en
Feedback
ራስን መለወጥ

ራስን መለወጥ

Open in Telegram

እንዴት ናችሁ? ቢዝነስ ፕላን(ቢዝነስ ዕቅድ) እንዲሰራለት የሚፈልግ በተመጣጣኝ ዋጋ  ቢዝነስ ፕላን እንሰራለን! በውስጥ መስመር ያናግረን! ለውጥ በትክክልም ይመጣል። 💪ዕድገታችንም ይሳካል!!! Hello everyone, we make best Business plan. In good price contact us inside! just pick a what kind of business plan! We can chang

Show more
9 785
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-8230 days
Posts Archive
photo content

እኛ የሚያስፈልገን🙏 አንድ በውብድና ብዙ ዓመት ያሳለፈና በጣም የሚያስፈራ በትዕቢት የተወጠረ እና ብዙ መሳሪያዎች የታጠቀ ሽፍታ ንስሀ መግባት ይፈልግና ወደ ካህን ዘንድ ይሄዳል። 60 ሰዎችን የገደለ ሽፍታ ሲሆን ወደ አንድ አባት መጥቶ ንስሃ ስጡኝ 60 ሰው ገድያለው አላቸው እሳቸው አንተማ #ሰይጣን ነህ እንዴት እንዲህ ታደርጋለህ ቢሉት እሳቸውንም ገደላቸው ና ሄደ። ወደ ሌላ አባትም በመሄድ "አባቴ ንስሀ ይስጡኝ። 60 ሰው ገድያለው ይህንንም ብዪ የጠየክዋቸው ካህን ሰይጣን ብለውኝ እሳቸውንም ገድያለው "ካህኑም አንተ #አረመኔ እኔንም ልትገድለኝ ነውን?" ቢሉት እሳቸውንም ገደላቸው በዚህ ሁኔታ ሌላ ሁለት ካህናትንም ገድሎ ተስፋ በመቁረጥ ንስሀውንም ባለማግኘት ወደ ለመደው ውንብድናው እየሄደ ሳለ አንድ ሽማግሌ መነኩሴ ውሃ ሊቀዱ እየሄዱ አገኘና አንቱ ሽማግሌ ይቁሙ አላቸው። "አቤት ልጄ" አሉት " 60 ሰዎቹን ገድዪ ንስሃ ልገባ ብጠይቅ አልፈቅድ ብለውኝ 4 ካህናትን ገድያለሁ እርሶንም ንስሃ ማይሰጡኝ ከሆነ እገድሎታለው "አላቸው እሳቸውም ስቅስቅ ብለው አለቀሱለት "በእውነት እግዚአብሄርን በድለሃል አስከፍተሀል እርሱ ግና መሃሪ አምላክ ነው" አሉት፡፡ ከፊት እየመሩ እንዲከተላቸው በመንገር ወደ ጫካ ውስጥ ይዘሁት ገቡ። ከዛም ወደ አንድ ጉድጉዋድ አካባቢ ወሰዱትና "ላንተ እጸልይልህ ዘንድ የጸሎት መጸሃፌ ጠዋት እዚ በዚህ ሳልፍ ወድቆዋልና አውጣልኝ።" አሉት። እሱም ሁኔታቸውን በማየት ገመድ ፈለገና ወደ ጥልቁ ጉድጓድ በገመድ አንጠልጥለው እሳቸው ከላይ ገመዱን ይዘው አስገቡት መግባቱን ሲያረጋግጡ ገመዱን ቆረጡት ወንበዴውም አንተ ሽማግሌ እገድልሃለው እያለ መዛት ጀመረ ካህኑም ጉርጓዱን ከላይ ሸፍነሁት ትተውት ሄዱ። ካሁን በየቀኑ ምግብና ውሃ ሲያመጡለት የያዘውንም ጦር ወደ ካህኑ ይወረውራል። "እገድላለሁ" እያለ እንደሚገላቸው ይዝታል። በሂደት ይዞት የነበረው መሳሪያ ወርውሮ ሁሉንም ጨረሰ። በህልዕና በትዕቢት ብቻ መሳደብ ሆነ ስራው። ካህኑመ "እንዴት ነህ ሲሉት" ሽፍታውም "አለቆትም ከዚህ ልውጣ እንጂ... እገድሎታለሁ።" በሂደት በሌላ ቀን ቆይተው መጡ "ልጄ እንደምን አለህ " ሲሉት "እ..ገ..ድል..ሀለው" አለ እጅግ በደከመ ድምጽ ምግቡን ሰጥተውት ሄዱ፡፡ ትንሽ ቀናት ቆይተው ተመለሱና "ልጄ እንደምን ዋልክ" ሲሉት """እግዚአብሄር ይመስገን""" አለ የሚያመጡትን ምግብ እያረፈዱ ከ 9 ሰአት በውሃል ቂጣ እና ውሃ ይዘው መምጣት ጀመሩ "ልጄ እንዴት ነህ "ሲሉት <እገድልሀለው> ሲል እንዳልነበር ዝምታን መረጠ። ካህኑም ምግቡን ከመፅሀፍ ቅዱስ ጋር ሰጡት። ከዛም ቀስ በቀስ እሱም መፅሀፍ ቅዱሱን ሲያነብ ካህኑም ከ12 ሰአት በውሃላ ተመለሱ "ልጄ እንደምን አለህ " ሲሉት ደከም ባለ ድምጽ ስለመፅሀፍ ቅዱሱን ካነበበው መጠየቅ ጀመረ። እሳቸውም ከላይ ሆነው እሱም ደግሞ ከስር ሲማማሩ ቀኖች እንደቀልድ አለፉ። ትዕቢቱ እና እልህ ቀስ በቀስ በጾም እና በመፅሀፍ ቅዱስ ተሸነፈ፡፡ ነብስ ስጋን አሸነፈች እሳቸውም በገመድ አውጥተው ንስሃን ሰጡት ከዚያ በኋላ የአምላክ ባርያ ሆኖም ኖረ፡፡'' ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ~ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ሁላችንንም ፈጣሪ አምላክ በቸርነቱ ፡ በምህረቱ ይጠብቀን !!!፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡~ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ አሜን!!! ሼር ያድርጉት

photo content

ተማሪዎቿን ለማዳን እሳት ውስጥ ገብታ የተሰዋችው መምህርት በጀግንነት እየተወደሰች ነው። ባንግላዲሻዊቷ የእንግሊዘኛ መምህርት ማሀሪን ቾውድሁሪ በምታስትምርበት ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ አንድ በስልጠና
+2
ተማሪዎቿን ለማዳን እሳት ውስጥ ገብታ የተሰዋችው መምህርት በጀግንነት እየተወደሰች ነው። ባንግላዲሻዊቷ የእንግሊዘኛ መምህርት ማሀሪን ቾውድሁሪ በምታስትምርበት ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ አንድ በስልጠና ላይ ያለ አወሮፕላን ይከሰከስና መማሪያው በእሳት ይያያዛል፡፡ ሁሉም ነፍሱን ለማትረፍ ማቄን ጨርቄን ሳይል ይፈርጥጣል፡፡ ማሀሪን ግን የለበሰችው ጨርቅ በእሳት መያያዙን እንኳን ልብ የምትልበት ቀልብ አልነበራም፡፡ “እባክሽ ነፍስሽን አትርፊ “ ሲል ባለቤቷ ይማጸናታል፡፡ ወትሮም ተማሪዎቿን እንደ ልጆቿ የሞትመላከተው ጀግናዋ መምህርት መልሷ ”ተማሪያቹ እኮ ለእኔም ልጆቼ ናቸው ።እየነደዱ እንዴት ብየ ልጭክንባቸው ?” የሚል ነበር። ዘላ ወደ ሚንቀለቀለው እሳት እየገባች የበርካታ ልጆችን ህይወት ብትታደግም እርሷ ግን አልተረፈችም። የትምህርት ቤቱ ርዕሰ -መምህርት ኸድጀ እንዲህ አለች፦ "ማሀሪን የሚጨክን ልብ አልነበራትም፡፡ የሃያ ህጻናትን ህይዎት ታድጋ፤ እሧ የተማሪዎቿን ሞት ሞተች ፡፡” FM Addis 97.1 t.me/changeitwow

#እውነተኛ ታሪክ አንድ ልጅ በየቀኑ ጋዜጦችን ለአንድ ቤት ያደርስ ነበር ፤  አንድ ቀን ግን የደብዳቤ ሳጥናቸው መዘጋቱን አስተዋለ። የደብዳቤ ሳጥኑን የዘጉትን ሰው ቤት በሩን አንኳኳ። አንድ አዛውንት በእርጋታ በሩን ከፈቱ። ልጁም፣ “አለቃ  የደብዳቤ ሳጥኖትን ለምን ዘጉት ?” ሲል ጠየቃቸው። ሰውየውም “ሆን ብዬ ነው የዘጋሁት” ሲሉ መለሱ። ፈገግ ብለው ፣ “ጋዜጣውን በየቀኑ ቤቴ ድረስ አምጥተህ፣ ደውሉን ደውለህ ወይም በሩን አንኳኳ በእጄ እንድትሰጠኝ እፈልጋለሁ” አለ። ልጁ ተገርሞ፣ “ያ ለሁለታችንም አይመችም? ጊዜ ያጠፋል” አላቸው ። ሰውየውም፣ “ጥሩ ፤ በሩን ለማንኳኳት በየወሩ ተጨማሪ ክፍያ እከፍልሃለሁ” ሲሉ መለሱ ። ከዚያም አዛውንቱ ቀጥለው ፣ “መቼም በሩን ስታንኳኳና ምላሽ ካጣህ እባክህን ለፖሊስ አሳውቅ ” አሉ ። ወጣቱ የጋዜጣው አከፋፋይ የአዛውንቱን ጥያቄ ሲሰማ በጣም ተገረመና “ለምን ጌታዬ?” ሲል ጠየቀ። ሰውየውም “ሚስቴ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፣ ልጄ ውጭ አገር ነው፣ እና እዚህ ብቻዬን ነው የምኖረው ፤  ጊዜዬ መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል?” ሲሉ መለሱ ። በዚያን ጊዜ ወጣቱ ጋዜጣ አከፋፋይ በአዛውንቱ አይኖች ውስጥ የእንባ እና የሐዘን ብልጭታ አየ። ሰውዬው ቀጠለ አደረጉና ፣ “ጋዜጣውን እንኳን አላነብም። በሩ ሲንኳኳ ወይም ደወሉ ሲጮህ መስማት እንድችል፣ የለመድኩትን ፊት ለማየት እና ጥቂት የደስታ ጊዜያት እንዲሰማኝ ያህል ነው ።" አዛውንቲ እጃቸውን እያጣጠፉ ፣ “ልጄ፣ እባክህ ውለታ አድርግልኝ፣ ይህ የልጄ ቁጥር ነው፤ ውጭ አገር ነው። አንድ ቀን በሩን ስታንኳኳ ካልከፈትኩኝ፣ እባክህ ለልጄ አሳውቀው” አሉ። ይሄን ልብ የሚነካ ታሪክ ስንመለከተው ሰዎች በእኛ ህይወት ውስጥ ያላቸውን ሚና ነው። እኛ ሰዎች በጋራ መኖርን የለመድን ነን። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በተለያየ ጊዜ በዋትሳፕ ፣ በቴሌግራም ፣ በ SMS በሜሴንጀር.  .  . ለምን  መልእክት እንደሚልኩልን እንጠይቅ ይሆናል። እንደ እውነቱ ከሆነ ሰላምታ ልክ እንደ በር ማንኳኳት ነው ።  አንዱ የሌላውን ደህንነት ለመፈተሽ እና ፍቅርን ለመግለጽ ያለመ ይሆናልና አንጥላው ። ለኛ ቦታ ያላቸው ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉና ። Via በታሪኩ ዘውዱ(ማህበራዊ ሚዲያ) ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

photo content

እንደወረደ‼️‼️‼️ ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴና ባለሀብቱ ኢ/ር ቢጃይ ናይከር ዐይን‼️ ቆይታ ከጀግናው አትሌት በኢ/ር ቢጃይ እንዲህ ተፅፏል✍️ ጭዌ.... ሜላት ሃይሌ ገ/ሥላሤ (የሃይሌ ልጅ) እና Abayomi Rotimi Mighty (ናይጄሪያዊ ጸሐፊ) 'Dissecting Haile ' የሚል አሪፍ መጽሐፍ ጽፈዋል። በሃይሌ ህይወት፣ሥራ፣ተሞክሮ ወዘተ ዙሪያ በደንብ ተከትቧል። በርግጥ ሃይሌ ተገልጦ የማያልቅ የህይወት ዘመን ተሞክሮዎች አሉት። ጥዋት ባለቤቱን ደርባባዋን ወ/ሮ አለም ተቻለንና ሁለቱን ሤቶች ልጆቹን በሚደንቅ ቅልጥፍናው ቤሮዬ ይዞ ከች አላለም ? አወጋን... ተጫወትን።ቴክኖሎጂ ይመሥጠዋል።አብሮ የመሥራት ኦፈሮችም አሉት። "ሃይሌ እሥቲ የሥራ መርሆዎችህን ንገረኝ? ጀማው ይከየፍ፣ ይነሣሣ፣ጭማቂ ተሞክሮ ያግኝበት፣በት በት፣ተፍ ፣ተፍ ይቅዳበት" አልኩት። "ዌል እንግዲህ"...አለ ከጭላሎ ተራራ ጀርባ እንደወጣች ጸሃይ በደመቀው ፍጹም ፈገግታ ታጅቦ። " 1- በል...Discipline and Hard Work ያሥፈልጋል ግብረገብነት እና ትጋት ማለት ነው ።“Business is like running. You have to train every day.” ሁሌ ሠልጥን እራሥህን አብቃ። 2-በል ...Start Small, Grow Steadily ያሥፈልጋል በትንሹ ጀምር ቀሥ ብለህ እደግ “I started with one building, now I have many.”ይገርምሃል። 3-በል...Invest in Ethiopia ሃገሬን በሥራ ማሣደግ እፈልጋለሁ“I want to change Ethiopia through business, not just charity.” 4-በል...Respect for Workers and Community ያሥፈልጋል... ሠራተኞችህን እና የአካባቢህን ማህበረሠብ አክብር “My workers are part of my team, like in running.” 5-በል...Learn from Others ከሌሎች መማር ጥሩ ነው። “I travel, I watch, I learn.” 6-በል...Staying Humble and Authentic ጨዋ እና ሃቀኛ ሁን።ሁሌም መርሆ ይሁኑህ። 7-በል...Diversification ያሥፈልጋል በተለያዩ ሃገርን በሚጠቅምና በሚያዋጣ ሥራዎች ውሥጥ ተሠማራ።ሆቴል፣ሪዞርት፣ቡና፣ት/ቤት፣ሥፖርት መዓከል፣ሪል እሥቴት፣ግብርና፣መአድን፣ ወዘተ ውሥጥ በመግባት ሪሥክንም መቀነሥ ይሆናል። 8-በል...Avoid Corruption and Stay Honest ሥርቆትን ተጸየፍ በአቋምህ ጽና ። በነጻ አእምሮ ተወዳደር።አቅምህ እሡ ነውና። 9.እንደአለም ጠንካራ ሚሥት ይኑርህ፣እንደነሜላት የተባረኩ የተመረቁ ልጆች ፈጣሪ ይህጥህ። " ይህን ያለው ጀግናው ሃይሌ ገ/ሥላሤ ነው። መጽሃፉ በተለያዩ ቋንቋዎች እየተተረጎመ ነው። አንብቡት ብዙ አሪፍ አሪፍ ጉዳዮችን ይዟል። እኔ ደግሞ እላችኋለሁ.... "you can't build a business ,until you've built your self" ...self discovery is important ።እራሥህን አግኝ።ራሥህን አብቃ። በርቱ! Via:- Bejai Nerash Naiker t.me/changeitwow

photo content

👉በአሜሪካ ውስጥ የሚኖረው ህንዳዊዉ የስራ አመራር ሳይንስ፤ የስነ ልቦና እና የስራ ዕድል ፈጠራ ምሁር ሽፍ ሼራ #You_Can_Win በሚል ሞራለ ገንቢ መፅሃፋቸዉ እንዳብራሩት፡- በአውሮፓዊያኖች አቆጣጠር በ1920ዎቹ አመተ ምህረት አካባቢ በመላዉ የሰሜን አሜሪካ አህጉር ቁጥር አንድ ባለፀጋ የነበረ Andrew Carnegie የሚባል ስኮትሽ አሜሪካዊ ሰዉ ነበር፡፡ ይሄንን ባለ ፀጋ ሰዉ ከልምዱ ለአለም ህዝብ ሀእንድያካፍል ዘንድ አንድ ታዋቂ ጋዜጠኛ ቃለመጠይቅ ያደርግለታል፡፡ በዚህ ቃለመጠይቅ “አንተ የአህጉራችን ቁጥር አንድ ባለፀጋ ነህ! ካንተ ቀጥለዉ 45 ያንተ ሰራተኞች ደግሞ በተዋረድ ሀብታሞች ናቸዉና ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? ያንተ የህይወት መመሪያስ ምንድን ነዉ?” ይለዋል፡፡ ባለጠጋዉ Andrew Carnegie ሲመልስ፡- "እኔ አንድን ሰዉ ባየሁ ጊዜ ሰዉየዉ ነጭ ይሁን ጥቁር አሊያም ቻይናዊ፤ ያለ ቀለምና ሃይማኖት ልዩነት ሰዉ ስለ ሆነ ብቻ አከብረዋለሁ፡፡ ማንኛዉም ሰዉ የሰዉነት ክራቴሪያ አማልቶ ወደዚህች ምድር ፈጣሪ ሲልከዉ ለዚህች ምድር ይዞ የመጣዉ በረከት እንዳለ አምናለሁ፡፡" "በመሆኑም እያንዳንዱን ሰዉ በማገኝበት ጊዜ ያ ሰዉ ለዚህች ምድራችን ይዞ የመጣዉ የሱ ብቻ የሆኔ የፈጣሪ ስጦታ ምን እንደሆኔ እመረምራለሁ፡፡ በመሆኑም ሰዉየዉን በማክበር በታላቅ ትህትና እና ጥሞና አዳምጠዋለሁ፡፡ " "አንድን ሰዉ በማነጋግርበት ወቅት ደግሞ ለአእምሮዬ የሚነግረዉ ነገር አሁን እኔ የወርቅ ማዕድን እየቆፈርኩ ነዉ ብዬ ነዉ፡፡ ታዲያ የወርቅ ማዕድን የሚቆፍር ሰዉ ደግሞ ብዙ ቆሻሻ አፈር ማስወገድ አለበት፡፡ ታዲያ ግን  ሰዉየዉ የሚያስወግደዉ ቆሻሻ ላይ ሳይሆን በሚያገኘዉ ወርቅ ማዕድን ላይ ማተኮር አለበት፡፡ እኔም የዚያ ሰዉ አመሉ አይገርመኝም!! እኔ የሚፈልገዉ አመሉን ሳይሆን ሰዉየዉ ከፈጣሪ ለዚህች ምድር ይዞ የመጣዉን በረከት ብቻ ነዉ፡፡ "የኔ ወርቅ እሱ ነዉ፡፡ የሰዉየዉ ስጦታ፡፡ ልክ የሰዉየዉን ስጦታ እንዳገኘሁ ወዲያዉኑ ለሰዉየዉ የሚያስፈልገዉን ማንኛዉም ነገር አማልቼ ሰዉየዉ ዉጠታማ እንድሆን በማድረግ ከፈጣሪ ይዞልን የመጣዉን በረከት ለምድራችን እንዲያበረክት አደርገዋለሁ፡፡ ይሄንን ሳደርግ ሀገሬ ትጠቀማለች! ሰዉየዉም ይጠቀማል!! እኔም እጠቀማለሁ!! ፈጣሪም በዚህ ደስ ይለዋል፡፡ አሁን አንተ የሚታየዉ የኔ ሀብት በጠቅላላ በዚህ መልኩ የተገኘ ነዉ፡፡ 45 የኔ ሰራተኛ የሆኑትና ከኔ ቀጥለዉ በተዋረድ ሃብታም የሆኑት ሰዎች ደግሞ እኔ ስጦታቸዉን ሥራ ላይ እዲያዉሉ አግዠያቸዉ በስጦታቸዉ የከበሩ ሰዎች ናቸዉ፡፡ ብሎ ለጋዜጠኛዉ መለሰለት፡፡ ወደ ምድራችን ሲመጣ የራሱን ስጦታ ከፈጣሪ የሚበረከትለት የሰዉ ልጅ ብቻ አይደለም!! እያንዳንዱ ሀገር ከፈጣሪዉ የተሰጠዉ በረከት አለዉ፡፡ ከማህበራዊ ትስስር የተገኘ ከትንሽ ማሻሻያ ጋር ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

photo content

አንድ አባት የ11 ዓመት ልጁ በዝምታ ሲያለቅስ አየው። ጠየቀውም። "ምነው ልጄ ምን ሆንክ?" ታዳጊው ልጅ መለሰ። "ሀብታም የክፍል ጓደኞቼ አሾፉብኝ፣ 'የአትክልተኛ ልጅ' ብለው ሰደቡኝ። አባትህ የሚኖረው ለሰዎች ተክሎችን በማጠጣትና በመንከባከብ በሚያገኘው ገንዘብ ብቻ ነው አሉኝ።" አባትየው ለአፍታ ዝም አለና ከዚያ እንዲህ አለው። "ና ልጄ፣ ጥቂት አበባዎችን እንትከል፤ ምናልባት ስሜትህን ሊያሻሽል ይችላል።" እጁን ይዞት ወደ አትክልት ስፍራው ወሰደው፣ ከዚያም ጥቂት የአበባ ዘሮችን አውጥቶ እንዲህ አለ። "አንድ ሙከራ እናድርግ። ሁለት አበባዎችን ለየብቻ እንተክላለን። አንዱን እኔ እንከባከበዋለሁ፣ ሌላኛውን አንተ ትከባከበዋለህ። እኔ የኔን ከሀይቁ በንፁህ ውሃ አጠጣዋለሁ፣ አንተ ግን ያንተን ከኩሬው በቆሸሸ ውሃ ታጠጣዋለህ። በቀጣዮቹ ሳምንታት ውጤቱን እናያለን።" ልጁ ከአባቱ ጋር አበባዎቹን በመትከሉ ተደስቶ ነበር። የአበባው ዘሮች ለመብቀል ጥቂት ቀናት ፈጅቶባቸዋል። በየፊናቸው እየተንከባከቧቸው ሲያድጉ ተመለከቱ። ከጊዜ በኋላ አባትየው ልጁን ወደ አትክልት ስፍራው አምጥቶ እንዲህ አለው። "ሁለቱን አበባዎች ተመልከትና ምልከታህን ንገረኝ።" ልጁም መለሰ። "የኔ አበባ ካንተ የበለጠ ጤናማና የተሻለ ይመስላል። ያንተ ውሃ የበለጠ ንፁህ ሆኖ ሳለ እንዴት ይህ ሊሆን ቻለ?" አባትየው ፈገግ አለና እንዲህ አለ። "ይህ የሆነው የቆሸሸ ውሃ ተክሉ እንዳያድግ ስለማያደርግ ነው፤ ይልቁንም እንዲያብብ እንደ ኦርጋኒክ ማዳበሪያ ሆኖ ያገለግለዋል። አየህ ልጄ፣ በህይወት ውስጥ ዝቅ የሚያደርጉህ፣ በህልሞችህ የሚያሾፉብህ እና ጭቃ የሚለቀልቁብህ አንዳንድ ሰዎች አሉ። ሁልጊዜም አስታውስ፣ በአንተ ላይ ምንም ችግር የለም፤ እነሱ ናቸው ችግር ያለባቸው ፤ የራሳቸው ትእቢት (ego) ያስቸገራቸው። ስለዚህ፣ የሰዎች ክፉ ቃላት እንዲጎዱህ አትፍቀድ፤ ይልቁንስ የተሻለ ሰው እንድትሆን ያበረታቱህ። ይህን በማድረግህ እንደ ተክሉ ትሆናለህ፤ እንደ አሉታዊነትና ክፉ ቃላት ባሉ ጭቃ ውስጥም እንኳ ታብባለህ።" ✍️ እወዳችኋለሁ ሶሻል ሚዲያ ራስን መለወጥ @follwer #follower

photo content

ጆሮውን ሰጥተ ስማ... የሆነ ትምህርት ታገኝበታለህ...! አንድ ጠበቃ የውሃ ጉድጓዱን ለመምህር ሸጠለት። ከሁለት ቀን በኋላ ጠበቃው ወደ መምህሩ መጥቶ እንዲህ አለው፡ "ጌታዬ፣ ጉድጓዱን ሸጥኩልህ እ
ጆሮውን ሰጥተ ስማ... የሆነ ትምህርት ታገኝበታለህ...! አንድ ጠበቃ የውሃ ጉድጓዱን ለመምህር ሸጠለት። ከሁለት ቀን በኋላ ጠበቃው ወደ መምህሩ መጥቶ እንዲህ አለው፡ "ጌታዬ፣ ጉድጓዱን ሸጥኩልህ እንጂ በውስጡ ያለውን ውሃ አልሸጥኩልህም! ውሃውን መጠቀም ከፈለግክ ተጨማሪ መክፈል አለብህ።" መምህሩ ፈገግ አለና እንዲህ ሲል መለሰ፡ "አዎ፣ እኔም ወደ አንተ ልመጣ ነበር። ልልህ የነበረው ውሃህን ከእኔ ጉድጓድ ውስጥ እንድታወጣ ነው፣ አለበለዚያ ከነገ ጀምሮ ኪራይ መክፈል ትጀምራለህ።" ይህን ሲሰማ ጠበቃው ተደናግጦ "ኦ! ዝም ብዬ እየቀለድኩ ነበር!" አለዉ። መምህሩ እየሳቀ "እንደ አንተ ያሉ ሰዎች እኮ ከእኛ ዘንድ ተምረው ነው ጠበቃ የሚሆኑት!" አለው። ይባላል።😜 ምንጭ_ሶሻል ሚዲያ @follower ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሰን። በዓሉ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት የድንግል ማርያም ልጅ ያድርግልን‼️ በእውነትም ተነስቷል✝️
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሰን። በዓሉ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት የድንግል ማርያም ልጅ ያድርግልን‼️ በእውነትም ተነስቷል✝️

እንግሊዛዊው ማይክል ካሮል ህይወትን ለማሸነፍ ፡ የሚረዳውን ስራ ሲፈልግ ፡ ሲወጣ ፡ ሲወርድ ቆየ ። ግን ለሱ የሚሆን ስራ የለም ። ለሱ የሚሆን ስራ ያለው አንድ ቦታ ብቻ ነው ። የእንግሊዝ መዘጋጃ ቤት ። እና የሎንዶን ከተማ ፡ መዘጋጃ ቤት. . የፅዳት ሰራተኞች እንደሚፈልግ ያወጣውን ክፍት የስራ ቦታ አይቶ ሄዶ ተመዘገበ ። ከቀናት በኋላም ተቀጠረ ። .............. ማይክል ይህንን ስራ በመስራት ላይ እያለ ፡ አንድ ቀን ካገኛት ገንዘብ ላይ ቆጥቦ ሎተሪ ቆረጠ ። ፈጣሪ በ19 አመትህ የለንደን ከተማ ፅዳት ሰራተኛ ሆነህ አትቅር ሲለው ፡ የቆረጠው ሎተሪ ደርሶት. .. የ18 .4 ሚሊዮን ዶላር አሸናፊ ሆነ ። ............. ማይክል ካሮል ፡ ከፅዳት ሰራተኝነት ፡ በአንድ ጊዜ ሚሊየነር ሆነ ። ህይወት ሳቀችለት ። ቤት ገዛ ፡ መኪኖች ኖሩት ። ከዚያን እለት ጀምሮም ፡ ስራ የሚባል ነገር አለርጂኩ ሆነ ። ጠዋት ይነሳል ፡ ሲጠጣ ይውላል ፡ ከብዙ ሴቶች ጋር መዋል ፡ ድራግ መጠቀም ጀመረ ። አኗኗሩ ቅጥ አጣ ። ................. በተለያዩ ወንጀሎች እየተከሰሰ ፡ ፍርድ ቤት መቅረብ ስራው ሆነ ። በዚህም ከሰላሳ ያላነሱ ጊዜያት በተለያዩ ትናንሽ ወንጀሎች ተከሶ ፍርድ ቤት እየቀረበ. .. ፡ በገንዘብ እና በቀላል እስር ይቀጣ ነበር ። ማይክል የአልኮል ሱሰኝነቱ ከመብዛቱ የተነሳ በቀን ፡ ሁለት ጠርሙስ ቮድካ ይጠጣ ነበር ። ............ በአንድ ወቅት የለንደን ከተማ ፅዳት ሰራተኛ ሆኖ  ድህነትን እንዳላጣጣማት ያሳለፈውን መጥፎ ጊዜ ረስቶ ፡ 24/7 ገንዘቡን መርጨቱን ቀጠለበት ። ..... በዚህ ሁኔታ ጥቂት አመታት ካለፉና ፡ በእጁ የነበረው ገንዘብ እንዳልነበር ሆኖ ፡  ቤት ፡ መኪና ፡ ንብረቱን  ሁሉ ከሸጠ በኋላ ማይክል ስራ መስራት እንዳለበት አሰበ ። ለአመታት ስራ የሚባል ነገር ትቶ መኖሩ ቆጨው ። እና አንድ ቀን ጠዋት ተነስቶ ወደ አንድ ቢሮ ሄዶ አንኳኳ ...... ሃላፊው እንዲገባ ፈቀዱለት እንዴት ኖት አላቸው ። ሰውየው ምቾት የለወጠውን ማይክልን በቶሎ ማስታወስ አልቻሉም ። ....... እርግጥ ነው ጊዜው ስለቆየ ረስተውኝ ይሆናል ። እኔ ማይክል ካሮል እባላለሁ ። ከአመታት በፊት እናንተ ጋር እሰራ ነበር ። ሰውየው አላስታወሱትም ። ምን  ነበር የምትሰራው ብለው ጠየቁት ፅዳት ሰራተኛ ነበርኩ ሰውየው ትዝ አላቸው ፡ ጥቂት ካወሩት በኋላ እና አሁን ምን ልርዳህ አሉት የበፊት ስራዬን ፡ ለመጀመር ማለት . .. የከተማ ፅዳት ሰራተኛ ፡  ከፈለጋችሁ ................ ......... ሰውየው ማይክልን ቀጠሩት ። ( እና ግን  በዛ ቅፅበት ሰውየው  በልባቸው " from hero to zero ? " ብለው ይሆናል ) .......... አሁን በለንደን ጎዳና ላይ ፡ አንድ ወፍራም ሰውዬ. ..  የፅዳት ስራ ሲሰራ ካያችሁት ፡ ያ ሰው ፡ በአንድ ወቅት ሚሊየነር የነበረውና ፡ ህይወት  የሰጠችውን እድል ሊጠቀምበት ባለመቻሉ ፡ ተመልሶ ፅዳት ሰራተኛ የሆነው ማይክል ካሮል እንደሆነ እወቁ ። ..... የተሰጠንን እድል በአግባቡ እንጠቀምበት ለማለት ያህል ወዲህ አመጣነው ። t.me/changeitwow

photo content

የ55 አመቱ ሊዊስ ሄርናዴዝ በደቡብ ስፔን አንድ ታዋቂ ምግብ ቤት ነበረው።ለብዙ አመታት የአገሩ ሰው እና ቱሪስቶች ይጎበኙታል፣ጥሩ ገበያም ነበረው። ከግዜ በኋላ ምግብ ቤቱ ተወዳዳሪ ባለመሆን ደንበኞች አጥቶ ኪሳራ ደርሶበት ምግብ ቤቱ ይዘጋል። ሊዊስ ምግብ ቤቱን ዘግቶ ያለስራ ተስፋ ቆርጦ ቤቱ ቁጭ ይላል። ሊዊስ ከስንት ግዜ በኋላ በአንድ ዝናባማ ምሽት ወደ ምግብ ቤቱ ሲሄድ፤ ቶማስ የሚባል በኑሮ ተስፋ የቆረጠ ሰው ህፃን ልጁን አቅፎ በምግብ ቤቱ በረዳ ላይ ከዝናብ ተጠልሎ፣ በብርድ እየተንቀጠ ይመለከተዋል። ሊዊስ ልጅ አቅፎ በረዳው ላይ ቁጭ ያለውን ቶማስን እዚህ ምን ታደርጋለህ በማለት ይጠይቀዋል ። ቶማስም " ስራዬን፣ ቤቴን እና ሚስቴን አጥቻለሁ እዚህ ከዝናብ ለመጠለል ነው ቁጭ ያልኩት" በማለት ይመልስለታል ። ምንም እንኳን ሊዊስ እራሱ ችግር ውስጥ ቢሆንም ዝም ብሎ ሊያልፈው አልፈለገምና ከዚህ የተሻለ መጠለያ እስከ እምታገኝ ድርስ በማለት በምግብ ቤቱ የምግብ ማብሰያ ኩሽና ውስጥ ከህፃኑ ልጅ ጋር እንዲኖር ፈቀደለት። ቶማስም ሊዊስን አመስግኖ በኩሽና ውስጥ ከልጁ ጋር መኖር ጀመረ። አንድ ምሽት ሊዊስ ምግብ ቤቱን ለማየት ጎራ ሲል ቶማስ ቀን ሲለምን በዋለው ገንዘብ እራት ሲያበስል ይመለከተዋል። ሊዊስ ቶማስ እያዘጋጀ ያለው የምግብ ሽታ ማእዛው ማራኪ እንደሆነ አስተዋለ ፣ የምግብ አዘገጃጀቱም ባለሙያ እንደሆነ ተመለከተ ምግብ ከተዘጋጀ በኋላም ምግቡን ሲቀምሰው በጣም ጣፋጭ ሆኖ አገኘው ። ቶማስ በትልልቅ ሆቴል የሚሰራ የተማረ የምግብ አዘጋጅ (ሼፍ) እንደሆነና በደረሰበት ችግር ስራውንም እንደማይሰራ ለሊዊስ ይነግረዋል ። የከሰረው የምግብ ቤት ባለቤት ሊዊስ ቶማስ ትልቅና ድብቅ የምግብ የማዘጋጀት ችሎታ እንዳለው ተረዳ። ለቶማስ አብረው እንዲሰሩ ሀሳብ አቀረበለት፤ቶማስም በሃሳቡ ተስማማ። ሊዊስ ገንዘብ በመበደር ከቶማስ ጋር እንደገና ምግብ ቤቱን ከፈተ። ቶማስ ምርጥ ሼፍ በመሆኑ ምግብ ቤቱ በደንበኞች ተጨናነቀ፣ የምግብ ቤቱ ቀድሞ ስም ዳግም ተመለሰ ። ምግብ ቤቱ ትርፋማ በመሆኑ ቶማስ ከልመና ስራ ወጥቶ ልጁን በእንክብካቤ ማሳደግ ጀመረ፤ ሊዊስ ተስፋው ለመለመ ፤ሁለቱም በህይወታቸው ስኬታማ ሆኑ። (90's History) ከአዳነ ካሳሁን ተፃፈ t.me/changeitwow

photo content

photo content