en
Feedback
Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

Zebidar Media (ዘቢዳር ሚዲያ)

Open in Telegram

# ይህ የዘቢዳር ቻናል የሀገራችን ብሎም የጉራጌ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካ፣ ኪነ ጥበብ፣ ታሪክ፣ ርዕዮት እና ሁለንተናዊ መልክ የሚዳሰስበት የመገናኛ የመወያያ እና የመጦመርያ አውድ ነው!

Show more
3 793
Subscribers
No data24 hours
-97 days
-3730 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ "የደንጣ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ" በሃድያ ዞን "የኮንቶማ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በቡታጀራ ከተማ ሊያደርጉት የነበረውን የመስራች ጠቅላላ ጉባኤ እንዳያደርጉ መከልከሉን ተ
+1
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ "የደንጣ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ" በሃድያ ዞን "የኮንቶማ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በቡታጀራ ከተማ ሊያደርጉት የነበረውን የመስራች ጠቅላላ ጉባኤ እንዳያደርጉ መከልከሉን ተቃውሞ መግለጫ አወጣ። የመግለጫው ሙሉ ክፍል ከታች ባሉት 2 ገጾች ያገኙታል Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የወልቂጤ ዩኒቨሪስቲ ድንቅ ስራ። የሚሰማ እስካለ መናገራችንን እንቀጥላለን! የወልቂጤ ዩኒቨሪስቲ በጉራጌ ዞኖች እንደ የግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት ያሉትን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶችን እንዝለላቸው ከተባ
+1
የወልቂጤ ዩኒቨሪስቲ ድንቅ ስራ። የሚሰማ እስካለ መናገራችንን እንቀጥላለን! የወልቂጤ ዩኒቨሪስቲ በጉራጌ ዞኖች እንደ የግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት ያሉትን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶችን እንዝለላቸው ከተባለ ብቸኛው የፌደራል ተቋማት ነው ማለት ይቻላል። ይህ ተቋም ለጉራጌ ውክልና የተሰጠ እንደመሆኑ መጠን ከዛሬ ሁለት አመት በፊት ከመግቢያ ዋና በሩ (Main gate) ጀምሮ ጉራጌአዊ መልክና ቁመና ሊኖረው ይገባል የሚል ትችት አቅርበን ነበር። በወቅቱ በርካታ የድጋፍ ሃሳቦችን ብናስተናግድም ጥቂት እማይባሉ ደግሞ በዘረኝነት ሲከሱን ነበር። የዩኒቨሪስቲው ቦርድ ቀድሞ በያዘው ውጥን ይሁን የማህበረሰቡን ፍላጎት መሰረት አድርጎ በወሰደው እርማት በአሁን ሰዓት የማህበረሰቡን ድንቅ የምህንድስና ጥበብ ሊያሳይ የሚችል እጅግ ውብ የሆነ የጉራጌ ጎጆ ቤት ንድፍ (design) በዋና መግቢያ በሩ ላይ ገንብቶ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል። እኛም እንደ ሚዲያ ለማህበረሰቡ ይበጃሉ ያልናቸውን ሃሳቦች በማጋራት፤ የሰሩ እጆችን በማወደስ፤ የተዘነጉ ተግባራትን በመጠቆም፤ የተበላሹ አሰራሮችን በመተቸት፤ የተገቡ ቃሎችንና የተረሱ ስራዎችን በማስታወስ እንቀጥላለን። ከጉራጌ ህዝብ ጥቅም ውጪ የምናጨበጭብለትም ይሁን የምንጮህበት ግለሰብም ሆነ የቡድን የለንም። መለኪያችን የህዝባችን ተጠቃሚነት ብቻ እና ብቻ ነው!። የወልቂጤ ዩኒቨሪስቲ የሰራው ስራ ይበል የሚያሰኝ ነውና አድናቆታችንን ልንቸረው እንወዳለን!። እናመሰግናለን! ሐምሌ 9,2015 ዓ.ል በዘቢዳር ያጋራነው እና የአስተያየት ሰጪዎች ሃሳብ ይህን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ። https://www.facebook.com/share/p/1BagrhA266/ Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ለ10 ቀን ተሰጥቶ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ነገ ተሰብሮ እንዲታይ ተቀጥሯል። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 10/2018 ዓ.ም ሃሙስ አመሻሽ ታስረው ሰኞ ከሰዓት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው የ10 ቀን
ለ10 ቀን ተሰጥቶ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ነገ ተሰብሮ እንዲታይ ተቀጥሯል። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 10/2018 ዓ.ም ሃሙስ አመሻሽ ታስረው ሰኞ ከሰዓት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸው የነበረው የጉራጌ ዞንና የወልቂጤ ከተማ አመራርሮችና የፖሊስ አዛዥ የቀጠሮ ቀኑ ተሰብሮ በነገው ዕለት መዝገባቸው እንደሚታይ የደረሰን መረጃ ያሳያል። ነገ ጠዋት በሆሳዕና ከተማ በሚሰየመው ችሎት የሚቀርቡት የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ነጋ አስፋው፤ የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ሰለሞን መርሻ እና የወልቂጤ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ አስቻለው ገብሬ መሆናቸው ታውቋል። የዞንና የከተማ የጸጥታ መዋቅሩ አመራርሮች ለእስር ከተዳረጉ በኃላ ባሳለፍነው ቅዳሜ ከምሽቱ 4:30 አካባቢ የታጠቁ ኃይሎች የከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት ላይ ጥቃት ለመፈጸም ሙከራ አድርገው በጽ/ቤቱ ጠባቂዎች በተከፈተባቸው የአጸፋ ምላሽ ያሰቡትን ሳያሳኩ ለማፈግፈግ ተገደዋል። በወቅቱም የመናኸሪያ አካባቢ ቀበሌ ሊቀ-መንበር ተኩሰው በማቁሰላቸው ሊቀ-መንበሩ ለህክምና ወደ ሆስፒታል መወሰዱን ምንጮቻችን በዕለቱ ገልፀውልን ነበር። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

በዞንና በከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ላይ ፍርድ ቤቱ የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 09/2018 ዓ.ል ያሳለፍነው ሳምንት አርብ ለእስር የተዳረጉት የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ
በዞንና በከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ላይ ፍርድ ቤቱ የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 09/2018 ዓ.ል ያሳለፍነው ሳምንት አርብ ለእስር የተዳረጉት የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊ አቶ ነጋ አስፋው፣ የከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስቻለው ገብሬና የጉራጌ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሰለሞን መርሻ ፍርድ ቤት ቀርበው ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቶባቸዋል። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የወባ ወረርሽኝ በጉራጌ ዞን #ዘቢዳር_ሚዲያ :- ህዳር 08/2018 በጉራጌ ዞን ቆላማ አካባቢዎች ከፍተኛ የወባ ወረርሽኝ መከሰቱ ተሰምቷል። በርካታ ነዋሪዎች በተለያዩ ጤና ተቋማት ተኝተው እየታከሙ
የወባ ወረርሽኝ በጉራጌ ዞን #ዘቢዳር_ሚዲያ :- ህዳር 08/2018 በጉራጌ ዞን ቆላማ አካባቢዎች ከፍተኛ የወባ ወረርሽኝ መከሰቱ ተሰምቷል። በርካታ ነዋሪዎች በተለያዩ ጤና ተቋማት ተኝተው እየታከሙ ሲሆን የጤና ተቋማት የመድሃኒት ችግር እንደገጠማቸው የዘቢዳር ምንጮች ገልፀዋል። በሽታው የሰው ህይወት እየቀጠፈ በመሆኑ መንግስትና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ፈጣን እርምጃ ሊወስዱ ይገባል ሲሉ ለዘቢዳር ሚዲያ መረጃ ጥቆማ የሰጡ ተወላጆች ገልፀዋል። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የቀቤናና የሰባት ቤት ጉራጌ ግንኙነቶች:: ክፍል 1 ★ ቀቤኖች ከሲዳማ አካባቢ መጥተው በሰባት ቤት ጉራጌ አካባቢ ከሠፈሩበት ጊዜ ጀምሮ በልዩ ልዩ መንገድ ይገለጽ የነበሩ ግንኙነቶች በቀቤናና በሰባት ቤት ጉራጌ መካከል ተፈጥረው እንደነበር የሚታወቅ ነው:: ቀቤኖች በሕዝባዊ የፍለሳ እንቅስቃሴ ሲዘዋወሩ ከቆዩ በኋላ። በመጨረሻም ዘናበነርና በወልቂጤ አካባቢዎች በተደራጀና በተጠናከረ ሁኔታ ኑሮአቸውን መምራት የጀመሩ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ስላማዊ ኑር መመስረት ችለዋል ለማለት አያስደፍርም በመሆኑም በተለያዩ ጊዜያት ከአካባቢ የሰባት ቤት ጉራጌዎች ጋር ጦርነቶች ማድረጋቸውን የአካባቢው አፈታሪክ ያረጋግጣል:: በዚያን ጊዜ በአካባቢው የነበሩ የሰባት ቤት ጉራጌዎች የቀቤኖችን መምጣት በዝምታ አልተመለከቱም በተለያዩ ጊዜያትም ጉራጌዎች በቀቤኖች ላይ ባደረጉት ጥቃት የሰፈሩባቸውን ቀበሌዎች ለመልቀቅ ተገደው እንደነበር ይታወቃል:: በቀቤናና በሰባት ቤት ጉራጌዎች ስለተከሰተው አለመግባባትና ስለግንኙነታቸው መሻከር በሚመለከት በቀቤና የትውፊት መረጃ ውስጥ ይገኛል:: አፈታሪኩም እንደሚከተለው ያብራራዋል:: በሁለቱ ሕዝቦች መካከል የተደረገው ጦርነት በአንድ የመስቀል በዓል ላይ በተጫረ ጠብ እንደነበር አፈታሪኩ ይገልጻል:: በዓሉን ለማድመቅ የቀቤናና የሰባት ቤት ጉራጌ ወጣቶች በምሽት ጭፈራ ላይ እያሉ የቀቤና ወጣቶች የጉራጌ ወጣቶችን በማጥቃታቸው ጠቡ እየሰፋ መጥቶ በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ለተከሰተው ጦርነት በምክንያትነት ይጠቀሳል :: በጦርነቱም ጉራጌዎች ቀቤኖችን ከይዞታቸው እንዳስለቀቁዋቸው ይነገራል:: በዚያን ጊዜ የቀቤኖች መሪ ኬሮ ማጋናሴ እንደነበር ይነገራል:: ይህም መሪ ቀቤኖችን ማፌድ ድረስ መርቶ የመጣ ነው:: ቀቤኖች በይዞተቸው ላይ ለመቆየት ሲሉ ልዩ ልዩ ዘዴዎችን ለመጠቀም ቢሞክሩም ጥረታቸው ባለመሳካቱ ክልላቸውን ለመልቀቅ ተገድደዋል:: በዚያን ወቅት የሰባት ቤት ጉራጌዎች ምሁርን፣ አክሊልንና ሶዶን ይዞ እስከ አይመለል ድረስ ያሉትን መሬቶች በይዞታቸው ሥር አድርገው ይኖሩ ነበር:: ቀቤኖች በይዞታቸው ሥር ያደረጉትን አካባቢ ከሰባት ቤት ጉራጌዎች በተደረገባቸው ግፊት ለቅቀው ከመሄዳቸው በፊት መሪያቸው አንድ ዕቅድ ወጥኖ እንደነበር አፈታሪኩ ያመለክታል:: ቀቤኖች አህዮቻቸውንና ዶሮዎቻቸውን ቤታቸው ውስጥ አስረው በሌሊት እንዲለቁ መሪያቸው ኬሮ መጋናሴ መመሪያ አስተላለፈ በተላለፈላቸው መመሪያ መሠረት ቀቤኖች አህዮቻቸውና ዶሮዎቻቸውን ቤታቸው ውስጥ አስረው ማፌድን በሌሊት ለቀቁ:: ሰባት ቤት ጉራጌዎች በቀቤኖች ላይ ጥቃት ለማድረስ በማለዳ ወደ ማፌድ ሲንቀሳቀሱ አንድም ሰው በመንደሩ ውስጥ ሊያገኙ አልቻሉም:: ያገኙት ነገር ቢኖር በየቤቱ ውስጥ የታሠሩትን አህዮችንና ዶሮዎችን ብቻ ነበር:: በመሆኑም ቀቤኖች ማፌድን መልቀቃቸውን ሲያረጋግጡ ወደ ክልላቸው ወደ ሰባት ቤት ጉራጌ ተመለሱ:: በአፈታሪኩ እንደተገለጸው ከሆነ ይህ ሁኔታ የተከሰተው ቀቤኖች ማፌድ ላይ ሠፍረው ኑሮአቸውን በሚገባ መመስረት ከጀመሩ በኋላ ነበር:: የሰባት ቤት ጉራጌዎች ወደ ክልላቸው ከተመለሱ በኋላ ኬሮ መገናሴ ዘናበነር ድረስ ሄዶ በአካባቢው ላይ ቅኝትና ስለላ ካከናወነ በኋላ ክልሉ ለሕዝቡ ኑሮና ለከብቶች አመቺነቱን አረጋገጠ:: በመጨረሻም ሕዝቡ ወደዚህ ሥፍራ ተንቀሳቅሶ እንዲሠፍርበት አደረገ ኬሮ መገናሴ ሕዝቡን መርቶ ዘናበነር ከመጣ ከጥቂት ዓመታት በኋላ እንደሞተ ይነገራል:: ይህ ፅሁፍ የቀቤና ልማት ማህበር (ቀልማ) 1988 ዓ.ል ወማ የቀቤና ብሔረሰብ ባህልና ታሪክ በሚል ካሳተመው መጽሃፍ የተወሰደ ነው። ገጽ 28-31 Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

በወልቂጤ ጉብርየ ክ/ከተማ የታሰሩ ወጣቶች ፍርድ ቤት ቀረቡ። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 05/2018 ከሰሞኑ የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ሶስት የከተማው ወጣቶችን ከጉብርየ ክፍለ ከተማ አስሯል። ፖሊስ በከተ
በወልቂጤ ጉብርየ ክ/ከተማ የታሰሩ ወጣቶች ፍርድ ቤት ቀረቡ። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 05/2018 ከሰሞኑ የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ሶስት የከተማው ወጣቶችን ከጉብርየ ክፍለ ከተማ አስሯል። ፖሊስ በከተማው ንብረት ማውደም ጠርጥሬአቸዋለሁ ሲል ያሰራቸው ወጣት ታምራት ተኸልቁ፣ ወጣት አሳየ ታደለ እና ወጣት ፍቃዱ ጠንክር መሆናቸው ታውቋል። ትላንት ዘቢዳር ሚዲያ የወልቂጤ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ኃላፊ አቶ አስቻለው ገብሬን በስልክ ስለወጣቶቹ እስር መረጃ የጠየቀች ሲሆን ኃላፊውም መረጃው ትክክል መሆኑን ገልጸው ከሰሞኑ በማህበር የተደራጁ የመንግስት ሰራተኞች መኖሪያ ቤት እንዲገነቡበተ በመንግስት በተሰጣቸው ቦታ ላይ የገነቡትን ግንባታ እንዲፈርስ ሲያስተባብሩ የነበሩ ናቸው ብለዋል። ባሳለፍነው ሳምንት ማንነታቸው ያልታወቁ ወጣቶች በተለምዶ 108 ተብሎ በሚጠራው መንደር ለቤተ-ክርስቲያን የተያዘ ነው ያሉት ቦታ ለሌላ አካል መሰጠቱ ተገቢ አይደለም ብለው ቅሬታ እያቀረቡ እንደነበር ተገልጿል። ለአቶ አሰቻለው ይሄንኑ ገልጸን ከዚህ ቀደም ቦታው በቤተ ክርስቲያን የተያዘ እንደነበር ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን ኃላፊውም ቦታው ንጹህና ከዚህ ቀደም በማንም በባለቤትነት ያልተያዘ የከተማ አስተዳደሩ ይዞታ እንደነበር ገልጸዋል። ከታሳሪ ቤተሰቦች የወጣት ፍቃዱ ጠንክር አባት አጋዝ ጠንክር ጋር ደውለን ያገኘናቸው ሲሆን እሳቸውም ልጃቸው ያለአግባብ መታሰሩን ገልፀው ድርጊቱ ተፈጸመ በተባለ ቀን አዲስ አበባ ለስብሰባ ሄዶ ስለነበር ለሶስት ቀናት በከተማውም እንዳልነበረ ገልጸዋል። ፖሊስ ዛሬ ወልቂጤ ከተማ ፍርድ ቤት አቅርቦ ቀሪ ግብራአበሮቻቸውን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋልና መረጃዎችን ለማሰባሰብ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ የጠየቀ ሲሆን ፍርድ ቤቱ የ6 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የጫሙት ሽካ መጽሐፍ ትረካ በኤፍ.ኤም ሬዲዮ ሊቀርብ ነው። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 05/2018 ከ60 ዓመታት ፊት በደራሲ አበጋዝ ገብረኢየሱስ ኃ/ማርያም የተጻፈው የተፃፈው የጫሙት ሽካ የጉራግኛ መ
የጫሙት ሽካ መጽሐፍ ትረካ በኤፍ.ኤም ሬዲዮ ሊቀርብ ነው። #ዘቢዳር_ሚዲያ:- ህዳር 05/2018 ከ60 ዓመታት ፊት በደራሲ አበጋዝ ገብረኢየሱስ ኃ/ማርያም የተጻፈው የተፃፈው የጫሙት ሽካ የጉራግኛ መጽሐፍ ከሚቀጥለው ሰኞ ጀምሮ በወልቂጤ ኤፍ ኤም 89.2 ሬዲዮ መቅረብ እንደሚጀምር አዘጋጆቹ አስታውቀዋል። በየሣምንቱ ሰኞ ከምሽቱ 3:20 እና በድጋሚ እሑድ ምሽት 2:30 በወልቂጤ ኤፍ ኤም እንደሚቀርብ ተገልጿል። የጫሙት ሽካ በሬዲዮ የቀረበ የመጀመሪያው የጉራግኛ ስራ ይሆናል። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ህገ-ወጥ ግንባታ በማስቆም ላይ የነበሩ የጉራጌ ዞንና የወልቂጤ ከተማ አመራሮች በኮማንድ ፖስት አስተባባሪዎች ታሰሩ #ዘቢዳር_ሚዲያ :- ህዳር 05/2018 ዛሬ ጠዋት በወልቂጤ ከተማ ከአበሩስ ት/ቤት
ህገ-ወጥ ግንባታ በማስቆም ላይ የነበሩ የጉራጌ ዞንና የወልቂጤ ከተማ አመራሮች በኮማንድ ፖስት አስተባባሪዎች ታሰሩ #ዘቢዳር_ሚዲያ :- ህዳር 05/2018 ዛሬ ጠዋት በወልቂጤ ከተማ ከአበሩስ ት/ቤት ጀርባ እየተገነቡ ያሉ ህገ-ወጥ ግንባታዎችን በማስቆም ላይ የነበሩ የዞኑና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች በኮማንድ ፖስቱ ለእስር ተዳርገዋል። የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ነጋ አስፋው፣ የከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አስቻለው ገብሬ እና የከተማው ፖሊስ አዛዥ ዋ/ሳጅን ይታገሱ መሆናቸውን የዘቢዳር ሚዲያ የአካባቢው ምንጮች ያደረሷት መረጃ ያሳያል። አመራሮቹ በአሁን ሰዓት ወደ ሆሳዕና ከተማ የተወሰዱ ሲሆን ህገ-ወጡ ግንባታም እንደቀጠለ መሆኑን ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል። ተጨማሪ መረጃዎች ሲደርሱን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የጉራጌ አመጣጥ ታሪክ ስለጉራጌ ሕዝብ አመጣጥ ፕሮፌሰር ቤርናል አንድ ሀሳብ ሰንዝ ሯል። ጉራግኛና ሌሎቹ የሴም ቋንቋዎች እድሜአቸው በጣም ረጀም ነው። ከዚህ ቀደም ታሪክ ፀሐፊዎች የመሰላቸውን ፅፈዋል። ኮንቲ ሮሲኒ ግእዝ ከባሕር ማዶ መጥቶ ሌሎች ሴማዊ ቋንቋዎችን ወለደ ብሎ ጽፏል። ያ ሀሳቡ አሁን በትምህርትና በእውቀት ተሽሯል። ቀርቷል። ተረት ሆኗል። የጉራጌን ቋንቋ ስንመለከት የ700 ዓመት አድሜ ያለው ቋንቋ ነው ለማለት የሚቻል አይመስለኝም። ጉራጌ የአምደ ፅዮን የጦር አበጋዝ ከሆነው አዝማች ስብሐት ጋር መጣ የሚል አፈታሪክአለ። ይህንን የፃፉት አለቃ ታዬ ናቸው። አለቃ ታዬ የታሪክ ምሁርአይደሉም። ታሪክ ለመፃፍ የሞከሩ ሀገር ወዳድ ናቸው። አለቃ ታዬ ከሚሲዮኖች ጋር ጥቂት ቆዩ፥ ጀርመንን ጎበኙ፥ ከዚያም የኢትዮ ጵያን ታሪክ ጻፍኩ አሉ። አሁን እሳቸው የጻፉትን መፅሐፍ ስናነብ ጨዋታ ነው የሚመስለን። የአለቃ ታዬ መጽሐፍ ጥሩ የተረት መጽሐፍ ነው። እኛ ስለ ሳይንስ ስለ ስነልሳን፥ ስለ ሰነድ መረጃና ስለ ስነዘዴ ነው የምንናገረው። እነዚህን መረጃዎች ለማሳጠርና ምርቱን ከግርዱ ለመለየት የሚችለው ደግሞ በመስኩ የተካነ ባለሙያ ነው። ዜና መዋዕል እኮ ጥሬ መረጃ ማለት ነው። ያንን ጥሬ መረጃ የሚተረጉም ባለሙያ ያስፈልጋል። እዚህ አገር ታሪክ ሲፃፍ የነበረው ሙያው ሳይኖር በድፍረት ነው። ታሪክ ለመፃፍ ግን የታሪክ ጥልቅ ሙያና እውቀት ያስፈልጋል። የጉራጌን ሕዝብ በተመለከተ የአምደ ዕዮንን ጦር ከወጉት አያሌ የድቡብ ሕዝቦች መካከል አንዱ የጉራጌ ሕዝብ ነው። የጉራጌ ሕዝብ የአምደፅዮን ሰራዊት አካል ቢሆን ኖሮ አምደ ፅዮንን መልሶ አይወጋም ነበር። ጉራጌዎች ከአምደፅዮን ሰራዊት ጋር መዋጋታቸው በራሱ በአምደ ፅዮን ዜና መዋዕል ተገልጿል። የጉራጌ ሕዝብ በደቡብ እንዳሉት ሌሎች ሕዝቦች ሁሉ ነባርና ጥንታዊ ሕዝብ ነው። የጉራጌ ሕዝብ በአምደፅዮን ዘመን ከሰሜን ኢትዮጵያ መጣ የሚለው አፈታሪክጥሩ ተረት ነው። እኛ የምንፈልገው ግን እውነተኛ ታሪክና እውቀት ነው። የጉራጌ ሕዝብ በአካባቢው ለብዙ ሺሀ ዓመታት መኖሩ የሚካድ ጉዳይ አይደለም። ፕሮፌሰር ቤርናል ለማረጋገጥ የፈለገው ይህንን እውነታ ነው። ሕዝቡ ነባርና ጥንታዊ ሕዝብ ነው። ከመቼ ጀምሮ እንደሆነ በአኃዝ ለማስቀመጥ ቢያቅተንም ለብዙ ሺህ አመታት ሕዝቡ በአካባቢው ይኖር እንደነበር ማወቅ አያዳግትም። ሁኔታዎችን በሚገባ ሳይመረምሩ በይሆናል ግምት ሕዝብን ማሳሳት ግን ተገቢ አይደለም። ዛሬ ያልታወቀ ነገር ነገ ይታወቃል። ሽማግሌ ዎች የጉራጌ ሕዝብ ከቅርብ ዘመናት በፊት ከሰሜን ኢትዮጵያ ነው የመጣው ስላሉ ብቻ እንደበቂ የታሪክ መረጃ ተደርጎ መወሰድ የለበትም። መመርመር አለበት። ያንን ለማጥናት ስነዘዴ ያስፈልጋል። ጊዜው በውል መታወቅ አለበት። ከዚያ በኋላ እውቀት ይሆናል። እውቀትን ሸሽተን በእምነት መንገድ እንጓዝ ከተባለ ሰው የፈለገውን ማመን ይችላል። ታሪክ ከሆነ ደግሞ በጠንካራ ማስረጃ ማስደገፍ ያስፈልጋል። ከሰሜን የመጡ ወራሪ ነገሥታት ጉራጌዎችን ወግተው ኣስገብረዋቸዋል። ከአምደ ጽዮን ጀምሮ የሰሜን ኢትዮጵያ ነገሥታት የጉራጌን ሕዝብ በተከታታይ ወግተውታል። በዚያን ወቅት የጉራጌ ሕዝብ የራሱ ቋንቋ፥ የራሱ ባህል፥ የራሱ ሃይማኖት ነበረው። ከወረራ በኋላ ጉራጌዎች ክርስትናንና እስልምናን ተቀብለዋል። የጥንቱን እምነታ ቸውን የያዙም አሉ። እነዚህ ሕዝቦች አሁን በአሉበት ቦታ ለብዙ ዘመናት ኖረዋል። ከሰሜን ኢትዮጵያ የመጡት ከ700 ዓመታት በፊት ነው የሚለው ሀሳብ ሚዛን አይደፋም። የሚያዋጣው ፕሮፌሰር ቤርናል ያቀረበውን ፈተና ለማለፍ ጥልቅ የታሪክ ምርምር ማድረግ ነው። ለዚህም በርትቶ ታሪክን ማጥናት ነው። አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ጥሩ ብሔራዊ ስሜት ስላለኝ ታሪክ እጽፋለሁ ወይም አስተምራለሁ ቢል አያዋጣም። ብሔራዊ ስሜቱን በኪነትና በመዝሙር መግለጽ ይችላል። ስሜት ግን እውቀት አይሆንም። የታሪክ ባለሙያም አያደርግም። የኢትዮጵያዊነት ታሪካዊ መሠረቶችና መሣሪያዎች ከገጽ 18-20 ላጲሶ ጌ. ድሌቦ Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

አቶ ታዬ ደንደአ ከሁለት ክሶች ነጻ ተባሉ! የቀድሞው ሰላም ሚኒስቴር አቶ ታዬ ደንደአ ዛሬ በዋለው ችሎት በሁለቱ ክሶች ነጻ መባላቸውን ጠበቃቸው አበራ ንጉሥ ለአሐዱ ሬዲዮ ገልጸዋል። በፌደራል ከፍተ
አቶ ታዬ ደንደአ ከሁለት ክሶች ነጻ ተባሉ! የቀድሞው ሰላም ሚኒስቴር አቶ ታዬ ደንደአ ዛሬ በዋለው ችሎት በሁለቱ ክሶች ነጻ መባላቸውን ጠበቃቸው አበራ ንጉሥ ለአሐዱ ሬዲዮ ገልጸዋል። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጸረ ሽብር ችሎት በዛራ ውሎው፤ "ከጠላት ጋር መተባበር" በሚል በአንቀፅ 251(ሐ)፣ መገፋፋትና ግዙፋዊ መሰናዳት አንቀፅ 257(ሰ) እንዲሁም፤ የፀና ፍቃድ ሳይኖር የጦር መሳሪያ ይዞ መገኘት በሚል ሦስት ተደራራቢ ወንጀሎች ተከሰው በክርክር ሂደት ላይ እንደነበሩ ይታወቃል። ይሁን እንጂ፤ የቀድሞ የሰላም ሚንስቴር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንደአን መዝገብ ሲመረምር የነበረው 1ኛ የፀረ-ሽብር እና ሕገመንግሥታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ዛሬ ሕዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ባስተላለፈው ውሳኔ 'ተከሳሹ ከተጠረጠሩበት ወንጀል ነጻ ናቸው' ብሏል። ጠበቃቸው አበራ ንጉሥ በሁለቱም የመጀመሪያ ክሶች ባቀረቡት የሰው፣ የሰነድ እና የቪዲዮ ማስረጃዎች በበቂ ሁኔታ ተከላክለዋል በማለት በአብላጫ ድምፅ በነፃ እንዲሰናበቱ ፍርድ መሰጠቱን የገለጹ ሲሆን፤ በ3ኛ ደረጃ ለቀረበባቸው የፀና ፍቃድ ሳይኖር የጦር መሳሪያ ይዞ መገኘት ወንጀል ግን 'ባቀረቧቸው ማስረጃዎች በበቂ ሁኔታ ማስተባበል አልቻሉም' በማለት የጥፋተኝነት ፍርድ በሙሉ ድምፅ ሰጥቷል ብሏል። እንዲሁም ጥፋተኛ በተባሉት አንድ ክስ የቅጣት አስተያየት ለመስማት ለሕዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል ሲሉ ጠበቃቸው አበራ ንጉስ ለአሐዱ ተናግረዋል። አሃዱን ጠቅሶ የዘገበው አንዳፍታ ዶት ኮም ነው Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

#ጉራጌ እና #አዲስ_አበባ በ1976 ብሔራዊ የሕዝብ ቆጠራ ውጤት ከአገሪቱ ጠቅላላ 42,061,699 ሕዝብ የጉራጌ ሕዝብ ብዛት 1,916,414 ወይም 4.6 በመቶ ከአዲስ አበባ ጠቅላላ 1,412,575
+1
#ጉራጌ እና #አዲስ_አበባ በ1976 ብሔራዊ የሕዝብ ቆጠራ ውጤት ከአገሪቱ ጠቅላላ 42,061,699 ሕዝብ የጉራጌ ሕዝብ ብዛት 1,916,414 ወይም 4.6 በመቶ ከአዲስ አበባ ጠቅላላ 1,412,575 ሕዝብ ደግሞ የጉራጌ ሕዝብ ብዛት 249,077 ወይም 17,6 በመቶ እንደሆነ ይታወሳል ። በአዲስ አበባ የመርካቶ ክፍለ ከተማ በተለይ የጉራጌዎች ዋናው ማዕከል ነው። በመርካቶ ክፍለ ከተማ የጉራጌዎች ዋናው ሥራ ደግሞ የጉሊት፣ የኪዎስክና የገበያ አዳራሽ ሥራ ጨምሮ ንግድ እንደሆነ የታወቀ ነው ። የመዲናው ታሪክ እንደሚያስተምረን ፤ በአዲስ አበባ የመርካቶ ክፍለ ከተማ ያገር ተወላጆች ሠፈር እንዲሆን በቀድሞ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ መሬት ላይ በ1928-1933 በወራሪ ፋሽስቶች የተቆረቆረ ነው ። ከፍ ሲል እንደተገለጸው ደግሞ ከ1881-1919 የጉራጌው የቸሀ-ውድማ ለም የእርሻ መሬት በፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴ መያዝ በዘመኑ ብዙ ጉራጌዎችን ወደ አዲስ አበባ ፍለሳ እንደ ሰደዳቸው የሚ ታወስ ነው ። በአዲስአበባ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ መሬት በታሪካዊ ዕድገትና ለውጥ የጉራጌ መኖሪያ ከተማ ሆነ ። የኢትዮጵያ የገባር ሥርአትና ጅምር ካፒታሊዝም ፡ 1900-1966 ገፅ 197-198 ላጲሶ ጌ. ድሌቦ (ዶ/ር) የዘቢዳር ጥያቄ:- ዛሬ ከ50 ዓመታት በኃል የጉራጌ ሕዝብ ቁጥር ስንት ነው? Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የእኖር ወረዳ ፖሊስ በአስገድዶ መድፈር  የተጠረጠረን ተጠርጣሪ በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል ከማህበረሰቡ ጋር ተናቦ እየሰራ መሆኑን ገለፀ። ጥቅምት 28, 2018 ዓ.ል በዚህ ሳምንት በእኖር ወረዳ አንድ የአዕምሮ ሕመምተኛ ነው የተባለ ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም ፈፅሞታል የተባለ የአስገድዶ መድፈር መነጋገሪያ ሆኖ ሰምብቷል። የወረዳው ፖሊስ በአንጻሩ በማህበራዊ ሚዲያ የሚወራው ከእውነታው በጣም የራቀና ማህበረሰቡን የሚያደናግር ነው ሲል መግለጫ አውጥቷል። ይህ መረጃ "አዛብተው አቅርበዋል" ያላቸውን በህግ ተጠያቂ እንደሚያደርግም በመግለጫው አክሎ ገጿል። #ዘቢዳር_ሚዲያ እየተሰራጩ ያሉትን የተራራቁ መረጃዎች ለማጥራት ባደረገችው ማጣራት ይስሃቅ ካሚል የተባለው የአዕምሮ ህመም ታማሚ እንደሆነ የተጠቀሰው ተጠርጣሪ በአንድ እናት አስገድዶ መድፈርና በሌላ የአስገድዶ መድፈር ሙከራ ወንጀል እንደፈጸመ ተገልጿል። በስልክ ስለሁኔታው ያነጋገርናቸው የወረዳው የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሰንብት በበኩላቸው በማህበራዊ ሚዲያ እየተነዛ ያለው ነገር ከእውነታው ፍፁም የራቀና ተጨባጭነት የሌለው መሆኑን በመግለጽ ከደረሰን የአንድ አስገድዶ መድፈር ሙከራ ውጪ ወደኛ የደረሰ ምንም አይነት ቅሬታ የለም ሲሉ ተናግረዋል። የፖሊስ አዛዡ አክለውም "ግለሰቡ ሐምሌ 2017 ዓ.ል ከገረንቦ ቀበሌ አንዲት ሴት ደፍሯል የሚል የክስ አቤቱታ ለወረዳው ፓሊስ መቅረቡን ተከትሎ ለህዝባችን የጥንቃቄ መልዕክት ከማስተላለፍ ጎን ለጎን ተጠርጣሪውን በመያዝ ለህግ እንዲቀርብ ለማድረግ ግለሰቡ ሊገኝ የሚችልባቸው አካባቢዎች ሁሉ የቀበሌ መዋቅሮች፣የወረዳው የፓሊስ አባላት፣አጋዥ የፀጥታ ኃይሎች እና የቀበሌ የሚሊሻ አባላት እንዲሁም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን  ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።" ሲሉ ለዘቢዳር ገልጸዋል። ዘቢዳር ከተጠርጣሪው ቤተሰቦች ባገኘችው መረጃ ተጠርጣሪው ከአካባቢው በመጥፋቱ ከሰባት ወር ወዲህ አየሁት የሚል ሰው በመጥፋቱ የት እንዳለም ማወቅ እንዳልቻሉ ገልጸዋል። #ማሳሰቢያ:- የተጠርጣሪውን ፎቶ ከቤተ-ዘመድና ከአካባቢው ማህበረሰብ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ማንኛውም የተጠርጣሪው ፎቶ ያለው ሰው በውስጥ ቢያደርሰን ለማህበረሰቡ እንዲደርስ የምናደርግ መሆኑን እናሳውቃለን። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ሰንጋተራ – ጉራጌ ሰፈር ከታች ፎቶው የተያያዘው የመላኩ ተገኝ (ዶክተር) ግለ ታሪክ፣ የዚያ ትውልድ የወቅቱ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ትዝታንና ትውስታን መሰረት ተደርጎ የተጻፈ ባለ 300 ገጽ መጽሐፍ ነው። በዚህ መጽሐፍ ላይ በ1940ዎቹ በአዲስ አበባ በተለይም ሰንጋ ተራ የሚኖሩ ጉራጌዎች ባህሪይ፣ ጠባይ እና የወቅቱ የአኗኗር ዘይቤ በጥቂቱ እንዲህ ሰፍሯል። ……………. “እኔና ወንድሜ የተወለድነው ሰንጋተራ ከ’ደሬ ውኃ ስንቁ” ሰፈርና ጉራጌ ሰፈር” መሀል ባለው በ’ብላታ በቀለ ግቢ ውስጥ ነው። እኔ ትዝ የሚለኝ ግን ጉራጌ ሰፈር ስንኖር ነው። ደሬ ጉራጌ ሰፈር ተብሎ የሚጠራው ዛሬ አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ካለበት በስተጀርባ የነበረው ሰፈር ነው። ወይን (“ንብ ባንክ እና ዙርያ ገባው” አካባቢ) የኛ ቤት በጉራጌ ሰፈር ዋናው መንገድ ላይ ሲሆን በጣም ብዙ ሰው የሚመላለስበት ነበር። ግመሎችን የሚነዱና ሸቀጥ በአህያ የጫኑ ነጋዴዎች ወደ መርካቶ ሲሄዱ፣ የኦርማ–ጋራዥ ሠራተኞችና ተማሪዎች በበራችን ሲያልፉ ትዝ ይለኛል። ደጃፍ እናቴ የምትሠራውን እየሠራች ቁጭ ብዬ ወጪ ወራጁን እመለከት ነበር። ለዓይን ያዝ ሲያደርግ የጎረቤታችን የወንድሙ አባት ክራራቸውን ሲጫወቱ የሚያመሹት ነገር ዛሬም ድረስ አልተረሳኝም። ጠዋት ጠዋት እማማ ትክከሏ #“በላለዴ ምጣ” ሳይሉ አያልፉም ነበር። ከበስተኋላችን ከሚኖሩት ጎረቤቶች ደግሞ ጠዋት ጠዋት ላም ስትታለብ፣ ቡና ሲወቀጥ፣ ልጆች ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ ሲዘገጃጁ ይሰማል፤ በሰንጋ ተራ። አብዛኛው ነዋሪ ትሑትና ሰው አክባሪ ነበር። በሳምንቱ በተወሰኑ ምሽቶች መንደርተኛው ሁሉ አቶ ባለሜና እማማ ትክከሏ ቤት ይሰባሰባል። ቡና በትልቅ ጀበና ይፈላል፤ የበቆሎ ቆሎ ቁርስ ይቆላል። ትላልቁ ሰው ቡና ሲጠጣ እኛ ኩታሮቹ ቆሏችንን እንበላና ከበሮ ይመጣል። ከዚያ በኋላ በጉራጊኛ ዘፈንና ጭፈራ ቤቱ ይደምቃል። እኔም ወንድ ልጅ መጨፈር ያለበትን የጉራጊኛ ጭፈራ ስልት ተማርኩ። ያኔ የነበሩ ጓደኞቼ አይረሱኝም። ፍቅሬ፣ ጉልላት፣ ፍቃዱ፣ እነ ገረመው ዘርጋው፣ ፍቃዱ ወልዴ፣ ግርማ ጣሴና አስራት ጣሴ ታላላቆቻችን ነበሩ። እናቴ ከጉራጌ ሰፈር ሴቶች ጋር ጥብቅ ወዳጅነት ስለነበራት ጉራጊኛ ልቅም አድርጋ ትናገር ነበር።” ከጌጡ ተመስገንን የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

በትራንስፖርት ክፍያ አለመግባሰት በተፈጠረ ግጭት የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ። ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥቅምት 23, 2018 ዓ.ል ትላንት ወልቂጤ ከተማ በተለምዶ ካምፕ 99 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የ
በትራንስፖርት ክፍያ አለመግባሰት በተፈጠረ ግጭት የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ። ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥቅምት 23, 2018 ዓ.ል ትላንት ወልቂጤ ከተማ በተለምዶ ካምፕ 99 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የባጃጅ አሽከርካሪና በተሳፋሪ መካከል በክፍያ ታሪፍ አለመግባባት ጸብ ተነስቶ የባጃጁ አሽከርካሪ ሕይወት አልፋለች። ሌላ ጊዜ ከካምፕ ሰፈር ጠረቆ የቦቆሎ ማሳ ድረስ 600 ብር ይከፈል የነበረ ሲሆን ሹፌሩ 800 ብር ካልሆነ አልሄድም በሚል የተጀመረ ጸብ መሆኑን ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያሳያል። በአጸፋው የሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች በመሰባሰብ አበሽጌ ወረዳ ጠረቆ የቦቆሎ ማሳ ተሰባስበው በመሄድ በአካባቢው በቀን ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ ሰዎች ላይ ጥቃት በመፈጸም 3 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን አንዱ በጽኑ ተጎድቶ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ይገኛል። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ያለከተማ መስተዳድሩ እውቅና ውጪ ሊገነባ ታስቦ በክልሉ መንግስት የታገደው የህንፃ ግንባታ ለማስቀጠል እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው። ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥቅምት 22, 2018 ዓ.ል ከአበሩስ ት/ቤት በስተ
ያለከተማ መስተዳድሩ እውቅና ውጪ ሊገነባ ታስቦ በክልሉ መንግስት የታገደው የህንፃ ግንባታ ለማስቀጠል እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው። ዘቢዳር ሚዲያ:- ጥቅምት 22, 2018 ዓ.ል ከአበሩስ ት/ቤት በስተጀርባ ሊገነባ ታስቦ በክልሉ መንግስት ጣልቃ ገብነት ግንባታው እንዲቆም የተደረገው የቀቤና ልዩ ወረዳ የሴክተር መስሪያ ቤቶች ግንባታ ከወልቂጤ ከተማ አስተዳደር እውቅና ውጪ ግንባታውን ለማስጀመር የልዩ ወረዳው የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የዘቢዳር ሚዲያ የአካባቢው ምንጮች ገልጸዋል። ከዚህ ቀደም የልዩ ወረዳው በቦታው ሊያደርገው የነበረ ህገ ወጥ ግንባታ በክልሉ መንግስት አማካኝነት እንዲቆም የተደረገ ቢሆንም አሁን ምን የተለወጠ ነገር በልዩ ወረዳው በኩል ተገኝቶ ወደ እንቅስቃሴ እንደተገባ ግልጽ የሆነ ነገር እንደሌለ ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል። የወልቂጤ ከተማ ፖሊስ ለህገ ወጥ ግንባታው ቅሳቁስ አቅርቧል የተባለ ሹፌር በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉ ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል። ከሰሞኑ በወልቂጤ ዙሪያ ላይ የተለያዩ ትንኮሳዎች እየታዩ እንደሆነና መንግስትም ይህን ያንዣበበውን ውጥረት በአፋጣኝ መቆጣጠር እንዳለበት የአካባቢው ነዋሪዎች አሳስበዋል። Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ሁላችንም እዲህ አይነት ክብረነክ ነገሮችን ስናይ ሪፖርት እናድርግ