ ነኝ❤️
‼️ለባለታሪካችን privacy ሲባል በስማቸው ላይ መጠነኛ ማሻሻያ አድርገናል
#ሼር
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
👩🦰ከእኔ ተማሩ..... 😐🙏
🙌ሰላም እንዴት ቆያቹ እኔ ደህና ነኝ ብዙ ጊዜ በዚህ page ላይ የሚለቀቁ መልዕክቶች በጣም እከታተላለሁ ያፅናኑኛል በብዙ ተጠቅሜበታለሁ ዛሬ እኔን ያስለቀሰኝ እንዳያስለቅሳችሁ ከእኔ ብትማሩ ብዪ መጥቻለሁ
👩🦰 ስሜ ሰሎሜ ይባላል 29 አመቴ ነው የሀዋሳ ልጅ ነኝ ቤተሰቦቼም ሆኑ የሚያውቁኝ ሰዎች ዝምተኛ እንደሆንኩ ይናገራሉ 😊 ይሄ ዝምታዪም ተከትሎኝ ወደ university ሄዶ ነበር ብዙም ከ class ብሎም ከ dorm ልጆች ጋር አላወራም ነበር በጣም ዝምታ ይቀናኛል በነገራችን ላይ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ነበር ምማረው እናም ህይወትን በዝምታ እየገፋው በነበረ ወቅት 2ተኛ አመት ላይ ከእረፍት መልስ ከሀዋሳ ስመለሰ ግቢ ውስጥ የማውቀውን እንዲሁ በአይን የምንተያየውን ልጅ መኪና ውስጥ አየውት (እውነት ለመናገር ዶርም ውስጥ ጎደኞቼ ብዙ ግዜ ስለእርሱ ሲያወሩ ስምቻለሁ ስለ ቁመናው ስለ ውበቱ በተለይ ስለ መንፈሳዊ ህይወቱ እና ተግባቦቱ አውርተው አይጠግብም ነበር ) 😊 እናም እርሱ ከተቀመጠበት አለፍ ብዪ ከበስተጀርባው ሄጄ ተቀመጥኩ ኤርፎኔንም አድርጌ መዝሙር እያደመጥኩ በዝምታ ረጅም መንገድ ተጓዝን ከዛም ለእረፍት ከመኪናው ስንወርድ ለሰላምታ እጁን ዘረጋ እርሱም፦ ሰላም ጎንደር አይደል ምትማሪው አለኝ
እኔም ፦ አዎን አልኩት
እርሱም ፦ ዘላለም እባላለሁ አለኝ ሰሎሜ እባላለሁ አልኩት
🤔ከዛም መኪና ውስጥ ገብተን ጉዟችንን ቀጠልን ጎንደር ገባን እስከ ግቢ የያዝኩትን ሻንጣ አግዞኝ ሀይስኩል ሀዋሳ ስለተማርንባቸው ትምህርት ቤቶች እያወራን ግቢ ደረስን እናም ስልክ ተለዋወጥን ሳሳጥረው በእዚህ መንገድ የእኔና የዘላለም ጎደኝነት ተጀመረ በጣም እየተግባባን መጣን ወደ ሀዋሳ ለእረፍት አንድ ላይ መመላለስ ጀመርን በግቢ ውስጥም ፌሎሽፕ ላይ አገልገሎት 😍አስጀመረኝ በህይወቴ የማልረሳውን የክርስቲያን ተማሪዎች አንድነት እንድካፈል ረዳኝ ስብእናው ማርኮኝ ነበር እንደተዋደድን ያሳብቅብን ነበር
🥰 አንድ ቀንም የፍቅር ጥያቄ አቀረበልኝ እኔም በደስታ ተቀበልኩት የፍቅር ህይወት ጀመርን እናም በግቢ በነበረን ቆይታ በጣም ተጠቅመን ነበር እናም በህይወቴ የማልረሳውን ጊዜ አሳለፍን ደግሞም ብዙ ስለወደፊት ህይወታችን እናወራ ነበር እንፀልያለን በትምህርታችን እንረዳለን ደግሞም ከተማ ውስጥ ያሉ ምግቦች አንዳቸው አይቀሩንም ነበር በግቢ ውስጥ 3 አመት የፍቅር ህይወት አሳለፍን
😇 የግቢ ቆይታችንን አጠናቀን ወደ ሀዋሳ ከተመለስን በኋላ እኔ ባንክ ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩ እርሱ ደግሞ የቤተሰቦቹን ንግድ ይሰራል ጥሩ ነበርን እንዋደድ ነበረ እንተሳሰብም ነበረ ሁሌ ከእናቱ ጋር እንደሚያስተዋውቀኝ ይነግረኝ ነበር ግን ጊዜው እስኪደርስ እንጠብቅ ነበር በድንገትም የአንድ ወዳጃችን ሰርግ ላይ እናቱን እና አባቱን እናም አክስቱን አስተዋወቀኝ በጣም ደስ የሚሉ ቤተሰቦች ነበሩ ከዛም ብዙ መቆየት ስለማይችል ተሰናብቻቸው ዞላ ሸኝቶኝ ወደ ቤት ሄድኩ ማታም በስልክ እያወራን አምሽተን የፀሎት ሰአታችን ሲደርስ እርሱ ፀልዮልን ተለያየን ነገር ግን በማግስቱ ስራ በዝቶብኝ ስለነበረ አልደወልኩለትም አመሻሽ ላይም ስልኩ ዝግ ነበር አላገኘውም 3 ቀን ሙሉ ሞላኝ text ሳደርግለትም አይመልስም ስራ ቦታው ሄጄ ስጠይቅም የአክስቱ ልጅም አልገባም አለችኝ ግን ሰላም እንደሆነ ነገረችኝ ግራ ገባኝ እንደ ቀልድ ሳምንት ሆነን በድንገትም ፀጉር ቤት ስሄድ መንገድ ላይ አየውት ዞላ ብዪ ስጠራውም እየሰማኝ አጠገብ የነበረ ባጃጅ ውስጥ ገብቶ ሄደ ..................
😍ይቀጥላል.......
#ሼር
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
Repost from Maranatha Digital Network
#MDN_BIBLE_VERSE
Digital Network
å @Maranatha_MDN å
.| @Maranatha_MDN2 |.
“ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠው ያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን ነገር እንዲያው እንዴት አይሰጠንም?” — ሮሜ 8፥32#ራራህልን 〽️aranatha
1 382
ጥያቄ፡
" እጮኛ ለመያዝ ምን ማድረግ አለብኝ? "
መልስ፡
ይህን ጥያቄ ስትጠይቀኝ ከነዚህ ሁለት አማራጮች አንዱ ላይ ልትሆን ትችላለህ።
1. እጮኝነት ለመጀመር ጊዜህ ደርሶ ትክክለኛ ሰው አተህ ምን ላድርግ በሚል አማራጭ ወይም
2. እጮኝነት ለመጀመር አማራጭ አግኝተህ ራስህን ዝግጁ የማድረጉ ምዕራፍ ላይ ልትሆን ትችላለህ።
••• አንድ ቁምነገረኛ ሰው በህይወቱ ሊወስናቸው ከሚችላቸው አንዱና ትልቁ ውሳኔ የፍቅር አጋር ምርጫ ነው። ታዲያ ይህን ውሳኔ ያዛቡ አንዳንዶች ሲጎዱ ጥቂቶች ደግሞ ደስተኛ ሆነው ሲቀጥሉ እናያለን። አንተ ግን. . .
ትክክለኛውን ጊዜና ትክክለኛዋን ሴት ጠብቅ።
••• ከላይ በፍቅር አጋር ምርጫ ወቅት የተሳሳተ ውሳኔ ወስነው የሚጎዱት ይህን አዛብተው ነው። ትክክለኛ ጊዜ ላይ ትክክለኛ ያልሆነች ሴት ብትመጣ ትርፉ ጉዳት ነው። ሌላው ደግሞ ትክክለኛዋ ሴት ትክክል ባልሆነ ጊዜ ብትመጣም ትርፉ ጉዳት ነው።
መጀመርያ ግን "የቱ ላይ ነኝ?" የሚለውን ለይ።
ትክክለኛ ጊዜ፡
••• አንድ ሰው እጮኝነት ለመጀመር ጊዜዬ ነው ለማለት ማየት ያለበት ብዙ ነገር አለ። ትክክለኛ ጊዜ ለመለየት መስፈርቶቹ ከሰው ሰው ሊለያይ ቢችሉም ግን የጋራ የሆኑ ነገሮችም አሉ። እነዚህን እኔ ብቁነት(መንፈሳዊ፣ስነልቦናዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብቁነት) በሚለው ጠቀልላቸዋለው።
መንፈሳዊ ብቁነት፡ እጮኝነት የስጋ ጉዳይ ብቻ አይደለም። የወደፊት የትዳር አጋርህ ምን እንድትሆን ትፈልጋለህ ብልህ "ጥሩ መንፈሳዊ ህይወት ያላት ብትሆን" ልትል እንደምትችል አልጠራጠርም። ስለዚህ አንተም በዛው ልክ ዝግጁ ሁንላት።
••• ሰይጣን በዚህ ዘመን የያዘው ትልቁ ትውልድን መጣያ መሳርያው እጮኝነት ላይ ያነጣጠረ ነውና ይህን ፈተና ለመቋቋም የሚረዳህን መንፈሳዊ ልምምድ(ፀሎት፣የቃል እውቀት፣ቅድስናን) ታጠቅ።
ስነልቦናዊ ብቁነት፡ እጮኝነት ውስጥ ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ አይደለም አለመግባባት ብሎም መለያየት ሊኖር ይችላል። መለያየት ደግሞ መጠኑ ከሰው ሰው ቢለያይም ስነልቦናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል። ይህን የስነልቦና ቀውስ ታዲያ ብዙ ሳይጎዱበት የሚያሳልፉት አስቀድመው ራሳቸውን ያስታጠቁ ናቸውና በእጮኝነት መሀል አለመግባባት ብሎም ለትዳር የማትሆን ከሆነች መለያየት እንዳለ አስቀድመህ ለራስህ ማወቁ መልካም ነው።
••• አስተውል ተጠራጣሪ ሁን እያልኩህ አይደለም።
ማህበራዊ ብቁነት፡ በዚህ ውስጥ ደግሞ ከሌላ ሰው ጋር ያለህ ተግባቦትህ፣ችግር አፈታትህና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ይጠቃለላሉ። ስለዚህ እነዚህ ጉዳዮች ላይ እንዴት ነኝ ብለህ ራስህን ጠይቅ ማስተካከል ያለብህ ነገር ካለም እርምጃ ውሰድ።
ኢኮኖሚያዊ ብቁነት፡ ይህን ለማብራራት እንዲረዳኝ ወደኋላ መለስ ብዬ በሰው ታሪክ ውስጥ ሰው እንዲህ በቴክኖሎጂ ከመከበቡ ምግብና ልብስ ቤት ድረስ Deliver ከመደረጉ በፊት የሰው ልጅ አዳኝ(hunter) ሆኖ የሚኖርበትን ጊዜን ላስታውሳችሁ። (በዛን ዘመንም ነበርክ እንዴ እንዳትሉኝ ደግሞ ገና ልጅ ነኝ እኔ😁)
••• በዛን ዘመን አንድ ወንድ አደን ላይ አሪፍ ከሆነና ለአደን በወጣ ቁጥር የሆነ ነገር በትከሻው ተሸክሞ ለቤተሰቡ የሚያመጣ ከሆነ ብዙ ሴቶች ይህን ወንድ ለባልነት ይፈልጉታል ምክንያቱም ወደፊት አግብተው ልጅ ቢወልዱ ልጆቻችንን መመገብ ይችላል ብለው ስለሚያስቡ። በተቃራኒው ደግሞ እንቅልፋምና አደንን ያልተለማመደን ወንድ እንኳን ለትዳር ሊያስቡት እንደ ወንድ ላይቆጥሩት ይችላሉ።
••• ብታምንም ባታምንም መለክያ መስፈርቱ ይለያይ እንጂ በዚህ ዘመንም እንዲህ አይነት አመራረጥ አለ። በዚህ ዘመንም አደን(hunting) አለ እንቅልፋም አዳኝ(hunter) ከሆንክ ለወደፊት ህይወታችን አይጠቅምም ትባልና ተፈላጊ ሳትሆን ትቀራለህ። የዚህ ዘመን አደን ደግሞ ቀለል ያለ ነው ሴትም አደን ላይ መሰማራት ስለጀመረች ከአንተ የሚጠበቀው ቢያንስ ግማሹን የአደን መንገድ መጓዝ ነው። በየት በኩል ነው ጫካውን አሳየኝና ማደን ልጀምር ካልክ ጫካው ውስጥ ነህና ተግተህ ስራ። ህይወት በጣም ከባድ ብትሆንም የወደፊት ልጆችህን እያሰብክ ኑሮህን እና ኢኮኖሚህን ለመለወጥ ትጋ።
••• ሌላው እጮኝነት ለመጀመር ኢኮኖሚያዊ ብቁነት አስፈላጊ የሚሆነው አንዳንድ ወጪ መኖሩ ስለማይቀር ነው። በትንሹ ለበአል ለልደት ምናምን ስጦታ ማሰብህ አይቀርም ታዲያ ከቤተሰብ ወይም ከጓደኛ ተቀብሎ ከመግዛት በራስ ገንዘብ እንደመግዛት ያለ ነገር የለም። ይህን እንደምሳሌ አነሳው እንጂ ሌሎች አስፈላጊ ወጪዎች መኖራቸው ግልፅ ነው ለዚህ ደግሞ አንተ በኢኮኖሚው ብቁ ብትሆን የተሻለ ነው የሚሆነው። ነገር ግን እንደ ግለሰቦቹ ይወሰናል ብዩ አስባለው ምክንያቱም በኢኮኖሚ እራሳቸውን ለመቻል በጋራ እየታገሉ ያሉ ወዳጆች ስላሉኝ (እናንተ አይመለከትም 😁)
ትክክለኛ ሰው፡
••• ይህ ከሰው ሰው ቢለያይም ግን እንደ ክርስቲያን ጌታን እንደግል አዳኝ አድርጋ የተቀበለች መሆኑዋ ትልቁ መስፈርት ነው። ሌላውን መስፈርት ለአንተ ብተወው መልካም ነው።
••• አንተ እጮኛ ለመያዝ ምን ላድርግ ያልከው ጊዜህ ደርሶ ከሆነ ትክክለኛዋን ሴት ጠብቅ። ነገር ግን ጊዜህ ሳይደርስ በዙርያህ ያሉ ሰዎች አዋክበውክ ወይም ጓደኞችህ ስለገቡበት ከሆነ ለመጀመር ያሰብከው ባትጀምር መልካም ነው።
••• ብዙ ጊዜ ልባችንን ለስብራት የምንዳርገው የእኛ ነው ብለን ያሰብነውን ሰው ወደ ህይወታችን የሚመጣበትን ጊዜ ፈጠን አድርገን አልያም አዘግይተን ከማይሆን ሰው ጋር እጮኝነት በመጀመር ነውና አምላክ በትክክለኛው ጊዜ ትክክለኛዋን ሰው ወደ ህይወትህ በማምጣት ይባርክህ።
ጨረስኩ! 😎
#ሼር
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
Repost from Maranatha Digital Network
#MDN_BIBLE_VERSE
Digital Network
@Maranatha_MDN
@Maranatha_MDN2
“በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ።” — ኤፌሶን 1፥6#ይመስገን 〽️aranatha
1 382
🤔የካምፓስ ላይፍ ቴንሽን ወይንም
የኮሌጅ ውጥረት - የአን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በትምህርት ላይ ስለሚያጋጥማቸው ውጥረት (ቴንሽን) እንዲህ ይላሉ፡
“የደም ስሮቼን በዕፅ ና በጫት ማጨናነቅን፣ ቁጥር ስፍር የሌላቸው የፍትወተ-ሥጋ ባልንጀሮች ማስተናገድን ወይም እድሜዬ ወደ ሃምሳው ሲደርስ የነርቭ ቀውስ የሚያስከትሉብኝን ችግሮቼን አንደሌሉ ማስመሰልን ከመሳሰሉ ምርጫዎች ጋር በተፋጠጥኩበት በኔው ዓለም፣ ተስፋዎቼን ሁሉ በአንድ ከመንደር የዘለለ እውቅና በሌለው አናጢና አምላክ በሚባል እርባነ ቢስ ምስቅልቅል ላይ ማሳረፍ ትርጉም ይሰጣልን?”
የቀለሙ ጫና ደብዛዬን ሊያጠፋና ሊደፈጥጠኝ በተቃረበበት በዚህ ወቅት፣ በፊቴ የቆሙ ተራሮችን ከፊቴ ከማንከባለል ባሻገር እኔን የመፍጠር አቅም በሌለው ጣዖት ጉያ መሸጎጥ ትርጉም ይሰጣልን? ጨርሶ አላደርገውም! ማገልገልም ካለብኝ እኔ የማገለግለው አምላክ ከእንጨት የተቀረፀን ጥጃ ሳይሆን፣ የማይገደብ ኃይል ያለው፣ አምሳያ የማይገኝለት ውበት፣ ሉዓላዊ ሥልጣንና የማይነጥፍ ጸጋ ምንጭ የሆነውን ነው ከዚያ ባሻገር ግን ውድ ጊዜዬን በከንቱ ማባከን ነው፡፡
ምንም እንኳን ኢየሱስን ከሰባት ዓመቴ ጀምሮ የማውቀው ቢሆንም፣ ወኔ ቢስ፣ የማልረባና ባዶ የሓይማኖት ጀሌ መሆኔ እስካታከተኝ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እስከሆንኩበት ጊዜ ድረስ እምብዛም አልነበርኩም፡፡ እግዚአብሔር የሰዎች ትውፊት/ወግ ወይንም አስተሳሰብ ውጤት አሊያም እርባነቢስ የልማድ አምልኮ ውጤት አለመሆኑን ለመረዳት ይህንን ያህል ረጅም ጊዜ ወስዶብኛል፡፡ እርሱ ከእኛ ጋር የቅርብ ግንኙነት እንዲኖረን ይሻል፡፡ (እውነተኛው አምላክ ከእኛ ጋር የቅርብ ግንኙነት እንዲኖረው የሚፈልግ አምላክ ነው፡፡) ከትናት ዛሬም ከእርሱ ጋር የበለጠ እንድቆራኝ አድርጎኛልና ዛሬ፣ ስሙን እጅግ ከፍ አድርጌ አመሰግናለሁ ምክንያቱም በነዚህ ሁሉ ሻካራ ሁኔታዎቼ ውስጥ በድንቅ ሁኔታ እንደተሸከመኝ አይቻለሁ ፍቅሩንም አጣጥሜአለሁ ፡፡
በሁኔታችሁ በማያላግጥ፣ በማይስቅባችሁና ጀርባውን በማይሰጣችሁ ፊት ሁሉን ነገራችሁን ዝርግፍ ማድረግ ምንኛ የሚያጓጓ እፎይታ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከእኔ ፍፅምናን አይጠብቅም፤ እርሱ ከእኔ የሚፈልገው ኀጢአቴን እንድናዘዝና እንድታዘዘው፣ ስለ እርሱም የእውነት ምስክር ሆኜ እንድኖር ብቻ ነው፡፡
በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት፣ ከእግዚአብሔር ጋር የግል ግንኙነት መመሥረት፣ ከሁሉ ልቆ እንዲወጣ ያደረገው ምኑ ነው? እፎይታው ድነት የአድርግ አታድርግ ዝርዝር ዶሴ ወይንም የማይቀረው የዘላለም ፍርድ ወይንም ኩነኔ ማስፈራሪያ አለመሆኑ ነው፡፡ በእኔም ላይ የተጫነ አሰቃቂ ሸክም አይደለም፡፡ ኢየሱስ ያለው፡
“እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።
ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤
ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና።”
ታዲያ ይህ ሁለንተናን የሚያድስ አይደለምን? ታዲያ ይህ ነፍስን የሚያስፈነድቅ አይደለምን?
ለደካሞች ምርኩዝ? እምብዛም ችግር የለበትም፣ ችግሮቹንም ያለ አንዳች እንከን ብቻውን ይወጣቸዋል የምትሉት አንድ ሰው ካለ አሳዩኝ፤ ሸክም ያላጎበጠው፣ የማያለቅስ፣ ጭንቀትና ውጥረት ያልከበበው አንድ ሰው ካለ እስኪ አምጡልኝ እንዲህ ዓይነት ሰው ካለ… ራሱን በገና አባት የማታለያ ቀልዶች ወይንም የፋሲካ ሰሞን ተረቶች የሚሸነግል ሰው ነው፡፡ የደካሞች ምርኩዝ? ኦ አዎን!
እርካታ የሞላበት ሕይወት በመጠጥ፣ በግሩም ውጤት፣ በመልካም ሥራ ወይንም በበጎ አድራጎት እንደማይገኝ አይቻለሁ፡፡ እኔ ሕይወት እንዲሆንላችሁ እንዲበዛላችሁም መጣሁ ብሎ (ኢየሱስ) ተስፋን ሲሰጥ ምን ማለቱ እንደሆነ የገባኝ ኀጢአቴን ስናዘዝ እና ኢየሱስ ክርስቶስን የሕይወቴ ጌታና አዳኝ አድርጌ ስቀበል ነው፡፡ አንድ ሰው ስለ አንድ ነገር ሕይወቱን ሊሰጥና ሌላውን ሰው ደስ ስለማሰኘት መጨነቅን ሊቆም የተገባ ነው፡፡ ሕመም እጅግ የምጠላው አላርጅኬ የመሆኑን ያህል፣ አንድ እምነት ሊሞትለት የሚገባ መሆኑን ራሱ ካላረጋገጠ በስተቀር እሞትለታለሁ ብዬ አልናገርም፡፡ እኔ፣ በዚህ በፕሪንስተን ኮሌጅ እንደሚገኙ እንደበርካቶች ሁሉ፣ ይህንን መሳዩን እምነት ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በጀመርኩት ኅብረት ውስጥ አግኝቼዋለሁ፡፡
ሁልጊዜ እግዚአብሔርን በፊቴ አየዋለሁ በቀኜ ነውና አልታወክም።
ስለዚህ ልቤን ደስ አለው ምላሴም ሐሴት አደረገች ሥጋዬም ደግሞ በተስፋ ታድራለች
(መዝሙር 16፥8-9)
#ሼር
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
1 382
🤔ጥያቄ አሎት?
👋ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ ቤተሰብ + ለጥቂት ጊዚያት አቁመን የነበረውን ጥያቄ ተቀብሎ ለመመለስ መሞከር አሁን ስለጀመር ጥያቄቹን በዚህ ላኩልን @Yegorebet_meskot 👈👈👈👈👈
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
•√ Christian Mindset •√
@christian_mind_set
@christian_mind_set
