ራስን መለወጥ
Open in Telegram
እንዴት ናችሁ? ቢዝነስ ፕላን(ቢዝነስ ዕቅድ) እንዲሰራለት የሚፈልግ በተመጣጣኝ ዋጋ ቢዝነስ ፕላን እንሰራለን! በውስጥ መስመር ያናግረን! ለውጥ በትክክልም ይመጣል። 💪ዕድገታችንም ይሳካል!!! Hello everyone, we make best Business plan. In good price contact us inside! just pick a what kind of business plan! We can chang
Show more9 785
Subscribers
No data24 hours
-337 days
-8230 days
Posts Archive
9 785
🙏እዮብ አመስጋኝ ነበር☘️
🙏እዮብ↔️ በጤናው አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ↔️ በበሽታውም አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ↔️ሀብት እና ንብረት ሞልቶት አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ↔️ ልጆቹ አልቀውበት አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ↔️ ሚስቱ ከድታው አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ↔️ ዘመዶቹ ፊት ነስተውት አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ↔️ቀን እና ሌሊቱ ተፈራርቀውበት ሲነጋ መች ነው የሚመሸው ሲመሽ መች ነው የሚነጋው እያለ ሰውነቱን ትል እያፈላ አመስጋኝ ነበር።
🙏እዮብ እንዴት አደርክ ሲሉት ተመስገን ነው የሚለው።
ታጋሽ እንደ እዮብ እንድንሆን ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን በማግኘት እና በማጣትም አመስጋኞች እንድንሆን ዘንድ አምላክ ማስተዋልን ያድለን!!!🙏🏻
ሁልጊዜም አመስጋኝ እንሁን ‼️
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow
#followerseveryone
#cha@changeitwow
9 785
የበቀል ትርፉ
ነጋችንን ላለማጣት ከበቀል እንራቅ !
አንድ ገበሬ የ4 አመት ልጁን ወደ እርሻ ይዞት ይሄድና ስራ ሲጀምር መሬት ላይ ልጁን አስቀመጠው ። ከዚያም መሬቱን እያረሰ እያለ ድንገትገበሬው ልጁ ሲጮህ ሰማና እየተቻኮለ ሲሄድ እባብ ነድፎት አገኘ። ወዲያው ግን እባቡ ፈጥኖ ሲሄድ በቁጣ ጮኸ እየጮክ ልጄ ሆይ አይሆንም! ያ እባብ እኔን አያመልጥም! ቆርጬ እሳት ውስጥ እጥለዋለሁ! በእሳቱ ጨርሶ አቃጥለዋለሁ! አለ "
ገበሬው ቶሎ ብሎ መጥረቢያውን አንስቶ እባቡን ማሳደድ ጀመረ፡፡ እባቡን ተከትሎ በሮጠ ጊዜ ድንጋይ ክምር ውስጥ ተንሸራቶ ገባ። እባቡን ለመያዝ ካቡን በየተራ ያነሳ ጀመር በመጨረሻም እባቡ በድንገት ወደ ጉድጓድ ገባ። እባቡን ለመያዝ ቆርጦ ተነሳ ጉድጓዱን ይቆፍር ጀመር:: አንድ ሰዓት ያህል ሳይታክት ቆፈረ ወደ እባቡ ተጠጋ። በመጨረሻም እባቡን ገደለው፡፡
ገበሬውም ወደ ልጁ ሲመለስ ደስም አለው፡፡ ነገር ግን ተመልሶ ሲያይ ልጁ የሞተ መስሎት በድንጋጤ ልጁን በእቅፉ ይዞ ወደ ሃኪም ጋር ይዞት በመሄድ፦
"እባክህ ልጄን ሕያው ለማድረግ የሚያስፈልገውን ሁሉ አድርግ!አለው
ልጁን ሲመረምር ሃኪሙ ተስፋ በመቁረጥ ጭንቅላቱን ነቅንቆ እንዲህ አለ።
"ልጅህ እባቡ እንደነደፈው ወደ እኔ ብትመጣ ኖሮ ነፍሱን ባዳንኩት ነበር። ነገር ግን በበቀል ተወጥረህ አደጋውን ማየት አልቻልክም... ልጅህም ዋጋውን ከፍሏል። ይቅርታ ነገር ግን አንዳንድ ትምህርቶች በአስከፊ ዋጋ ይመጣሉ!
በቀል ብዙ ጊዜ ያጠፋናል ፍርዳችንን ያደበዝዝብናል ልባችንን ይመርዛል። ንዴትን ስንይዝና በቀልን ስንፈልግ ሌሎችን ብቻ ሳይሆን እራሳችንንም ሊጎዳ በሚችል የስቃይና የጥፋት አዙሪት ውስጥ እራሳችንን እንጠምዳለን። እውነተኛ ጥንካሬ ያለው ይቅር በማለት እና በመተው ውስጥ ነው። ይቅርታን በመምረጥ ለለውጥ ለሰላም በር እንክፈት፡፡
ከKasahun Brhanu
t.me/changeitwow
ራስን መለወጥ
9 785
#ከሚስት_ለባል_የተላከ…
#ውዱ_ባለቤቴ፦ አንዳንዴ ጥንካሬህን ከየት እንዳመጣህ ሳስበው እገረማለሁ።
ለራስህ ልብስ ሳትገዛ በአንድ ልብስ ለወራት ትቆያለህ ፤ ምክንያቱም ጠረጴዛው ላይ ለልጆችህ ምግብ ማስቀመጥ ስለፈለግክ ነው።
ቤተሰብህም ጠግበው እንዲበሉ እና ምግብ እንዲተርፋቸው አንተ ግን ትራባለህ።መራብህን ግን ለማንም አትናገርም።
አንዳንድ ጊዜ ምንም አቅጣጫህን ሳትናገር ከቤት ትወጣለህ።ነገር ግን አሁንም ገንዘብ ይዘህ ወደ ቤት ትመለሳለህ።
ልጆችህ እንዲማሩ መሰረታዊ ትምህርት ማግኘት ሲገባህ ራስህን እንዴት እንደካድክ አውቃለሁ።
ሥራ ተገኘም አልተገኘ ፣ ከፋህም ለማህ ቤተሰብህ እጅህን እንደሚጠብቅ አውቀህ ፣ በሕይወት እንድኖሩልህ ስትል ብቻ አርተህም ፈስተህ ምግብ ታቀርባለህ።
የምትወደውን ሴት ለማግባት ለሙሽሪት ትልቅ ዋጋ ትከፍላለህ፣ እናም በመጨረሻም ቤተሰቧን ፣ ወንድሞቿን እና እህቶቿን እና የራስህንም ቤተሰብ ጭምር ትንከባከባለህ።
ለእናትህ ፣ ለሚስትህ እና ለልጆችህ ያለመታከት መታገል ዋንኛው ሥራህ ነው። ሁሌም አከብርሃለሁ።
ውድ ወንዶች.. #እግዚአብሔር አምላክ ረጅም እድሜና ድፍረትን ፣ ጤንትን በእያንዳንዱ ቀን ለማለፍ ባርኮ ይስጣችሁ።
እኛ ሁልጊዜም አፍሪካዊያን ነን‼️
t.me/changeitwow
We are Africans
ከምድረ ገነት አርባምንጭ #newpost #best #followerseveryone #highlightseveryonefollowers2025 #fact #new #like #Ethiopia #ethiopian_tik_tok #post #ethiopian #share@changeitwow
9 785
አንበሳ ጫካ ውስጥ አንድ ህፃን ልጅ ያገኛል ህፃኑንም ይዞ ዋሻ ውስጥ ያስቀምጠውና የሚበላውን እያበላ ያሳድገዋል። አንበሳው ለአደን የሚወጡትን ሁሉ እየገደለ ጦራቸውን እየያዘ ወደ ዋሻው ያከማቻል። በዚህ ሁኔታ ልጁም አድጎ ትልቅ ሆነ።
ጎረምሳውም ያሳደገውን አንበሳ "እባክህ ፍቀድልኝና መሰሎቼን አግኝቼ ተጫውቼ ልምጣ " ብሎ ጠየቀው። አንበሳውም "እሺ ሂድ ግን እባክህ እንዳታማኝ ፣ ስለኔ ምንም መጥፎ ነገር አትናገር" ብሎ ሸኘው።
ጎረምሳውም ሄደ ከመሰሎቹ ጋር ተገናኘ። መሰሎቹ ስለ አንበሳው ብዙ መረጃ ለመጠየቅ ቢሞክሩም ምንም ሳይነግራቸው ቀረ። ነገር ግን ሰዎቹ በጣም ጨቀጨቁት ያን እንዲህ አለ።
"አንበሳው መልካም አሳዳጊ ነው ነገር ግን አብረን ስንተኛ ብብቱ ይሸታል ማታ ማታ ፌንጣ ይበላል ከዛ በተረፈ ማለፊያ ነው" አላቸው።
አንበሳው ተደብቆት መጥቶ ስለነበር ወጣቱ ልጅ ያለውን በሙሉ ሰምቶ እጅግ አዝኖ ወደ ዋሻው ሄደ። ልጁም ወደ ዋሻው እንደተመለሰ
"ልጄ ከነዚህ ጦሮች ውስጥ ጠንካራውን ምረጥና በደንብ አድርገህ ውጋኝ " አለው።
ልጁም ፍፁም እንደማይችልና እንደሚወደው ገለፀለት። አንበሳው ግን " በሰው ፊት አምተኸኛልና እባክህ ጦሩን አንስተህ ውጋኝ ያንን የማታደርግ ከሆነ ግን እንደማትወደኝ ነው የማረጋግጠው " አለው።
ልጁም ጠንካራውን ጦር አነሳና በሃይል ወጋው ። ጦሩ ሙሉ በሙሉ በአንበሳው ሰውነት ውስጥ ተሰነቀረ። አንበሳውም "ንቀለው" አለው። ልጁም ነቀለለት።
እናም አንበሳው እንዲህ አለ። "ልጄ እኔ ከልጅነትህ ጀምሮ ብዙ ዋጋ ከፍዬ እያደንኩ አሳድጌሃለሁ። አንተ ደግሞ በተራህ አሁን ታስታምመኛለህ " አለው።
ልጁም በተካነበት የአደን ስልት በሬውንም ፣ ጎሹንም እያደነ እያመጣ አንበሳውን መቀለብ ጀመረ። አንበሳውም ወደ ቀድሞ ጤንነቱ ተመለሰ። ሙሉ ለሙሉ ከተሻለው በኋላ ልጁን እንዲህ አለው።
" ልጄ ጦሩ የገባበት ቦታ ቁስል እንዳለ እስኪ ተመልከት" አለው።
ልጁም ቢፈልግ ፣ ቢፈልግ ቁስል የሚባል ነገር አጣ።
ያን ጊዜ አንበሳ "አየህ ልጄ በጦር የወጋኸኝ ድኗል በምላስህ ያቆሰልከኝ ግን እስካሁን አልዳነም" አለው። ይባላል።
ቁስልም ይድናል የምላስ በትር ግን በመድሃኒትና በምግብ ሊድን አይችልምና ለምንናገረው ነገር ሃላፊነት እንውሰድ።
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow
9 785
ከ30 ዓመትህ በኋላ ማድረግ ያለብህ 10 ወሳኝ ነገሮች:-
1. የትኛውም አይነት ጎጂ ሱስ ካለብህ አሁኑኑ አቁም። ህይወትህን እስከወዲያኛው ያመሰቃቅለዋልና። ይህ ማለት ግን ሀያዎች ውስጥ እያለህ አታቁም ማለት አይደለም።
2. ከ30 ዓመትህ በኋላ ቢበዛ 15 ዓመት ነውና ጠንክረህ መስራት የምትችለው ማድረግ ስለምትፈልገው ነገር አተኩረህ አስብ ህይወት 2ኛ ዕድል ላትሰጥህ ትችላለችና።
3. ራስህን ከሰዎች ጋር ማወዳደርህን አቁም። ይህ ጊዜ ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚያስደስትህን ነገር የምታደርግበት ወቅት ነው።
4. በ20ዎቹ ዕድሜህ ሳትሰራው ስላለፍከው ነገር አትፀፀት። ያለፈ አልፏል አሁንም ቢሆን ከ20ዎቹ ዕድሜህ ባልተናነሰ ጠንክረህ የምትሰራበት ረጅም ጊዜ አለህ።
5. በፍቅር ግንኙነትህ መቀለድ የምታቆምበት ጊዜ ላይ ነህ። እዛም እዚም ማለት አቁም አንዷ ላይ ማምረር ግድ ይልሀል።
6. social media ላይ ጊዜ አታባክን። አሁን ጊዜህን ለወደፊቱ መሠረት የምታሲዝበት ወሳኙ ጊዜ ላይ። መጠቀም ግድ ከሆነብህም ጥቂት ሰዓት ብቻ ይሁን። ምርጫህም ከዓለም ጋለሪ ይሁን አትፀፀትበትም።
7. መቆጠብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ግድ የሚልህ ሰዓት ላይ ነህ በዚህ እንዳትቀልድ። የምትቀፍልበት ጊዜ ላይ አይደለህም።
8. የህይወት ዘመን ጓደኞች የምታፈራበት ወሳኙ ጊዜ ላይ ነህ መልካም ጓደኞች ይኑሩህ ለመልካም ህይወትህ ስትል።
9. አንድ ነገርን ሳትፈልግ እንድታደርግ የሚያደርግ የጓደኛ ወይም ሌላ ግፊት ካለ No ማለት ጀምር ይሉኝታ አይያዝህ። ከዚህ በኋላ ሌላ ዕድል አይኖርህምና።
10. ወላጆችህ ከመቼውም ጊዜ በላይ አንተን ይፈልጉሀል። ዕድሜያቸው እየመረሸ ነው። ምርጡ ጊዜህን ከነሱ ጋር አሳልፍ።
ሶሻል ሚዲያ
t.me/changeitwow
ራስን መለወጥ
#new #like #Ethiopia #share #ethiopian_tik_tok #followerseveryone #highlightseveryonefollowers2025 #newpost
9 785
አስገራሚና አስተማሪ ታሪክ
👇👇👇👇👇👇👇👇
አንድ ቅቤ አምራች ገበሬና ዳቦ አምራች ነጋዴ እንደ አጋጣሚ ድግስ ላይ ተገናኝተው ያወራሉ፡፡
በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡
ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡
በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ፡፡ በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?›ሲል ጠየቀው፡፡
ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡ ገበሬውም አዘነ፡፡
‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡
ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡ ነጋዴው አፈረ 😥
.
‹የምታገኘው ለሌላው ባደረግከው ልክ ነው፡፡ 150 ሰጥተህ 300 ልታገኝ አትችልም፤ እባብ ሰጥተህ እርግብ ፣ ድንጋይ ሰጥተህ ዳቦ፣ እሬት ሰጥተህ ማር ልታገኝ አትችልም፤ አንተ ብቻ ብልጥ ልትሆን አትችልም፤ ሻማውን አጥፍተህ ብርሃን ልታገኝ አትችልም፤ ሌላው ገድለህ አንተ በሰላም ልትኖር አትችልም› አለው ገበሬው፡፡
ሁሉም የሰጠውን ይቀበላል እና በህይወት እስካለን ድረሰ በጎ ነገር ብቻ እንስራ። 🥰
9 785
አንድ ቀን ስራ ውዬ ወደቤት ስገባ ሚስቴ ወደራት ግብዣ ቦታ ስሄድ የምለብሰውን ልብሴን አዘገጃጅታ ጠበቀችኝ።
እኔም ራት ውጭ "እንብላ ብለሽ ነው?" ስላት
ሚስቴም ኮስተር ብላ "እኔ እንኳን አልወጣም። ነገር ግን ዛሬ ሁሌም አይታ የማታምንህ ነፍሷ እስኪወጣ ከልቧ በጣም የምታፈቅርህና ድሮ አንተም ፍቅርህን ትገልጥላት የነበረች ሴት ስላለች እሷን ይዘህ ሂደህ ከእሷ ጋር ብቻችሁን ሆናችሁ እየተዝናናችሁ ራት እንድትበሉ፣ ጊዜ እንድትሰጣትና የልብ የልባችሁን እንድታወጉ ፈልጌ ነው" አለችኝ።
ደነገጥኩ። ምን እያለችኝ እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም። እንዴት ሚስቴ ራሷ አዘንጣ አልብሳ ከሌላ ከልቧ ከምታፈቅረኝ ሴት ጋ ለራት ግብዣ ወደሆቴል ትልከኛለች። ያች ነፍሷ እስኪወጣ ታፈቅርሀለች አንተም አሁን ፍቅርህን መግለፅ ብታቆምም ከልብህ ታፈቅራት ነበር ያለችኝ ሴት ማን ናት? ልትፈትነኝ ፈልጋ ነው ወይስ ልትፈታኝ አስባለች ማለት ነው? እያልኩኝ በሀሳብ ተውጨ ራሴን በጥያቄ ሳዋክብ ቆየሁና የራት ልብሶቸን የምታስተካክለውን ሚስቴን "ምን እያልሽኝ እንደሆነ አልገባኝም?" አልኳት።
ሚስቴም "ፈገግ ብላ አይዞህ ውዴ! ጋብዛት ያልኩህ ሴት በእኔና በአንተ መካከል የምትገባ ሳትሆን አንተን የሰጠችኝና ከአንተ ጋር ያጋባችኝ እናትህ ናት። ዛሬ ከእናትህ ጋር ደስ ወደሚል ቦታ ሂዳችሁ ብቻችሁን ሆናችሁ ራት እንድትበሉና ስትጫወቱ እንድታመሹ ስለፈለግኩ ነው። እኔና ልጀ ደግሞ ቤት ውስጥ እንጫወታለን አለችኝና አለባብሳ ላከችኝ!
በፍጥነት እናቴ ቤት ስሄድ እርጅናው ያጎበጣት እናቴ ብቻዋን ቁጭ ብላ ትተክዛለች። በጊዜ ማጣት ምክንያት ከጠየቅኳት ስለዘገየሁ ተሳሳምንና "በዚህ ምሽት የመጣኸው በሰላም ነው? አለችኝ በናፍቆት፣ በስስትና በመደናገጥ ስሜት እያየችኝ።
እኔም "በሰላም ነው ማሚ። ወጣ ብለን እየተጫወትን ራት እንድንበላ ብዬ ነው" አልኳት።
ወጭው እንዳይጎዳኝ በማሰብ "ይቅርብኝ እዚሁ እሰራና እንበላለን" አለችኝ።
ውጭ እንድንበላ አሳመንኳትና ወጣን። የትኛውን ሆቴል እንደምትመርጥ ስጠይቃት ድሮ አባዬ በህይወት እያለ ይዞን ወደሚሄድበት ሆቴል ብንሄድ ደስ እንደሚላት ነገረችኝና በየአመቱ ከአባየ ጋር የጋብቻ አንቨርሰሪያቸውን ሲያከብሩ የምትለብሰውን ልብሷን ለበሰችና ወደሆቴሉ ሄድን። ሜኑ ሲመጣልን "ድሮ እኔ ነበርኩ ሙሉውን አንብቤ የማስመርጥህ፣ አሁን ግን አይኔ እምቢ ስላለኝ አንብብልኝ" አለችና ፈገግ እያለች አቀበለችኝ። ልጅ እያለሁ እሷ ታደርግልኝ እንደነበረው እኔም ሙሉውን አንብቤ አስመረጥኳት ራት በላን፣ ወይንም ጠጣን። አባዬ ከሞተ በኃላ ለራት ግብዣ ወጥታ እንደማታውቅ፣ ብቸኝነትና ህመም እንደሚሰማት አወራችኝ። ወጣትነቷን የሚያስታውሳትን ቆየት ያለ ሙዚቃ አስከፍቸ አስደነስኳት። በእጅጉ ተደሰተች! እኔም በእጅጉ ተደስትኩ!
በመጨረሻም ቤቷ አደረስኳት። አመስግናኝና መርቃኝ ወደቤቷ ስትገባ "በቀጣይ ደግሞ እኔ ነኝ የምጋብዝህ" አለችኝ። ደስ ይለኛል አልኳትና ወደቤቴ ሄድኩኝ።
ሚስቴ እንዴት ነበር አለችኝ። በጣም ደስ ይል ነበር ብዬ የዚህ ሀሳብና ደስታ ምንጭ የሆነችውን ሚስቴን አመሰገንኳት።
ከቀናት በኃላ ተደውሎ በአስቸኳይ እናቴ ቤት ድረስ ተባልኩ። ስሄድ እናቴ በልብ ህመም ምክንያት በድንገት አርፋለች። ከቀብር ተመልሰን ወደምኝታ ቤቷ ስገባ የእለት ከእለት ክንዋኔዎቿን የምትፅፍበትን ማስታወሻዋን(ዳየሪዋን) ከሸልፉ ላይ አገኘሁት። ከጎኑ ብዙ ገንዘብ አለ። በጋበዝኳት ቀን ገብታ የፃፈችን ሳነብ እንዲህ ይላል።
"ዛሬ ልጀ ከስንት ጊዜ በኃላ አስታወሰኝና ራት ጋበዘኝ። ጊዜ ሰጥቶ ብቸኝነቴን አስረስቶኝ አመሸ። ባለቤቴ ከሞተ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ደነስኩ። በጣም ተደሰትኩ። ልጀ እንዳልተወኝና እንዳልረሳኝ ስረዳና ድሮ እንዝናናበት በነበረው ሆቴል አብረን ስንዝናና ነፍሴ በደስታ ልትወጣ ነበር። ረስቶኛል ትቶኛል ብዬ አዝኘበት የነበረው ልጅ አስታውሶ ጊዜ ሰጥቶ ጋብዞ አብሮኝ ስላመሸ ከደስታዬ ብዛት ቤት ገብቸ አነባሁ። ለሁሉም ወዳጆቸ እየደወልኩ የሆነውን ሁሉ ነገርኳቸው። ከዚህ በኃላ ሞትም ቢመጣ በደስታ ነው የምቀበለው። በቀጣይ እሱንና ሚስቱን ልጋብዛቸው ነው። እስከዚያ ካልደረስኩም በዚህ ገንዘብ ሚስቱን ጥሩ ሆቴል ወስዶ እንዲያዝናናት እፈልጋለሁ" ይላል።
የምለው ጠፋብኝ። በስራ ብዛትና በጊዜ እጥረት ምክንያት እናቴን በደስታ እንድትኖር ባላረጋትም በመጨረሻው ሰዓት በደስታ እንድትሞት እንዳደርጋት ያስቻለችኝን ውዷን ሚስቴን ሮጨ ሂጀ አቀፍኳትና አመሰገንኳት።
#መልዕክት፦ ስራ በዛብኝ፣ ሌላ ቀን ይደርሳል፣ ጊዜ የለኝም፣ አልተመቸኝም፣ አይመቻቸው ወይም አይፈልጉ ይሆናል፣ ምንምን እያልን ትንሽ ጊዜም ሳይለዩን ተንከባክበው አስደስተው ላሳደጉን ወላጆቻችንና ታላላቆቻችን ትንሽ ጊዜም ብትሆን ለእነሱት እጅግ ትልቅ ቦታና ትርጉም ስላላት በቻልነው ልክ ጊዜ ሰጥተን እንደምናስባቸው፣ እንደምንወዳቸውና እንደምናከብራቸው እናሳያቸው ለማለት ነው!
ከተመቻችሁ #Share እና #like በማድረግ ለሌሎችም አድርሱ!
ከሶሻል ሚዲያ
9 785
አባባ ልብስ ሰፊ ነበር....
ትዝ ይለኛል ልጅ እያለሁ ከአባቴ ጋ ከቤት ወጥቼ ሳንቡሳ አየሁና ካልገዛክልኝ ብዬ አስጨነቅኩት።
አባባም "ሳንቡሳ ጥሩ አደለም ውስጡ ጠጠር አለ ያሳምምካል"ብሎ አስፈራርቶኝ ይዞኝ አለፈ።
ትንሽ ቆይቼ ደሞ አንድ ህፃን ከረሜላ ሲመጥ አይቼ አሁንም ካልገዛክልኝ አልኩት አባባም "አይ ልጄ ጣፋጭ ጥርስክን ያሳምምካል"ብሎ አታለለኝ።
የሆነ ቦታ ደርሼ ግን አልሔድም አልኩት...
የቆምኩበት ዳቦ መሸጫ ሱቅ ነበር።ቢያስፈራራኝ ጭራሽ ጩኸት የቀላቀለ ለቅሶዬን ለቀቅኩት ታድያ ይህንን ስታይ የነበረችው የዳቦ ቤት ሰራተኛ ጠርታኝ ትኩስ ዳቦ ሰጠቺኝና ሄድን...
እናም አድጌ ሰሞኑን የማትሪክ ውጤት ሳይመጣልኝ ቀርቶ ተበሳጭቼ ሳለቅስ አባባ ይዞኝ ቤተክርስትያን ሄደና አረፍ እንዳልን…
ልጄ ያኔ ልጅ ሆነህ ትዝ ይልካል??በየመንገዱ ያየከውን ካልገዛክልኝ ስትለኝ?? አለኝ ፣ አይን አይኔን እያየ።
አዎ አልኩት ግራ ገብቶኝ።
ያን ጊዜ በፅኑ ህመም እሰቃይ ነበር።አንተን ይዤ ስወጣ ሆስፒታል ነበር ምሄደው።መድሀኒት ሁሉ ነገሬን ጨርሶት ያን ቀን ተበድሬ ነበር ስሄድ የነበረው።
ላንተ ዳቦ ብገዛ ብር ይጎለኝና መድሀኒት አጥቼ እሞታለሁ ፤ ባልገዛልህ ታለቅስብኛለህ ፤ ብቻ ያን ቀን በልቤ አባት ነህና ልጄ ፊት አታዋርደኝ ብዬ በቆምኩበት ፀለይኩ።
ወድያው ያቺ ሴት ጠርታ ምትፈልገውን ሰጠችክ እኔም መድሀኒቴን ገዝቼ ገባሁ።
የሚገርምህ ግን እሱን መድኃኒት ድጋሚ ልገዛ አልሔድኩም።
እንዴት አባባ??
ከዛች ቀን ወዲህ ጠዋት እየሄድኩ መጠመቅ ጀመርኩ ።ፈጣሪ የአንድ ቀን ፀሎቴን ሰምቶ የእድሜ ልክ ህመሜን ነቀለልኝ።
መድሀኒት ምገዛበትን ብር እናንተን በሰላም ማሳደግ ጀመርኩ አየህ ፈጣሪ አንዳች ክፉ ነገር በኛ አያደርግም።
እያንዳንዷ ህመማችን ወደ ፈጣሪ መዳረሻ መንገዳችን ናት። ያኔ ባንተ ባልፈተን አምላኬን ባልጠየቅኩ ባልዳንኩ ነበር።
ስማ ልጄ...እግዜር ጊዜያዊ ችግር የሚሰጠን የዘላለም መፍትሔ እንዲሆነን ነው።
ዛሬ የወደቅከው ነገ ለመነሳት ቢሆንስ?
መንገድህ ሌላ ቢሆንስ??
ልብስ ሰፊ ጋ የተቀደደ ልብስ ይዘህ ስትሔድ ለሰፊው የተቀደደውን ቦታ ታሳያለህ።
ልክ እንደዛው ጉድለት ሲገጥምህ አለምን ሰፍቶ ፈጥሮ ላበጃጃት ጌታህ መጥተህ አሳይ።ሰፊው ላትቀደድ ላትጠፋ አድርጎ አድሶ ይመልስሀል።
ማርያምን እግዚአብሔር በህይወታችን አይጠረጠርም!!!
በአምላክ እጅ ከሆነ መውደቅ እራሱ መነሳት ነው!!!
ወደ ሰፊው ሂዱና ቅዳጅ ማንነታችሁን አሳዩ ፣ እንደገና አበጃጀኝ ፣ አድሰኝ ፣ አዲስ አድርገኝ ፣ እንዳልቀደድ አድርገህ በቃልህ መርፌነት ስፋኝ በሉት ።
ሰናይ ቀን!
፡
፡
Cha Cha
ከምድረ ገነት አርባምንጭ(ሶሻል ሚዲያ)
9 785
የዲሲፕሊ ስኬታማነት
ዲሲፕሊን ሁለት ገጽታ አለው፡-
1. አንድን ማድረግ ያለብኝን ነገር ስሜቴ ቢፈቅድም ባይፈቅድም መደረግ ስላለበት ብቻ ማድረግ፣
2. አንድን መደረግ የሌለበትን ነገር ምንም ያህል ብፈልገውም አለማድረግ፡፡
እነዚህን ሁለት የዲሲፕሊን ገጽታዎች መለማመድማ ሆነ አለመለማመድ የሚከተሉት ሁለትውጤቶች አላቸው፡-
1. ዲሲፕሊን ከማዳበራችን የተነሳ መልካም ልምምዶችን ስንለማመድ ያልተጠበቀ አስገራሙ ውጤቶችን እናገኛለን፡፡
2. ዲሲፕሊን ከመጉደሉ የተነሳ ጤና-ቢስ ነገሮችን ስንለማመድ ደግሞ ያለተጠበቁ አጉል ውጤቶችን እናጭዳለን፡፡
ማንኛውም ችሎታና ብቃት ከዲሲፕሊን ውጪ ከንቱ ነው፡፡ ምክንያቱም ዲሲፕሊን ከሌለኝ ምንም እንኳ የማድረጉ ብቃት ቢኖረኝና በነገሩ ባምንበትም ያንን ነገር ማድረግ ያስቸግረኛል፡፡ በሌላ አባባል ዲሲፕሊን ከሌለኝ መልካም ልማድን ለማዳበር ፈጽሞ አልችልም፡፡ ሕይወቴን በዲሲፕሊን ካልመራሁ የምተገብረውን ነገር የሚወስንልኝ ያመንኩበት መርህ ሳይሆን የእለቱ “ሙድ” ይሆናል፡፡ ይህ እንዳይሆን ራሳችንን ለመምራት ጤናማ የሆነን ዲሲፕሊን ማዳበር የግድ ነው፡፡
ዲሲፕሊንን ለመለማመድ መውሰድ የምትችላቸው እርምጃዎች፡-
1. ለማግኘት የምንፈልገውን ውጤት ማወቅ
ማከናወን የምንፈልገውንና ጊዜያችንን ልንሰዋለት የሚገባንን ተግባር በግልጽ ማወቅ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ ቀዳሚና እጅግ ወሳኝ የሆነ ጉዳይ ነው፡፡ ማንነታችን የሚፈልገውን በሚገባ ሳናውቅ ማንነታችንንን ለመምራት መሞከር ጊዜን ማባከን ነው፡፡
2. ለፈለግነው ውጤት የሚመጥነውን ዲሲፕሊን ለይተን ማወቅ
እያንዳንዱ ለማዳበር የምንፈልገው ነገር የራሱ የሆነ ባህሪይ አለው፡፡ ለዚያ ለማዳበር ለምንፈልገው ነገር ምን አይነት ዲሲፕሊንና ልማድ ብናዳብር ስኬታማ እንደምንሆን ማወቁ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡
3. እንጀምር፣ ከጀመርን ደግሞ አናቁም
ለማዳበር የምንፈልገውን ነገር ለነገ ሳናስተላልፍ መተግበር እንጀምር፡፡ ሆኖም መጀመር ብቻ በቂ እንዳልሆነም እናስታውስ፡፡ የጀመርነውን ነገር ለማቆም ምንም አይነት ምክንያት አንስጥ፡፡ ውጤት እስከምናገኝ ድረስ እንቀጥል፣ ስናቆመውም እንደገና እንጀምር፡፡
9 785
_ጆሮ ያለው ሁሉ ይስማ፣ማንበብ የቻለ ሁሉ ያንብብ!!
አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ
_በተለይ ወጣቶች ወጣትነታችሁን ያለ አግባብ አትግደሉት.. አንብባችሁ ተጠቀሙበት...
1. የወሲብ ስሜታችሁን መቆጣጠራችሁ የስኬታችሁ ወይም የውድቀታችሁ ምክንያት ይሆናል።
2. ፖርኖግራፊና ግለ ወሲብ የስኬት ትልቁ ጠላቶች ናቸው፡፡ አእምሯችሁን ያኮስሳሉ፣ ያጠፋሉ።
3. ልክ ግመል ውሃ እንደሚጠጣው አልኮል ከመጠጣት ተቆጠቡ፡፡ ህሊናችሁን ስታችሁ ሞኞች ከመሆን የከፋ ነገርየለም።
4. ደረጃችሁን ከፍ አድርጉ፤ ዝም ብሎ ስለተገኘ ብቻ ዝቅ ባለ ነገር አትርኩ፡፡
5. ከእናንተ የበለጠ ብልህ ሰው ካገኛችሁ፣ ከእነሱ ጋር ስሩ እንጂ ሩሳችሁን አታወዳደሩ።
6. ችግሮቻችሁን ሊፈታላችሁ የሚመጣ ማንም የለም፡፡ የህይወታችሁ 100% የራሳችሁ ኃላፊነት ነው፡፡
7. በህይወት መድረስ ከምትፈልጉበት ደረጃ ካልደረሱ ሰዎች ምክር አትቀበሉ።ከፍላጎታችሁና ከአላማችሁበጋርበየሚሄድ አስተማሪ ገፆችን መርጣችሁ ተከተሉ።
8. የገንዘብ፣የጊዜ እና የእምነት ነፃነታችሁ ጠብቁ።ገንዘብ የምታገኙበት አዳዲስ መንገዶችን ፈልጉ። ገንዘብ ስሩ፤ በሚያሾፉባችሁና በሚቀልዱባችሁ ፌዘኞች ጊዜ አታጥፉ/ችላ በሏቸው፡፡
9. ለመለወጥ ብዙ መፅሀፍ ማንበብ ወይም መርጃ መጻሕፍት ማገላበጥ አያስፈልጓችሁም፤ የሚያስፈልጋችሁ ተግባርና ራስን መገዛት ብቻ ነው። ራሳችሁን ግዙ!
10. አደንዛዥ እጾችን አስወግዱ። በተለይ እንደ ጫትና ሀሺሽ ‚አልኮል መጠጥና ሲጋራ ያሉትን አስወግዱ። @changeitwow
11. በኔትፍሊክስ የማይረባ ይዘት እየተመለከታችሁ ጊዜያችሁን ከምታጠፉ፣ ከዩቲዩብ ክህሎቶችን ተማሩ፣ከGoogle scientifical research...
12.ማንም ስለእናንተ ግድ የለውም። ስለዚህ ዓይን አፋርመሆናችሁን አቁሙና ወጥታችሁ እድሎቻችሁን ፍጠሩ።
13. ምቾት ከሁሉ የከፋ ሱስና ወደ ድብርት/ጭንቀት የሚወስድ ርካሽ ትኬት ነውና አምልጡ።
14. ለቤተሰባችሁ ቅድሚያ ስጡ። መጥፎ ቢሆኑም ወይም ሞኞች ቢሆኑም እንኳ ተከላከሉላቸው፤ ነውራቸውን ሸፍኑ፣ታዘዙ፣ተንከባለቡ፣አክብሯቸውም!
15. አዳዲስ እድሎችን ፈልጉ፤ ከእናንተ የቀደሙ ሰዎችን ተሞክሮ በመውሰድ ተማሩ።
16. መታመናችሁን ቀጥሉበት ሰውን ማመናችሁን ግን አስቡበት፣ማንንም አትመኑ።አንድም ሰው ቢሆን፣ ምንም ያህል ብትፈተኑ እንኳ። በራሳችሁ እመኑ።
17. ተአምራትን አትጠብቁ፤ እንዲፈጠሩ አድርጉ። አዎ፣ ሁልጊዜ ብቻችሁን ላታደርጉት ትችላላችሁ፤ ነገር ግን የሰዎችን አስተያየት አትስሙ።
18. ጠንክሮ መሥራትና ጽናት ማንኛውንም ነገር እንድታሳኩ ያስችሏችኋል። ራስን ዝቅ ማድረግ ከፍ ያደርጋችኋል።
19. ራሳችሁን እስክታገኙ/እስክታውቁ ድረስ መጠበቅ አቁሙ። ይልቁንስ ራሳችሁን ፍጠሩ።
20. ዓለም ለእናንተ ስትል ፍጥነቷን አትቀንስም/አትዘገይምና አታማሩ።በምትችሉትና በአቅማችሁ ተንቀሳቀሱ... @changeitwow
21. ማንም ሰው ስለ እናንተ ምንም ዕዳ የለበትም።ለራሳችሁ ራሳችሁን ተጠያቂ አድርጉ።
22. ህይወት የአንድ ተጫዋች ጨዋታ ናት። ብቻችሁን ትወለዳላችሁ፤ ብቻችሁን ትሞታላችሁ። ሁሉም ትርጓሜዎቻችሁ የራሳችሁ ብቻ ናቸው፡፡ በሶስት ትውልድ ውስጥ ትረሳላችሁ ማንምም ለእናንተ ግድ አይሰጠውም። ከመምጣታችሁ በፊትም ማንም ግድ አልሰጠውም ነበር። ሁሉም ነገር የአንድ ተጫዋች ነው፡፡
23. የህይወታችሁ መንገድ ሁልጊዜ ጥገኛ፣ የተጨነቃችሁና ደካማ እንድትሆኑ በሚያደርግ መልኩ የተነደፈ ሊመስል ይችላል። ነገር ግን መውጫው አንድ ብቻ ነው፤ እሱም ለመውጣት መወሰን። ከራሳችሁ በቀር ማንም እናንተንም ሆነ የምትወዷቸውን ሰዎች አያድንም።
24. ሁሉም ሰው እንደናንተ አይነት ልብ የለውም።
t.me/changeitwow
9 785
በ2014ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ'Z' ቅርጽ የተቆረጠ ፀጉር ይዞ ብቅ ብሎ ነበር። የዚህን ትርጉም የማያውቁ ብዙ ደጋፊዎች ያፌዙና ይሳለቁበት ነበር።
በርካቶች ያላወቁት ነገር ቢኖር፣ ይህ የፀጉር ቅርጽ በኮርቲካል ዲስፕላሲያ (የአእምሮ ህመም) ለሚሰቃየው የ10 ወር ህፃን ኤሪክ ኦርቲዝ ክሩዝ የተደረገ ልብ የሚነካ ድጋፍ መሆኑ ነው። ህፃኑ ለመዳን 83,000 ዶላር የሚያስወጣ ቀዶ ሕክምና ያስፈልገው ነበር።
ሮናልዶ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ የተጠየቀው ለጨረታ የሚሆን ፊርማ ያለበት ማሊያ እንዲለግስ ቢሆንም፣ እርሱ ግን ለቀዶ ህክምናው የሚያስፈልገውን ሙሉ ወጪ ራሱ ከፍሏል ተብሏል።
በፀጉሩ ላይ ያለው 'Z' ቅርጽ፣ ህፃኑ ኤሪክ ከቀዶ ህክምና በኋላ የሚኖረውን ጠባሳ የሚያሳይ ምልክት እንደሆነ ይነገራል። ይህም ከቃል በላይ የሆነ የትብብር እና የርህራሄ ምልክት ነው።
እውነተኛ ክብር። አድናቆት ❤️
ሶሻል ሚዲያ
ራስን መለወጥ
#like #Ethiopia #share #ethiopian_tik_tok #ethiopian_tik_tok🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 #ethiopian_tik_tok🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
9 785
ሴትዮዋ ከአንድ ባለታክሲ ጋር አውሮፕላን ጣቢያ ድረስ እንዲያደርሳት ከተስማሙ በኋላ ተሳፍራ ጉዞ ጀመሩ፡፡ አንድ ትንሽ የሰፈር መንገድ ማቋረጫ ጋ ሲደርሱ ከዚህ መጣ ሳይባል አንድ መኪና በፍጥነት እየበረረ ወደ ዋናው መንገድ ገባ፡፡ በዚህ ጊዜ ሴትዮዋን ከጫነው ታክሲ ጋር ሊጋጭ ሲል የታክሲው ሾፌር በፍጥነት ፍሬን ሲረግጥ ታክሲው በአለበት ተሽከርክሮ ፊቱ ወደ መጣበት አቅጣጫ ዞረ። በታክሲው ሾፌር ቅልጥፍና የተነሳ የሴትዮዋ እና የታክሲ ሾፌሩ ሕይወት ተረፈ፡፡
ጥፋተኛ የነበረው መኪና አሽከርካሪ በሠራው ከፍተኛ ስህተት ከመፀፀት እና ይቅርታ ከመጠየቅ ይልቅ የታክሲውን አሽከርካሪ መሳደብ ጀመረ። የታክሲ አሽከርካሪው ግን ምንም ሳይናደድ በፈገግታ እጁን እያውለበለበ ለሚሳደበው አሽከርካሪ ሰላምታ ሰጠው፡፡ ሰላምታው እጅግ በጣም ሰላማዊ እና ከልብ ነበር።
ተሳፋሪ በሁኔታው በጣም የተደነቀችው የታክሲዉን አሽከርካሪ እንዲህ በማለት ጠየቀችው:: “ይህ ሰው ሁለታችንንም ገድሎን ነበር። መኪናህንም ከጥቅም ውጭ ሊያደርጋት ነበር። ያም ሆኖ ይቅርታ ከማለት ይልቅ ይሳደብ ነበር:: ታዲያ ይህን ሁሉ አድርጎህ እንዴት ሰላምታ ሰጥተህ በፈገግታ ትሸኘዋለህ?''
የታክሲ አሽከርካሪው በጣም እረጋ ብሎ እንዲህ በማለት አስረዳት፡፡ “በጣም ብዙ ሰዎች ከአንድ ቦታ ቆሻሻ ጭኖ ሌላ ቦታ ወስዶ እንደሚያራግፍ መኪና ናቸው:: ውስጣቸዉን በቆሻሻ ሞልተው ከቦታ ቦታ ይንቀሳቀሳሉ፡፡ በውስጣቸው የያዟቸው የቆሻሻ ዓይነቶች ጭንቀት፣ ብስጭት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ክፋት፣ ቅናት፣ ቁጣ፣ ተንኮል፣ እና ምቀኝነት የመሳሰሉት ናቸው፡፡
“ልክ የቆሻሻው መኪና የያዘው ቆሻሻ በማጠራቀሚያው ውስጥ ሲሞላ አንድ ቦታ ወስዶ እንደሚያራግፈው ሁሉ ሰዎችም ውስጣቸው የተጠራቀመው ቆሻሻ ሲሞላ የሚደፉበት ቦታ ይፈልጋሉ፡፡ ካልተጠነቀቅን እነዚህ ሰዎች የያዙትን ቆሻሻ እኛ ላይሊደፉብን ይሞክራሉ፡፡ ቀደም ሲል ያየሽው ሰው ይህን ቆሻሻውን ነበር ሊያራግፍብኝ የሞከረው፡፡ ይህ ሲሆን እኛ መቀበል የለብንም፡፡ ስለዚህ እንደዚህ ዓይነት አጋጣሚ ሲገጥመን ማድረግ ያለብን በፈገግታ ሰላምታ ሰጥትን ማሰናበት እና የእራሳችንን ጉዞ መቀጠል ነው:: በምንም ዓይነት መንገድ የቆሻሻቸው መድፊያ መሆን የለብንም። አንዴ የእነሱን ቆሻሻ ከተቀበልን የእኛም የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ይሞላ እና ሌሎች ሰዎች ላይ ለማራገፍ እንገደዳለን" አላት፡፡
ሁላችንም በተለያየ ጊዜ ቆሻሻቸውን ሊደፉብን የሚፈልጉ ሰዎች ይገጥሙናል፡፡ የእነሱን ቆሻሻ ከተቀበልን እኛም የቆሻሻ ማራገፊያ ለመፈለግ እንገደዳለን። ስለዚህ መጀመሪያውነ- የማንንም ቆሻሻ አለመቀበሉ በጣም ተመራጩ ዘዴ ነው።
👉<< የቆሻሻ ማጠራቀሚያው ሲሞላ የግድ ማራገፊያ ቦታ ይፈለጋል >>
ሶሻል ሚዲያ
ራስን መለወጥ
#Ethiopia
#like
#share
9 785
ልብ ያለው ይማርበታል!
በአገር ውስጥ አንድ ሀብታም ባለጠጋ ሰው ይኖር ነበር ። ለጋብቻም የደረሰች ልጃገረድ የሆነች ሴት ልጅ ነበረችውና ልጅህን ዳርልን ጥያቄ በተደጋጋሚ ከብዙ ወንዶች ይቀርብለት ነበር ። ታድያ በዚህ የተማረረው አባት ልጁን ለማንም ለመዳር ፈቃደኛ አለመሆኑን ቢያሣውቅም የጠያቂዎችን ቁጥር በይበልጥ ጨመረው እንጂ
ሊያስቆመው አልቻለም ።
ታድያ በዚህ ግራ የተጋባው አባት እንደ ባህሉና ስርአቱ ወደ አገር ሽማግሌዎች በመሄድ እየሆነ ያለውን በሙሉ ያሥረዳል ። ሽማግሌዎችም ነገሩን በጥሞና ካዳመጡ በዋላ አንድ ምክር ይለግሡታል ፣ እንዲህም አሉት፣ ለልጅህ በጣም ብዙ ኪስ ያለው ሱሪ ታሰፋና በእያንዳንዱ ኪስ ውስጥ ሳንቲሞችን ሙላበት ። ሳንቲሙን እስከ አፉ ድረስ ከሞላህ በዋላ ለጋብቻ ጥያቄ ያቀረቡትን በሙሉ
ሠብሥበህ አንድ ትእዛዝ እዘዛቸው እንዲህም በላቸው።
ልጄን ከፊት ለፊታችሁ እንድትሮጥ አደርጋለው ። ከናንተም መካከል አሮጦ የያዘ ሰው እሱ ልጄን የሚያገባ ይሆናል ይላቸዋል ። በዚህም ግዜ ሰዎቹ ባባትየው ትእዛዝ ይስማማሉ ። ከዛም አባትየው ወደ ልጁም ይሄድና ልጄ እያባሩሽ ሳለ አንድ ሰው ሊይዝሽ ሲደርስብሽ ሳንቲሙን ከኪስሽ እያወጣሽ መሬቱ ላይ በትኚው ብሎ ይነግራታል ።
ልጅቷም ያባቷን ትእዛዝ በመቀበል ሩጫው ይጀመራል ። ከዛም ከሩዋጮቹ መካከል አንዱ ሊይዛት ሲደርስባት ሳንቲሙን አውጥታ ትበትናለች ከዛም ሰውየው እሷን ትቶ ሳንቲሙን መልቀም ይጀምራል ። ሊይዟት የደረሡት ላይ በሙሉ ሳንቲሙን እያወጣች ስትበትን እሷን
ትተው ሳንቲሙን መልቀሙን ተያያዙት ።
ልጅቷም ሸክሙ እየቀለለላትና ፍጥነት እየጨመረች ሄደች ሊይዟትም የደረሱባት ሁሉ እሷን ትተው ከኪሷ የሚበተነውን ሳንቲም ወደ መልቀም ተቀየሩ። አንድ ምስኪን ደሀ ሰው ግን ከኪሷ የሚበተነው ሣንቲም ሳያጓጓው እሷን ራስዋን አሳዶ በመያዝ ልጅቷን የራሱ አደረጋት
ይህንንም የተመለከተ አባት ለልጁ ባል ሊሆን የሚችል ሰው
በማግኘቱ ደስ አለው ። ልጁንም ዳረለት ።
ብዙዎቻችን ወደ እግዚአብሔር ቤት ለምንድነው የምንሄደው ? በረከትን ፣ ገንዘብን ፣ ትዳርን ፣ ቤት ፣ መኪና ፣ ትርኪ ምርከኪ ፍለጋ ፣ ወይስ እግዚአብሔርን ራሱን ፍለጋ ? ማናችንም እግዚአብሔርን አናታልለውም።
የእያንዳንዳችንን የተሰወረ የልብ መሻት ያውቃል ።
እጁን ሳይሆን ልጁን ፍትፍቱን ሳይሆን ፊቱን ፈላጊ እንሁን ፡፡
ስለዚህ አንተም ይህ አሁን ያነበብከው መጣጥፍ ትምህርት ሰጪ ሆኖ ካገኘኸው ዘመዶችህ እንዲያነቡትና ትምህርት እንዲወስዱ ዘንድ ሼር
አድርጉላቸው ።
ከወደዳችሁት ሼር (ሶሻል ሚዲያ)
t.me/changeitwow
ራስን መለወጥ
#Ethiopia@changeitwow
