en
Feedback
ራስን መለወጥ

ራስን መለወጥ

Open in Telegram

እንዴት ናችሁ? ቢዝነስ ፕላን(ቢዝነስ ዕቅድ) እንዲሰራለት የሚፈልግ በተመጣጣኝ ዋጋ  ቢዝነስ ፕላን እንሰራለን! በውስጥ መስመር ያናግረን! ለውጥ በትክክልም ይመጣል። 💪ዕድገታችንም ይሳካል!!! Hello everyone, we make best Business plan. In good price contact us inside! just pick a what kind of business plan! We can chang

Show more
9 785
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-8230 days
Posts Archive
"እንዳትመራመረኝ በጥቂት ነገር ማረኝ "ታክሲ ውስጥ ገብቼ እንደተቀመጥኩ አጠገቤ ካለች ልጅ ስልክ የወጣ ድምፅ ነው።መዝሙር ካደመጥኩ ረጅም አመት ሆኖኛል።ድሮ በልጅነቴ የማውቃቸውም ጠፍተውኛል።ዛሬ ግን ድንገት በጆሮዬ ሽው ያለው መመዝሙር ምናል ባላለቀ እስክል ቀልቤን ስቦኛል።ልጅቷም እስክሪኗ ላይ እንደተተከለች ናት።መጀመርያ ያየሁት እስከባቷ ድረስ ያለ እርቃኗን ነበር።ትንሽ ቀና ስል ጥቁር ቀሚስ ለወጉ ጣል ያደረገች ናት።ከዛ በላይ ቀና ብዬ ላያት ፈራሁ ...መዝሙሩ ከቲክቶክ ላይ እየዘመረ መሆኑ የገባኝ ሲደጋገም ነበር። መኪናዋ ልትሄድ ስትል የሞት ሞቴን ቀና እንዳልኩ መጀመርያ እንባ ከሚያፈሰው አይኗ ጋ ተገጣጠምኩ።አፊንጫዋ ላይ ትልቅ ቀለበት ተንጠልጥሏል። ሽፋሽፍቷ ላይ ያለው ቀለም እንደ ጥቁር ወንዝ እየፈሰሰ በሊፕስቲክ የቀላ ከንፈሯን አርጥቦታል።ደረቷ ተራቁቶ እርቃኗ ይታያል።አሁንም አሁንም መላልሶ መዝሙሩ ይዘምራል..... እንዳትመራመረኝ በጥቂት ነገር ማረኝ ይላል "ጥቂት ነገር"ምን ይሆን ብዬ መለስ ስል እራሴን ጠየቅኩት።ፈጣሪ እንደው በጥቂት ነገር ማረኝ ብለው እንኳ ጥቂት ነገሬ ምን ይሆን??ለመሀላ እንኳ ስሙን ጠርቼ አላቅም።ደጁን ረግጩ አላቅም።ፆሜ ፀልዬ መፅውቼ አላቅም።ታድያ የኔ ጥቂት ነገር ምን ይሆን???እያልኩ እያሰላሰልኩ ያቺ ሴት "ወራጅ "አለች። ድምጿ በሲቃ ብዛት ይቆራረጣል።ዝም ብዬ እስክትወርድ በአይኔ ተከተልኳት።መዝሙሩ አላቆመም እሷም ማልቀሷን አልተወችም።ታክሲዋ በቆመችበት ጥላት ልትሄድ ስትል ግን እኔም ድንገት ወራጅ አልኩኝ።የሴቲቱን መጨረሻ ለማየት እንጂ መውረጃዬ አልነበረም።እንደወረድኩ መንገድ ስትሻገር አይቼ ተከተልኳት።የስድስት ኪሎን አደባባይ ተሻግራ ትንሽ እንደተራመደች ማርቆስ ቤተክርስትያን ጋ ስትደርስ በሩ ላይ ሂዳ ወደቀች......ለመጀመርያ ጊዜ እኔም እራሴን ቤተክርስትያን በር ፊት አገኘሁት።ቅድም በመዝሙሩ ስሰማው የነበረውን ጥቂቱን ነገር እየመራ ሲያስደርሰኝ ቤቱን ሲያስረግጠኝ አምላኬን አየሁት።ጥቂቱን ነገር እንዳረግ ከረዳኝ እኔ ደሞ እንደሴቲቱ ተንበርክኬ ድምፄን እያንሾካሾክኩ ቶሎ ቶሎ ማረኝ ማረኝ ማረኝ አልኩት።እድሜ ዘመኔን ቋጥሬ ያኖርኩት እንባዬን በፊቱ አፈሰስኩት።ለካ ናፍቆኝ ነበር??? "እንዳትመራመረመኝ በጥቂት ነገር ማረኝ" ጥቂት ነገሬ ምን ይሆን???በምን ትምረኝ ይሆን??

photo content

💚ከስደት ወደ ወደ እንስሳ ማደለብ የገባቸው ና ትርፋማ የሆነችው ወጣት‼️ ከስደት ተመላሽዋ ሞሚና ጀማል በሚሊዮኖች የሚቆጠር ትርፍ ያስገኘላት የእንስሳት እርባታ ኢንቨስትመንት ሞሚና ጀማል በሳውዲ
💚ከስደት ወደ ወደ እንስሳ ማደለብ የገባቸው ና ትርፋማ የሆነችው ወጣት‼️ ከስደት ተመላሽዋ ሞሚና ጀማል በሚሊዮኖች የሚቆጠር ትርፍ ያስገኘላት የእንስሳት እርባታ ኢንቨስትመንት ሞሚና ጀማል በሳውዲ በስደት በምትኖርበት ወቅት በአሰሪዎቿ ዘንድ የተመለከተችውን የእንስሳት እርባታ ሥራ ወደ ሀገሯ ስትመለስ ለመተግበር አቅዳ ነበር። ይህንንም ዕቅዷን እውን አድርጋለች። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ ቤንች ሸኮ ዞን፣ ጉራ ፈርዳ ወረዳ የእንስሳት ማድለብ እና የወተት ላሞችን በማርባት ሥራዋን የጀመረችው ሞሚና፣ ብዙም ሳይቆይ በስኬት ጎዳና ላይ ለመጓዝ በቅታለች። ከእንስሳት እርባታው ጎን ለጎን የእንስሳት ተዋጽኦ መሸጫ ሱቅ በመክፈት የንግድ ሥራዋን ማስፋት የቻለችው ሞሚና፣ ከወተት ላሞቿ በተጨማሪ ንብ በማነብ፣ በጎችን፣ ፍየሎችን እና ዶሮዎችን በማርባትም ሥራዎቿን አዘምነዋለች። ሞሚና ከስደት ያመጣችውን ገንዘብ በአግባቡ በመጠቀም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ትርፍ ማግኘቷን ትናገራለች። ስኬታማዋ ኢንቨስተር ከራሷ አልፋ ለአካባቢዋ ሰዎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር የበኩሏን አስተዋጽኦ እያበረከተች ትገኛለች። የእርሷ ታሪክ ለሌሎችም ስደተኞች ጥሩ አርዓያ መሆኑንም ገልጻለች። እናንተስ ከስደት ስትመለሱ ምን ለመስራት አስባችዋል:: አስተያየታችሁን አካፍሉን via ጉርሻ ፔጅ

የሚገርም አጋጣሚ t.me/changeitwow
የሚገርም አጋጣሚ t.me/changeitwow

#ባለፀጋነት (ምርጥ አጭር ታሪክ) አንዲት ትንሽዬ ልጅ ናት… የምትኖረው ትንሽዬ ከተማ ውስጥ ሲሆን ስሟ አበባ ነው፡፡ ዕድሜዋ ሰባት አካባቢ ነው፡፡ ዛሬ ከስንት አንድ ጊዜ የሚደረግ በዓል ሲመጣ ብቻ የሚሆነው ከእናቷ ጋር ወደ ገበያ ሄደዋል፡፡ እናትና ልጅ ለበዓል እና አጠቃላይ የቤት የሚያስፈልጉ ዕቃዎችን እየጠየቁ ስሄዱ… አበባ ዓይኗ አንድ ወጣት የያዘው የጌጣጌጥ መሸጫ ሳጥን ላይ አርፏል፡፡ እናትየው የልጅቷ እጅ ስትጎት ቆመችባት… ልጅቷ ወደየችበት ስታይ ሁኔታዋ አንጀቷን በላው፡፡ አበባም ወደ እናቷ ዓይኗን እያርገበገበች ‹እማ… ያንን የአንገት ሀብል ግዢልኝ…› አለቻት፡፡ እናትም የልጇን ሁኔታ ካየች በኋላ ቦርሳዋን ከፍታ ከአጠቃላይ ግዢ በኋላ ሊቀራት የሚችለውን ብር አሳባ ከጨረሰት በኃላ ወደ አርቴፊሻል ጌጣጌጥ ሻጩ ዋጋውን ስትጠይቅ ከአሰበችው በላይ ሆነ… ‹አበባዬ የያይዝኩት ብር አይበቃም… ባይሆነ ለአዲስ ዓመት አበባዮሽ ብለሽ እና አጎትሽ ሲመጣ ከምታገኘው ብር ግዢ…› አለቻት፡፡ አበባም ዓይኗ ከሀብሉ ላይ ሳትነቅል የእናቷ አሳብ ተረድታ አንገቷን በመስማማት ነቀነቀች፡፡ አበባ ከገበያ ግዥያቸው ጨርሰው ወደቤት ሲመጡ በፍጥነት ያደረገችው ስለሀብሉ ማማርን ውብነት ለቅርብ ሰዎቻቸው በመንገር የምትገዛበት ብር ማሰበሳብ ነበር፡፡ እና ለሀብሏ ብሩን ማጠራቀም… እንደተባለው ለአዲስ ዓመት አበባዮሽ ከጓደኞቿ ጋር ጨፍረው ካገኙት ብር ድርሻዋን ስታገኝ… አጎቷም ደግሞ እንደተለመደው ለአዲስ ዓመት እነሱን ለመጠየቅ ሲመጣ ችቦ በተበራበት ወቅት ለብቻዋ አበባዮሽ በመጨፈር እና ጉዳዩን በማስረዳት ሙሉ የሀብሉን መግዣ ብር አገኘች፡፡ አበባ እንደተመኘችው ሀብሉን ገዛችና የራሷ አደረገችው… ሀብሉን ሁልጊዜም ታደርገዋለች፡፡ የምታወልቀው እናቷ ውሃ ሲነካው ገላሽ ያበላሸዋል ስላለቻት ገላዋን ስትጣጠብና ወንዝ ከልጆች ጋር ልትጫወት ስትሄድ ብቻ ነበር፡፡ አበባ በጣም የሚወዳት እሷም የምትወደው አባት አላት… ሁልጊዜም ማታ አባቷ ከእርሻው ሲመጣ እግሩን አጥባ አጠገቡ በመቀመጥ ታሪክና የተለያዩ በቀኑ ያጋጠመውን ነገር ሲነግራት እሷ ደግሞ ስለአጋጠማትና ደስ ያላት ነገር ያወራሉ እንቅልፏ መጥቶ ወደ አልጋዋ እስክትሄድ ድረስ። አንድ ቀን አባቷ… ወደ አልጋ ልትሄድ ስትል እንዲህ አላት፡፡ ‹አበባ ትወጂኛለሽ?› አላት፡፡ ‹በጣም እንጂ አበባ… እሱንማ አንተም ታውቃለ…› አለችው ‹እሱን ሀብል ሲጪኝ፡፡› አላት፡፡ አበባም ደነገጠች፡፡ ዐይኗ እንባ እያቀረረ ‹አባዬ በጣም የምወደው እባክህ አጎቴ ያመጣልኝን አሻንጉሊት ውሰድ…› አለችው፡፡ አባቷም አሺ በማለት ተስማማ፡፡ አባቷ እና ማታ ማታ እንደዚሁ እየተጫወቱ ከሳምንት በኋላ አባቷ አበባን በድጋሚ እንዲህ አላት። ‹አበባ ትወጂኛለሽ?› እሷም ፈገግ ብላ ‹በጣም እንጂ አበባ… በጣም …› አለችው ‹እሱን ሀብል ሲጪኝ፡፡› አላት፡፡ አበባም በሀዘን ጭንቅለቷን እየነቀነቀች… ዐይኗ እንባ እያቀረረ… ‹አባዬ ከፈለክ እናቴ የሰራችልኝን ያንን የምወደውን የእጅ ጌጥ ውሰደው› አለችው፡፡ ሀበቷም እንዳለችው አደረገ፡፡ እንደዚሁ ቀናት አለፉና አባት አበባ ሲመለከት በጣም አዝናለች፡፡ ቦታው ላይ ሲቀመጥ አበባም ቶሎ ብላ የእግርና የእጅ ውሃ አመጣችለት፡፡ አባቷም አንገቷ ላይ ሀብሉ የለም… ራት ተብልቶ እንደተለመደው ጨዋተ ሊጀምሩ ሲሉ አበባ እያዘነች ለአባቷ ራሷ የሰራችውን ትንሽዬ ሙዳዬ ይዛ መጥታ ሰጠችው፡፡ አባቷም በጥያቄ ሲመለከታት አንዲህ አለችው፡፡ ‹አባዬ ሀብሉ ውሰደው… › አለችው… ትንሽዬ ሙዳዩን ሲከፍተው የእሷ የምትወደው አርቴፊሻል የወርቅ ቅብ የተቀባው ሀብል ውስጡ ተቀምጧል፡፡ አባቷም ፈገግ ብሎ ሁልጊዜም ከሚታጠቀው ቀበቶ ላይ አንዲት ሳጥን አወጣ ለአበባ ሲሰጣት፡፡ አበባም ከፍታ ስትመለከተው ንፁህ ወርቅ የተሰራ ሀብል ነበር… አባቷ ይሄን ንፁህ ወርቅ የተሰራ ሀብል ሁልጊዜም ይዞት ይዞር ነበር… ግን መጀመሪያ አበባ ከአርቴፊሻሉ ራሷን ማላቀቅ ነበረባት፡፡ እንግዲህ ባለፀጋነት እንደዚህ ነው የሚገነባው፡፡ አሊስ ግሬ the treasure ብሎ ከፃፈው ባለፀጋነት ተብሎ ወደ እኛ ሀገር እንዲመች ተደርጎ ተተርጉሞ የተፃፈ … በጣም ስለተመቸኝ ላጋራችሁ ብዬ ከታሪኩ የተማራቹትን አጋሩኝ፡፡ ዘላለም ቦጋለ ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

photo content

ዝምታን አልመረጥንም ልንመርጥም አንችልም # ትክክለኛውን ነገር በትክክለኛው ቦታና በተገቢው ሁኔታ ካልተናገርክ ምን ወርቅ ሐሳብ ቢኖርህ በጨርቅ ተጠቅልሎ እንደተቀመጠ ወርቅ ነው። ⭐ ያንን ጥቅልል ጨ
ዝምታን አልመረጥንም ልንመርጥም አንችልም # ትክክለኛውን ነገር በትክክለኛው ቦታና በተገቢው ሁኔታ ካልተናገርክ ምን ወርቅ ሐሳብ ቢኖርህ በጨርቅ ተጠቅልሎ እንደተቀመጠ ወርቅ ነው። ⭐ ያንን ጥቅልል ጨርቅ የሚያይ ሁሉ ካልተገለጠለት በቀር በውስጡ ንጹህ ወርቅ እንዳለ በምን ይታወቃል? ✔ መልካምና ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ የሚሆን፣ ለሀገራችን ፍቅርና ሰላምን ሊሰጥ የሚችል ሐሳብም በዝምታ ተጠቅልሎ ከተቀመጠ ትርጉም የለውም። ✔ ዝምታ ማለት አለመናገር አይደለም – በጥልቀት ማስተዋል እንጂ፡፡ ዝምታ ማለት አስፈላጊና ግድ የሚሉ እውነቶችን አለመናገር ዝምታ ሳይሆን ፍራቻ ነው። ዝምታ የሚያስፈልገው በእውነተኛ ነገሮች ላይ ሳይሆን ለማይጠቅምና በሕይወታችን ላይ ትርጉም ለሌለው ነገር ከሆነ ብቻ ነው ዝምታ የሚያስፈልገው ካልሆነ እውነትን አለመናገር ዝምታ ሳይሆን ፍራቻ ነው።። እናማ እውነትን ይዞ ማንሾካሾክ ዝምታ አይደለም....

ንግድ ከመጀመርህ በፊት እነዚህን ክኒኖች ዋጥ፦ 💊 ቤተሰብህም ቢሆን ማንም ለእዳህ ሀላፊነት እንደማይወስድልህ አስበህ ተዘጋጅ፦ ጓደኞችህ ስለሚያውቁህ ብቻ ከአንተ እንዲገዙ፣ ቤተሰብ እንዲያበረታታህ ወይም ችኮላህን እንዲያስተዋውቅ አትጠብቅ። አብዛኛዎቹ የመጀመሪያ ደንበኞችህ እንግዳዎች ይሆናሉ። እንግዶች ባልፈው ነገርህ ላይ ሳያተኩሩ ስለምታቀርበው ዋጋ ያስባሉ። እነሱ ችላ ሊሉህ የማይችሉትን ጥሩ ነገር በመገንባት ላይ አተኩር። 💊 በመጀመሪያዎቹ ጊዜያት ጠንክረህ ሰርተህም ላታተርፍ እንዲያውም ልትከስር ሁሉ ትችላለህ፦ በአብዛኛው ይህ የሚገጥምህ ንግድህ እስከሚረጋጋ ድረስ ነው። ነፃነት ነፃ አይደለም። ላብህን ትከፍልበታለህ። 💊 በንግድ ውስጥ የገንዘብ ችግሮች አሉ፦ በገንዘብ አያያዝህ ቸልተኛ ከሆንህ በንግድ ውስጥ ያልጠበቅኸው ከፍተኛ እዳ ሊመጣብህ ይችላል። የገንዘብ ፍሰት አስተዳደርን፣ በጀት ማውጣትን፣ ለታክስ መቆጠብ እና ትርፍን እንደ ደሞዝ የመመልከት ፍላጎትህን መቃወም መማር ያስገፈልግሃል። ገበያ የሚቀዘቅዝባቸው ወራት፣ ከደንበኞች የሚዘገዩ ክፍያዎችና ድንገተኛ ወጪዎች ይኖራሉ። ንግድ የገንዘብ አያያዝ ጥሩ ልምድ ይጠይቃል። 💊 የንግድ መክሊት በቂ አይደለም፤ መዋቅር (system) ያስፈልጋል፦ የንግድ ተሰጥኦና ጥሩ ሀሳቦች አሉኝ ልትል ትችላለህ። የአሰራር ሂደቶች፣ የስራ ፍተሻ ዝርዝሮች፣ የጊዜ መርሐግብር ዘዴዎችና ውክልናዎች ያስፈልጋሉ። እነዚህን ስትጠቀም በታመምህበት ወይም በእረፍት በወጣህበት ቀን ንግድህ አይፈርስም። ምርጥ ንግዶች በአዋቂነት ብቻ ሳይሆን በመዋቅር ጭምር ይሰራሉ። 💊 ንግድ የማንነትህን የእያንዳንዱን ክፍል ይፈታተናል። ባለጌ ደንበኞች፣ ስራህን አመሳስለው የሚሰሩ ሌሎች ነጋዴዎች፣ የገንዘብ እጥረት፣ የማይጠቅሙና ክፉ ሰራተኞች፣ የተበላሹ ሽርክናዎች፣ ከባድ ውሳኔዎችና ጥርጣሬዎች ይፈታተኑሃል። ንግድህን ለመገንባት እነዚህን የመፍታት ችሎታህን አዳብር። የበለጠ ጠንካራ፣ ብልህ፣ ስነስርዓትህ የተሞላ፣ ትኩረት ያለህና ስልታዊ መሆን ያስፈልግሃል። ንግድ መጀመር በህይወት ውስጥ ጠቃሚ ከሆኑት መንገዶች አንዱ ነው። ነገር ግን አቋራጭ መንገድ አይደለም፤ ውጣ ውረዶች እንዳሉት ማወቅ ያስፈልጋል። ይዘረጋል፣ ይሰብራል፣ ያድሳል። ንግድ እንደ ጦር ሜዳ እምነትህን ይፈትሻል። join us @changeitwow @ራስን መለወጥ

photo content

ከልብ አክብሮት አለን‼️ ታሪክ ተሰራ በሀገራችን ዶክተሮች ህፃን ሚኪያስም እያገገመ ይገኛል:: ለሀገራችንም ሆነ ለአህጉራችን ኩራት የሆነ ፈር ቀዳጅ የህጻናት የልብ ቀዶ ጥገና በሀገር ልጆች በአገራች
ከልብ አክብሮት አለን‼️ ታሪክ ተሰራ በሀገራችን ዶክተሮች ህፃን ሚኪያስም እያገገመ ይገኛል:: ለሀገራችንም ሆነ ለአህጉራችን ኩራት የሆነ ፈር ቀዳጅ የህጻናት የልብ ቀዶ ጥገና በሀገር ልጆች በአገራችን የሕክምና ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ። የሁለት ዓመት ሕፃን ልጅ ላይ በልብ ጡንቻ እብጠት (Hypertrophic Cardiomyopathy - HOCM) ምክንያት የተፈጠረ ከባድ የልብ በሽታ፣ በሀገር ውስጥ የህክምና ባለሙያዎች ባልተለመደ ቀዶ ጥገና ተስተካከለ። ትናንት ለሰባት ሰዓታት የፈጀው ይህ ቀዶ ጥገና፣ የግራ ልብ መውጫን የዘጋውን የልብ ጡንቻ በማስተካከል እና ከፍተኛ የኋላ መመለስ (Mitral Regurgitation) ችግርን በመፍታት የሕፃኑን ሕይወት አድኗል። በሂደቱ ሁለት ጊዜ ልብን በማሽን ላይ በማቆም ከፍተኛ ትግል የተደረገ ሲሆን፣ መጨረሻ ላይም አስደናቂ ውጤት ተገኝቷል። ሕፃኑም በአሁኑ ወቅት ጥሩ የማገገም ሁኔታ ላይ ይገኛል። 🙏Dr. Fekade Agwar

"ኬንያዊው ሰው" የዓለማችን ትልቁ ባለሀብት የኤለን ሙስክ ልጅ ነኝ እያለ ነው። እናንተስ ምን ትላላችሁ??????‼️ ግን እውነት ይሆን????! ከምር ግን አይመሳሰሉም????? @followers
"ኬንያዊው ሰው" የዓለማችን ትልቁ ባለሀብት የኤለን ሙስክ ልጅ ነኝ እያለ ነው። እናንተስ ምን ትላላችሁ??????‼️ ግን እውነት ይሆን????! ከምር ግን አይመሳሰሉም????? @followers

➛➛ከመናገር ማሰብ ይቅደም➛➛ ➲ በድሮ ጊዜ አንድ ሰው ጥፋት ያጠፋና ዳኛ ፊት ይቀርባል። ታድያ ዳኛው ሦስት ዓይነት የቅጣት ምርጫ አቀረቡለት፡፡ አንድ ኪሎ ሽንኩርት እየላጠ መብላት፤ ፡ አንድ መቶ
➛➛ከመናገር ማሰብ ይቅደም➛➛ ➲ በድሮ ጊዜ አንድ ሰው ጥፋት ያጠፋና ዳኛ ፊት ይቀርባል። ታድያ ዳኛው ሦስት ዓይነት የቅጣት ምርጫ አቀረቡለት፡፡ አንድ ኪሎ ሽንኩርት እየላጠ መብላት፤ ፡ አንድ መቶ ጅራፍ መገረፍ፤ ፡ አምስት መቶ ብር መክፈል፡፡ ፡ ሰውዬው ለማሰብ የሚሆን ልቡና የሌለው ነበርና የመጀመርያ ምርጫ ሆኖ ስላየው ብቻ "ሽንኩርቱን እበላለሁ" አላቸው፡፡ : አንድ ኪሎ ሽንኩርት ቀረበለት፡፡ ገና አንድ ሁለት መብላት ሲጀምር ታድያ ዓይኑ ማልቀስ ፣ ለሐጩም መዝረብረብ ጀመረ፤ አልቻለም። ከመቀመጫው ተስፈንጥሮ ተነሣና «መቶ ጅራፍ መገረፍ ይሻለኛል» አላቸው፡፡ ፡ ወዲያው ኃይለኛ ገራፊዎች ተጠሩና እየተፈራረቁ ይለበልቡት ጀመር፡፡ ግማሽ እንደደረሰ አልቻለም፡፡ እጁን ወደ ላይ አነሣ፡፡ ፡ «እህሳ» አሉት ዳኛው፡፡ ፡ «አልቻልኩም» አላቸው፡፡ ፡ «ታድያ ምን ይሻላል» አሉት እየሳቁ፡፡ ፡ «በቃ አምስት መቶ ብሩን እከፍላለሁ» አለ ከተኛበት እየተነሣ፡፡ ፡ «ያንተ ትልቁ ጥፋት መጀመርያ ወንጀል መሥራትህ ብቻ አይደለም፡፡ ማሰብ አለመቻልህ እንጂ፡፡ ምናለ አስበህ ከሦስቱ አንዱን ብትመርጥ ኖሮ፡፡ እኔ ከሦስቱ አንዱን እንድትቀጣ ነበር የወሰንኩት፡፡ አንተ ግን መናገር እንጂ ማሰብ ባለመቻልህ ሦስቱንም ተቀጣህ፡፡» አሉት። ✍ብዙዎቻችን ከመናገራችን በፊት ማሰብ ሳንቸል ቀርተን በዘፈቀደ በተናገርነው ቃል እራሳችንን ፣ ቤተሰቦቻችንን ፣ ጎረቤታችንን አልፎም ሀገርን እረብሸናል፤ ጎድተናል፡፡ ሁሌም ከማውራታችን ከመፃፋችን በፊት የምናገረው ፣ የምፅፈው ነገር ሰዎችን ያስከፋል? እውነት ነው ብለን እንጠይቅ፡፡ እውነት እራሱ የብዙሀንን ሰላም ለመጠበቅ ሲባል ካለቦታውና ካለወቅቱ አይገለፅም፡፡ መልካም ቀን ይሁንላችሁ🙏 ራስን መለወጥ @followers t.me/changeitwow

ውዶች....! በውቄን ታውቁታላችሁ..... Bewketu Seyoum !! ሢጽፍ፣ሢገጥም፣ሢኸይሥ፣ሢኮምክ፣...ሢጫወት...ሢጫወት...በዛ ልዩ ከለር ባለው ድምጹ.. ታሪክ ሢተርክ...እጅግ ድንቅ ሠብ ነው
ውዶች....! በውቄን ታውቁታላችሁ..... Bewketu Seyoum !! ሢጽፍ፣ሢገጥም፣ሢኸይሥ፣ሢኮምክ፣...ሢጫወት...ሢጫወት...በዛ ልዩ ከለር ባለው ድምጹ.. ታሪክ ሢተርክ...እጅግ ድንቅ ሠብ ነው።ደፋር ነው።2008 ላይ 'ቤሥት ወጣት ጸሃፊነትን' ሽልማቷን ላፍ ያደረገ ከባድ ሠው ነው። ኗሪ አልባ ጎጆዎች፥2000 ላይ. በራሪ ቅጠሎች፥2004 ላይ የእሳት ዳር ሃሳቦች፥ 2009 ላይ ሀሰሳ ስጋ፥2012 ላይ እንቅልፍ እና እድሜ,... መግባት እና መውጣት,.... ከአሜን ባሻገር፥2015 ላይ የማለዳ ድባብ፥ 2017 ላይ አዳምኤል፥2020 ላይ ..... ጥቂቶቹ የማሥታውሣቸው የአእምሮው ጭማቂዎቹ፣የልቡ ፍቃዶቹ ፣የእጁ ሥራዎቹ ናቸው። እዮብ ምህረታብ (ነፍሡ በሠላም ትረፍና) "በእውቄ እኮ ከባድ ኢትዮጵያዊ ጸሃፊ እና ገጣሚ ነው።ልክ እንደ ቺሊው ጸሃፊ እና ገጣሚ Pablo Neruda ነው። " ይለኝ ነበር።ሊያገናኘን ብዙ ቀጠሮ ይዞ ነበር።ግን ይኸው በግዜው ተገናኘን። በእውቄ ቴክኖሎጂ እንደምወድ ከወዳጃችን ሣሮን ይሠማል። ከጀርመን Think Faster,Talk Smarter እና Surrounded by Ideots የሚባሉትን መጽሃፍቶች እናም ከአሜሪካ How Things Work የሚል አሪፍ መጽሃፍ አምጥቶ ጀባ ብሎኛል።ቡና እየጋበዘ ሸልሞኛል። በእውቄ ፈቅ ያለ እድሜ ከጤና ጋር ጀሊሉ ይወፍቅልኝ። እኔ ደግሞ መጽሃፍ የሚሸልመኝ ሠው የመጨረሻ የጀግንነት ኒሻን የሚሸለም ቢሆንልኝ እመኛለሁ። መጽሃፍቶቹ ለክረምት አሪፍ ናቸው።አንብቧቸው እሥኪ። በርቱ! via bajai narash t.me/changeitwow

#በአዳም_ረታ_የተከተበ "ጥናት ከሌለ ዕዉቀት የለም። ዕዉቀት ከሌለ መለወጥ የለም። ልበ ሙሉነት ያለ ትክክለኛ መረጃ ምንም ነዉ። ማወቅ ሲገባህ ካላወክ ደደብ ነህ። ዕዉቀት ስሜትን መቆጣጠር አለበት።
#በአዳም_ረታ_የተከተበ "ጥናት ከሌለ ዕዉቀት የለም። ዕዉቀት ከሌለ መለወጥ የለም። ልበ ሙሉነት ያለ ትክክለኛ መረጃ ምንም ነዉ። ማወቅ ሲገባህ ካላወክ ደደብ ነህ። ዕዉቀት ስሜትን መቆጣጠር አለበት። ስሜት እዉቀትን መያዝ ወይም ማሰር የለበትም። የለዉጥ ስሜትህን አይተዉ እሱንም ከእዉቀትህ አምታተዉ ሳታዉቅ አዉቀሃል ካሉህ ጠላቶችህ ናቸዉ። ሹራቡ ላይ ጠላትህ ነኝ ብሎ ፅፎ እንዲመጣ ትፈልጋለህ?" #መረቅ (የብዙ መፅሀፎች ደረሲ) #አዳም t.me/changeitwow

ማህተበ ጋንዲ መርህ‼️ ከከበበኝ ጨለማ ይልቅ በደጄ የማያት የብርሃን ጭላንጭል ለኔ ቅርብ ናት። ብዙ ግዜ እሳሳታለሁ፤ አጠፋለሁም። እምነቴ ግን ሳይሳሳት በፈጣሪ ላይ ብቻ ተመስርቷል። ባለራዕይ ነኝ
ማህተበ ጋንዲ መርህ‼️ ከከበበኝ ጨለማ ይልቅ በደጄ የማያት የብርሃን ጭላንጭል ለኔ ቅርብ ናት። ብዙ ግዜ እሳሳታለሁ፤ አጠፋለሁም። እምነቴ ግን ሳይሳሳት በፈጣሪ ላይ ብቻ ተመስርቷል። ባለራዕይ ነኝ ብዬ አልዋሽም፤ ቅዱስ ነህ የሚሉኝንም አይደለሁም እላለሁ። እኔ ከምድር የወጣሁ፤ ምድራዊ ነኝ። እንደ እናንተው ለብዙ ድክመቶች ተጋልጫለሁ። ነገር ግን፦ ዓለምን አይቻታለሁ፤ በተከፈቱ ዓይኖቼ አስተውያታለሁ። በሰው መንገድ የተወረወሩ ፍላፃዎች በእኔም መንገድ ላይ በተደጋጋሚ ወድቀዋል። የዚህ ሁሉ ድምር ግን በሥርዓት አንፆኛል። ማህትማ ጋንዲ t.me/changeitwow

ገበሬ እና ሀገር #እውነት! የገበሬን ያህል እምነት ማን አለው? በሀምሌ ወቅት ከጎታው አውጥቶ በምድር ላይ ያፈሳል። ቀና ብሎ ለአምላኩ “ከጎርፍና ከወፍ የተረፈውን ለልጆቼ መልስ” ይለዋል። ዝቅ ብሎ
ገበሬ እና ሀገር #እውነት! የገበሬን ያህል እምነት ማን አለው? በሀምሌ ወቅት ከጎታው አውጥቶ በምድር ላይ ያፈሳል። ቀና ብሎ ለአምላኩ “ከጎርፍና ከወፍ የተረፈውን ለልጆቼ መልስ” ይለዋል። ዝቅ ብሎ ለምድር “እኔት ጥንተም አፈር፣ ነገም ምድር ነኝና አደራሽን ተወጪ። የበላሽውን በልተሽ የተረፈውን በወቅቱ ለልጆቼ ስጪ” ይላታል። እግዜሩ ከሰማይ ይሰማል። ዝናብ ካቆመ፣ ዘሩን ወፍ ይጨርሰዋል። ዶፍ ቢያዘንብ፣ ጎርፍ ይጠርገዋል። እግዜሩ አመጣጥኖ ያዘንባል። ለወፎችም ለገበሬውም። “ የሰማይ አሞሮችን አታዩም…” ብሎ ቃል ገብቶ እሱም እዳ ውስጥ ነው። ወፎቹም ይበላሉ፣ ገበሬውም ከወፍና ከጎርፍ የተረፈውን ከሰብሉ ያገኛል። ለገበሬውም እምነት ይገዛል-እግዜሩ። ለገበሬ በሬ የበኩር ልጁ ነው። ባለሟሉ፣ የመከራም የደስታም ደራሹ ነው። አልፎ አልፎ ምስጢር ሁሉ ለበሬው ይነገረዋል። የልብ ሰው ሲያጣ። ጊዜ ሲሸሸው ሰው ሲዋሸው። “ አንድ በሬ ነበረኝ እንደ እኔ የከፋው ብሶቴን ብነግረው የጉንጩን ሳር ተፋው” የሚለው ብሂል ከዚህ የተቀዳ ሀቅ ነው። ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የገበሬና የበሬ ውጤት ናት። አሁን አሁን ከሶስቱ አንዱ የጎደለ ይመስለኝና እጨነቃለሁ። ሀገር ከሌለ ገበሬ የለም። ገበሬና በሬ ካልተገናኘ ሀገር የለም። በሬ ከሌለ ገበሬ የለም። ገበሬ ከሌለ ሀገር የለም። በሬውን ብቻ ሳይሆን ሀገሩንም ለገበሬ መስጠት የዘመን መሻገሪ ይመስለኝ ይዟል። ከልጆቹ አፍ ቀንሶ ዘሩን ለመሬት በአደራ የሰጠ ገበሬ፣ ሀገሩን ቢሰጡት በእምነቱ ይጠብቃታል፣ በጉልበቱ ያፀናታል! ✍️ዘላለም ጥላሁን via Social media t.me/changeitwow

photo content

#ፈጣሪ_ድንቅ_ነው ድንቅ ሴት‼️ 👉በሰባት ወሯ የተወለደች 👉ከተወለደችም በኋላ ከአንድ ወር በላይ በህይወት አትቆይም የተባለች 👉ዶክተሮቹ ከሞት ብትተርፍ እንኳን መናገር አትችልም ብለው ያረጋገጡ
#ፈጣሪ_ድንቅ_ነው ድንቅ ሴት‼️ 👉በሰባት ወሯ የተወለደች 👉ከተወለደችም በኋላ ከአንድ ወር በላይ በህይወት አትቆይም የተባለች 👉ዶክተሮቹ ከሞት ብትተርፍ እንኳን መናገር አትችልም ብለው ያረጋገጡላት 👉በመጨረሻም ይህች K.Visalini የተባለች ህንዳዊ እንስት የአለማችን የከፍተኛ IQ ባለቤት ሆናለች። 👉"መጀመሪያህን አይተው መጨረሻህን ዝቅ አድርገው ለሚገምቱ ሰዎች ቦታ አትስጥ።" via ኢትዮጵያዊነት ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

ከፖሊስ አባላትንና ከሃይማኖት አባቶችን ሂሳብ የማያስከፍሉ ባጃጅ አሽከርካሪ ወንድማማቾች በአርባምንጭ ከተማ ሂሳብ የማይቀበሉ ወንድማማች የባጃጅ ሹፌሮች 👇 ስማቸው ሠላሙ አበበ እና አስቻለው አበበ
ከፖሊስ አባላትንና ከሃይማኖት አባቶችን ሂሳብ የማያስከፍሉ ባጃጅ አሽከርካሪ ወንድማማቾች በአርባምንጭ ከተማ ሂሳብ የማይቀበሉ ወንድማማች የባጃጅ ሹፌሮች 👇 ስማቸው ሠላሙ አበበ እና አስቻለው አበበ ይባላሉ ።እነዚህ ወንድማማቾች በአርባምንጭ ከተማ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሲሆን የትኛውም እምነት ተከታይ ሆነው የሃይማኖት አባትነት ወይም መሪነት ልብስ የለበሱ እና ሚሊቴሪ ለለበሱ ለሁሉም የፀጥታ አካላት በመንገዳቸው ሲያገኙ ያለ ክፍያ በነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣሉ ። እነዚህ ወንድማማቾች ለምን ነፃ አገልግሎት እንደሚሰጡ ምክንያታቸውን ሲናገሩ የሃይማኖት አባቶች በፀሎታቸው ከእግዚአብሔር ምህረት ያሰጡናል ብሎ እንደሚያምኑና የፀጥታ ሃይሎች ደግሞ በሰላም ሰርተን ወደ ቤታችን እንድንገባ ከእግዚአብሔር በታች መከታችን ናቸው ብለዋል ። እናመሰግናለን ፈጣሪ ስራችሁን ይመልከት እና እንደአሳባችሁ ይሁን🤲‼️ ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

ከሰዎች ጋር ያለንን ተግባቦት ለማዳበር የሚረዱ ጠባያት 1. ጥሩ አድማጭ መሆን ተግባቦትን ለማዳበር ከሚረዱ ጠባያት ዋነኛው ጥሩ አድማጭነት ነው፡፡ ሰዎች በሚናገሩበት ሰዓት ተናግረው እስኪጨርሱ አለማቋረጥ፤ ዓይናቸውን መመልከት፤ በንግግር መሃልም መረዳታችሁን ለማመልከት ጭንቅላታችሁን ወደ ላይና ወደ ታች መነቅነቅ፤ ተናግረውም ከጨረሱ በኋላ መናገር የፈለጉትን ሃሳብ በጥቂት ቃላት ማጠቃለል የጥሩ አድማጭነት ምልክቶች ናቸው፡፡ 2. የፊት ገጽታችንና የእጅ እንቅስቃሴአችን በንግግር ወቅት ያለን የፊት እና የእጅ እንቅስቃሴ ስለምንናገረው ሃሳብ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ አለ፡፡ ለምሳሌ አስደሳች ሃሳብ ለመናገር እየሞከርን የፊት ገጽታችንን ማኮሳተር፤ ማጨማደድ እና የዓይን ሽፋሽፍትን መሰብሰብ ለአድማጭችን ተቃራኒ መልዕክት ይልካል፡፡ ስለዚህም ከምንናገረው ሃሳብ ጋር ውህደት ያለው የፊት ገጽታና የእጅ እንቅስቃሴ ሊኖረን ይገባል፡፡ 3. ፍሬ ሃሳቡን በተወሰኑ ቃላት መግለጽ የሰው ልጅ ትኩረትን ሰጥቶ አንድን ድርጊት መከወን የሚችው ለጥቂት ደቂቃዎች ስለሆነ በንግግር ወቅት በጥቂት ቃላት የምንፈልገውን ሃሳብ መግለጽ ይገባል፡፡ የምናናግረውም ሰው በዚያች በሚያናግረን ሰዓት ብዙ የሚያሳስቡት እና ጊዜ ሊሰዋላቸው የሚፈልጋቸው ብዙ ጉዳዮች እንዳሉት በማመን አጭርና በተመረጡ ቃላት የተሟላ ንግግር ብናደርግ ጥሩ ተግባቦት ይኖረናል፡፡ 4. ትኩረት የሚያሳጡ ነገሮችን ማራቅ ተንቀሳቃሽ ስልክ እንዲህ የዕለት ተዕለት ኑሯችን ውስጥ ዘልቆ በገባበት ጊዜ ውስጥ ከሰዎች ጋር በምንነጋገርበት ወቅት የምንጠቀማቸው ከሆነ ተገቢ ያልሆነ ትርጉም ይሰጣል፡፡ ለምናናግረው ሰው ውይም ስሚናገረው ሃሳብ ግድ እንደሌለን ያሳብቃል፡፡ ስለዚህም በንግግር ወቅት ተንቀሳቃሽ ስልካችንን ጨምሮ የምንከውነውን ማንኛውንም ስራ አቁመን ሙሉ ትኩረታችንን በመስጠት ልናዳምጥ እንዲሁም ምላሽ ልንሰጥ ይገባል፡፡ 5. አቀማመጥን ማስተካከል ወደ ጀርባችን ተለጥጦ መቀመጥ፤ ጀርባችንን መስጠት ወይም ፊትን ወደ ተቃራኒው አቅጣጫ ማዞርን የመሳሰሉ አቀማመጦች ተግባቦትን አስቸጋሪ ሊያደርጉ ስለሚችሉ ወደ ምናናግረው ሰው አቅጣጫንን ማስተካከል እንዲሁም ጠጋ በማለት አቀማመጣችንን ማስተካከል ይገባናል፡፡ 6. የሚያናግሩትን ሰው ስሜት መረዳት እጅግ የሚያሳዝን ታሪክ እየተነገረን ስሜታቸውን ከቁብ ሳንቆጥር ቅጭም ባለ አኳኋን “የምተለው ይገባኛል” ብንል ተአማኒነት ያሳጣል፡፡ የተናጋሪውን ስሜት ወደእኛም ዘልቆ እንዲገባ መፍቀድ ከቻልን መልካም ተግባቦት ይኖረናል፡፡ 7. ንግግርህ ፍሰት ያለው እና ያልተዘበራረቀ እንዲሆን ማድረግ ከአንድ ሃሳብ ወደ ሌላ ሃሳብ መዝለል ውልና ማሰሪያ የሌለው ንግግር፤ ውይይትና ክርክር ማድረግ መጨረሻቸው የማያምር ነው፡፡ ስለዚህም ትኩረትን በአንድ ሃሳብ ላይ ብቻ በማድረግ ያልተዘበራረቀ እንዲሁም ፍሰቱን የጠበቀ ንግግር ማድረግ እርሱንም አጠናቆ ወደሌላው መሻገር ተገቢ ነው፡፡ 8. በየንግግሩ መሃል የሚገቡ ድምጾችንና የቃላት ድግግሞሽን ማስቀረት ብዙውን ጊዜ ሰዎች ሃሳባቸውን ከመከታተል ይልቅ ወደዚህ ጽምጸት አትኩረው እንዲያፌዙ ይጋብዛል፡፡ ስለዚህም “አ….. “ “አም….” የሚሉ ድምጸቶችን ማስወገድ ይገባል፡፡ እንዲሁም “እና” ፤ “ማለት ነው” እና “ምናምን” የሚሉ ቃላትን መደጋገም ንግግራችንን አሰልቺ ሊያደርጉት ስለሚችሉ ማስወገድ ይገባል፡፡ 9. የድምጻችንን ቃና እንደየሃሳባችን ማቀያየር በንግግር ወቅት አንድ ቃና ብቻ ያለው ወጥ ንግግር ማድረግ፤ ለሃዘኑም ለደስታውም ለቁጣውም ተመሳሳይ ድምጸት መጠቀም የአድማጭ ትኩረት እንዲበታተን የሚጋብዝ ነውና አንዴ ከፍ አንዴ ዝቅ አንዳንዴም ለጥቂት ሰኮንዶች ዝም እያልን በተለያየ ቃና የታጀበ ንግግር ማድረግ የአድማጭን ትኩረት ለመሳብና እስከ ንግግሩ መጨረሻ ሰብስቦ ለማቆየት ይረዳል፡፡ ተግባቦት የብዙ ሰው ችግሮ ነውና share በማረግ ለሌሎች እነዚህን ቁልፍ ነገሮች እናሳውቅ ፔጃችንን Like በማረግ በየቀኑ አዕምሮዎን በመልካም ሀሳብ ይመግቡ (በዘመነ ቴዎድሮስ) t.me/changeitwow