cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Walta Tv ዋልታ ቲቪ

✅Walta tv news Official Telegram Channel Join Us For more Update

Show more
Advertising posts
4 676
Subscribers
-124 hours
+157 days
+10330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጫካ ፕሮጀክት ላይ እየሠሩ ላሉ ሠራተኞችን፣ ለበዓል በተዘጋጀ የምሳ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው፣ የእንኳን አደረሳችሁ መልክት አስተላልፈዋል::
Show all...
"ዛሬ ማልደን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙ አቅመ ደካሞች እና የሃገር ባለውለታ የከተማችን ነዋሪዎችን በአብረሆት ቤተ መጽሃፍትፆም አስፈትተናል:: ትንሳኤ የፍቅር እና የርህራሄ ተምሳሌት በመሆኑ እኛም ጎብኚ እና ጠያቂ ከሌላቸው ነዋሪዎቻችን ጋር ምግብን ብቻ ሳይሆን ፍቅርን ተጋርተናል:: ሁላችንም በያለንበት አቅመ ደካሞችን እና ጠያቂ የሌላቸውን እያሰብን በዓሉን በፍቅርና በአብሮነት እናሳልፍ:: ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!" የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Show all...
👍 1
ኤፕሲዊች ታዉን ወደ ፕሪሚዬር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ ሚያዚያ 26/2016 (አዲስ ዋልታ) ኤፕስዊች ታዉን ከ22 ዓመታት በኋላ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ተመለሰ። በቅፅል ስማቸው ዘትራክተር ቦይስ የሚባሉት ኤፕስዊቾች ዛሬ ከሃደርስፊልድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉቸውን ተከትሎ ወደ ታላቁ ፕሪሚዬር ሊግ ማደጋቸውን አረጋግጠዋል። የቡድኑ ማደግ አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ ባለፈው ዓመት ከሶስተኛ ዲቪዚዮን ወደ ሻምፒዮንሽፑ አድጎ ባመቱ ደግሞ ወደ ፕሪሚዬር ሊጉ መመለሱ ነው የተገለጸው። ይህም ሳውዝሃምፕተን እ.ኤ.አ 2012 ካስመዘገበው ታሪክ ጋር እንዲጋራ አስችሎታል። በሻምፒዮንሽፑ 24 ቡድኖች የሚሳተፉ ሲሆን በደረጃ ሰንጠረዥ አንደኛና ሁለተኛዎቹ ቡድኖች በቀጥታ ወደ ፕሪሚዬር ሊጉ ያድጋሉ። ሌስተር ሲቲ በኬራን ማኬና ከሚሰለጥነው ኤፕስዊች ታዉን ቀደም ብሎ ወደ ፕሪሚዬር ሊጉ መመለሱ ይታወሳል። ቀጣዮቹ አራት ቡድኖች የደርሶ መልስ ጨዋታ አድርገው አንደኛ የወጣው ቡድን በሶስተኝነት ፕሪሚዬር ሊጉን ይቀላቀላል፡
Show all...
👍 4
አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር የትንስኤ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
Show all...
👍 2
የክልል ርዕሠ መስተዳድሮች የ2016 የትንስኤ በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ሚያዝያ 26/2016 (አዲስ ዋልታ) የክልል ርዕሠ መስተዳድሮች የ2016 የትንስኤ በዓልን በማስመልከት ለክርስትና አምነት ተከታዮች የእንከን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም የትንሳዔ በዓል መታዘዝን፣ይቅርታንና ምህረትን እንዲሁም አንዱ ለሌላው መተሳሰብ እንዳለበት የሚያስተምረን ነው ብለዋል፡፡ መረዳዳትንና መጠያየቅን ከተለመደው ባህል ባለፈ በፍጹም መንፈሳዊነት ስሜት በጎዳና ላይ የወደቁትን በማሰብ፣በህግ ጥላ ስር ያሉትን በመጠየቅ፣ታመዉ የተኙትን በማጽናናትና ካለን ላይ በማካፈል በአብሮነት ትንሳኤውን የምናከብርበት በዓል ሊሆን ይገባልም ስሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። የደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ለትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈው ክርስቶስ የአዳምን ዘር ከበደል ቀንበር ነፃ ያወጣበት፤ ለሰው ልጆች ምሕረትና ድኅነት፤ ሰላምና ፍቅር የተገኘበት በድምቀት የሚከበር ታላቅ በዓል ነው ብለዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳደሩ አክለውም “በዓለ ትንሣኤው የዕርቅ፤ የይቅርታና የሰላም መገለጫ ነው፡፡ በሰውና በፈጣሪ መካከል የነበረ የጥል ግድግዳ በአምላክ ይቅር ባይነት የፈረሰበት፣ ዕርቅና ሰላም ወርዶ አዲስ የምሕረት ምዕራፍ የተከፈተበት በመሆኑ በዓሉን ስናከብር ቂም፤ ቁርሾና በቀልን በይቅርታ በመሻገር ሊሆን ይገባል” ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
Show all...
👍 4
እንኳን ለ2016 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
Show all...
👍 4
በአቃቂ የገበያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 ንግድ ሱቆች ተቃጠሉ ሚያዝያ 25/2016 (አዲስ ዋልታ) በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አቃቂ የገበያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ 16 ንግድ ሱቆች ሙሉ በሙሉና በከፊል መቃጠላቸው ተገለጸ። ትላንት ምሽት 3:10 ሰዓት ላይ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር አምስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ ሁለት የውሃ ቦቴ ከ44 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር መሰማራቲንና እሳቱ ወደ ገበያ ማዕከሉ ተስፋፍቶ በሰውና በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ መቆጣጠር እንደተቻለ ተገልጿል። የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አደጋውን ለመቆጣጠር ሁለት ሰዓት መፍጀቱን ገልጾ በአደጋ መቆጣጠሩ ሂደት የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጋቸውን አመልክቷል። በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩም ተገልጿል።
Show all...
👍 2
የትንሳኤ በዓልን በአዲስ ዋልታ ከአስታራቂዎች ጎጆ #ትንሣኤ_በዓል
Show all...
👍 2
ምክትል ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ባሕር ዳር ገቡ።
Show all...
👍 6
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋሩ ሚያዚያ 24/2016 (አዲስ ዋልታ) ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርተዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው መደጋገፍ የእለት ተዕለት ተግባር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። መጪውን የትንሳኤ በዓል ከአቅመ ደካማ ወገኖች ጋር አብሮ ማሳለፍ እንደሚገባም ተናግረዋል። ድጋፍ የተደረገው በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ለሚኖሩ አቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ ኑሮ ላይ ለሚገኙ ወገኖች መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።
Show all...
👍 2