2 742
Subscribers
-224 hours
-117 days
-4830 days
Posts Archive
2 740
ፈርናንዴዝ በዩናይትድ የሮናልዶን ሪከርድ ተጋርቷል።
ሮናልዶ በዩናይትድ ቆይታው 103 ግቦችንና 37 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን በፕሪሚየር ሊጉ አስመዝግቧል።
ብሩኖ ደግሞ 70 ግብና 70 ለግብ የሆኑ ኳሶችን በማስቆጠር ከሮናልዶ እኩል 140 የፕሪሚየር ሊግ ግቦች ላይ ተሳትፏል።
2 740
+3
ማንቸስተር ዩናይትድ ብሬንትፎርድን አሸነፈ።
በኦልድ ትራፎርድ በተደረገው ጨዋታ ዩናይትድ ንቦቹን 2 ለ 1 አሸንፏል። ካስሚሮና ቤንጃሚን ሸሽኮ ለባለሜዳዎቹ ፣ ማቲያስ የንሰን ደግሞ ለብሬንትፎርድ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ብሩኖ ፈርናንዴዝ በአንድ የውድድር አመት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን የማቀበል ሪከርዱን ለመጋራትና ለመስበር ተቃርቧል። ለሸሽኮ ግብ ያመቻቸው ፖርቱጋላዊ ከሜሱት ኦዚል ጋር ያስተካከለውን 19ኛ የግብ ኳስ አስመዝግቧል።
በቀሪ 4 የሊግ ጨዋታዎች 1 ማቀበል ከቻለ በቴሪ ኦንሪና በኬቨን ደብሩይነ የተያዘውን ሪከርድ መጋራት ይችላል። 1 ኳሶችን ካመቻቸ ክብረ ወሰኑን ለብቻው ይይዛል። ብሩኖ በማይክል ካሪክ የአሰልጣኝነት ጊዜ ብቻ በ13 ጨዋታዎች 14 ግቦች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ አድርጓል።
ማንቸስተር ዩናይትድ ነጥቡን ወደ 61 ከፍ በማድረግ የ3ኛ ደረጃውን ያጠናከረ ሲሆን በቀጣዩ ጨዋታ ሊቨርፑልን ካሸነፈ የቻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊ መሆኑን ያረጋግጣል።
2 740
ቸልሲ አሰልጣኝ ሊያም ሮሲናን አሰናበተ።
አሰልጣኙ እስከ 2032 የሚያቆይ ውል ቢኖረውም ከ4 ወር ቆይታ በኋላ ተለያይቷል።
ወጣቱ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን ተክቶ ወደ ስታንፎርድ ብሪጅ መምጣቱ ይታወሳል።
2 740
+2
ሌስተር ሲቲ ከ17 አመታት በኋላ ወደ 3ኛ የሊግ እርከን ወረደ።
ሌስተር ሲቲ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ካነሱ ከአስር ዓመታት በኋላ አስደንጋጭ ውድቀት ውስጥ ገብተዋል።
ትላንት ከሃል ሲቲ ጋር 2 ለ 2 በሆነ ውጤት መለያየታቸውን ተከትሎ "ቀበሮዎቹ" ከአስራ ሰባት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሶስተኛው ዲቪዚዮን ወርደዋል። እ.ኤ.አ. ግንቦት 2 ቀን 2016 በጃሚ ቫርዲ ቤት ተሰብስበው የሊጉን ዋንጫ ማሸነፋቸውን ያከበሩት ሌስተር ሲቲዎች፣ ያ አስደናቂ ታሪክ ከተመዘገ ከ10 ዓመት ሊሞላው 12 ቀናት ሲቀሩት ይህ መራራ ዕጣ ገጥሟቸዋል።
ክለቡ በፋይናንሻል ደንብ ጥሰት ምክንያት የ6 ነጥብ ቅጣት ተጥሎበት የነበረ ሲሆን፣ ይህም በተጫዋቾች ስነ-ልቦና ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
ስፔናዊው አሰልጣኝ ማርቲ ሲፉንቴስ በጥር ወር ቢሰናበቱም፣ ተተኪዎቻቸው አንዲ ኪንግ እና ጋሪ ሮውት ቡድኑን ከውድቀት ሊታደጉት አልቻሉም።
እንደ ንዲዲ እና ማክአቲር ያሉ ቁልፍ ተጫዋቾችን የሸጠው ክለቡ፣ በምትካቸው እንደ አስሚር ቤጎቪች ያሉ ተጫዋቾችን በነፃ ዝውውር ቢያስፈርምም ውጤታማ ሊሆን አልቻለም።
# የሌስተር ሲቲ አስደናቂ ጉዞ
2016፡ በክላውዲዮ ራኒየሪ መሪነት በታሪክ የማይታመን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አሸነፉ።
2021፡ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን በማንሳት በታሪካቸው ትልቅ ስኬት አስመዘገቡ።
2023፡ ከፕሪሚየር ሊግ ወደ ሻምፒዮንሺፕ ወረዱ።
2026፡ ታሪካዊውን ዋንጫ ባነሱ በ10ኛው ዓመታቸው ወደ ሶስተኛው ዲቪዚዮን መውረዳቸው ተረጋገጠ።
ከዚህ ቀደም በሪያድ ማህሬዝ እና ንጎሎ ካንቴ ድንቅ ብቃት አውሮፓን ጭምር ሲያናውጥ የነበረው ክለቡ፣ አሁን ግን በአስቸጋሪ የፋይናንስ እና የውጤት ቀውስ ውስጥ ይገኛል።
2 740
+1
አባትና ልጅ በአል-ናስር የመጀመሪያው ቡድን ሊጫወቱ ነው።
የ16 ዓመቱ ወጣት ክርስቲያኖ ጁኒየር በሳውዲ አረቢያ እያሳየ ያለው ድንቅ ብቃት፣ ከሚቀጥለው የውድድር ዘመን ጀምሮ ወደ ዋናው ቡድን እንዲያድግ መንገድ እየከፈተለት መሆኑ ተሰምቷል።
እንደ ዘገባው ከሆነ፣ በአል-ናስር አካዳሚ ውስጥ የሚገኘው የሮናልዶ ልጅ በክለቡ ባለስልጣናት ከፍተኛ ትኩረት እየተሰጠው ነው። ወጣቱ አጥቂ እያሳየ ባለው ፈጣን እና ተከታታይነት ያለው እድገት ክለቡ እጅግ መደሰቱን ተከትሎ፣ ከሚቀጥለው የውድድር ዘመን ጀምሮ ከዋናው ቡድን ጋር ልምምድ እንዲጀምር ሊደረግ ይችላል።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ጁኒየር በመጪው ሰኔ ወር 16ኛ ዓመቱን የሚይዝ ሲሆን፣ ይህ እድገት በፕሮፌሽናል እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ እጅግ ብርቅዬ የሆነውን ክስተት እውን ሊያደርገው ይችላል። ከአባቱ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ጋር በአንድ ሜዳ ላይ ሲጫወቱ ማየት የብዙ እግር ኳስ ወዳጅ ጉጉት ነው።
አል-ናስር ለወጣቱ ተጫዋች ልዩ የእድገት እቅድ አውጥቶለት የነበረ ቢሆንም፣ ከጠበቁት በላይ በሆነ ፍጥነት እያደገ በመምጣቱ ወደ ዋናው ቡድን የማደጉ ሂደት ሊፋጠን ችሏል።
አባትና ልጅ በአንድ የፕሮፌሽናል ቡድን ውስጥ አብረው የመጫወታቸው ጉዳይ በእግር ኳስ ታሪክ አልፎ አልፎ የሚታይ ክስተት ነው።
ሮናልዶ ቀደም ሲል ልጁ እሱ ገና ሳይለቅ አብሮት የመጫወት ፍላጎት እንዳለው በይፋ መናገሩ ይታወሳል።
አል-ናስር የወጣቱን ተሰጥኦ በአግባቡ ለመያዝ ጥረት እያደረገ ሲሆን፣ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችም የሮናልዶን ትውልድ በአንድ ሜዳ ላይ ለማየት በጉጉት እየጠበቁ ይገኛሉ።
2 740
ቤሊንግሃም የክሪኬት ቡድን የባለቤትነት ድርሻ ገዛ።
የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን እና የሪያል ማድሪድ እግር ኳስ ተጫዋች ጁድ ቤሊንግሃም በርሚንግሃም ፊኒክስ (Birmingham Phoenix) በተባለው የክሪኬት ቡድን ውስጥ የ1.2% ድርሻ ገዛ።
በኤጅባስተን የሚገኘው ይህ ቡድን፣ ባለፈው ዓመት ለሽያጭ ከቀረቡት ስምንት ‘ዘ ሀንድረድ’ ፍራንቻይዞች አንዱ ሲሆን፣ የቤሊንግሃም የቀድሞ ክለብ የበርሚንግሃም ሲቲ ባለቤት የሆነው የአሜሪካው የኢንቨስትመንት ቡድን ናይትሄድ ካፒታል ማኔጅመንት 49% የሚሆነውን ድርሻ በ40 ሚሊዮን ፓውንድ ገዝቷል።
የዋርዊክሻየር ክለብ ደግሞ 51% ድርሻውን እንደያዘ ቆይቷል።
ቤሊንግሃም ከእያንዳንዱ ወገን የ0.6% ድርሻ የወሰደ ሲሆን፣ ይህም ማለት ዋርዊክሻየር አሁንም 50.4% ድርሻ በመያዝ የበላይነቱን ይቆጣጠራል ነው።
ወደ 1 ሚሊዮን ፓውንድ ገደማ ዋጋ ያለው ይህ ስምምነት ዛሬ በይፋ ይረጋገጣል ተብሏል።
የ22 አመቱ ቤሊንግሃም የክሪኬት አድናቂ ሲሆን፣ በዎርሴስተርሻየር በሚገኘው የሀግሌይ ክሪኬት ክለብ ውስጥ በታዳጊነት ተጫውቷል።
ባለፈው ዓመት በነበረው ቃለ ምልልስ "ከየትኛው ስፖርተኛ ጋር ቦታ መለዋወጥ ትፈልጋለህ?” ተብሎ ሲጠየቅ፣ የእንግሊዝ ቴስት ክሪኬት አምበል የሆነውን ቤን ስቶክስን ጠቅሶ ነበር።
ታዋቂው የNFL ተጫዋች ቶም ብራዲ የዚህ የናይትሄድ ኢንቨስትመንት ቡድን አባል መሆኑ ይታወቃል።
2 740
+1
ሊቨርፑል ከ3 ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ተመልሷል። ወጣቱ ንጉሞሃና ሳላህ ባስቆጠሯቸው ግቦች ፉልሃምን 2 ለ 0 ረተዋል።
ንጉሞሃ በፕሪሚየር ሊጉ አንፊልድ ላይ በትንሽ እድሜው ግብ የማስቆጠር ሪከርድን ከራሂም ስተርሊንግ ወስዷል።
2 740
+1
ሀሪ ማጓየር በዩናይትድ ውሉን አራዘመ።
እንግሊዛዊው ተከላካይ እስከ 2027 የሚያቆይና 1 ተጨማሪ አመት አማራጭ ያለው ስምምነት አድርጓል።
