አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት
Open in Telegram
This is offical account of Addis Ababa Abattoris Enterprise Website: www.aaae.gov.et Facebook: www.facebook.com/AAAEKERA Corporate -Email - info@aaae.gov.et
Show more298
Subscribers
-124 hours
-27 days
No data30 days
Posts Archive
ለትንሳዔ በዓል ከ 6ሺ በላይ የእንስሳት እርድ ማከናወኑን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ገለፀ!
ሚያዚያ 29፤ቀን 2015 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የእርድ አገልግሎትና ስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት በለጠ በዘንድሮ የፋሲካ በዓል በዋናው ቄራ 3,275 የዳልጋ ከብት እንዲሁም 2,719 ትናንሽ እንስሳት/ በግ እና ፍየል/ በአጠቃላይ 5,994 እንስሳት እርድ እንደተከናወነ ገልፀዋል፡፡
በፋሲካ በዓል የቤት ውስጥ እርድ እና ቅርጫ በህብረተሰቡ ዘንድ የተለመደ ማህበራዊ ተግባር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ይሁን እንጂ ለእርድ አገልግሎት ወደ ድርጅቱ የቀረቡትን የእርድ እንስሳቶች ተቋሙ በሙሉ ሃይሉ የእርድ አገልግሎት በመስጠትና በማሰራጨት የታረደውን ስጋ ለደንበኞች ማስረከብ ችለናል ሲሉ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል በአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የአቃቂ ቅርንጫፍ ቄራ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ሚሌ በቅርንጫፍ ቄራው 525 የዳልጋ ከብት እንዲሁም 81 ትናንሽ እንስሳት/ በግ እና ፍየል/ የእንስሳት እርድ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡
በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው በጥቅሉ 6,600 የእንስሳት እርድ የተከናወነ ሲሆን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የእርድ መጠኑ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቅሰው አንደአጠቃላይ የበዓል ስራው ከአምናው የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበበት ነው በማለት ሃላፊዎቹ ገልፀዋል ፡፡
ለተገኘዉ ዉጤት የአንበሳውን ድርሻ በመውሰድ ከአቅማቸው በላይ በመስራት የበዓል ስራውን ውጤታማ ላደረጉት የእርድ አገልግሎትና ሥጋ ስርጭት የስራ ሂደት ሰራተኞችን በሙሉ እና ህገ ወጥ እርድን በመጠየፍ ሁሌም ከአንጋፋው ድርጅታችን ከአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅትን ጎን በመሆን አገልግሎታችንን ለሚጠቀሙ ለክቡራን የእርድ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ልባዊ ምስጋናቸውን ሃላፊዎቹ አቅርበዋል፡፡
🌺ሰላም ውድ የዚህ ግሩፕ ተከታታዮች🌺
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴራችን ዶ/ር አብይ አህመድ የጀመሩትን "ፅዱ ጎዳና" ኑሮ በጤና የሚለውን ራዕይ ለማሳካት የሀገራችን ህዝቦች በተለይም የከተማችን አመራሮችና ነዋሪዎች ንቅናቄውን ተቀላቅለው አስተዋፅኦ እያደረጉ ይገኛሉ እኔም የበኩሌን አስተዎፅኦ አድርጌለሁኝ !! እናንተም ይህንን መልካም ተግባር ሃሳብ ለማሳካት የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታደርጉ እያሳሰብኩኝ ገቢ የሚደረግበትን የሂሳብ ቁጥር ከዚህ በታች ሌኬላችኃለሁኝ ገቢ ካደረጋችሁ በኃላ ስክሪንሹት አድርጋችሁ በግሌ ቴሌግራም ፖስት እንድታደርጉ በአክብሮት እጠይቃለሁኝ!!!
🌹መልካም አዳር🌺
በአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለመጪው የትንሳንዔ በዓል ከ 8ሺ በላይ የእንስሳት እርድ ይከናወናል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለፀ!
ሚያዚያ 22፤ቀን 2016 ዓ.ም
የ2016 የትንሳዔ በዓል ቅድመ ዝግጅትን እና በመዲናዋ በስፋት የሚከናወነውን የህገ ወጥ የእንስሳት እርድ አስከፊነት በተመለከተ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመስጠት አዲስ አበባ ቄራዎችና የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማህበር እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን በጋራ በመሆን ለመንግስትና ለግል የሚዲያ አካላት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰኢድ እንድሪስ ለመጪው የፋሲካ በዓል ከ 4000 እስከ 4,500 የዳልጋ ከብት እንዲሁም 3500 ትናንሽ እንስሳት/በግ እና ፍየል/ የእንስሳት ዕርድ ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል በማለት ገልፀዋል፡፡
በበዓላት ወቅት ለእርድ የሚቀርበው የእንስሳት መጠን ከፍተኛ ስለሆነ 250 ተጨማሪ የሰው ሀይል የተዘጋጀ ሲሆን የታረደውን ስጋ በፍጥነት ወደ ልኳንዳ ቤቶች ለማሰራጨት 37 የስጋ ስርጭት መኪናዎች ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው አስፈላጊ ግብዓቶችን የእርድ መሳሪያዎችና አልባሳትን በሟሟላት ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቀናል ሲሉ ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
በሚዲናዋ ህገ ወጥ የእንስሳት እርድ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡ በበዓላት ወቅት ደግሞ መጠኑ እጥፍ ይሆናል፡፡ ተቋሙ ይህንን ለመቀነስ ከሌሎች ተቋሞች ጋር በቅንጅት በመስራት ከ1,141 በላይ የሚሆኑ የስጋ መሸጫ ሱቆች ላይ ፍተሻ በማከናወንና በመርመር 241 ሱቆች በህገወጥ መንገድ ታረደ ስጋ ይዘው የተገኙ ሲሆን 85 ሱቆች ሙሉ ለሙሉ እንዲታሸጉ መደረጉን ገልፀው አጠቃላይ በተደረገው ከፍተኛ ምርመራ 15,295 ኪ.ግ ህገ ወጥ ስጋ ተሰብስቦ እንዲወገድ ተደርጓል በማለት 209 ህገ ወጥ በግና ፍየል የተወረሰ መሆኑን ዋና ስራ አስኪያጁ አብራርተዋል፡፡
የቁጥጥር ሂደቱ ቀጣይነት ያለው ሲሆን ይህን ህገ ወጥ ስራ የሚያከናውኑ አካላት ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ ከሆነ ንግድ ፍቃዳቸውን በማሰረዝና ማንነታቸውን በማህበራዊ ድረ ገፅ በማሰራጨት ለህብረተቡ ይፋ በማድረግ በፍታብሔር ወንጀል መቅጫ መሰረት ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን እናሳስባለን ሲሉ ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበርና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡
በከተማዋ የሚገኙ ልኳንዳ ቤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በቂ የስጋ አቅርቦት እንደሚኖር የገለፁት የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር ስራ አስኪያጅ አቶ አየለ ሳህሌ ህብረተሰቡ ከበዓሉ እለት ጀምሮ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
የልኳንዳ ማህበሩ ለህብረተሰቡ ጤንነቱን የጠበቀ ስጋ ለማቅረብ ከአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑን ገልፀው ግለሰቦች ስጋ ለመግዛት ወደ ልኳንዳ ቤቶች ሲያመሩ በአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የታረደ መሆኑንና ስጋው ላይ የማረጋገጫ ማህተም መኖሩን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል ሲሉ አቶ አየለ ሳህሌ አሳስበዋል፡፡
ለህብረተሰቡ የሚቀርበው ስጋ ጤንነቱ የተረጋገጠ እንዲሆን በሶስቱም ቄራዎች 33 የስጋ መርማሪ ሀኪሞችን አዘጋጅተናል ሲሉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶአደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን የእንስሳት ምርመራ ቡድን መሪ ዶ/ር ክበበው ኤርቤቶ ገልፀዋል፡፡
ህገ ወጥ እርድ ማለት ለንግድ ተግባር ተብሎ ከተፈቀደላቸው ቄራዎች ውጪ የሚታረድ የእንስሳት እርድ ክንውን ሲሆን ይህም ከእንስሳት ወደ ሰው ለሚተላለፍ በሽታ ተጋላጭ የሚያደርግ በመሆኑ ህብረተሰቡ በእንስሳት ሃኪም ተመርምሮ በህጋዊ ቄራዎች የታረደ መሆኑን እና ስጋው ላይ የማረጋገጫ ማህተብ መኖሩን እንዲያስተውል ሲሉ ዶ/ር ክበበው መልክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ሀብት አለማስመዝገብ ምን ምን ቅጣቶችን ያስከትላል?
1, በመደበኛ ወይንም በተራዘመለት የማስመዝገቢያ ጊዜ ያላስመዘገበ ሰው ብር 1,000.00 ከፍሎ በ5 ቀናት ውስጥ ሊያስመዘግብ ይችላል፡፡
2, ሙሉ በሙሉ ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው በወንጀል ህግ አንቀጽ 419/2 ድንጋጌ አፈጻጸም ያፈራው ሀብት ሁሉ ምንጩ እንዳልታወቀ ንብረት ሆኖ በህግ ሊያስጠይቀው ይችላል፡፡
3, የሀብቱን ምንጭ ማስረዳት ካልቻለ ንብረቱ ይወረሳል፣ እስከ 5 አመት በሚደርስ እስራትም ሊቀጣ ይችላል፤ እንደ መስሪያ ቤቱ አሰራርና ውስጠ ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃዎች ሊወሰዱበት ይችላል፡፡
ከሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 የተወሰደ
+1
የጥቅም ግጭት እየተበራከቱና ስር እየሰደደ በሄዱ ቁጥር በግለሰቦች መብት፣በሰራተኛና በሀገር ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳትን ያስከትላል።
ጉዳቶቹም፦
፨ የመንግስትና የህዝብ ገንዘብ (ሀብት) ለታለመለት አላማ እንዳይውል ያደርጋል፤
፨ በስራ ቦታ ፍትሀዊና ሚዛናዊ አሰራር ስርአትን ያዛባል፤
፨ በህጋዊ መንገድና በጠንካራ የሙያና የስራ ስነ-ምግባር በሚገኝ የገቢ ምንጭ የተመሰረተ የአኗኗር ስርአት እንዳይኖር ያደረጋል፤
፨ በራስ ወዳዶች የሰዎች ማህበራዊ ህወትና የኑሮ እድገት ደረጃ ተመጣጣኝ እንዳይሆን ያደርጋል፤
፨ የነፃ ገበያ ስርአትን ያዛባል፤
፨ ለተቋም ማስፋፊያ ስራዎች እንቅፋት ይሆናል፤
፨ በተቋምም ሆነ በሀገር ፍትሀዊ የአሰራር ስርአቶች እንዳይኖሩ ያደርጋል፤
፨ የመንግስት ተቋማት አሰራር እና የአስተዳደሩ ስርአት በሰራተኞች ዘንድ አመኔታ እንዳኖረው ያደርጋል፤
፨ የሃላፊዎችንና የሰራተኞችን ግንኙነት ያሻክራል፤
፨ የተቋምን አልፎም የሀገርን ሰላምና ፀጥታን ያውካል፤
፨ የማህበራዊ ተቋማትን የመልካም አስተዳደር ስርአትን ያዛባል፤
፨ የስራ ባህልን በመሸርሸር ጥራት የጎደለው አገልግሎት አሰጣጥ እንዲፈጠር ያደርጋል
ሁሉም አካል በሃላፊነትና በባለቤትነት ስሜት በመስራት ለእኔ ብቻ የሚለውን አመለካከት በመተው ለእኛ በሚለው በመተካት ለጋራ ተጠቃሚነት ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባዋል፡፡
+5
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የቴክኒክና ጥገና የስራ ሂደት ዓመታዊ የግንባታና የጥገና ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የታላቁ አብይ ፆም ከተጀመረ ሳምንታትን አስቆጥሯል፡፡ ስለሆነም በፆም ወቅት በተቋሙ የእንስሳት እርድ የማይከናወን በመሆኑ የእርድ ክፍሎች፣ የተረፈ ምርት ማቀነባበሪያ ክፍሎች እንዲሁም የበረቶች ዓመታዊ ጥገና የሚከናወንበት ወቅት ነው፡፡
የተቋሙ የቴክኒክና ጥገና የስራ ሂደት የህንፃ ግንባታና ጥገና ክፍል ዓመታዊ የጥገና እና የግንባታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ጥገናው አምስቱን የእርድ ክፍሎች፣ የተረፈ ምርት ማቀነባበሪያ ክፍሎችን ከጣራ እሰከ ወለል ቀለምን ጨምሮ ሙሉ ጥገና ያካተተ እንደሆነ የድርጅቱ የህንፃ ግንባታና ጥገና ሱፐርቫይዘር አቶ ዘላለም እሸቱ ገልፀዋል፡፡
በበዓላትና በከባባድ የስራ ወቅት በስራ ጫና ምክኒያት የእርድ ክፍሎች ላይ የወለል መቆፋፈርና የግድግዳ ቀለም መላላጥ ስለሚያጋጥም እነዚህን ክፍሎች በመለየትና ከአስራ ሶስት በላይ ጊዜያዊ የግንባታ ባለሙያዎችን በመቅጠር የጥገና ስራው እየተከናወነ ይገኛል ሲሉ ሱፐርቫይዘሩ ተናግረዋል፡፡
ጥገናው ስምንት ሳምንታትን የሚፈጅ ሲሆን በእቅዳችን መሰረት ለመጨረስ በከፍተኛ ሞራልና ተነሳሽነት እየሰራን እንገኛለን በማለት የግንባታ ስራ ሙያንና ልምድን እንዲሁም ክህሎትን የሚጠይቅ የስራ ዘርፍ መሆኑን በመረዳት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ሲሉ አቶ ዘላለም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በስነ-ምግባር የታነፀ ማህበረሰብ እንዴት ይገነባል ?
*******
በስነ-ምግባር የታነፀ ማህበረሰብ ለመገንባት የተለያዩ ተቋማትን ማለትም የመንግስት፣ የሚዲያ፣ የትምህርት ፣ የሀይማኖት ተቋማትና የሌሎች የህዝብ ተቋማት ሁሉን አቀፍ ቅንጅት ይጠይቃል። ለትውልድ ግንባታ አንድ ነጠላ መፍትሔ ባይኖርም ፣ ሥነ-ምግባራዊ ማኅበረሰብን ለማዳበር አስተዋፅዖ የሚያደርጉ አንዳንድ ዘዴዎች፡-
1. የግልጽነትና ተጠያቂነት እሴት ማጎልበት፡- የግልጽነትና ተጠያቂነት እሴቶችን ማጠናከር በስነ- ምግባር የታነፀ ማህበረሰብን ለማፍራት ወሳኝ ነው ። ይህም የህግ የበላይነትን ማስፈን፣ ሙስናን መዋጋት እና ጥፋተኞች ለድርጊታቸው ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግን ያካትታል። ጠንካራ ተቋማት፣ ገለልተኛ የፍትህ አካላት እና ውጤታማ የቁጥጥር ማዕቀፎች በህብረተሰቡ ውስጥ የፍትሃዊነት ስሜት ለመፍጠር ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
2. ትምህርት እና ግንዛቤ፡- ትምህርት የስነ-ምግባር እሴቶችን እና ባህሪን በመቅረጽ ረገድ መሰረታዊ ሚና አለው ። ጥራት ያለው አስተሳሰብን የሚያበረታታ፣ የሞራል አስተሳሰብን እና መተሳሰብን የሚያበረታታ የትምህርት ሥርዓት ላይ ኢንቨስት ማድረግ ጠቃሚ ነው ። የሥነ- ምግባር ትምህርት እንደ ታማኝነት፣ መከባበር እና ማህበራዊ ኃላፊነትን የመሳሰሉ እሴቶችን ማሳደግ ላይ ማተኮር ያስፈልጋል ። በተጨማሪም ብዝሃነትን ያከበረ ሀገራዊ አንድነትን ማጉላት ይመከራል።
3. የስነ-ምግባር አመራር፡- መሪዎች በመንግስት፣ በቢዝነስ ወይም በሲቪል ማህበረሰብ ውስጥ በህብረተሰቡ የሥነ ምግባር ደረጃዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አላቸው። የሥነ ምግባር አመራርን ማበረታታት እና መደገፍ አስፈላጊ ነው። መሪዎች በአርአያነት መምራት፣ ታማኝነታቸውን ማሳየት እና ከግል ጥቅም ይልቅ የጋራ ጥቅም ማስቀደም አለባቸው። በድርጅቶቻቸው እና በማህበረሰባቸው ውስጥ ስነ-ምግባርን የሚያበረታታ ሁኔታ መፍጠር አለባቸው።
4. የህዝብ (ሰራተኞች)ተሳትፎ ፡- በስነ- ምግባር የታነፀ ማህበረሰብ መገንባት የሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ንቁ ተሳትፎን ይጠይቃል። በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ የህዝብ ተሳትፎን ማበረታታት፣ የውይይት እና የአንድነት ባህልን ማሳደግ እና የዜጎችን ተሳትፎ ማሳደግ ስነ-ምግባር ያለው ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ መንገዶች ናቸው። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለሥነ- ምግባር እሴቶች ጥብቅና በመቆም እና ተቋማትን ተጠያቂ ለማድረግ ወሳኝ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ።
5. ሥነ-ምግባራዊ የንግድ ተግባራት፡- በንግዱ ዘርፍ የሥነ ምግባር ባህሪን ማሳደግ ሥነ ምግባራዊ ማኅበረሰብን ለመገንባት ወሳኝ ነው። ንግዶች ፍትሃዊነትን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የስነ-ምግባር አቅርቦት ሰንሰለቶች ያሉ ኃላፊነት የሚሰማቸው እና ዘላቂ አሰራሮችን እንዲከተሉ ማበረታታት ለህብረተሰቡ አጠቃላይ የስነ-ምግባር መዋቅር አስተዋጽኦ ያደርጋል። በንግድ ስራ ላይ ስነ-ምግባርን የሚያበረታቱ ደንቦች በጣም አስፈላጊ ናቸው ።
6. ማህበራዊ ትስስር እና የባህል እሴቶች፡ የስነ-ምግባር ባህሪን የሚያበረታቱ ማህበራዊ ትስስር እና ባህላዊ እሴቶችን ማጉላት አስፈላጊ ነው። የበለጸጉ ባህላዊ ቅርሶች እንደ ሽማግሌዎች አክብሮት፣ የጋራ ኃላፊነት እና የማህበራዊ ስምምነት አስፈላጊነትን የመሳሰሉ የስነ-ምግባር እሴቶችን ለማጠናከር ሊጠቀሙበት ይችላሉ። በተለያዩ ጎሳ፣ ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ ቡድኖች መካከል ውይይት እና መግባባትን ማሳደግ በህብረተሰቡ ውስጥ የአንድነት ስሜት እና የጋራ እሴቶችን ያጎለብታል።
7. ሥነ ምግባራዊ የውሳኔ አሰጣጥ ማዕቀፎች፡- ሥነ ምግባራዊ የውሳኔ አሰጣጥ ማሳደግ ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሥነ- ምግባራዊ ኃላፊነት የተሞላበት ምርጫ እንዲያደርጉ ይመራቸዋል።
በአጠቃላይ በሥነ- ምግባር የታነፀ ማህበረሰብ መገንባት የግለሰቦችን፣ የህብረተሰብን፣ የተቋማትንና የመንግስትን የጋራ ጥረት የሚጠይቅ ነው ። የስነ-ምግባር እሴቶችን ለማሳደግና ስነ -ምግባራዊ ባህልን ለማዳበር የረጅም ጊዜ የሁሉም ዜጋ ቁርጠኝነትን ይጠይቃል።
በአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የጉድጓድ ውሃ የኤሌክትሮ መካኒካልና የሲቪል ስራዎች ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቆ የመጀመሪያ ዙር ርክክብ ተከናውኗል፡፡
የካቲት 9፤ቀን 2016 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከ60 ዓመታት በላይ ለመዲናዋ ነዋሪዎች ንፅህናውን የጠበቀ የእንስሳት እርድ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ አንጋፋ ተቋም እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ንፅህናውን የጠበቀ የእርድ አገልግሎት ለማከናወን ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ አስፈላጊ እንደመሆኑ መጠን ተቋሙ በተደጋጋሚ የውሃ እጥረት ሲያጋጥመው ይስተዋላል በተለይም ከባባድ የበዓላት ስራ ላይ በውሃ እጥረት ምክኒያት ስራው እንዳይስተጓጎል ከሌሎች ተቋማት የውሃ አቅርቦት ድጋፍ ይደረጋል፡፡
ተቋሙ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ከፍተኛ ፕሮጀክት ቀርፆ የጉድጓድ ውሃ የኤሌክትሮ መካኒካልና የሲቪል ስራዎች ፕሮጀክት ግንባታ በማጠናቀቅ የሁለት መቶ ሺ ሊትር ታንከር ውሃ አቅርቦት እና ተከላ አከናውኗል ሲሉ የድርጅቱ የፕሮጀክት ጥናትና ትግበራ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ደግአምላክ ደንድር ገልፀዋል፡፡
የፕሮጀክቱ አላማ ባለፈው አመት ተቆፍሮ የጎለበተውን የጥልቅ የጉድጓድ ውሀ ቁፋሮ የውሀ ፓንፕ በመግጠምና ፓንፕ በማድረግ በታንከር በማጠራቀም ወደ እርድ እና ምርት ኦፕሬሽን በማሰራጨት የድርጅታችን የውሀ አቅም ማሳደግ ሲሆን በተለይም ተቋሙ በአሁን ሰዓት በሶስት ሽፍት ለ24 ሰዓታት የእርድ አገልግሎት እየሰጠ እና ከፍተኛ ምርት እያመረተ የሚገኝ በመሆኑ የውሀ ፍላጎታችን ለሟሟላት ታቅዶ የተተገበረ ፕሮጀክት ነው በማለት ሃላፊው አብራርተዋል፡፡
የፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ መካኒካልና የሲቪል ስራዎች ግንባታ ኮንትራክተር ማአግ ኢንጂነሪንግ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ ሲሆን የኦሮሚያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ ከፍተኛ አማካሪ በመሆን መሳተፉን ፅ/ቤት ሃላፊው ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም ከሶስት ወራት በላይ በሙሉ አቅሙ እንዲሰራ ከተደረገ በኋላ ውስን ማስተካያ በኮንትራክተሩ ተከናውኖ በውሉ መሰረት የድርጅቱ ፣የአማካሪው እና የተቋራጩ ተወካዮች ባሉበት የመጀመሪያ ርክክብ (provisional handover) የተከናውነ ሲሆን የመጨረሻው ርክክብ ከአንድ አመት በኋላ የፕሮጀክቱ defect liability period ሲጠናቀቅ ይከናወናል በማለት አቶ ደግአምላክ ደንድር ጨምረው ገልፀዋል፡፡
የዚህ የፕሮጀክት መሳካት ቁልፍ ምክኒያቱ በጋራ መስራታችን ነውና ለፕሮጀክቱ ኮንትራክተር ማአግ ኢንጂነሪንግ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ እንዲሁም በማማከር ለተሳተፉት የኦሮሚያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ከዚህም በተጨማሪም በስራው ላይ በሙያቸው፣በዕውቀታቸው እንዲሁም በጉልበታቸው ለተሳተፉት በሙሉ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ በማለት ሃላፊው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
+4
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ሴት ሰራተኞች "ሴቶችን እናብቃ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ 113ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ48ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአለም የሴቶች ቀን ማርች 8 በፓናል ዉይይት አክበረዋል፡፡
በዚህ መሪ ቃል መከበሩ የሴቶችን መብትና ደህነት ማስከበር እንዲሁም በሁሉም መስኮች ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደግና ጥቅማቸውን ማስጠበቅ የስርዓተ – ጾታ እኩልነትን ከማስፈን ባሻገር ድህነትን በመዋጋት የዘላቂ ልማት ግቦችን እውን ለማድረግ ያለመ ነው ሲሉ የፓናል ውይይቱን የመሩት የድርጅቱ የሰው ሃይል ልማት ከፍተኛ ኤክስፐርት ወ/ሪት ሜላት ዋለ ገልፀዋል፡፡
መሪ ቃሉ ሴቶች ለማህበረሰብ ለውጥ፣ ለአገር እድገትና ብልጽግና በአጠቃላይም ለሰላማችንና ለህልውናችን ወሳኝና ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ለማህበረሰቡ አጽዕኖት ሰጥቶ ለማስገንዘብና የሴቶችን መብትና ደህንነት በማስከበር ረገድም የሚመለከታቸው አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ የጋራ መግባባት ለመፍጠር መሆኑን ኤክስፐርቷ በፓናል ውይይቱ ተናግረዋል፡፡
ለታላቁ የዓብይ ፆም እና የረመዷን ፆም ቅበላ ከ6 ሺ በላይ የእንስሳት እርድ ማከናወኑን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታወቀ!
የካቲት 2፤ቀን 2016 ዓ.ም
በክርስትና እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ቦታ ከሚሰጣቸው አፅዋማት መከካከል ትልቁን ቦታ ሚወሰወዱት የታላቁ የዓብይ ፆም እና የረመዷን ፆም እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ዘንድሮ የሁለቱም አፅዋማት ቅበላ በተመሳሳይ ቀን የዋለ መሆኑ ደግሞ ሁነቱን ልዪ ያደርገዋል፡፡
ይህንን ምክኒያት በማድረግም በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ የስጋ ፍላጎት የሚኖር በመሆኑ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የህብረተሰቡን የስጋ ፍላጎት ለሟሟላት ከ6 ሺ በላይ የእንስሳት እርድ በማከናወን እና ለደንበኞች በማሰራጨት የዘወትር ተግባሩን በስኬት አከናውኗል፡፡
በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው 5,069 የዳልጋ ከብት እንዲሁም 1,556 ትናንሽ እንስሳት በጥቅሉ 6,625 እንስሳት እርድ ተከናውኗል ሲሉ የድርጅቱ የእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ዳሬክተር ወ/ሮ ገነት በለጠ ገልፀዋል፡፡
የቅበላ ስራው ከመጀመሩ ከቀናት በፊት በዋና ስራ አስኪያጁ የሚመራ የመወያያ መድረክ በማዘጋጀት ከባለድርሻ አካላት ጋር የዝግጅት ስራን የተመለከተ ውይይት ተደርጓል፡፡እንዲሁም ከሰራተኞች ጋር በተለያየ ፈረቃና በአነስተኛ መድረኮች የተደረገው ውይይት በሰራተኛው ዘንድ ከፍተኛ የስነ ልቦና መነቃቃት እንዲፈጠር አድርጓል ሲሉ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ የእርድ ግብዓትና አልባሳትን በበቂ ሁኔታ በሟሟላት እንዲሁም የስጋ ስርጭት ተሸከርካሪዎችና የእርድ መገልገያ መሳሪያዎች አስቀድሞ ሙሉ ጥገና በማከናወን የታረደውን ስጋ በፍጥነትና ቅልጥፍና ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል በማለት ገልፀዋል፡፡
የ2016 ዓ.ም ቅበላ ስራ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ገልፀው አፈፃፀሙም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእንስሳት እርድ ቁጥር ጭማሪ ማሳየቱን የገለፁት ወ/ሮ ገነት ለዚህም ዋና ምክኒያቱ የሁለቱ አፅዋማት ቅበላ በተመሳሳይ ቀን መግባቱ ሲሆን ሰሞኑን በመዲናችን የህገወጥ እርድና ስጋ ዝውውር ቁጥጥር የጋራ ግብረ ሃይል ያከናወነው ከፍተኛ ኦፕሬሽን ህገ ወጥ እርዱ እንዲቀንስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አብርክቷል ሲሉ ዳይሬክተሯ አብራርተዋል፡፡
በመጨረሻም ስራውን በመከታተል ውሳኔ ለሚፈልጉ ጉዳዮች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ሃላፊነታቸውን ለተወጡ የድርጅቱ አመራሮች፣ የአንበሳውን ድርሻ በመውሰድ ለስራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፆኦ ላበረከቱት ለእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ሰራተኞች እንዲሁም ከተለያዩ የሙያ ዘርፍ ቀድሞ ያለውን ልምዳቸውን ተጠቅመው ድጋፋቸውን ላበረከቱልን ለሁሉም የስራ ሂደት ሰራተኞች እና ህገ ወጥ እርድን በመጠየፍ ሁሌም ከአንጋፋው ድርጅታችን ከአዲስ አበባቄራዎች ድርጅትን ጎን በመሆን አገልግሎታችንን ለሚጠቀሙ ለክቡራን የእርድ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች በሙሉ ልባዊ ምስጋናቸውን ሃላፊዋ አቅርበዋል፡፡
በመጨረሻም መልካም የፆም ወቅት እንዲሆን በመመኘት ህብረተሰቡ ህገ ወጥ እርድን በመከላከል ጤናማነቱ በህክምና ባለሙያ የተረጋገጠ በቄራ ብቻ የታረደ ስጋን በመመገብ ከእንስሳት ወደ ሰው ከሚተላለፉ በርካታ ገዳይ በሽታዎች እራሱን በመጠበቅ ሀላፊነቱን እንዲወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
