en
Feedback
Sport24

Sport24

Open in Telegram

EtSport24 sport news channel

Show more
2 740
Subscribers
-324 hours
-117 days
-5030 days
Posts Archive
Sport24
2 740
photo content

Sport24
2 740
photo content

Sport24
2 740
ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከ52 ዓመታት በኋላ ለዓለም ዋንጫ አለፈች ****** በኢንተር ኮንፌደሬሽን ጥሎ ማለፍ የተሳተፈችው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ጃማይካን 1 ለ 0 በማሸነፍ በ2026 የዓለም ዋንጫ መሳተፏን አ
+3
ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከ52 ዓመታት በኋላ ለዓለም ዋንጫ አለፈች ****** በኢንተር ኮንፌደሬሽን ጥሎ ማለፍ የተሳተፈችው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ጃማይካን 1 ለ 0 በማሸነፍ በ2026 የዓለም ዋንጫ መሳተፏን አረጋግጣለች፡፡ በሜክሲኮ በተደረገው ጨዋታ የቀድሞው የማንችስተር ዩናይትድ ተከላካይ አክስል ቱዋንዜቤ የዴሞክራቲክ ኮንጎን ግብ አስቆጥሯል፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ በ1974 ዓለም ዋንጫ ተሳታፊ የነበረችው ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከአምስት አስርት ዓመታት በኋላ ወደ ትልቁ መድረክ ተመልሳለች፡፡ ዴሞክራቲክ ኮንጎ 48 ሀገራት ለመጀመርያ ጊዜ በሚሳተፉበት ዓለም ዋንጫ አፍሪካን የምትወክል 10ኛዋ ሀገርም ሆናለች፡፡

Sport24
2 740
በሪያል ማድሪድ ዲስቲፋኖና ሮናልዶም ይተቹ ነበር ! የሪያል ማድሪዱ አጥቂ ኪልያን ምባፔ በስፔን ቆይታው በደጋፊዎችና ሚዲያዎች የሚሰነዘርበትን ትችት በተመለከተ በሰጠው ምላሽ፤ ትችት የክለቡ ማንነት
በሪያል ማድሪድ ዲስቲፋኖና ሮናልዶም ይተቹ ነበር ! የሪያል ማድሪዱ አጥቂ ኪልያን ምባፔ በስፔን  ቆይታው በደጋፊዎችና ሚዲያዎች የሚሰነዘርበትን ትችት በተመለከተ በሰጠው ምላሽ፤ ትችት የክለቡ ማንነት አካል መሆኑንና ይህም እንደማያሳስበው አስታውቋል። ምባፔ ከጉዳት መልስ ባደረጋቸው ጥቂት ጨዋታዎች ላይ ያሳየው ብቃት አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ ቢሆንም፣ በቅርቡ ለፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ከብራዚል ጋር ባደረገው ጨዋታ ግብ በማስቆጠር ሙሉ ጤንነቱ ላይ መሆኑን አረጋግጧል። ለቴሌፉት በሰጠው ቃለ በስፔን እግር ኳስ በከፍተኛ ስሜት ነው የሚታየው፤ ሪያል ማድሪድ ደግሞ እንደ ሃይማኖት ነው። እዚህ ክለብ ውስጥ እንደ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ እና አልፍሬዶ ዲ ስቴፋኖ ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች እንኳን  ተተችተዋል፤ ስለዚህ እኔ የተለየ እሆናለሁ ብዬ አላስብም ብሏል። የ27 ዓመቱ ምባፔ በዚህ የውድድር ዘመን ባደረጋቸው 35 ጨዋታዎች 38 ግቦችን በማስቆጠር አስደናቂ ብቃት ላይ ይገኛል። ማድሪድ በቻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍጻሜ ከባየር ሙኒክ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ትልቅ እምነት እንዳለው የገለጸው ምባፔ፣ "ባየርን ሙኒክን ማሸነፍ የሚችል ቡድን ካለ እሱ ሪያል ማድሪድ ነው" በማለት በራስ መተማመኑን ገልጿል። ምባፔ ዘንድሮ የመጀመሪያውን የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ከሪያል ማድሪድ ጋር ለማንሳት አልሟል።

Sport24
2 740
በሊቨርፑል ሳላህ፣ ማኔ እና ፊርሚኖ ማስተዳደር ፈታኝ እንደነበር የርገ ክሎፕ ተናገሩ። ጀርመናዊው አሰልጣኝ ከዴይሊ ሜል ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሊቨርፑል በነበራቸው ቆይታ ታዋቂውን የፊት መስመር ጥም
+1
በሊቨርፑል  ሳላህ፣ ማኔ እና ፊርሚኖ ማስተዳደር ፈታኝ  እንደነበር  የርገ ክሎፕ ተናገሩ። ጀርመናዊው አሰልጣኝ ከዴይሊ ሜል  ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በሊቨርፑል በነበራቸው ቆይታ ታዋቂውን የፊት መስመር ጥምረት ሳላህ፣ ማኔ እና ፊርሚኖ የመምራት ውስብስብነት እና ከሞሃመድ ሳላህ ጋር የነበራቸውን አለመግባባት ይፋ አድርገዋል። ክሎፕ እንደገለጹት፤ ሳላህ እና ማኔን በአንድ ላይ ማስተዳደር እጅግ ፈታኝ ነበር። ሁለቱም ጠንካራ ባህሪ ያላቸውና በራሳቸው የሚተማመኑ ተጫዋቾች መሆናቸው ግጭቶችን ይፈጥር ነበር ብለዋል። ከሦስቱ ተጫዋቾች መካከል ምንም ዓይነት አስቸጋሪ ባህሪ ያልነበረው ብራዚላዊው ሮቤርቶ ፊርሚኖ ብቻ እንደነበረ ክሎፕ ገልጸዋል። ሳላህን በማፈራረቅ ጨዋታ ለማሳመን አስቸጋሪ እንደነበር ሲገልጹ፤ "በሳምንት ሦስት ጨዋታ መጫወት አትችልም ስለው፣ እሱ ግን እችላለሁ ይለኝ ነበር ብለዋል። እ.ኤ.አ. በሚያዝያ 2024 በዌስትሃም ጨዋታ ወቅት ከሳላህ ጋር በካሜራ ፊት የነበራቸውን አወዛጋቢ ጭቅጭቅ በተመለከተ በወቅቱ ነገሩ የጦርነት ያህል ታይቶ ነበር፤ ነገር ግን በሚቀጥለው ቀን ጠዋት ሁሉንም ነገር ጨርሰን ነበር። በሕዝብ ፊት ስለነበረ ነገሩ የከፋ መስሎ ታየ እንጂ በመካከላችን የነበረው አክብሮት አልቀነሰም ብለዋል። በ88ኛው ደቂቃ ላይ ቀይሬው በመውጣቱ ተቆጥቶ ነበር፣ እኔም ለምን ይሄ ሁሉ ድራማ አስፈለገ? ብዬ ነበር ሲሉ አስታወሰል። መሃመድ ሳላህ በዚህ የውድድር ዘመን ማብቂያ  ሊቨርፑልን እንደሚለቅ ማረጋገጡን ተከትሎ፤ ክሎፕ የሳላህ በሊቨርፑል የነበረው ታሪክ እንደ ሲኒማ ድንቅ ስራ  እንደነበር ገልጸዋል። የሳላህ የስንብት ፕሮግራም በግንቦት ወር  ታላቅ እና ልዩ እንደሚሆንም አክለዋል።

Sport24
2 740
ባየር ሙኒክ የሳዑዲ አረቢያን የዝውውር ሙከራ በመፍራት የሃሪ ኬንን ውል ለማራዘም እየተጣጣረ ነው። የባየር ሙኒኩ ፕሬዝዳንት ኡሊ ሆነስ እንዳሉት ክለቡ የሃሪ ኬንን ቆይታ ከ2027 በኋላ ለማራዘም ቢ
ባየር ሙኒክ የሳዑዲ አረቢያን የዝውውር ሙከራ በመፍራት የሃሪ ኬንን ውል ለማራዘም እየተጣጣረ ነው። የባየር ሙኒኩ  ፕሬዝዳንት ኡሊ ሆነስ እንዳሉት ክለቡ የሃሪ ኬንን  ቆይታ ከ2027 በኋላ ለማራዘም ቢፈልግም፣ ከሳዑዲ አረቢያ ሊቀርብ የሚችል ከፍተኛ የገንዘብ ጥያቄ የተጫዋቹን እቅድ ሊቀይረው ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሃሪ ኬን እ.ኤ.አ. በ2023 ክለቡን ከተቀላቀለ በኋላ ባደረጋቸው 136 ጨዋታዎች 133 ግቦችን በማስቆጠር እና 29 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት የቡድኑ የጀርባ አጥንት መሆኑን አስመስክሯል። ኬን ከ2027 በኋላም እዚህ ቢቆይ ምኞታችን ነው፤ እርሱና ቤተሰቡም በሙኒክ ደስተኛ እንደሆኑ አውቃለሁ" ያሉት ሆነስ፣  "ከሳዑዲ አረቢያ ድንገት ሊመጣ የሚችለውን እጅግ ከፍተኛ የገንዘብ ጥያቄ ምን ሊያመጣ እንደሚችል አታውቁም" ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። ሃሪ ኬን ስለ ወደፊት ቆይታው የሚሰጠውን ማንኛውንም ውሳኔ እስከ ዓለም ዋንጫው ማጠናቀቂያ ድረስ ለማራዘም ወስኗል። ይህም ባየር ሙኒክን ለተወሰነ ጊዜ ባለመተማመን ውስጥ እንዲቆይ አድርጎታል። ባየር ሙኒክ ኮከብ አጥቂው በክለቡ ረጅም ጊዜ እንዲቆይ ቢመኝም፣ የሳዑዲ ክለቦች የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን ዝውውሩን እውን ሊያደርገው ይችላል ተብሎ ይፈራል።

Sport24
2 740
ሰበር ዜና ! የነገው ጨዋታ ለደጋፊዎች ክፍት ሆነ። ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ ከ ሳኦቶሜ በዝግ እንዲካሄድ በካፍ የተላለፈው ውሳኔ ተቀይሯል። የኢትዮጵያ እግር ኳ
+1
ሰበር ዜና ! የነገው ጨዋታ ለደጋፊዎች ክፍት ሆነ። ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ ኢትዮጵያ ከ ሳኦቶሜ  በዝግ እንዲካሄድ በካፍ የተላለፈው ውሳኔ ተቀይሯል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ጸሃፊ አቶ ባህሩ ጥላሁን በማህበራዊ ገጻቸው እንዳሳወቁት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በስታዲየሙ ዙርያ የተሰጡ የግምገማ አስተያየቶችን መሰረት በማድረግ በፍጥነት ለማስተካከል በወሰደው እርምጃ እንዲሁም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጨዋታው ለተመልካች ክፍት እንዲሆን ባደረገው ከፍተኛ ጥረት ጨዋታው ለደጋፊ ክፍት ሆኗል። የካፍ ሴኪዩሪቲ ኦፊሰር በአካል ተገኝተው ከገመገሙ በኋላ በላኩት ሪፖርት መሰረት ካፍ 10,000 ተመልካች በድሬ ዳዋ ስታዲየም ተገኝቶ እንዲከታተል ውሳኔ አሳልፏል። ዋሊያዎቹ የመጀመሪያውን ጨዋታ ከሜዳው ውጭ 3 ለ 0 አሸንፎ የመጣ ሲሆን የደጋፊው መግባት ትልቅ የአሸናፊነት ወኔ ይፈጥርለታል። ብሄራዊ ቡድኑ ከ5 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሜዳው ይጫወታል። በድሬ ዳዋና አካባቢው የሚገኙ ሁሉ ቡድኑን ለማበረታታት የተገኘውን እድል በሚገባ ይጠቀሙበታል ተብሎ ይታመናል። መልካም እድል ለዋሊያው።

Sport24
2 740
በጉዳት ከብሄራዊ ቡድን ውጭ የሆነው የመድፈኛው 11 ክፍለጦር
+1
በጉዳት ከብሄራዊ ቡድን ውጭ የሆነው የመድፈኛው 11 ክፍለጦር

Sport24
2 740
photo content

Sport24
2 740
የ2026 ዓለም ዋንጫ የቲኬት ዋጋ ንረት ቅሬታ አስነሳ። በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የ2026 ዓለም ዋንጫ የወጣው የቲኬት ዋጋ ከመጠን ያለፈ እና ደጋፊዎችን ያገለለ ነው
የ2026 ዓለም ዋንጫ የቲኬት ዋጋ ንረት ቅሬታ አስነሳ። በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የ2026 ዓለም ዋንጫ የወጣው የቲኬት ዋጋ ከመጠን ያለፈ እና ደጋፊዎችን ያገለለ ነው በሚል  ለአውሮፓ ኮሚሽን  ይፋዊ ክስ ቀረበ። ክሱን ያቀረቡት የአውሮፓ እግር ኳስ ደጋፊዎች ማህበር እና የሸማቾች መብት ተሟጋች ተቋማት ናቸው።ፊፋ  በቲኬት ሽያጭ ላይ ያለውን ብቸኛ ስልጣን ተጠቅሞ ፍትሃዊ ያልሆነ እና ግልጽነት የጎደለው አሰራር ተከትሏል በሚል ነው ክሱ ። ለፍፃሜው ጨዋታ ያቀረቡት ዝቅተኛ የቲኬት ዋጋ 4,185 ዶላር ሲሆን፣ ይህም በ2022 በኳታር ከነበረው የፍፃሜ ጨዋታ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር የሰባት እጥፍ ጭማሪ አሳይቷል። የፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ለዋጋው መናር ምክንያቱ ከፍተኛ የቲኬት ፍላጎት መሆኑን በመጥቀስ  እንደ አሜሪካ ባሉ ሀገራት የዋጋ መለዋወጥ  የተለመደ መሆኑን ተናግረዋል። ደጋፊዎች ፊፋ በቅርቡ ያስተዋወቀው የ60 ዶላር  ቅናሽ ቲኬት በጣም አነስተኛ ቁጥር ያለውና ለብዙሀኑ ደጋፊ የማይደርስ በመሆኑ ለማስታወቂያ ያህል ብቻ የቀረበ ነው ሲሉ ተችተዋል። በተጨማሪም የቲኬት ዋጋው በየጊዜው የሚቀያየርበት አሰራር እንዲቆም እና በሚቀጥለው የቲኬት ሽያጭ ወቅት ዋጋው ተረጋግቶ እንዲቆይ ጠይቀዋል። ይህ የአውሮፓ ኮሚሽን ውሳኔ በቅርቡ በሚጀመረው  የቲኬት ሽያጭ ላይ ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ይጠበቃል።

Sport24
2 740
ሞሪሺዮ ፖቸቲኖ የእንግሊዝ እግር ኳስ ናፍቆኛል አለ። የቀድሞው የቶተንሃም እና የቼልሲ አሰልጣኝ ሞሪሺዮ ፖቸቲኖ የእንግሊዝ እግር ኳስ ድባብ እና ባህል በእጅጉ እንደናፈቀው ገለጸ። በአሁኑ ወቅት የአ
ሞሪሺዮ ፖቸቲኖ የእንግሊዝ እግር ኳስ ናፍቆኛል አለ። የቀድሞው የቶተንሃም እና የቼልሲ አሰልጣኝ ሞሪሺዮ ፖቸቲኖ የእንግሊዝ እግር ኳስ ድባብ እና ባህል በእጅጉ እንደናፈቀው ገለጸ። በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ ብሄራዊ ቡድን  አሰልጣኝ የሆነው አርጀንቲናዊው ታክቲሻን፣ ለ2026ቱ አለም ዋንጫ  በዝግጅት ላይ ቢሆንም፣ ልቡ ግን አሁንም በፕሪምየር ሊጉ ላይ እንዳለ አልሸሸገም። ፖቸቲኖ ከቢቢሲ ስፖርት ጋር በነበረው ቆይታ አንድ ቀን ወደ ፕሪምየር ሊግ የመመለስ ፍላጎት አለኝ ሲል ተናግሯል። እንግሊዝን ለፉክክር እና ለችሎታ መፈተኛ ተመራጭ ቦታ እንደሆነችም ገልጿል። ፖቸቲኖ ክለቡን በ2019 ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ማብቃቱ የሚታወስ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የቀድሞ ክለቡ ቶተንሃም አስከፊ ጊዜ ላይ ይገኛል። ስፐርስ በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ 17ኛ ደረጃ ላይ ሆኖ ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት ብርቱ ትግል እያደረገ ነው።   አሰልጣኙ ቼልሲን በጋራ ስምምነት ከለቀቀ በኋላ፣ በአሁኑ ወቅት የአሜሪካን ቡድን ለ2026ቱ አለም ዋንጫ እያዘጋጀ ይገኛል። ፖቸቲኖ በአሜሪካ ሆኖ ናፍቆቱን ሲገልጽ፣ በለንደን በኩል ግን ክለቡ በ49 አመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የወራጅነት አፋፍ ላይ ይገኛል። ካለፉት 13 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች በአንዱም ማሸነፍ ያልቻሉት ስፐርሶች ፣ ከኢጎር ቱዶር ሌላ አሰልጣኝ ለመቅጠር ፍለጋ ላይ ናቸው። ለማንኛውም ተወዳዳሪ መንፈስ ላለው እና ችሎታውን ለመፈተን ለሚፈልግ ሰው፣ እንግሊዝ ተስማሚ ቦታ ናት ያለው ሞሪሺዮ ፖቸቲኖ ምናልባት ወደ ቀድሞ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ተብሏል። ሮቤርቶ ዲዘርቢም ቶተነሃም በሊጉ ከቆየ በአማራጭ ውስጥ የገባ አሰልጣኝ ነው።

Sport24
2 740
ሮሜሎ ሉካኩ ከብሄራዊ ቡድኑ ውጭ ሆነ። ቤልጂየም ለ2026 ዓለም ዋንጫ ዝግጅት ከአሜሪካ እና ከሜክሲኮ ጋር ለምታደርገው የወዳጅነት ጨዋታ የቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሮሜሉ ሉካኩ እንደማ
ሮሜሎ ሉካኩ ከብሄራዊ ቡድኑ ውጭ ሆነ። ቤልጂየም ለ2026 ዓለም ዋንጫ ዝግጅት ከአሜሪካ እና ከሜክሲኮ ጋር ለምታደርገው የወዳጅነት ጨዋታ የቡድኑ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሮሜሉ ሉካኩ እንደማይሰለፍ ታውቋል። የ32 ዓመቱ አጥቂ በዚህ የውድድር ዘመን በናፖሊ በጉዳት እና በተቀያሪ ወንበር ላይ በማሳለፉ፣ አሁን ላይ ብቃቱን ለማስተካከል እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለመስራት መርጧል። ከሉካኩ በተጨማሪ ሌ አንድሮ ትሮሳርድ፣ ሃንስ ቫናከን እና ግብ ጠባቂው ቲቦ ኮርቱዋ በጉዳት ምክንያት በስብስቡ ውስጥ የሉም። የቀድሞው የማንቸስተር ሲቲው ኮከብ ኬቪን ደ ብሩይነ ከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ቡድኑ ተመልሷል። ቤልጂየም ከ አሜሪካ ቅዳሜ በአትላንታ እንዲሁም ሚያዝያ  ከሜክሲኮ ቺካጎ ላይ ይጫወታሉ ።

Sport24
2 740
ሴቪያ አዲስ አሰልጣኝ ሾመ። ሴቪያ ስፔናዊውን አሰልጣኝ ሉዊስ ጋርሲያ ፕላዛን እስከ 2027 በሚያቆይ ውል በማስፈረም በይፋ መሾሙን አስታውቋል። የ51 ዓመቱ አሰልጣኝ ሰኞ ዕለት ከኃላፊነታቸው የተነሱ
ሴቪያ አዲስ አሰልጣኝ ሾመ። ሴቪያ ስፔናዊውን አሰልጣኝ ሉዊስ ጋርሲያ ፕላዛን እስከ 2027 በሚያቆይ ውል በማስፈረም በይፋ መሾሙን አስታውቋል። የ51 ዓመቱ አሰልጣኝ ሰኞ ዕለት ከኃላፊነታቸው የተነሱትን ማቲያስ አልሜዳን ተክተዋል። አልሜዳ በ8 ወር ቆይታ ብቻ ነው የተለያየው። ሴቪያ በአሁኑ ወቅት ከወራጅ ቀጠናው በ3 ነጥብ ብቻ ርቆ ስለሚገኝ፣ የአዲሱ አሰልጣኝ ቀዳሚ ተግባር ክለቡን በሊጉ ማቆየት ይሆናል። ጋርሲያ ፕላዛ በላ ሊጋ ከ200 በላይ ጨዋታዎችን የመምራት  ልምድ አላቸው። የመጨረሻ ስራቸው በአላቬስ የነበረ ሲሆን፣ በታህሳስ 2024 (እ.ኤ.አ) ክለቡን ለቀው ነበር።

Sport24
2 740
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከሪያል ማድሪድ ጋር ስሙ መያያዙን ተከትሎ ምላሽ ሰጥቷል። ተጫዋቹ ከስፔኑ ክለብ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እንዳልተደረገ በግልጽ ተናግሯል። አሁን ላይ ሙሉ ትኩረ
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከሪያል ማድሪድ ጋር ስሙ መያያዙን ተከትሎ ምላሽ ሰጥቷል። ተጫዋቹ ከስፔኑ ክለብ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እንዳልተደረገ በግልጽ ተናግሯል። አሁን ላይ ሙሉ ትኩረቱ በቼልሲ የቀሩት የውድድር ዘመን ጨዋታዎች ላይ እንደሆነና ቡድኑ በተሻለ ደረጃ እንዲያጠናቅቅ መርዳት እንደሚፈልግ ገልጿል። ኢንዞ የወደፊት ቆይታው የሚወሰነው በሰሜን አሜሪካ ከሚካሄደው የ2026 ዓለም ዋንጫ በኋላ እንደሚሆን ፍንጭ ሰጥቷል። ኤንዞ በቡድኑ ውስጥ ያለው የመሪነት ሚና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ፣ ለክለቡ እቅድ እጅግ አስፈላጊ ተጫዋች ሆኗል። በተመሳሳይ ሌላኛው የቸልሲ አማካኝና የኢንዞ አጣማሪ  ሞይሰስ ካይሴዶ ወደ ስፔኑ ግዙፍ ክለብ ሪያል ማድሪድ ሊዘዋወር ይችላል ተብሎ የሚናፈሰውን ወሬ ውድቅ አደረጓል። ካይሴዶም በአሁኑ ወቅት ሙሉ ትኩረቱ በቼልሲ ላይ ብቻ እንደሆነና በክለቡም የታሪክ አካል የመሆን ህልም እንዳለው ገልጿል። "ሙሉ ትኩረቴ ክለቤ ላይ ነው። ከቼልሲ ጋር ኮንትራት አለኝ፤ ፈጣሪ ቢፈቅድ ኢዝሁ ታሪክ መስራት እፈልጋለሁ" ሲል ምላሽ ሰጥቷል። ተጫዋቹ በአሁኑ ወቅት በጥሩ ብቃት ላይ እንደሚገኝና ለሚመጡት ጨዋታዎች ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል። ካይሴዶ ይህንን የተናገረው የኢኳዶር ብሄራዊ ቡድን ከሞሮኮ ጋር ለሚያደርገው የወዳጅነት ጨዋታ በስፔን ልምምድ እያደረገ ባለበት ወቅት ነው።

Sport24
2 740
አሽራፍ ሀኪሚ ወደ ሪያል ማድሪድ የመመለስ ፍላጎት እንዳለው ተሰማ። ከዓለማችን ምርጥ የመስመር ተከላካዮች አንዱ አሽራፍ ሀኪሚ፣ ፕሮፌሽናል እግር ኳስን ወደ ጀመረበት ሪያል ማድሪድ ለመመለስ እያሰበ
+2
አሽራፍ ሀኪሚ ወደ ሪያል ማድሪድ የመመለስ ፍላጎት እንዳለው ተሰማ። ከዓለማችን ምርጥ የመስመር ተከላካዮች አንዱ አሽራፍ ሀኪሚ፣ ፕሮፌሽናል እግር ኳስን ወደ ጀመረበት ሪያል ማድሪድ ለመመለስ እያሰበ መሆኑን የራዲዮ ማርካ ጋዜጠኛ ራሞን አልቫሬዝ  ዘግቧል። ሀኪሚ ከፒኤስጂ ጋር እስከ 2029 የሚያቆይ ውል ቢኖረውም፣ በሁለቱ ክለቦች መካከል ያለው መልካም ግንኙነት ዝውውሩን ሊያቀላጥፈው ይችላል ተብሎ ይታሰባል። የዳኒ ካርቫሃል ውል በሰኔ ወር የሚጠናቀቅ በመሆኑ እና ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ እንደተጠበቀው ሆኖ ባለመገኘቱ፣ ማድሪድ በአስቸኳይ ቀኝ ተከላካይ ይፈልጋል። ሀኪሚ በሪያል ማድሪድ ቤት ከኪሊያን ምባፔ ጋር ያለው የጠበቀ ወዳጅነት እና ከሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አጋሩ ብራሂም ዲያዝ ጋር ያለው ግንኙነት ለዝውውሩ ትልቅ ግፊት ይሆናል ተብሏል። ማድሪድ ከሀኪሚ በተጨማሪ የሉካ ሞድሪች እና የቶኒ ክሮስ ተተኪ ሊሆን የሚችለውን የፒኤስጂውን አማካይ ቪቲሀን  ለማስፈረም ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል።

Sport24
2 740
ማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ አሰልጣኝ የመፈለግ ሂደቱን አዘገየ ። ክለቡ ለክረምቱ የአሰልጣኝ ቅጥር ከመቸኮል ይልቅ፣ አሁን ቡድኑን እየመራ የሚገኘው ማይክል ካሪክ ላይ ትኩረት ለማድረግ መወሰኑን ስካይ
ማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ አሰልጣኝ የመፈለግ ሂደቱን አዘገየ ። ክለቡ ለክረምቱ የአሰልጣኝ ቅጥር ከመቸኮል ይልቅ፣ አሁን ቡድኑን እየመራ የሚገኘው ማይክል ካሪክ ላይ ትኩረት ለማድረግ መወሰኑን ስካይ ስፖርት ዘግቧል። ካሪክ ቡድኑን መምራት ከጀመረ በኋላ ዩናይትድ በደረጃ ሰንጠረዡ ላይ መሻሻል አሳይቷል። ይህም ለቋሚ አሰልጣኝነት ጠንካራ ተፎካካሪ እንዲሆን አድርጎታል። ዩናይትድ የዘንድሮውን የውድድር ዘመን በደረጃ ሰንጠረዡ ለአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ደረጃ ካጠናቀቀ፣ ካሪክ በቋሚነት የመቀጠል ዕድሉ በጣም ከፍተኛ ይሆናል። ክለቡ እስካሁን ከሌሎች አሰልጣኞች ጋር ምንም አይነት ይፋዊ ንግግር አላደረገም። ይልቁንም የካሪክን ውጤት እስከ ውድድር ዘመኑ መጨረሻ ለመታዘብ መርጧል። ካሪክ ቡድኑን በማረጋጋት ረገድ ውጤታማ ቢሆንም፣  ያለው  የልምድ ማነስ ግን አሁንም እንደ ስጋት ይነሳል። በአሁኑ ወቅት ዩናይትድ በካሪክ ስር እያሳየ ያለው መሻሻል ለደጋፊው ትልቅ ተስፋ ሰጥቷል።

Sport24
2 740
ሸሽኮ ድንቅ አጥቂ እንጂ ድንቅ ተቀያሪ አይደለም። የማንቸስተር ዩናይትዱ አጥቂ ቤንጃሚን ሸሽኮ ወኪል፣ ተጫዋቹ "ድንቅ ተቀያሪ" (Super Sub) ተብሎ መጠራቱን እንደማይደግፍ ተናገረ። ሼሽኮ "ድን
+1
ሸሽኮ ድንቅ አጥቂ እንጂ ድንቅ ተቀያሪ አይደለም። የማንቸስተር ዩናይትዱ አጥቂ ቤንጃሚን ሸሽኮ ወኪል፣ ተጫዋቹ "ድንቅ ተቀያሪ" (Super Sub) ተብሎ መጠራቱን እንደማይደግፍ ተናገረ። ሼሽኮ  "ድንቅ አጥቂ" (Super Striker) ሊባል እንደሚገባው አሳስቧል። የ22 ዓመቱ ስሎቫኪያዊ አጥቂ በዘንድሮ የውድድር ዘመን በፕሪሚየር ሊጉ 10 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል። ወኪሉ ኤልቪስ ባሳኖቪች እንደገለጸው፣ ሸሽኮ ካስቆጠራቸው ጎሎች መካከል ግማሾቹን በቋሚነት ተሰልፎ፣ ቀሪዎቹን ደግሞ ተቀይሮ በመግባት ያስቆጠራቸው ናቸው። ይህም ተጫዋቹ በየትኛውም ሁኔታ ጎል የማስቆጠር ብቃት እንዳለው ያሳያል ብሏል። በጊዜያዊ አሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ለቻምፒዮንስ ሊግ ለማለፍ በሚያደርገው ትግል የሸሽኮ ሚና ከፍተኛ ሆኗል።

Sport24
2 740
የአርሰናሉ ኤበሬቺ ኢዜ በጡንቻ ጉዳት አንድ ወር ከሜዳ እንደሚርቅ ታውቋል። የ27 አመቱ ተጫዋች ይህ ጉዳት የገጠመው ባሳለፍነው ሳምንት ቡድኑ ባየር ሌቨርኩሰንን ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ ሲሆን፥ በዚህም
የአርሰናሉ ኤበሬቺ ኢዜ  በጡንቻ ጉዳት  አንድ ወር ከሜዳ እንደሚርቅ ታውቋል። የ27 አመቱ ተጫዋች ይህ ጉዳት የገጠመው ባሳለፍነው ሳምንት ቡድኑ ባየር ሌቨርኩሰንን ባሸነፈበት ጨዋታ ላይ ሲሆን፥ በዚህም ምክንያት እሁድ እለት በማንቸስተር ሲቲ ለተሸነፉበት የካራባኦ ካፕ ፍፃሜ ሳይሰለፍ ቀርቷል።   የመጀመሪያ ደረጃ ምርመራዎች እንደሚያሳዩት ኢዜ ከአራት እስከ ስድስት ሳምንታት ሊርቅ ይችላል። የተጫዋቹን ትክክለኛ የጉዳት መጠን ለማወቅ በዚህ ሳምንት ተጨማሪ ምርመራ  ይደረግለታል። አርሰናል በፕሪምየር ሊግ፣ በቻምፒዮንስ ሊግ እና በኤፍኤ ካፕ ዋንጫዎችን ለማሸነፍ በሚታገልበት በዚህ ወሳኝ ወቅት የኢዜ መራቅ ለሚኬል አርቴታ ትልቅ ራስ ምታት ሆኗል። የቡድኑ አምበል ማርቲን ኦዴጋርድ ከጉዳት እያገገመ መሆኑ ለቡድኑ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። ኦዴጋርድ ከጉዳቱ ሙሉ በሙሉ ለማገገም ሲል ከኖርዌይ ብሄራዊ ቡድን ውጭ እንደሆነ ይታወቃል። አርሰናል ቀጣይ ጨዋታውን ከዓለም አቀፍ የብሄራዊ ቡድኖች ጨዋታ  በኋላ ሚያዝያ 4  በኤፍኤ ካፕ ሩብ ፍፃሜ ከሳውዝሃምፕተን ጋር የሚያደርግ ይሆናል።

Sport24
2 740
መሀመድ ሳላህ በውድድር አመቱ መጨረሻ ከሊቨርፑል ጋር ይለያያል።
መሀመድ ሳላህ በውድድር አመቱ መጨረሻ ከሊቨርፑል ጋር ይለያያል።

Sport24
2 740
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አምበል የሆነው ጋቶች ፓኖም በወላጅ አባቱ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት ወደ ሞሮኮ ከሚጓዘው ልዑክ ሳይካተት ቀርቷል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አምበል የሆነው ጋቶች ፓኖም በወላጅ አባቱ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት ወደ ሞሮኮ ከሚጓዘው ልዑክ ሳይካተት ቀርቷል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት በጋቶች ፓኖም ወላጅ አባት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለተጫዋቹ እና ለቤተሰቡ መጽናናትን እንመኛለን።