en
Feedback
አማራ ሚዲያ ማዕከል (AMC / VAR)

አማራ ሚዲያ ማዕከል (AMC / VAR)

Open in Telegram
4 635
Subscribers
-124 hours
-47 days
-7130 days
Posts Archive
ከአንድ ወዳጀ FB ላይ ነፍሱን ይማረውና በዓሉ ግርማ በመጽሀፉ ስለኛ ኢትዮጵያውያን የፃፈውን እስኪ ላጋራችሁና ፍረዱ! የጋሽ በአሉ ግርማ መልእክት ምን.... «እኔ ኢትዮጵያውያንን አላምንም ከራሴ ጀምሮ። በጭንብል ተሸፍነን የምንኖር ህዝቦች ነን። ለሰው የምናሳየው ገፅታና እውነተኛው ባህሪያችን የተለያዩ ናቸው። እንደ ተረታችን ፣ ስነ ፅሁፋችንና ንግግራችን ባህርያችንም ሰምና ወርቅ ነው ... በዚህ ላይ ደግሞ ክፉውና በጎውን ነገር አንዱን ከሌላው ለይተን የምናይበት መለኪያ የለንም ፤ የማንኛውም ነገር መሠረታዊ መለኪያችን የግል ጥቅማችን ነው። ለዚህም ነው ተንኮል የሚበዛው፤ መተማመን የሌለው፤ የወዳጅነት ወይም የጓደኝነት ትርጉሙ የማይታወቀው ፤ ሀሜት አሉባልታና እርስ በዕርስ መበላላት የሚበዛው።  ኢትዮጵያዊያን ስንባል የምናውቀው መርህ አንድ ብቻ ነው ፤ የግል ጥቅም! ከራስ በላይ ነፋስ ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል... ሰውን ማመን ቀብሮ ፥ ይሉታል ከነተረቱ። የሚያሳዝን ነው... ለግል ጥቅማችን የሚበጅ ከሆነ እንዋሻለን። ስንዋሽ ህሊናችንን ቅንጣት ታህል አይቆረቁረንም። እንዴት አድርጎ ለግል ጥቅም የተገዛ ህሊና ሊቆረቁረው ይችላል? ለተንኮል አንመለስም የምንሸርበው ተንኮል ጓደኛን፤ ወዳጅን ፤ የስጋ ዘመድን አይለይም ቅናት ባህላችን ነው። ምግባር የሚባለውን ነገር በአፍ ካልሆነ በቀር በተግባር አናውቀውም። በአጠቃላይ ክፉውንና በጎውን ለይቶ የሚያይ ህሊና የለንም፤ ያስተማረንም የለም። የተማርነው ነገር ቢኖር በአደባባይ ሰው መስሎ መታየትን ነው፤ ሰው መሳይ በሸንጎ ይሉ የለም? በአደባባይ ሁሉም ጨዋ፣ ልበ ሙሉ፣ ጀግና፣ አትንኩኝ ባይ፣ ኩሩና ቅን፣ በጎ አሳቢና ታማኝ፣ አስተዋይና ትሁት ነው። በአደባባይ የምናጠልቀው ጭንብል ይህ ነው። በግል ኑሮአችን ግን ከስብቅ ፣ ከምቀኝነት ፣ ከተንኮል፣ ከቅናት ፣ ለውሸት፣ ከአሉባልታና ከሀሜት፣ ለግል ጥቅም ለመልከስከስና ለመልፈስፈስ ከፍርሃትና ከአድር ባይነት ርቀን አንገኝም። መለያ ባህርያችን ግብዝነት ነው። የግብዝነት ጭንብል አጥልቀን ነው የምንኖረው። ያለ ጭንብል እናስቀይማለን... ወይም እናምራለን፤ አይታወቅም። ያለ ጭንብል ታይተን አናውቅማ!»  በዓሉ ግርማ የቀይ ኮከብ ጥሪ ገፅ 234

MWAO_IPR_V11No2_22June2024_የብልጽግና_ኦሮሙማው_አገዛዝ_በ_240626_181107.pdf2.56 KB

Letter_to_the_UN_and_International_Community_ABiy'_240526_171230.pdf2.09 KB

MWAO_IPR_V11No1_14April2024_የአብይ_አህመድ_አገዛዝ_በአዲስ_አበባ_የሚያደርሰውን_አስከፊ.pdf2.51 KB

MWAO_IPR_V11No1_14April2024_የአብይ_አህመድ_አገዛዝ_በአዲስ_አበባ_የሚያደርሰውን_አስከፊ.pdf2.51 KB

Emailing 4_5823216436302058850.pdf

JCAS Press Release-121823-1.pdf