en
Feedback
ራስን መለወጥ

ራስን መለወጥ

Open in Telegram

እንዴት ናችሁ? ቢዝነስ ፕላን(ቢዝነስ ዕቅድ) እንዲሰራለት የሚፈልግ በተመጣጣኝ ዋጋ  ቢዝነስ ፕላን እንሰራለን! በውስጥ መስመር ያናግረን! ለውጥ በትክክልም ይመጣል። 💪ዕድገታችንም ይሳካል!!! Hello everyone, we make best Business plan. In good price contact us inside! just pick a what kind of business plan! We can chang

Show more
9 785
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-8230 days
Posts Archive
photo content

#ሞቶም_ደግነት❗️ የተወዳጁ የቴሌቪዥን ዝግጅት አቅራቢ አስፋው መሸሻ መኪና በጨረታ ተወሰደች #አስፋው_መሸሻ በህይወት ሳለ በአርቲስት ሰለሞን ቦጋለ እና በጓደኞቹ ለተመሰረተው ህብረት ለበጎ የተሰኝ
#ሞቶም_ደግነት❗️ የተወዳጁ የቴሌቪዥን ዝግጅት አቅራቢ አስፋው መሸሻ መኪና በጨረታ ተወሰደች #አስፋው_መሸሻ በህይወት ሳለ በአርቲስት ሰለሞን ቦጋለ እና በጓደኞቹ ለተመሰረተው ህብረት ለበጎ የተሰኝ የበጎ አድራጎት ድርጅት በልግስና የሰጣት 1993  G.C ሱዚኪ መኪና ለጨረታ የቀረበች ሲሆን ጋዜጠኛ ዮናስ ከበደን ጨምሮ በርካቶች በጨረታው ላይ ቢሳተፉም የሱዙኪ መኪና አስመጪ ኩባንያ በ2.2 ሚሊዮን ብር መኪናዋን የግሉ ማድረግ መቻሉን የደራው መጽሔት ተመልክቷል።ገቢውም ህብረት ለበጎ ለሚያሰራው ሆስፒታል የሚውል ስለመሆኑ ከአዘጋጆቹ ሰምተናል። t.me/changeitwow

ጠቃሚ ምክሮች !! ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 1ኛ ከሰዎች ጋር ሮጠህ ያልደረስክበት ነገር ካለ ወደ ተነሳህበት ተመልስህ ከፈጣሪህ ጋር መሮጥ ጀምር፣ያኔ ካስብክበት ሳይሆን ካሰበልህ ቦታ ትደርሳለህ። 2 በአ
ጠቃሚ ምክሮች !! ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ 1ኛ ከሰዎች ጋር ሮጠህ ያልደረስክበት ነገር ካለ ወደ ተነሳህበት ተመልስህ ከፈጣሪህ ጋር መሮጥ ጀምር፣ያኔ ካስብክበት ሳይሆን ካሰበልህ ቦታ ትደርሳለህ። 2 በአብዛኛው ጊዜ ሴቶች የፍቅርን ትርጉም የሚጠፋባቸው በውበታቸው ማምለክ ሲጀምሩ ሲሆን ወንዶች ደግሞ በገንዘባቸው ማምለክ ሲጀምሩ ነው። 3 መጀመርያ ለራስህ ራስህ መሆን ስትጀምር ለማን ምን መሆን እንዳለብህ ትገነዘባለህ። ያኔ ሰዎችንም ታግዛለህ 4 የሰው ልጅ የማስብ ችሎታው ሲጨምር የጓደኞቹን ብዛት ይቀንሳል። በብዛት ሳይሆን በጥራት እመን 5 ዝቅተኛ እውቀት ባለህ ቁጥር የምትተኛው እንቅልፍ ከፍተኛ ይሆናል ። 6 ጓደኛን አለማመን ከመካድ የከፋ ነው። ታላቁ እምነትን ግን ለፈጣሪ ስጥ 7 የራስህን ትኩስ እንጀራ ለመጋገር ስትል የሌላውን ቂጣ አትርገጥ። 8 አንዳንድ ስዎች የሚወድቁት ሌሎችን በሁለት እግሮቻቸው ሁለት የተለያየ ቦታ ለመርገጥ ሲጣጣሩ ነው። 9 ሰው ከጊዜ እና ከማጣት ብዙ ይማራል። 10 አንዳንዴ ሽንፈትም ከድል የበለጠ ዋጋ አለው/ ከማሽነፍ ይልቅ በመሸነፍ ውስጥ ብዙ እውቀት አለ። 11 አንዳንድ ሠው የበለጠ እያገኘ በሄደ ቁጥር የበለጠ ስግብግብ እየሆነ ይሄዳል። 12 ሠዎች ትርጉም ያለው ሥራ መስራት ካልቻሉ የመኖር ትርጉምም ይጠፋባቸዋል። 13 የሰው ልጅ ከስደታው ይልቅ የሀዘኑን ጊዜያት መቁጠር ይወዳል። በትዝታም ይኖራል 14 ባንኮች ዝናብ ሳይኖር ዣንጥላ ያበድሩህና መዝነብ ሲጀመር ግን ዣንጥላውን ይነጥቁሃል። 15 አዋቂ ሆኖ ለመታየት የምናደርገው ጥረትና ከንቱ ድካም አላዋቂ አድርጎ ያስቀራል:: አስተማሪ ሆኖ ካገኙት ለሌሎች ያጋሩት ራስን መለወጥ #Ethiopia #ethiopian #ethiopian_tik_tok #ethiopian_tik_tok🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

➡ ትክክለኛ ሰው ለመሆን የሚረዱ 20 ህጎች 1. ንግግርህን አሳንስ፣ ምልከታህን አብዛ — እውነተኛ ኃይል ዝምታ ውስጥ ነው። 2. በፍጹም አታሳድድ — እነሱ የሚከተሉት አንተ ሁን። 3. በጣም አስከፊ
➡ ትክክለኛ ሰው ለመሆን የሚረዱ 20 ህጎች 1. ንግግርህን አሳንስ፣ ምልከታህን አብዛ — እውነተኛ ኃይል ዝምታ ውስጥ ነው። 2. በፍጹም አታሳድድ — እነሱ የሚከተሉት አንተ ሁን። 3. በጣም አስከፊ ቀናትህ ላይ እንኳ እንደ ስኬታማ ሰው ተላበስ። 4. ፈጣን ምላሽ አትስጥ — ነገሥታት እኮ እነሱ እንዲጠብቋቸው ያደርጋሉ። 5. የወዳጆችህን ክበብ ትንሽ አድርግ፣ ምስጢሮችህን ደግሞ ከዛም በላይ ጥብቅ አድርግ። 6. ፈገግታህን ቀንስ፣ ግርማ ሞገስህን ጨምር። 7. ደግ ሁን፣ ነገር ግን በፍጹም ልፍስፍስ አትሁን። 8. ትኩረትህን እንደ ገንዘብ በልክ ስጥ — ሁሉም ሰው ሊገዛው አይችልም። 9. ቦታው ያንተ ባይሆንም እንኳ፣ የራስህ እንደሆነ አስመስለህ ተራመድ። 10. አትከራከር — ውጤቶችህ ይናገሩ። 11. ሳይጠበቁ ብቅ በል — ከዚያም በበለጠ ፍጥነት ከእይታ ስወር በል። 12. በዝምታ ራስህን ገንባ — ድምፅህን ከፍ አድርገህ የምትፎክረው አንድ ጊዜ ብቻ ይሁን። 13. ግድ ቢሰጥም ባይሰጥም እንዲገምቱ አድርጋቸው። 14. ያደረግኸውን ፈጽሞ አታብራራ — መናፍስት አይናገሩም። 15. ንዴትህን ተቆጣጠር — የጠላትህ ምርጥ ሰላይ እሱ ነው። 16. በጩኸት ሳይሆን በዝምታህ አደገኛ ሁን። 17. እንደ እሳት ተጫዋች (አሽኮርማሚ) ሁን፣ ቁርጠኝነትህ ግን እንደ በረዶ ይሁን። 18. ህመምን ወደ ኃይል ለውጥ — ሁልጊዜ። 19. ስምህ ከህልውናህ የበለጠ ክብደት እንዲኖረው አድርግ። 20. ስትሄድ ትዝታን ሳይሆን አሻራን ትተህ እለፍ። ከሳሙኤል ጥሩነህ t.me/changeitwow

🌅🌄 💚💛❤️ በአዲስ ዓመት የአባቶች ምርቃት እንካችሁ!! 💚💛❤️!
🌅🌄 💚💛❤️ በአዲስ ዓመት የአባቶች ምርቃት እንካችሁ!! 💚💛❤️!

#ኤለን_መስክ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃርነት ስፍራውን አስረከበ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር የነበረው አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤለን መስክ የቀዳሚነት ስፍራውን በኦራክል ኩባንያ መስራች ላሪ ኤሊሰን አስረክ
#ኤለን_መስክ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃርነት ስፍራውን አስረከበ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር የነበረው አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤለን መስክ የቀዳሚነት ስፍራውን በኦራክል ኩባንያ መስራች ላሪ ኤሊሰን አስረክቧል። አጠቃላይ 385 ቢሊየን ዶላር ሀብት የነበረው ኤለን መስክ እስከ ትናንትና ድረስ 101 ቢሊየን ዶላር ሃብት በነበረው ላሪ ኤሊሰን በስምንት ቢሊየን ዶላር ተበልጦ የዓለም ቁጥር ሁለት ቱጃር ሆኗል። ላሪ ኤሊሰን ትናንትናው ባወጣው የገቢ ሪፖርት አጠቃላይ ሀብቱ ወደ 393 ቢሊየን ዶላር ከፍ በማለቱ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር ለመባል በቅቷል። የዳታ አስተዳደር ኩባንያ ባለቤቱ አሊሰን በዚህ ፍጥነት ተምዘግዝጎ የዓለም ቁጥር አንድ ቱጃር መሆኑ ብዙዎችን ማስገረሙን ብሉምበርግ ዘግቧል። የኩባንያው የአክሲዮን ዋጋ ዛሬ ማለዳ ላይ በ40 በመቶ ከፍ ማለቱም ተነግሯል። t.me/changeitwow

1. የሌሎችን ምስጢር የሚነግሩህን ሰዎች አትመን፣ ምክንያቱም የአንተንም ይነግሩበሀል። 2. ደስተኛ ስትሆን ቃል አትግባ ፣ ምክንያቱም ስሜቶች ይጠፋሉና። 3. በተናደድክ ጊዜ ውሳኔ አትወስን፣ምክንያቱም በአመክንዮ ማሰብ አትችልምና። 4. ችላ የሚሉህን አታሳድድ ምክንያቱም ዋጋህን ታጣለህና። 5. ሳታስብ አትናገር ፣ ምክንያቱም ቃላት ወደ ኋላ መመለስ አይቻልም። 6. በአንድ ሰው ህይወት ላይ አትቅና ፣ ምክንያቱም ትግላቸውን ስለማታውቅ። 7. ያለፈውን ነገር ከመጠን በላይ አታስብ ፣ ምክንያቱም አይለወጥምና ። 8. ከትንሽ ለመጀመር አትፍራ፣ ምክንያቱም ትልልቅ ነገሮች ጊዜ ይወስዳሉ። 9. በሌሎች ላይ ፈጥነህ አትፍረድ፤ ምክንያቱም ዕውነት የመሰለን ቶሎ ግልፅ ላይሆን ይችላልና። 10. ዕቅዶችህን ቀደመህ ለማንም አትንገር ፣ ምክንያቱም ጉልበት በጩኸት ውስጥ ይጠፋልና። 11. እራስህን ለሁሉም አትግለጽ፣ ምክንያቱም ሁሉም ሰው ግልጽነትህ አይገባቸውም። 12. የግል ጉዳይህን ከስራ ጋር አትቀላቅሉ ፣ ምክንያቱም ድንበር አስፈላጊ ነው። 13. ታማኝነትን ከሁሉም ሰው አትጠብቅ ፣ ምክንያቱም ሁሉም ሰው እውነተኛ አይደለም። 14. ሁሉንም ሰው በህልምህ ጉዳይ አትመን ፣ ምክንያቱም ሁሉም እድገትህን አይደግፉም። 15. እራስህን ለመግለፅ ጊዜ አታባክን ፣ ምክንያቱም የምታደርገው ነገር ውጤቱ ጮክ ብሎ ይናገራል። 16. ዝምታን ደካማነት አድርገህ አትውሰድ ፣ ምክንያቱም ብዙውን ጊዜ ጥበብ ነው። 17. ሁልጊዜ ትክክል እንደሆንክ አድርገህ አታስብ ፣ ምክንያቱም መማር የማያቋርጥ ነው። 18. የአለህበትን ሁኔታ ከሌሎች ጋር አታወዳድር፣ ምክንያቱም የሁሉም ግብ መድረሻ የራሱ ግዜ አለውና። 19. ለበለጠ ነገር እያሰብክ ባነሰ ስኬት - የስኬት ጫፍ እንደደረስክ አታስብ። 20. ሁሌም ጥሩ መስለህ አትታይ ፈውስ እውነቱን መቀበል ያስፈልገዋልና። በጩኸት በተሞላ አለም ውስጥ፣ የምታመነውን መምረጥ በጊዜህ፣በዕምነትህ እና በጉልበትህ በትክክል መምረጥ የጥንካሬ አይነት ነው። መቼ እንደምትናገር ፣ መቼ እንደምትንቀሳቀስ እና እስከ መቼ መቆየት እንዳለብህ በመማር ሰላምህንን ጠብቅ። አስታውስ ▪▪▪ እድገትህ እሴቶችህንን ምን ያህል እንደሚጠብቅ እና ወደ ህይወትህ እንዲገቡ በፈቀድክላቸው ሰዎች ላይ ይወሰናል። አባት ለልጅ የሰጠው ምክር ሶሻል ሚዲያ ራስን መለወጥ t.me/changeitwow #Ethiopia #like #post #share@changeitwow

#ድንቅ_እውነተኛ_ታሪክ (the gifted hand) እንደ ፈረኝጆቹ አቆጣጠር በ 1961 ጥቁሮች በሚገፉበት እና በስንፍና ብቻ የሚታዩበት ወቅት ሂግንስ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚማር አንድ ጥቁር የአስር አመት የአምስተኛ ክፍል ተማሪ ልጅ ነበር። በክፍል ውስጥ ያሉ ተማሪዎችም ሆነ መምህራን ትምህርት የማይገባው ተማሪ ማነው ቢባሉ መጀመርያ የሚጠሩት ይሄን ልጅ ነበር። ልጁም ራሱን የሚያስበው ትምህርት እንደማይገባው ሰው ነው ይህ ልጅ የሚኖረው ከእናቱና ከአንድ ወንድሙ ጋር በሃገረ አሜሪካ በደቡብ ምዕራብ ዴትሮየት ግዛት ስፕሪንግዌልስ የምትባል የነጮች መንደር ውስጥ በከፋ ድህነት ውስጥ ነበር ምክንያቱም እናትና አባቱ በ8 አመቱ ተለያይተዋል እናት ደግሞ ቤተሰቡን ለመምራት አቅም ያንሳት ነበር። ይሄ ነገር ብዙ የማይገባው ልጅ ብዙ ጊዜውን የሚያሳልፈው በመዝፈንና ጌም በመጫወት ነበር ታድያ ከሚያገኘው የትምህርት ውጤት ማሽቆልቆል የተነሳ ከትምህርት ቤት ሊባረር ሆነ እናት ደግሞ ፣ ልጆቿ ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ከልቧ ታምናለች። እንዴት ስኬታማ እንደሚሆኑ ነው ያላወቀችው። ማሰብ ማሰላሰሏን ግን አላቋረጠችም። የሰፈሯን የድህነት አኗኗር በደንብ ታውቀዋለች። የሃብታሞች ሰፍር ሄዳ ቤት ስታፀዳም አኗኗራቸውን ትመለከታለች። ድሆቹንና ሃብታሞቹን የሚያለያቸው ምንድነው? አስተዋይ መሆኗ ጠቀማት። አንድ ቀን፣ በሃብታም ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ሰፊውን ክፍል እያፀዳችና ቴሌቪዥን የተቀመጠበትን አካባቢ እየጠራረገች ሳለ… ተገለጠላት። ተደራርበው የተቀመጡት መፃህፍት ቴሌቪዥኑን በከፊል ከልለውታል። አንዳንዶቹ መፃህፍት ገለጥ ገለጥ ተደርገው ተቀምጠዋል። ቀና ስትል… ያን የሚያክል ሰፊ ክፍል፣ ከወለል እስከ ጣራ ድረስ… መደርደሪያው ሁሉ በመፃህፍት ተጠቅጥቋል። በቃ! ገባት። ያን እለት በየቦታው ለሥራ ስትደክም ውላ ማታ ወደ ቤት ስትመለስ፣ ሁለቱ ልጆቿ አሮጌ ቴሌቪዥን ላይ አፍጥጠው አገኘቻቸው። ቴሌቪዢኑን አጠፋችው። “ ከዛሬ ጀምሮ፣ እዚህ ቤት ሶስት ህጓች አሉ:: 1ኛ በሳምንት የተመረጠ ሁለት የቲቪ ፕሮግራም ብቻ ነው የምታዩት:: 2ኛ ውጪ ወጥታችሁ ለመጫወትም ሆነ ቲቪ ለማየት መጀመርያ የቤት ስራቸሁን መጨረስ ግዴታ አለባችሁ:: 3ኛ በየሳምንቱ ሁለት መጽሃፍት ከቤተ መጽሃፍ ማንበብና ያነበባችሁትን ዘገባ ማቅረብ ይኖርባችኋል::" በመጀመርያ በሃሳቡ ያልተሰማማሙት ልጆች የናታቸው ድቆሳና ጫና ሲባዛባቸው የተባሉትን ማድረግ ጀመሩ መፅሃፍ ማንበብ፣ ለነሱ ቀላል አልሆነላቸውም። ትግል ነው። ግን ደግሞ፣ መፃህፍቱ ውስጥ በሚያገኟቸው አስደናቂ ታሪኮችና እውቀቶች… ተገርመዋል። እስካሁን የማያውቁትና ጨርሶ ያልጠበቁት አይነት ልዩ ደስታ አግኝተውበታል። ብዙም ሳይቆይ፣ መፅሃፍ ማንበብ፣ “ግዴታ” መሆኑ ቀረ። በንባብ ፍቅር፣ መፅሃፍ እንደያዙ ሌሊቱ ይጋመሳል። መፅሃፍ አንብቡ እያለች ስትወተውታቸው የነበረችው እናት፣ ቶሎ አንብበው በጊዜ እንዲተኙ መምከር ጀመረች። ብዙም ሳይቆይ ያ ትምህርት የማይገባው ልጅ በክፍል ውስጥ ጥያቄ ሲጠየቅ መልሱን እርሱ ብቻ ማወቅ ጀመረ:: ይህ ልጅ ፣ “ደደብ” እንዳልሆነ ገባው። የሳይንስም ሆነ የሂሳብ፣ የቋንቋም ሆነ የታሪክ ትምህርቶችን ሁሉ በቀላሉ መረዳት እንደሚችል ሲያይ፣ ለማመን ከብዶት ነበር። ግን፣ የፈተና ውጤቱም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሻሽሏል። በሁለተኛው አመት ደግሞ፣ ከክፍሉ አንደኛ ወጣ። ከዚያም ከትምህርት ቤቱ አንደኛ በመሆን ተሸለመ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ሲያጠናቅቅ በመላ አሜሪካ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎችን አወዳድሮ ወደሚቀበለው ዬል ዩኒቨርስቲ ገባ - በከፍተኛ ውጤት ነፃ የትምህርት እድል ተሰጥቶት። በቃ፤ የሚያቆመው አልተገኘም። ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ ገብቶ፣ የአንጎል ቀዶ ህክምናን በማጥናት ተመረቀ። በሳይንሳዊ ጥናቶች ዙሪያ፣ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲን የሚስተካከል የትምህርት ተቋም በአለማችን የለም። 33 የዩኒቨርስቲው ተመራቂዎችና አስተማሪዎች የኖቤል ተሸላሚ ሆነዋል። በዚህ ዩኒቨርስቲ ተምሮ መመረቅ ራሱ፣ለእርሱ ትልቅ ስኬት ነው። ግን አልበቃውም። ይህ የትናንቱ ልጁ የዛሬው ትልቅ ሰው ዶ/ር ቤንጃሚን ካርሰን ይባላል በየአመቱ ከሶስት መቶ በላይ ከባድ የቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት የብዙ ሰዎችን ህይወት አድኗል ይህ ብቻ አይደለም። በ1987 አ.ም ሁለት ጭንቅላታቸው ተጣብቀው የተወለዱ የሁለት ወር መንትዬች ሃያ ሁለት ሰአት በሚፈጅ ቀዶ ጥገና ማለያየት ችሏል ይሄን ስኬትም ያስመዘገበ ዶክተር ከዛ በፊት በአለም ላይ አልነበረም:: ዶ/ር ቤን ካርሰን በ2016 ዓ.ም ለአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ተወዳድሮ ነበር በኃላ ላይ ራሱን ከምርጫው ቢያገልም:: "ሁሉም ሰው አቅም አለው! መጽሃፍት ደግሞ ያንን አቅም ያወጡታል::" 'ቤን ካርሰን' ታሪኩን ሙሉውን ለማወቅ :- the gifted hand:- the ben carson story የሚል ድንቅ ፊልም ሙሉውን ታገኙታላችሁ። t.me/changeitwow ራስን መለወጥ #Ethiopia #like #share

photo content
+1

የእኔም ጉዳይ ነው! አንዲት አይጥ የቤቱ ባለቤት ወጥመድ ገዝቶ ወደ ቤት ሲገባ ትመለከታለች፡፡ አይጧ በጣም ደነገጠች፤ ወዲያውኑ ወደ ሰውዬው እርሻ ቦታ እየሮጠች በመሄድ ጮክ ብላ “በእርሻው ውስጥ ላሉ የቤት እንስሳት ወጥመድ እየተጠመደላችሁ ነው፤ ወጥመድ! ወጥመድ!!” በማለት ትጮሃለች፡፡ ይህን ድምፅ በንቃት የሰማችው ዶሮ "ካጎነበሰችበት ቀና በማለት “አይጦ" ላንቺ ምን ያህል እንደሚያስጨንቅሽ ይገባኛል፤ ነገር ግን እኔን አይመለከተኝም” አለቻት፡፡ አይጥም በግ ወደ ሚገኝበት ቦታ ትሄድና የቤቱ ባለቤት ወጥመድ ገዝቶ እንደመጣ ትነግረዋለች፡፡ በጉ በንቀት አይን እየተመለከታት “ይቅርታ አድርጊልኝ አይጦ ምንም ልረዳሽ አልችልም” ይላታል፡፡ በመጨረሻም አንድ የቀራት በሬ ነበርና ወደርሱም በመሄድ “ወጥመድ ተገዝቷል” ትለዋለች፤ በሬውም ከት ብሎ እየሳቀ “አይጦ ምን ነክቶሽ ነው! እኔ እንደው ወጥመድ ቆዳዬን እንኳ እንደማይጎዳው እያወቅሽ ፤ በይ አትቅልጂ” በማለት ያባርራታል፡፡ አይጧ በጣም ተበሳጭታ አንገቷን አቀርቅራ የገበሬውን ወጥመድ ብቻዋን ልትጋፈጥ ወደ ቤቷ ትመለሳለች፡፡ በዚያው ቀን ምሽት ሰው ሁሉ በተኛበት ወጥመዱ ከፍተኛ ድምፅ አሰማ፡፡ የገበሬው ሚስት "አስቸጋሪዋ አይጥ ተያዘች" በማለት አይጧ ወጥመዱን ጎትታ ይዛው እንዳትሄድ አስባ ወደስፍራው ታቀናለች፡፡ ነገር ግን እንዳሰበችው አይጧ ሳይሆን በወጥመዱ የተያዘውን አደገኛ እባብ ነበር እባቡም ሴትዮዋን ነደፋት፡፡ ገበሬው በፍጥነት ሚስቱን ወደ ሆስፒታል ይወስዳትና፤ ከታከመች በኋላ ወደ ቤት ትመለሳለች። ጎረቤቱ ሁሉ እየመጣ ይጠይቃት ጀመር በዚህ መሀል "የዶሮ" መረቅ መድሃኒት ነው ዶሮ ይታረድላት ይባልና ዶሮዋ ታረደች። ከጥቂት ቀናት በኋላ ደግሞ በቶሎ እንድታገግም ተብሎ "በግ" ይታረድላት ሲባል ከቀናት በኃላ "በጉ" ታረደ። ይህ ሁሉ እየተደረገላትም ህመሟ እየበረታ ሄደ በመጨረሻም ሴትዬዋ ሞተች። ለለቀስተኛው ዘመድ አዝማድ እና ጎረቤት "በሬው" ታርዶ ተበላ። አይጧ ይህንን ሁሉ ድርጊት በዛች የግድግዳ ቀዳዳ አጮልቃ ትመለከት ነበር፡፡ በድርጊቱ በጣም አዘነች፡፡ 📌.አለመደማመጥ እና አለመተባበር ብሎም ለችግራችን የጋራ መፍትሄ በአንድነት አለመፈለግ ደግሞም ችግሩ እኔን አይመለከተኝም በማለት ችግሩን ላለመጋፈጥ ችላ ማለትና መሸሽ ነገ እያንዳንዳችንን ትልቅ ዋጋ ያስከፍለናል። ስለዚህ አንድነት ኃይል ነውና ለማንኛውም ችግር በጋራ እንቁም❗ t.me/changeitwow

photo content

የሕክምና ገጠመኝ እውነተኛ ታሪክ ከዛሬ 11 ዓመት በፊት የተከሰተ ጤና ይስጥልን ኢትዮጵያዊት ዶክተር ነኝ ጳጉሜ 5 - 2005 ዓ/ም ዕለተ ማክሰኞ ከሌሊቱ 5:00 ሰዓት የሕክምና ገጠመኝ ቦታው ጅማ ዩኒቨርሲቲ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማህጸንና ጽንስ ሕክምና ክፍል ነገ እኮ በዓል ነው መስከረም 1 ነው አዲስ ዓመት ነው አውዳመት ነው እኛ ግን ሥራ ላይ ነን ====================== ዶ/ር S እባላለሁ በዕለቱ ተረኛ ኢንተርን ዶክተር ስለነበርኩኝ የተረኛ ቡድኑ አባላት አንድ ላይ ሆነን በ36 ሰዓታት አድካሚ የሥራ ግዳጅ ላይ ነበርን። ቀኑ አድካሚ የሥራ ቀን ነበረ። በእናቶች የምጥና ወሊድ ክፍል ውስጥ ነበርን። በቀኑ ከ30 በላይ እናቶችን በመደበኛ ምጥ በሠላም አዋልደን አዳዲሶቹን ጨቅላ ሕጻናት በሠላም ተቀብለናቸዋል። ጎንበስ ቀና ማለቱ እና ድካሙ ስለበዛብን ምሳ ለመብላት ምንም አይነት ፋታ አላገኘንም። ምሳ ሳንበላ በሥራ ተጠምደን መሸብን። ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ ሲሆን አጣዳፊ ምጥ የያዛት ሌላ ወላድ እናት ወደ ሆስፒታላችን ደረሰች። የታካሚያችን ስሟ ማርታ መሐመድ የምትባል፣ ዕድሜዋ 30 ገደማ፣ ከአጋሮ የመጣች፣ አጋሮ ላይ የራሷ የምግብ ቤት ያላት፣ ወፍራምና ቁመተ ረጅም፣ መልከ መልካም፣ ስትሆን እህቶቿ ና ወንድሞቿ ደግሞ ሁሉም እንደእርሷ ረጃጅሞችና መልከ መልካሞች ነበሩ። እናትየዋ ምጥ ላይ ከመሆኗና ለመውለድ ከመምጣቷ በቀር ፍጹም ጤናማ ነበረች እናም ወደ ምጥና ወሊድ ክፍል ተቀብለናት የእርሷንና የጽንሷን ጤንነት በሙሉ ንቃትና በተጠንቀቅ እየተከታተልን 3 ሠዓታትን በሠላም ከተሻገርን በኋላ ከደቂቃዎች በአንዱ ድንገተኛ ቸግር ተከሰተ በሆዷ ውስጥ ጽንሱ ድንገት መታፈን ጀመረ..... ይህ አይነቱ ሁኔታ የእንግዴ ልጁ እትብት ሲጠመጠም ወይም ሲታነቅ ሊከሰት ይችላል አስቸኳይ እርዳታ ተረባርበን ተጠራርተን ለእናትየዋ ብናደርግላትም ደግሞ ለጽንሱም የተለያዩ የሕክምና እርዳታዎችን ብናደርግለትም... ሰኮንዶቹ በቆጠሩ ቁጥር ጽንሱ መታፈኑን እየቀጠለ ነበር ...... እናትየዋ ግን ደህና ናት በመረባረባችን ግን አንዳች ነገር ታውቆአታል ተደናግጣለች ደቂቃዎች እየፈጠኑ ነው የጽንሱን ሕይወት ማትረፍ አለብን በብርሃን ፍጥነት መንቀሳቀስ ይኖርብናል አንዳች ስህተት ወይም መዘግየት የሕይወት ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል እናዝናለን ጽንሱን ከሞት ለመታደግ ድንገተኛ አስቸኳይ ኦፕራሲዮን ልናደርግሽ ያስፈልጋል አልናት ተባባሪ ነበረች እሺ አለች ወዲያውኑ መስማሚያውን ፈረመች ግን ለቤተሰቦቼ ንገሩልኝ አለችን ነገርናቸው ኦፕራሲዮን መሆን አለባት ስንላቸው እነዚያ መልከ መልካሞቹ እህቶቿና ወንድሞቿ በቁመታቸው ልክ እንባ እያፈሰሱ ድምጻቸውን አሰምተው ማልቀስ ጀመሩ እኛም ልባችን በሀዘን ድባብ ተመታ ግን ምንም ጊዜ የለንም ቆራጥ መሆንና ለመፍትሄው መቸኮል አለብን እና ወደ ኦፕራሲዮን ክፍል ይዘናት ገባን ከምሽቱ 5:00 ሰዓት ነበር ወዲያው ቆንጅዬ ሴት ሕጻን በሕይወት ሳለች ደረስንላትና ተወለደች ለእናትየዋ እህቶች ሕጻኗን ሰጥተናቸው ታቅፈዋት ያጫውቷት ጀመር። ሰዓቱ ከሌሊቱ 5:30 ሲደርስ እናትየዋ ማርታ ከሠመመኗ መንቃት ነበረባት ግን አልነቃ አለች ድምጻችንን ከፍ አድርገን ተራ በተራ ደጋግመን "ማርታ ማርታ!!! ንቂ!!! እስቲ ምላስሽን አውጪ!! ምላስሽን አውጪው!!" ብንላትም እርሷ ግን አልነቃም አለች እየተነፈሰች አይደለም "አምቡ ባግ" በሚባለው መሣሪያ ታግዘን እኛው ራሳችን በጉልበት ትንፋሽ እየሰጠናት ነበርን ሞት በመካከላችን ገብቶ አንዲትን ነፍስ ለመንጠቅ በሙሉ ሀይሉ እየተጋጠመን እየተታገለን ነበር ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ሆኖ ነበር "ማርታ ማርታ!!! ንቂ!!! እስቲ ምላስሽን አውጪ!" እርሷ አሁንም የለችም ዋናው ሰርጂናችን ዶ/ር ፋንታ በሀዘን ተውጦ እንባውን ጠብ ሲያደርግ ሁላችንም አለቀስን የሰው ልጅ ሞትና ስቃይ ምንኛ አስከፊ ነው???!!!!!!!??? አስቡት ነገ እኮ በዓል ነው አዲስ ዓመት ነው እርሷ ከሞተች ግን በበዓል ምድር ለቅሶ፣ በበዓል ምድር ድንኳንና ሀዘን.... ስናስበው ሁላችንም መቆም አቃተን አቅም ከዳን። ግን እርዳታችንን አላቋረጥንም ሐኪም ተስፋ ሳይቆርጥ ጥረት ካደረገ የሞተ አካል ሕይወት ሊዘራ ይችላልና ጥረታችንን አላቆምንም እስከ ሌሊቱ 10:00 ሰዓት ድረስ በራሳችን እጅ በራሳችን ጉልበት "አምቡ ባግ" የትንፋሽ እርዳታ እየሰጠናት ከጽኑ ሕሙማን /icu/ ክፍል ተጨማሪ እርዳታ ደረሰልን ከዚያ በኋላ ወደ አርቴፊሻል መተንፈሻ ማሽን /ሜካኒካል ቬንቲሌቴር/ አዛወርናት ወደ icu ገባች ከዚህ በኋላ ለካ ምሳ አለመብላታችን ትዝ አለን ግን በምን አፔታይት ነው የምንበላው ታካሚያችን ከሠመመን አልነቃ ብላ አልተነፍስ ብላ icu ገብታ እንዴትስ ይበላልናል ነጋና መስከረም 1 ሆነ ዕለተ ረቡዕ 2006 ዓ/ም እኔም ሁሉን ነገር ትቼ አሁን አሁን ወደ icu እሮጣለሁ የማርታን ሁኔታ ለማየት። አሁንም አልነቃ ብላለች ያው ለጤና ባለሙያ በዓል ማክበር ብሎ ነገር አይታሰብም ያ የታወቀ ነው እኛስ ለምደነዋል ዛሬ ግን ማርታም በበዓል ቀን icu ውስጥ በአርቴፊሻል ማሽን ላይ ናት ቤተሰቦቿም በሀዘን ተውጠው በዓሉ ትዝም አላላቸውም መስከረም 2 ሆነ ዕለተ ሐሙስ አሁንም አልነቃ ብላለች አሁን ተረኛ ባልሆንም የማርታን ጉዳይ መከታተል የ 24 ሰዓት ሥራዬ አድርጌአለሁ መስከረም 3 ዕለተ አርብ አሁንም ከሠመመኑ አልነቃ ብላለች ይህ አይነቱ ችግርና ሞት ወፍራም ሰዎች ላይ ሊያጋጥም የሚችል ነው መስከረም 4 ዕለተ ቅዳሜ ከቀኑ 5:00 ሰዓት አከባቢ እያየሁዋት መንጠራራት ማስነጠስ ማሳል ጀመረች ልትነቃ ነው ማለት ነው ፈጣሪ ሆይ ዙፋንህ በሰማይ ከፍ ከፍ ይበል በእንባ ታጠብን ግን እኮ እኛ ቤተሰቦቿ ዘመዶቿ ሳንሆን ዶክተሮቿ፣ ነርሶቿ ነን። መስከረም 4 ቅዳሜ ከሰዓት 9:00 ሰዓት ላይ ማርታ ከሰመመኗ ሙሉ በሙሉ ነቅታ የ4 ቀን ዕድሜ ያላትን ጨቅላ ሕጻኗን ጡት እያጠባች ነበር ማርታ እንዴት ነሽ? ራስ ምታት ያመኛል። የኦፕራሲዮኑ ቦታ ይጠዘጥዘኛል ትላለች። አረ ከሞት ተርፈሻል እኮ ወዲያኑ ይሻልሻል... አይዞሽ በሠላም በጤና እናትየውና ሕጻኗ ወደ ቤታቸው ሊሄዱ በቁ በዓሉን ግን ሳያከብሩት አለፈ.... ከዚያ ቀን በኋላ በዓል በደረሰ ቁጥር እንደ ማርታ ያሉ ሕሙማንና ሟቾች ትዝ ይሉኛል እንጂ በዓል ትዝ ብሎኝም አያውቅም አክብሬም አላውቅም።""""""" ......... ......... ===================== ዶ/ር S ነኝ ሠላማችሁ ይብዛ (ሶሻል ሚዲያ ጤናዎ ፔጅ) ራስን መለወጥ #Ethiopia #like #share

" ሀብታም ባለቤቴን ሳገኛት ድሃ ነበርኩ።" ሳሙኤል ኤቶ:-🗣‼️ "ሀብታም ባለቤቴን ሳገኛት ድሃ ነበርኩ። ከባለቤቴ ጋር ስተዋወቅ አሁንም በፈረንሳይ አማተር እግር ኳስ ተጫዋች ነበርኩ። ኖንትስ ሊወ
" ሀብታም ባለቤቴን ሳገኛት ድሃ ነበርኩ።" ሳሙኤል ኤቶ:-🗣‼️ "ሀብታም ባለቤቴን ሳገኛት ድሃ ነበርኩ። ከባለቤቴ ጋር ስተዋወቅ አሁንም በፈረንሳይ አማተር እግር ኳስ ተጫዋች ነበርኩ። ኖንትስ ሊወስደኝ ፈቃደኛ አልነበረም ፣ ግን ባለቤቴ ሁል ጊዜ በእኔ እምነት ነበራት። እኔ ትንሽ የካሜሮን የንግግር ዘዬ አለቀቀኝም፣ እሷ በኖንትስ የፀጉር ቤት ነበራት። ዛሬ እሷ በአፍሪካ አህጉር ውስጥ በጣም የተከበረ የእግር ኳስ ተጫዋች ሚስት ነች፣  እኔ ደግሞ በዓለም ላይ በጣም ታጋሿ ሴት ባል ነኝ። ሕይወት የአጭር ርቀት ሩጫ ሳትሆን አገር አቋራጭ ሩጫ ናት!" ከሶሻል ሚዲያ t.me/changeitwow

#እውነተኛ_ታሪክ ይህ ምስኪን መካኒክ ከዚች ቆንጆ ልጅ ጋር ኢንተርኔት ላይ ይገናኛሉ። አንድ ቀን ልጅቷ እሱ ጋር ለመምጣት የትራንስፖርት ገንዘብ እንዲልክላት ጠየቀችው። ምስኪኑ መካኒክ ተገረመ። ልጅቷ የምታታልለው መስሎት ነበር። እንደዚች አይነት ቆንጆ ልጅ ወደ እሱ ልትመጣ እንደምትፈልግ ማመን አልቻለም። ግን ቢሆንም አመናት ከሁለት ቀን በኋላ ከአለቃው ገንዘብ ተበድሮ ወደ ልጅቷ ላከ። በጣም የሚገርመው ልጅቱ እሱን ለማየት ከአቡጃ ወደ ሌጎስ ናይጄሪያ በረረች። እሱ ግን ያላወቀው ይህች ቆንጆ ልጅ በጣም ሀብታም ከሆኑ ቤተሰብ የተገኘች እና እውነተኛ ፍቅር አሁንም እንዳለ እና ሁሉም ሴቶች የወንዶችን ገንዘብ እንደማይፈልጉ ለወንዶች እውነቱን ለማሳየት ፈልጋለች። መጀመሪያ ሰውዬው ወደአላት አድራሻ ሄዳ ፍቅረኛዋ ባለ አንድ ክፍል አፓርትመንት ውስጥ ከሌሎች 7 ወንዶች ጋር እንደሚኖር አወቀች። ፍቅረኛዋን የት እንደምታገኝ ጠይቃቸው መንገድ ላይ ስራ ላይ እንደሆነ ነገሯት። የሚሠራበት ቦታ ድረስ ሄዳ ሰርፕራይዝ ለማድረግ በራይድ ሄደች ። የሚሰራበት አካባቢ ስትደርስ መንገድ ላይ ልጁን እየጠየቀች መጣች እና ሰዎች 'ያ አስቀያሚ ልጅ በሰው መኪና ስር አንድ ቦታ ተኝቷል ሙሉ በሙሉ ልብሱ ቆሽሾ ያለው ' እያሉ ያሾፉባት ጀመር። ልጅቷ ፍለጋዋን ቀጠለች በመኪናቸው ውስጥ ያሉት ሀብታሞች ትኩረቷን ፈልገው ሲያፏጩም እሷ ግን በመጨረሻ የቆሸሸውን ልጅ ፍቅረኛዋን ከመኪና ጀርባ ተቀምጦ ስታገኘው እቅፍ አድርጋ ሮጣ ሄዳ ተጠመጠመችበት ልጁ ማልቀስ ጀመረ። እናም እንዲህ አለ፡- ‘ከሟች እናቴ በስተቀር በአዋቂነት ህይወቴ በሙሉ ልታቅፈኝ ይቅርና እጄን ለመጨበጥ የተስማማች ሴት አንድም የለችም። ሁለቱም ማልቀስ ጀመሩ። በኋላ ልጅቷ ለ 5 ዓመታት በከተማ ውስጥ አፓርታማ ተከራይታ ለሥራው የሚጠቀምበት ሞተር ብስክሌት ገዛችለት. አሁን ሁለቱም ወደ ካናዳ ለመጓዝ አቅደው ዝግጅት ላይ ናቸው ። ከሶሻል ሚዲያ ራስን መለወጥ t.me/changeitwow #Ethiopia

photo content

ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ከተሰማህ ይህንን አንብብ፤ 1. ይህ አንድ ምዕራፍ ነው፡፡ አስቸጋሪ ጊዜያት የአንድ ምዕራፍ አካል ናቸው፡፡ ለዘላለም አይቆዩም፡፡ ሕይወት የደስታና የሐዘን ዑደት ነው፡፡ ይህም ያልፋል የሚለውን አስታውስ፡፡ አሁን በማዕበል ውስጥ ነህ፣ ነገር ግን ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት ሰማዩ ይጠራል፡፡ ታገስ፡፡ 2. ከምታስበው በላይ ጠንካራ ነህ። የብቃትህን መጠን በፍጹም አትገምትም፡፡ • መጥፎ ቀናትህን 100% ተቋቁመሃል፡፡ • በውስጥህ ተደብቆ የሚገኝ ጥንካሬ አለህ፡፡ • ችሎታህ ከማንኛውም ችግር ይበልጣል፡፡ ከምታስበው በላይ ጠንካራ እና ብቃት ያለው መሆንህን አስታውስ፡፡ 3. ትናንሽ እርምጃዎች ይቆጠራሉ፡፡ እድገት ሁልጊዜ ትልቅ ዝላይ አይደለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ፣ እዚህ ግባ የማይባሉ ጥቃቅን እርምጃዎች ናቸው፡፡ እያንዳንዱ እርምጃ፣ ምንም ያህል ትንሽ ቢሆን፣ ወደ ግብህ ያቀርብሃል፡፡ በእያንዳንዱ እድገትህ ደስ ይበልህ፡፡ ቀስ እና ፀጥ ያለው መንገድ አሁንም ውድድሩን ማሸነፍ ይችላል፡፡ ወደፊት መሄድህን ቀጥል፡፡ 4. ለምን እንደጀመርክ አስታውስ፡፡ ወደ ኋላ ተመልሰህ ለምን እንደጀመርክ አስብ፡፡ ከቀድሞ መነሳሳትህ እና ግቦችህ ጋር እንደገና ተገናኝ፡፡ 5. ውድቀት የድል መሰላል ነው፡፡ መውደቅ ምንም ማለት አይደለም፣ ነገር ግን እንደገና መነሳትህ አስፈላጊ ነው፡፡ እያንዳንዱ ውድቀት የመማሪያ ዕድሎችን ይዞ ይመጣል፡፡ እያንዳንዱ ታላቅ የስኬት ታሪክ መሰናክሎችን ማለፍን እንደሚያካትት አስታውስ፡፡ መቀጠልህን አትተው፡፡ ታሪክህ እየተጻፈ ነው፡፡ 6. ለራስህ ጊዜ ስጥ፡፡ በአስቸጋሪ ጊዜያት ለራስህ ትኩረት መስጠት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ • ምግብህን ተመገብ፣ • በቋሚነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አድርግ፣ • በቂ እንቅልፍ አግኝ፣ • ከምትወዳቸው ሰዎች ጋር ተገናኝ፣ • ደስታን በሚያመጡልህ ነገሮች ላይ ተሳተፍ፡፡ ይህ ራስ ወዳድነት አይደለም፣ ለህልውናህ ነው፡፡ ደህንነትህ ወሳኝ ጉዳይህ ነው፡፡ 7. እርዳታ መጠየቅ ተገቢ ነው፡፡ በዚህ ጉዞ ብቻህን አለመሆንህን አስታውስ፡፡ • ጓደኞችን፣ ቤተሰብን ወይም ባለሙያዎችን አግኝ፣ • ስላለብህ ችግር በግልፅ ተናገር፣ • እርዳታ በሚያስፈልግህ ጊዜ እርዳታ ፈልግ፣ ጥንካሬ በዝምታ መጽናት ብቻ አይደለም፡፡ እርዳታ የሚጠይቁበትን ጊዜ ማወቅም ጭምር ነው፡፡ ለራስህ ታገል፡፡ ምንም ያህል አስቸጋሪ ቢሆን፣ በራስህ ላይ ተስፋ አትቁረጥ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ያ ብርሃንህ ይመለሳል፡፡ ደስተኛ፣ ጤናማ እና አስተዋይ ሆነህ ትወጣለህ፡፡ በዚህ ውስጥ አብረን ነን፡፡ ከሳይክ አዲስ (Aginechew Ayalew) ራስን መለወጥ t.me/changeitwow

photo content

#ምክር_ለሚቀበል_ወጣት 1. ወላጆችህ ለዘላለም ከአንተ ጋር አይቆዩም።በራስ መቆምን ልመድ።" 2. የምትወዳቸው ሰዎች ሆን ብለውም ይሁን ባለማወቅ ይጎዱሃል።ይሄን የዓለም እውነታ መገንዘብ አለብህ።"
#ምክር_ለሚቀበል_ወጣት 1. ወላጆችህ ለዘላለም ከአንተ ጋር አይቆዩም።በራስ መቆምን ልመድ።" 2. የምትወዳቸው ሰዎች ሆን ብለውም ይሁን ባለማወቅ ይጎዱሃል።ይሄን የዓለም እውነታ መገንዘብ አለብህ።" 3. "ጓደኞችህ ከምትገምተው በላይ በፍጥነት እንግዳ ሊሆኑ ይችላሉ።ሁሌም በዝግጅት ጠብቅ።" 4. "ቤተሰብ እና ገንዘብ ከሁሉም በላይ አስፈላጊ ናቸው።አጥብቀህ ያዛቸው " 5. "ሕይወት አይቀልም - አንተ ብቻ ነው የምትጠነክረው።" 6. "የልብ ስብራት እና ውድቀቶች የህይወት አካል ናቸው።መንፈሳዊ ጥንካሬን ይሻሉ።" 7. ሰበብህን ማንም ግድ አይሰጠውም፣ ውጤትህን እንጂ። 8. ስኬት ብዙውን ጊዜ የተወሰነ ምቾትን መስዋዕት ማድረግን ይጠይቃል። 9. በሕይወት ውስጥ የምታገኛቸው መልካም ነገሮች እንዲሁ በነጻ አይመጡም፤ አንተ ራስህ ነህ በግል ልፋትህና ጥረትህ የምታገኛቸው። ከኢትዮጵያዊነት ራስን መለወጥ @like@changeitwow

እኔም የተስማማሁበት አሳብ ይህ ትውልድ ነፃነቱን ብቻ ሳይሆን ከሱ ጋር የሚመጣውን የትውልድ ዕድልና ኃላፊነትን ተሸክሞ ማደግ አለበት። ሄኖክ ፋሲል እንደፃፈው በአንድ ወቅት አዶናይ የሚባል ወጣት ስላሳለፈው ሕይወት በድፍረት ሲያወራ ነበር።በቅርብ ደግሞ አንዲት ብላቴና ስላሳለፈችው ሕይወትና ከነበረባት አላስፈላጊ ሱስ እንዴት እንደወጣች በግልጽና በነፃነት ሚዲያ ላይ ስትናገር ነበር።ብዙዎች ይህን ነጻነታቸውን በድንቅና በግርምት ተመለከቱ።ይህ ድርጊታቸውም የነጻነትን ወሰን ያሰፋ፣ የግልና ሚስጥራዊ የነበሩ ጉዳዮችን ወደ የሕዝብ ውይይት መድረክ ያመጣ አዲስ ክስተት ሆኖ ይታይ ጀመር። ይህ ነጻነት የድፍረትና የግልጽነት መገለጫ ሲሆን ሌሎች ተመሳሳይ ችግር ያለባቸው ሰዎች ድምጽ እንዲያገኙና ከሐፍረት እስር ቤት እንዲፈቱ መንገድ ጠራጊ ሊሆን ይችላል።ነገር ግን ይህ ሁሉ ነጻነት ለምን ዓላማ ነው? ጥያቄው የሚጀምረው እዚህ ጋር ነው። ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ እንዳሉት "ነፃነት ከኃላፊነት ጋር ካልተያያዘ ነፃነት አይደለም።" ብላቴናዋ በጣም ነፃ ናት።ኃላፊነትን መሸከም ግን ገና አልጀመረችም።የነጻነት አጠቃቀም የራሱ የሆነ ኃላፊነትን ይጠይቃል።ስለግል ስብራትና ሱስ በይፋ ማውራት፣ ችግሩን ለማቃለል ወይም አደገኝነቱን ለመቀነስ ያስችላል ወይ? ወይስ ስሜትን ለተመልካች እንደመዝናኛ አቅርቦ የመሄድ ስህተት ይፈጥራል? ኃላፊነት የጎደለው የነጻነት አጠቃቀም የውስጣችንን "እብደት" በሌላው ላይ "ፕሮጀክት" የማድረግ ያህል ነው።ይህ አዲስ ትውልድ በነፃነት የመናገር መብቱን ሲጠቀም፣ የነጻነትን ሁለተኛ ገጽታ መረዳት አለበት — ኃላፊነትን።የነፃነት ፍሬ ለመፈወስ፣ ለማስተማር እና ሌሎችን ለማነቃቃት ሲውል፣ የኃላፊነትን ሸክም ተሸክሟል ማለት ነው።ይህ ትውልድ ነፃነቱን ብቻ ሳይሆን ከሱ ጋር የሚመጣውን የትውልድ ዕድልና ኃላፊነትን ተሸክሞ ማደግ አለበት። ታዲያ ይህ ትውልድ ነፃነቱን ሲጠቀም መሸከም ያለበት ኃላፊነት የት ላይ ነው? ራስን መለወጥ T.me/changeitwow

photo content