ራስን መለወጥ
Open in Telegram
እንዴት ናችሁ? ቢዝነስ ፕላን(ቢዝነስ ዕቅድ) እንዲሰራለት የሚፈልግ በተመጣጣኝ ዋጋ ቢዝነስ ፕላን እንሰራለን! በውስጥ መስመር ያናግረን! ለውጥ በትክክልም ይመጣል። 💪ዕድገታችንም ይሳካል!!! Hello everyone, we make best Business plan. In good price contact us inside! just pick a what kind of business plan! We can chang
Show more9 785
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-8230 days
Posts Archive
9 785
#የግዕዝ_ትምህርት፡ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ጥበብ ለመጪው ትውልድ መክፈት‼️
@መሀመድ ያሲን እንደፃፈው!
ግዕዝ የኢትዮጵያ ጥንታዊ የጽሁፍ ቋንቋ ከመሆኑ ባለፈ ለአማርኛ፣ ለትግርኛ እንዲሁም ለበርካታ ቋንቋዎች መሰረት መሆኑ ታውቆ ያደረ እውነታ ነው። ነገር ግን በኔ አተያይ ግዕዝ ከቋንቋም በላይ ነው፤ ይኸውም ለኢትዮጵያዊያን የስልጣኔ መገለጫ፣ የማንነት ማሳያ፣ የእድገት መሰላል እና የቀጣይነት ምልክት ጭምር ነው።
እናም ዛሬ ላይ በአማራ ክልል የግዕዝን ቋንቋ በመደበኛ የትምህርት ፕሮግራም ላይ አካቶ እንዲሰጥ መወሰኑ የሚኖረውን ፋይዳ በውል በመገንዘብ እንደ ሐገር በሁሉም ክልሎች መሰጠት የሚገባው የትምህርት አይነት ሆኖ እንዲወሰን ምክረ ሃሳብ ማቅረብ ተገቢ ይመስለኛል።
ምክኒያቱም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የቀደምት ስልጣኔ መገለጫ የሆነ የበለፀገ የስነ-ፅሁፍ ቅርስ ያለው ሐገር ዜጋ በመሆኑ ከሚሰማው የስነ ልቦና ከፍታ ባሻገር የግዕዝ ትምህርትን በአንደኛና በመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተደራሽ መደረጉ አያሌ ጥቅሞችን ያስገኛል የሚል እምነት ስላለኝ ነው።
1️⃣ የኢትዮጵያን ልዩ ልዩና ዘርፈ ብዙ ጥንታዊ የብራና ጽሑፎችን እና ታሪካዊ እውቀቶችን ለመጠበቅ ከማገዙ ባለፈ ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ በእጅጉ ያስችላል።
2️⃣ እንደሚታወቀው ግዕዝ የዘመናችን የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መነሻ በመሆኑ ይህንን ቋንቋ መማር ተማሪዎች የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውን መነሻና ጥልቅ ትርጉሞች በመገንዘብ በሂደቱም የሰዋሰው፣ የቃላት እና የቋንቋ ግንዛቤያቸውን ለማሳደግ ያስችላቸዋል።
3️⃣ ለጥንታዊ ቋንቋ እውቀት አእምሮን ክፍት ማድረግ የተማሪዎችን የማስታወስ ችሎታ፣ አወንታዊ አስተሳሰብን ለማጎልበት፣ የፍልስፍናና የፈጠራ አቅምን ለማሳደግ እንዲሁም ችግርን የመፍታት ብቃትን ለማዳበር በእጅጉ ያግዛል።
4️⃣ ግዕዝ ከዓለም ጥንታዊ የጽሑፍ ቋንቋዎች አንዱ እንደመሆኑ መጠን ካሪኩለም ተቀርፆለት በትምህርት ቤቶች መሰጠቱ ዓለም አቀፍ ምሁራንን ይስባል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ የቋንቋ ቅርስ ጠባቂ መሆኗን የሚያመላክት ተግባር በመሆኑ የባህል ዲፕሎማሲውን ያሳድጋል።
በጥቅሉ ይህ ውሳኔ በሐገር አቀፍ ደረጃ ወደ ተሟላ ተግባር ውስጥ ከተገባ እንደ አንድ የትምህርት ሪፎርም ብቻ ተደርጎ የሚወሰድ አይመስለኝም። ይልቁንም ያለፈውን፣ አሁን ካለው እና ከተተኪው ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ለመገንባት በትውልድና በሐገር ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት ጭምር ነው።
t.me/changeitwow
9 785
🤔ሁልጊዜም ስኬት አንድ መስመር የለውም!
🇦🇷ካርሎስ ቴቬዝ 🗣️🎤 : "በልጅነቴ ትምህርት ላይ ጎበዝ አልነበርኩም። ነገርግን ሁሌም በትምህርታቸው ጎበዝ ከሚባሉት ልጆች አጠገብ መቀመጥ ስለምወደው ከአጠገቤ የተቀመጠው ጎበዝ ተማሪ መኖሩን አረጋግጥ ነበር። በክፍል ውስጥ የተሳሳተ መልስ ስሰጥ ሴቶቹ ይስቁብኝ ነበር። በጣም መጥፎው ነገር በምሳ ሰአት፣ ስለ እኔ ሲያወሩ ስሰማ ነው፣ እንዲህ ይሉ ነበር 🗣️"በጣም ይገርማል፤ አጭር አእምሮ ያለው አጭር ሰው አለ።"
"እንደ እድል ሆኖ፣ አብረውኝ ከሚማሩት ልጆች ጋር በእግር ኳስ ጨዋታ አሸነፍኩኝ። እናም ሁሉም ነገር ተለወጠ። ያፌዙብኝ የነበሩት ልጆች እራሳቸውን በማስተዋወቅ እና የገንዘብ እርዳታ ጠየቁኝ።" በትምህርት ቤት ውስጥ "ሞኙ" እያሉ ሲሳለቁብኝ በነበረው ነገር ቂም አልያዝኩም። የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን የረዳኋቸው የሰፈሬ ልጆች ስለሆኑ ነው።"
"ትምህርት ጥሩ ነው።ነገርግን ብቸኛው የስኬት መንገድ አይደለም። በትምህርት ጎበዝ ካልሆንክ በህይወትህ ትልቅ ደረጃ አትደርስም ማለት አይደለም። እንደውም ብዙ ቢሊየነሮች ጥሩ የትምህርት ታሪክ የላቸውም። ስኬት የሚመጣው ጎበዝ በሆንክበት ነገር አምነህ እና ጠንክረህ በመስራት ነው።"
💞💝ቴቬዝ 💪 🇦🇷
ከኢንፍርም ኢትዮጵያ
t.me/changeitwow
9 785
#የናፖሊዮን_የህይወት_ፍልስፍናዎች
#አንድ
ጸጸት የሌለበት ብቸኛው ድል ድንቁርና ላይ የሚቀዳጁት ድል ነው!
#ሁለት
ሰዎች የሚገፉት በሁለት መፈንቀያዎች ነው፤ በፍርሃት እና በግል ፍላጎት!
#ሶስት
ቃልን የመጠበቂያ ምርጡ መንገድ ከመጀመሪያው ቃልን አለመስጠት ነው!
#አራት
በዓለም ሁለት ኃይሎች አሉ፤ ጎራዴ እና አእምሮ። በረዥም ጊዜ ግን አእምሮ ሁልጊዜ ጎራዴን ያሸንፋል!
#አምስት
ዓለም ስቃይ ላይ ነች። የምትሰቃየው ግን በመጥፎ ሰዎች በደል ሳይሆን በጥሩ ሰዎች ዝምታ ነው።
#ስድስት
ሽንፈትን የሚፈራ እሱ በርግጥም ተሸንፏል!
#ሰባት
ቻይና ያንቀላፋ ጭራቅ ነው፤ ተውት ይተኛ! ከነቃ ግን ዓለምን ያንቀጠቅጣታል!
#ስምንት
ብዙ ሰዎች የሚወድቁበት ዋናው ምክንያት በጣም የሚፈልጉትን ነገር በጊዜው ለሚፈልጉት ነገር ስለሚሸጡት ነው!
#ዘጠኝ
ሞት ተሸንፎ መኖር ነው፤ ኃፍረት ደግሞ በየቀኑ መሞት ነው።
#አስር
የሚናገሩ አስር ሰዎች ዝም ካሉ አንድ ሺህ ሰዎች በላይ ድምጽ ያሰማሉ።
ከየህይወት_ፍልስፍና
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow
#ethiopia #like@changeitwow
9 785
እውነተኛ ታሪክ ነው -
***
ባለትዳርና የሁለት ሴት ልጆች እናት ነኝ አንድ የመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ ተቀጥሬ እሰራለሁ ከዛች ክፉ ምሽት በፊት በትዳሬ በልጆቼ ባጠቃላይ በኑሮዬ እንደኔ ደስተኛ ሰው አልነበረም።
ያንን ቀን እንደ ሁልግዜው በስራ ገብታዬ ነበር ያሳለፍኩት ሆኖም አመሻሽ ላይ መጨረስ የሚኖርብኝ ስራ ስለነበር በመደበኛ ሰዓቴ አልወጣሁም። ለባለቤቴም ትንሽ ማምሸቴ ስለማይቀር በጊዜ ልጆቹ ጋር እንዲገባ ደውዬ ነግሬው ወደ ስራዬ ተመለስኩ ከምሽቱ 3:40 ስራዬን አጠናቅቄ ከቢሮዬ ወጣሁ በዛን ሰዓት ሚኒባስ ታክሲ ማግኘት የማይታሰብ ስለነበር የኮንትራት ታክሲዎች ከተደረደሩበት ስፍራ ደርሼ በወቅቱ ከነበሩት ሹፌሮች እድሜው በ40ዎቹ አጋማሽ የሚገመት ጎልማሳ መርጬ ወደሰፈሬ ለማድረስ የጠየቀኝን ሂሳብ ምንም ሳልከራከር ተስማምቼ ገባሁ ላዳዋ ግን ከፊትም ከኃላም ታርጋ አልነበራትም ግራ ገብቶኝ ስጠይቀው አሁሁን ነው ትራፊኮች የፈቱብን አለኝ እኔም ብዙ ሳልጨነቅ ጉዞ ጀመርን።
የአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ስላማረረን እኔና ባለቤቴ ከከተማ ትንሽ ወጣ ያለ ቦታ ቡራዩ አከባቢ መሬት ገዝተን ቤት ሰርተን ከገባን ገና አመት አልሆነንም ነበር። ሹፌሩ በማላውቀው ወይም ባልለመድኩት መስመር ላዳዋን አዙሮ ሲነዳ ግራ ተጋብቼ የኔ ወንድም ወዴት ነው የምትወስደኝ ስለው አይ በዚ በኩል አቋራጭ መንገድ አለ ይቀርበናል ብዬ ነው አለኝ እኔም በጣም ስለመሸ ምናልባት እንዳለውም ቶሎ ያደርሰን ይሆናል ብዬ ዝም አልኩ ጥቂት ከተጓዝን በኃላ የመብራት ብርሃን እንኳን በሌለበት ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ በድንገት መኪናዋን አቆማት ምነው ምን ሆንክ አልኩት ደንግጬ። እኔንጃ መኪናዋ ተበላሽታ ነው መሰለኝ ቆይ ወርጄ ከኃላ ልያት አለኝና ወርዶ የኃላውን ኮፈን ከፈተው ብዙም ሳይቆይ እኔ የነበርኩበትን የኃላ በር ከፍቶ ይቅርታ ከጎንሽ የእጅ ባትሪ አለ አቀብይኝ አለኝ ግራ ተጋብቼ "የቱጋ ነው" ብዬ ወደጎኔ ስዞር አንገቴ ስር የሽጉጥ አፈሙዝ ደቀነብኝ፡፡
አንዲት ነገር እተነፍሳለው እጮሃለው ብትይ በአንዲት ጣቴ ብቻ ምላጯን ስቤ እስከዘላለሙ አሰናብትሻለው አለኝ ወንድሜ ገንዘብ ከፈለክ ቦርሳዬ ውስጥ ያለውን ሁሉ ውሰድ እያልኩ ተንተባተብኩ፡፡ ገንዘብሽን ሳይሆን ገላሽን ነው የምፈልገው አሁን አንድ በአንድ የለበስሽውን አውልቂ አለኝ ለመንኩት እባክህ የሁለት ልጆች እናት ነኝ እባክህ ባለትዳር ነኝ አልኩት ግን አልተሳካልኝም ሽጉጡን ወደኔ እያቀረበው በሄደ ቁጥር ነፍሴ ተጨነቀች ልጆቼ በአይምሮዬ ውስጥ ተመላለሱ እንባ ሳይሆን ደም እያነባሁ ያለኝን ነገር ሁሉ ፈፀምኩ የተመኘውን ገላ እንደልቡ ተጫውቶበት ሲያበቃ ለፖሊስ እጠቁማለው ለሰው አወራለው ብትይ እጨርስሻለው አለኝ።
እራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩና ህመሜን ስብራቴን ዋጥ አድርጌ ውይ ምን ችግር አለው በፊትም እኮ ሳታስገድደኝ እንዲሁ ብትጠይቀኝ እንስማማ ነበር ሽጉጡን ስላየሁ ነው እንጂ የደነገጥኩት ምንም ችግር አልነበረውም ባይሆን ስልክ ቁጥርህን ስጠኝና ሌላ ጊዜ ተደዋውለን በሰፊው አሪፍ ጊዜ እናሳልፋለን አልኩት።
ከት ብሎ ሳቀና ባንቺ ቤት አሁን ምንም የማላውቅ ፋራ አርገሽኛል አለኝ እኔም ያለ የሌለ መሀላ እየደረደርኩ ላሳምነው ሞከርኩ በመጨረሻም ያንቺን ስልክ ቁጥር ስጪኝና እኔ ደስ ባለኝ ቀን እደውልልሻለው አለኝ ሰጠሁት ከዛም ወደ ቤቴ አድርሶኝ ልክ ምንም እንዳልተፈጠረ እየሳኩኝ ደስተኛ መስዬ አመስግኜው ተለየሁት።
እቤት ስደርስ ቁጭ ብሎ የሚጠብቀኝ ባለቤቴ ላይ ተጠምጥሜ እያለቀስኩ ያጋጠመኝን ሁሉ ነገርኩት ድንጋጤ ድንዝዝ ቢያደርገውም እኔ እንድረጋጋ ብቻ አቅፎ ሲያባብለኝ ቆየና ጠዋት ለፖሊስ እንደምናመለክት ነግሮኝ አደርን።
በንጋታው ወደ ሆስፒታል ሄጄ ሙሉ ምርመራ አድርጌ ኤች አይ ቪ ለመመርመር ከ3 ወር በኃላ ደግሜ እንድመጣ ነግረውኝ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ካመለከትን በኃላ ወንጀለኛውን ለመያዝ ብቸኛው አማራጭ ያን ቀን ስልኬን ስለሰጠሁት እስኪደውል ብቻ መጠበቅ ነበርና ከ1 ሳምንት በኃላ ቅዳሜ ቀን የማላውቀው ቁጥር ተደወለ ሳነሳው እሱ ነው ምንም እንዳልተፈጠረ እንባዬን ወደ ውስጤ እየመለስኩ በሰላም አወራሁት ድምፁንም እየቀዳሁት ነበር።
ሰሞኑን ሁኔታዎችን አመቻችቶ እንደምንገናኝ ነገረኝና ዘጋው እሄን ለፖሊስ አመልክቼ በቀጣይ እስኪደውል መጠባበቅ ጀመርኩ ከ3 ቀን በኃላ በሌላ ስልክ ቁጥር ደወለ አሁንም ሰላም ብሎኝ ዘጋው በንጋታው በሌላ ስልክ ቁጥር ደወለ አሁንም አንምግሮኝ ዘጋ በ4ኛው ላይ ልክ መጀመርያ ቀን በደወለበት ስልክ ደግሞ ደወለ ሰሞኑን እንደምንገናኝ ነገረኝ ፖሊሶችም ድጋሜ የደወለበትን ስልክ ይዘው የታክሲ ደንበኛ በመምሰል ደወሉለትና ለስራ እንደሚፈልጉት ነግረው ያዙት እኔ ተጠርቼ ሄድኩኝ ሳየው እራሱ ነው ዘልዬ ላንቀው ስል አጠገቤ የነበረው ፖሊስ ያዘኝ የክስ መዝገብ ተከፍቶ ምርመራ ተደርጎበት ሰውዬው ከዚ በፊትም ብዙ የወንጀል ሪከርድ እንደነበረበት ታውቆ የ16 አመት እስራት ተፈረደበት።
እኔ ከ 3 ወር በኃላ ሀኪም ቤት ሄጄ ኤች አይ ቪ ስመረመር በደሜ ውስጥ ቫይረሱ እንዳለ ተነገረኝ። ዛሬ ፈጣሪና ውዱ ባለቤቴ ከጎኔ ባይኖሩ ኖሮ በህይወት አልኖርም ነበር እራሴን ለማጥፋት ስሞክር ስንቴ ከሞት አፋፍ ተርፌያለሁ ቆይቼ ሳስበው ግን ቢያንስ ለልጆቼና በቫይረስ መያዜን እንኳን እያወቀ እስከዛሬ ከጎኔ ላልተለየኝ ባለቤቴ ስል መኖር እንዳለብኝ ገብቶኛል። ግን ሁሌም እፈራለው ምክንያቱም ሴት ልጆች ወልጃለው የኔ እጣ እንዳይደርሳቸው ሁሌም እፈራለው ከትምህርት እስኪገቡ እንኳን ልቤ አይረጋጋም እንደ እስረኛ ከግቢ አላሶጣቸውም ሱቅ እቃ እንዲገዙ እንኳን አልካቸውም።
ይህ ሁሉ ከሆነ 7 አመት አልፎታል እኔ ግን ዛሬም ህመምተኛ ነኝ ልቤ ተሰብሯል ፈሪ ነኝ ትንሽ ነገር ያስደነግጠኛል እራሴን አሞኝ ከተኛሁ በዛው ሞቼ የምቀር ይመስለኛል ልጆቼ የኔ እጣ እንዳይደርሳቸው ያስጨንቁኛል እኔን ብሎ ብዙ የተጎዳው ባለቤቴ ያሳዝነኛል። የኔ ውድ ባለቤቴ የልጅነቴ ታመምሽ ተበላሸሽ ብሎ ያልሸሸኝ እሱ ብቻ ነው። ሴት እህቶቼ ሴት ልጆቼ ከኔ ታሪክ ተማሩ ተጠንቀቁ።
ከቁምነገር ሶሻል ሚዲያ
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow
9 785
#ትውስታ
ታሪኩ እንዲህ ነው...
ክቡር ዳኛው የክስተቱን ዝርዝር ሁኔታ ከሰሙ በኋላ ልጁን እንዲህ ሲሉ ጠየቁ...
"በእርግጥ የሆነ ነገር ሰረቅክ? ዳቦና አይብ ሰርቀህ መደርደሪያ ሰባበርክ?"
ልጁም አንገቱን ደፍቶ በሃፍረት፡- "አዎ" ሲል መለሰ።
ዳኛ፡ "ለምን ሰረቅክ?"
ታዲጊው ልጅ: "በጣም ፈልጌው ነው።"
ዳኛ፡ "ከመስረቅ ይልቅ መግዛት አልቻልክም ነበር?"
ልጅ፡ "ምንም ገንዘብ አልነበረኝም። "
ዳኛ፡ "ወላጆችህን ገንዘብ ልትጠይቅ ትችል ነበር። "
ልጅ፡ "እኔ ያለኝ፣ አልጋ ላይ የተኛች እና ስራ የሌላት የታመመች እናት ብቻ ነው... ለሷ ስል ዳቦና አይብ ሰርቄያለሁ"😪
ዳኛ፡ "እና አንተ... ምን እየሰራህ ነው? ሥራ የለህም?"
ልጅ፡- "የመኪና አጣቢ ሆኜ እሰራ ነበር። እናቴን ለመርዳት አንድ ቀን ዕረፍት ወሰድኩ፣ ለዚህም ነው ያባረሩኝ።"
ከልጁ ጋር የነበረው ውይይት ካለቀ በኋላ ዳኛው ፍርዱን አስታወቁ፡-
“ሌብነት በተለይም ዳቦ መስረቅ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው። ለዚህ የስርቆት ወንጀል ሁላችንም ተጠያቂ ነን። ለዚህ የስርቆት ወንጀል ዛሬ እኔ ራሴን ጨምሮ እዚህ ክፍል ውስጥ የተገኘ ሁሉ ተጠያቂ ነው” አሉ።
በመቀጠልም "ሁሉም ተሰብሳቢዎች 10 ዶላር ይቀጣሉ እና ማንም ሰው 10 ዶላር ሳይከፍል ከአዳራሹ አይወጣም::"
ዳኛው ከኪሳቸው የ10 ዶላር ቢል አውጥተው እስክሪብቶ አነሱና እንዲህ ብለው መጻፍ ጀመሩ።
"በተጨማሪም የተራበውን ልጅ ለፖሊስ ያደረሰው ሱቅ ባለቤት 1000 ዶላር እንዲቀጣ አዝዣለሁ እናም ቅጣቱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ካልተከፈለ ሱቁ ተዘግቶ ይቆያል።"
ዳኛው አክለውም “አንድ ሰው ዳቦ ሲሰርቅ ከተያዘ መላው የዚች ሀገር ህዝብና መሪ ሊያፍር ይገባል” አሉ።
በአዳራሹ ውስጥ የነበሩት ሁሉ ልጁን/ታዳጊውን/ ይቅርታ ጠይቀው ሙሉ ገንዘቡን ሰጡት።
ዳኛው እንባቸውን ለመደበቅ እየሞከሩ ከችሎቱ ወጡ።
ተሰብሳቢዎቹ የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ ዓይናቸው በእንባ ተሞላ።
ከማህበራዊ ሚዲያ አግኝተነው ስለወደድነው አጋራናችሁ።
እናንተስ ይህን ታሪክ በሚመለከት ምን ትላላችሁ?
እኛ ሀገር ቢሆን ምን የሚፈጠር ይመስላችዋል?!
ሃሳባችሁን አጋሩን።
ታሪኩን አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ #like #share ማድረግን #አትርሱ
በዚሁ አጋጣሚ በፊታቸው የሚቀርቡትን ሁሉ በእዝነት እና እጅግ ትህትና በተሞላበት መንገድ በማናገር፣ በፍፁም ቅንነት በመዳኘት እና ችግራቸውንም ለመረዳት በሚያደርጉት ጥረታቸው በዓለም እጅግ ልበቀና በመባል ለሚታወቁት ዳኛ ፍራንክ ካፕሪዮ ነፍስ ይማር እንላለን።
ከሶሻል ሚዲያ
t.me/changeitwow
9 785
ታሪኩ እንዲህ ነው...
ክቡር ዳኛው የክስተቱን ዝርዝር ሁኔታ ከሰሙ በኋላ ልጁን እንዲህ ሲሉ ጠየቁ...
"በእርግጥ የሆነ ነገር ሰረቅክ? ዳቦና አይብ ሰርቀህ መደርደሪያ ሰባበርክ?"
ልጁም አንገቱን ደፍቶ በሃፍረት፡- "አዎ" ሲል መለሰ።
ዳኛ፡ "ለምን ሰረቅክ?"
ታዲጊው ልጅ: "በጣም ፈልጌው ነው።"
ዳኛ፡ "ከመስረቅ ይልቅ መግዛት አልቻልክም ነበር?"
ልጅ፡ "ምንም ገንዘብ አልነበረኝም። "
ዳኛ፡ "ወላጆችህን ገንዘብ ልትጠይቅ ትችል ነበር። "
ልጅ፡ "እኔ ያለኝ፣ አልጋ ላይ የተኛች እና ስራ የሌላት የታመመች እናት ብቻ ነው... ለሷ ስል ዳቦና አይብ ሰርቄያለሁ"😪
ዳኛ፡ "እና አንተ... ምን እየሰራህ ነው? ሥራ የለህም?"
ልጅ፡- "የመኪና አጣቢ ሆኜ እሰራ ነበር። እናቴን ለመርዳት አንድ ቀን ዕረፍት ወሰድኩ፣ ለዚህም ነው ያባረሩኝ።"
ከልጁ ጋር የነበረው ውይይት ካለቀ በኋላ ዳኛው ፍርዱን አስታወቁ፡-
“ሌብነት በተለይም ዳቦ መስረቅ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው። ለዚህ የስርቆት ወንጀል ሁላችንም ተጠያቂ ነን። ለዚህ የስርቆት ወንጀል ዛሬ እኔ ራሴን ጨምሮ እዚህ ክፍል ውስጥ የተገኘ ሁሉ ተጠያቂ ነው” አሉ።
በመቀጠልም "ሁሉም ተሰብሳቢዎች 10 ዶላር ይቀጣሉ እና ማንም ሰው 10 ዶላር ሳይከፍል ከአዳራሹ አይወጣም::"
ዳኛው ከኪሳቸው የ10 ዶላር ቢል አውጥተው እስክሪብቶ አነሱና እንዲህ ብለው መጻፍ ጀመሩ።
"በተጨማሪም የተራበውን ልጅ ለፖሊስ ያደረሰው ሱቅ ባለቤት 1000 ዶላር እንዲቀጣ አዝዣለሁ እናም ቅጣቱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ካልተከፈለ ሱቁ ተዘግቶ ይቆያል።"
ዳኛው አክለውም “አንድ ሰው ዳቦ ሲሰርቅ ከተያዘ መላው የዚች ሀገር ህዝብና መሪ ሊያፍር ይገባል” አሉ።
በአዳራሹ ውስጥ የነበሩት ሁሉ ልጁን/ታዳጊውን/ ይቅርታ ጠይቀው ሙሉ ገንዘቡን ሰጡት።
ዳኛው እንባቸውን ለመደበቅ እየሞከሩ ከችሎቱ ወጡ።
ተሰብሳቢዎቹ የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ ዓይናቸው በእንባ ተሞላ።
ከማህበራዊ ሚዲያ አግኝተነው ስለወደድነው አጋራናችሁ።
እናንተስ ይህን ታሪክ በሚመለከት ምን ትላላችሁ?
ሃሳባችሁን አጋሩን።
ታሪኩን አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ #like #share ማድረግን #አትርሱ
በዚሁ አጋጣሚ በፊታቸው የሚቀርቡትን ሁሉ በእዝነት እና እጅግ ትህትና በተሞላበት መንገድ በማናገር፣ በፍፁም ቅንነት በመዳኘት እና ችግራቸውንም ለመረዳት በሚያደርጉት ጥረታቸው በዓለም እጅግ ልበቀና በመባል ለሚታወቁት ዳኛ ፍራንክ ካፕሪዮ ነፍስ ይማር እንላለን።
የህይወት ፍልስፍና
9 785
$$$💰600 ሚሊዮን ዶላር በእርሻው ቦታ ያገኘው ገበሬ...
እናንተ ብትሆኑ ምን ታደርጋላችሁ?
አንድ ኮሎምቢያዊ ገበሬ በእርሻው ላይ ሲሰራ 600 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ተቀብሮ አገኘ
📌ገንዘቡ የሟቹ አደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ የነበረው ፓብሎ ኤስኮባር ሊሆን ይችላል ተብሏል።
የኮሎምቢያ ሚዲያን ዋቢ በማድረግ ማርካ የተባለ የየቀን ጋዜጣ ድረ-ገፅ ከቀናቶች በፊት እንደዘገበው አንቲዮኪያ በተባለ ቦታ የተገኘው ገንዘብ ማንነቱ እንዳይገለጽ የፈለገው ገበሬ፣ የእርሻ ቦታውን ሲያሰፋ ከመሬት አንድ ሜትር በላይ ጥልቀት ላይ የተቀበሩ በርካታ የዛገ የብረት በርሜሎች አገኝቷል።
በርሜሎቹ በመቶዎች የሚቆጠሩ በጥቅል የታሰሩ በዋነኝነት የአሜሪካ ዶላር የባንክ ኖቶች የያዙ ሲሆን፣ እነዚህም በጥሩ ሁኔታ ተጠብቀው ተገኝተዋል።
የኮሎምቢያ ባለስልጣናት ግኝቱ እንደተነገረ ወዲያውኑ ገብተው የገንዘቡን ትክክለኛ ምንጭ ለመወሰን ምርመራ ጀመሩ። የመጀመሪያው ግምት እንደሚያሳየው፣ ገንዘቡ የ1980ዎቹ እና 1990ዎቹ የሜደሊን ካርቴል ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በቀላሉ ህጋዊ ማድረግ ወይም ማንቀሳቀስ ስላልተቻለ ለማከማቸት ይጠቀሙባቸው ከነበሩት መደበቂያዎች አንዱ ሊሆን ይችላል ተብሏል።
ይህ የፓብሎ ኤስኮባር ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘበት አይደለም። ዝናው በከፍተኛ ደረጃ በነበረበት ጊዜ፣ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪው ራሱ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በእርሻ ቦታዎችና በጫካ ውስጥ ደብቆ ነበር። ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹ በ1993 ከሞተ በኋላ ተረስተው ነበር።
ይህ ግኝት ስለ አፈ ታሪካዊው "ፓብሎ ኤስኮባር ሀብቶች" ፍላጎትን እንደገና አነሳስቷል፣ ነገር ግን የገበሬውን እና የቤተሰቡን ደህንነት በተመለከተም ስጋትን ፈጥሯል።
የጉስታቮ ፔድሮ መንግስት አሁን ገንዘቡን መውረስ ወይም ለገበሬው ሽልማት መስጠት እንዳለበት እያጤነ ነው።
ከሶሻል ሚዲያ
ራስን መለወጥ
9 785
አስተማሪ የሆነ ንግግሮች!
=======////=======
1. ጎንበሥ ቀና ብዬ ባገለግላቸው ከወንዝ የተገኘ ድንጋይ
መሠልኳቸው
2. መዶሻ ጭንቅላት ያለው ሰው ሁሉም ሰው ሚስማር
ይመስለዋል
3. ከሰራህ ትበላለህ ካልሰራ ሲበሉ ታያለህ
4. ቅናት ያገረጣዉ ፊት ቅባት አያወዛዉም
5. እስቲ ይሁን ብለን የተከልነዉ ቀጋ ጎንበስ ጎንበስ አለ እኛኑ
ሊወጋ
6. መሀይም ሀብታም፤ ደሃን የፈጠረ ይመስለዋል
7. ምን ጊዜው ቢረዝምም ቋንጣ እና ባለ ስልጣን መውረዱ
አይቀርም
8. የቅንድብ ፀጉርና ምቀኛ አያድጉም
9. ንፁህ ህሊና ምቹ ትራስ ነዉ
10. ጧት ስትሄድ በእንቅፋት የመታህ ድንጋይ ማታ ከደገመህ
ድንጋዩ አንተ እንጂ እሱ አይደለም
11. ጠጋ ጠጋ በሉ ሁሉም ቅርብ ወራጅ ነው ከፈጣሪ በቀር
12. የሰው ልጅ አረም የበዛበት የመከራ ተክል ነው
13. የሚፈልገውን ያላገኘ ልብ ዘውትረ መንገደኛ ነው
14. የአለም ሙቀት መጨመር መንስኤ ጭቅጭቅ ነው
15. ባለጌና ዋንጫ ወደ አፉ ሰፊ ነው
16. ማንበብ ከቻልክበት ሁሉም ሰው መፅሀፍ ነው
17. ለኛ ከራሳችን የበለጠ የሚያስብልን የለም
18. ማንም ሠው የጣለውን ሲያነሱበት አይወድም
19. ሲጠሉህ ሳይሆን ሲወዱህም ለምን በል
20. አለመዘጋጀት ለውድቀት መዘጋጀት ነው
21. ኑሮና ታክሲ ካልታገሱት አይሞላም
22. አንድን ሳትይዝ ሁለትን አታገኝም
23. ሱሪህን ሳይሆን ራስህን ዝቅ አድርገህ ኑር
24. ለመኖር ብላ እንጂ ለመብላት አትኑር
25. የጊዜ እንጂ የሰው ጀግና የለውም
26. እንደ ባሪያ ከሰራ እንደ ንጉስ ትኖራለህ
27. ሰዉን ማመን ቀብሮ ሳይሆን ቀብድ ተቀብሎ ነዉ
28. በፍቅር ለወደቀ የመሬት ስበት ተጠያቂ አይደለም
29. በሰዉ ላይ ከምትስቅ መጀመሪያ ራስህን እወቅ
30. ዝቅ ብሎ የሠራ ከፍ ብሎ ይኖራል
31. የሰነፍ አእምሮ የሰይጣን ቤተ ሙከራ ነዉ
32. ለስራ ያልታደለ አእምሮ ለተንኮል ማንም አይወዳደረዉም
33. የሴት ልጅ ውበቷ ታማኝነቷ
34. መኖር ደጉ ብር ባያስቆጥረን ቀን ያስቆጥረናል
35. የእናት ሞትና የድንጋይ መቀመጫ እያደር ይቆሮቁራል
36. "ቀስ ብሎ ማደግን ሳይሆን ቁሞመቅረትን ፍራ"አለች
ባጃጅ!!!
ከሶሻል ሚዲያ
t.me/changeitwow
9 785
+1
የሀበሻ እጀ ሰፊነት ተመሰከረ
📌ኢትዮጵያዉን ችሮታ በማድረግ ከአለም ሀገራት 22ኛ ደረጃን ያዙ።
በየአመቱ የአለም ሀገራትን የችሮታ ደረጃ የሚያወጣው የአለም ልግስና ሪፖርት በ2025 ኢትዮጵያን ከ101 ሀገራት 22ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧል።
ሪፖርቱ ኢትዮጵያውያን የገቢያቸውን 1.51 ፐርሰንት ለበጎ አድራጎት ስራዎች፣ ለሀይማኖታዊ ምፅዋትና ለሌሎች ልገሳዎች ያውላሉ ብሏል።
ሪፖርቱ አፍሪካውያን ከሌሎች አህጉራት ጋር ሲነፃፀር የተሻሉ ለጋሾች እንደሆኑም አሷይቷል።
አውሮፓዉያን የገቢያቸውን 0.64 ፐርሰንት ሲለግሱ አፍሪካውያን ግን የገቢያቸውን 1.5 ፐርሰንት ወይም የአውሮፖውያንን እጥፍ ያህል ይለግሳሉ።
አፍሪካውያን በብዙ ኢኮኖሚያዊ ጫና ውስጥ ሆነዉ የተሻለ ልገሳ ማድረጋቸው ችሮታ ከሀብት በዘለለ ከጥብቅ ማህበረሰባዊ ግኑኝነትና ሀይማኖታዊ ምክንያቶች የሚመነጭ እንደሆነ አሷይቷል።
ራስን መለወጥ
9 785
«ግመሏን እንጂ አልማዞቹን አልገዛሁም ስለዚህ አሁኑኑ አልማዞቹን ለባለቤቱ መመለስ አለብኝ»
ግመል ነጋዴው በገበያው ውስጥ ገብቶ ለሽያጭ ከቀረቡት ግመሎች መካከል በአንዱ እጅግ ስለተሳበ ከሻጩ ጋር በዋጋ ለመስማማት በዋጋ መደራደር ጀመረ።
በኋላም በዋጋ ተስማምቶ ግመሉን ገዝቶ ወደ ቤቱ ሄደ።
የግመል ነጋዴው ቤቱ እንደደረሰ አገልጋዩን ጠርቶ የግመሉን አናቦ እንዲያወርድ ይነግረዋል።
አገልጋዩ የግመሉን አናቦ ሲፈታ ከአናቦው ሥር አነስተኛ መጠን ያላት የተቋጠረች ከረጢት ያገኛል።
ከረጢቷን ሲፈታ በውድ የአልማዝ ማእድን ተሞልታለች።
አገልጋዩም "አለቃ የገዟት ግመል በነጻ ጭና ያመጣችውን በረከት ይመልከቱ!" ሲል በደስታ ተሞልቶ ጮኸ።
ነጋዴውም በአገልጋዩ መዳፍ ላይ በጸሐይ ብርሀን የሚንቦጎቦጉ የአልማዝ እንክብሎች ሲመለከት እጅግ ተደነቀ።
ይሁንና "ግመሏን እንጂ አልማዞቹን አልገዛኋቸውም። አሁኑኑ ለባለቤቱ መመለስ አለብኝ" አለ - ነጋዴው።
አገልጋዩም "ምን የማይረባ አለቃ ነው ያለኝ?!" ሲል በሆዱ ካወራ በኋላ "ማንም ሰው የአልማዞቹን ትክክለኛ ባለቤት ሊያውቅ አይችልም! ሲል ተናገረ።
ይሁንና ነጋዴው ምክሩን ችላ ብሎ ጊዜ ሳይወስድ ባለቤቱን ፍለጋ ወደ ገበያው ተመለሰ።
ብዙም ሳይለፋ የተቀሩ ግመሎችን ለመሸጥ ገዢ ሲጠብቅ የነበረውን የግመል ሻጭ አግኝቶ ትንሿን ከረጢት መለሰለት።
የግመል ሻጩም እጅግ ተደስቶ " እጅግ የከበሩ ማእድናቴን በአናቦው ስር መደበቄን ዘንግቼ ነበር።
አሁን ሽልማት እንዲሆንህ በከረጢቱ ውስጥ ካሉት አልማዞች ውስጥ ለዐይንህ ደስ ያሰኘህን ውሰድ!' አለው...
"ለከፈልኩት ገንዘብ ጥሩ ግመል ሽጠህልኛል።
ተጨማሪ ሽልማትም ስጦታም አልቀበልም።" አለ - ነጋዴው።
ነጋዴው ስጦታውን አልቀበልም ቢልም ግመል ሻጩ እንዲቀበለው ይወተውተው ጀመር።
በመጨረሻም ነጋዴው በፈገግታ ተሞልቶ "ከረጢቱን ልመልስልህ ስወስን ሁለት እጅግ የከበሩ አልማዞችን እራሴ ዘንድ አስቀርቻለሁ! ከእነርሱ የሚልቅ ሽልማት የለም!" አለው።
የግመል ሻጩ የነጋዴው የእምነት ቃል ሲሰማ እጅግ ተበሳጭቶ በከረጢቱ ውስጥ ያሉትን ውድ አልማዞች የጨርቅ እራፊ ላይ ደፍቶ ይቆጥራቸው ጀመረ።
ይሁንና ቆጠራውን እንደጨረሰ በእፎይታ ተሞልቶ "በከረጢቱ ውስጥ ከነበሩት አልማዞቼ መካከል አንድም አልጎደለም። የትኞቹን ውድ አልማዞች ነው ለራሴ አስቀርቻለሁ ያልከኝ?"
ነጋዴውም በኩራት ተሞልቶ «እኔ ዘንድ ያስቀረኋቸው ውድ አልማዞች ታማኝነቴና ለእራሴ ያለኝ ክብር ናቸው!» ሲል መለሰለት።
hሶሻል ሚዲያ
ራስን መለወጥ
9 785
ማይክል ጆርዳን & ስኬት
ሰዎች እኔ በተፈጥሮ ችሎታ እንደተወለድሁ ይመስላቸዋል…
ነገር ግን ስንት ጊዜ እንደወደቅኩ አያውቁም።
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የቡድን የስም ዝርዝር በተለጠፈ ሰዓት ስሜ አለመጻፉን ባየሁ ጊዜ ዓለም ተደፍታብኝ ነበረች በክፍሌ ውስጥ ዘግቼ፣ በዝምታ አምርሬ አለቀስሁ።
በኮሌጅ ውስጥ በቂ አቅም ጉልበትና ችሎታ የለህም ተብዬ ተነገርኝ። በNBA ውስጥ በተደጋጋሚ ተሰልፎ ጨዋታ እድል አጣሁ፣ ማድረግ ነበረብኝ የማልቻለው ግድግዳ ነበር፣ በዝምታም ክብደቱን ተሸከመሁ። ከ9,000 በላይ ኢላማቸው ያልጠበቁ ውርወራዎችን ሆኖው ከሸፉብኝ፣ 26 ጊዜ የጨዋታውን ድል የሚያመጣ ውርወራ በእጄ ነበር… ነገር ግን አልተሳካልኝም እና አልቻልኩም። ነገር ግን በህይወቴ የሚያሳዝነኝ ጊዜ በመዳረሻ ላይ አልነበረም።የአባቴ መግደል ነበር። እርሱ ምርጥ ጓደኛዬ፣ መካሪዬ፣ መምህሬ ሁለንትናዬ ነበር። ከዚያ በኋላ ከቅርጫት ኳስ (ከባስኬት ቦል) ርቄ ሄድሁ። ህመሙ በጣም ጥልቅ ነበር እንኳን ኳስ መጫወት ኳስን መንካት አልቻልኩም።
ከዚያ በኋላ ላይ ያባቴ ለኔ መልካምነት ላደረገልኝ ጥሩነገሮች እሱን ማክበር ምስጋና ለመናገር ምርጥ መንገድ በየጨዋታው እንደ መጨረሻ ጨዋታዬ በመጫወት መመለስ መሆኑን ተረዳሁ። ምክንያቱም እሱ በኔ አመነ፣ እኔ በእራሴ ባላመንኩበት ጊዜ እንኳ።
አንዳንድ ሰዎች “አትችልም” ሲሉህ አትተው።
አንዳንድ ጊዜ ዛሬ እንደ መሸነፍ የሚሰማው ነገር ዘላቂ ለሆነ ሕይወትህን የሚለውጠው ግፊት ሊሆን ይችላል።
ህመም አያጠፋህም — ያሻሽልሃል።
ከፈቀድህለት።
— ማይክል ጆርዳን በትንሹ
ማይክል ጄፍሪ ጆርዳን፣ የ“ኤይር ጆርዳን” ተብሎ የሚታወቀው፣ ቀድሞ የባስኬትቦልና የቤዝቦል ባለሙያ ተጫዋች፣ ንግድ ሰው እና የጽናትና የጥንካሬ አርማ ነው። በ1963 ዓ.ም ተወለደ፣ ጆርዳን በዘመናት ውስጥ ከሁሉ ታላላቅ የባስኬትቦል ተጫዋቾች አንዱ በመሆኑ በበለጠ ይታወቃል። በ1990ኛው ዐሥርተ ዓመት የቺካጎ ቡልስን ወደ ስድስት የNBA ሻምፒዮናዎች መሪ ሆኖ ያመጣ ሲሆን፣ በያንዳንዱ ጊዜም የፋይናል ተፅዕኖ ተጫዋች (MVP) ተመርጧል። ጆርዳን የመዝለል ችሎታውና የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎቹ የጥንካሬ ተምሰሌቶቹ በስም አድርገው የጠሩትን ቅድመ ስም ፣ ይህም በኋላ ታዋቂ የናይክ ጫማ ተወዳጅ ብራንዱ ስም ሆኗል።
t.me/changeitwow
