en
Feedback
አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት

አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት

Open in Telegram

This is offical account of Addis Ababa Abattoris Enterprise Website: www.aaae.gov.et Facebook: www.facebook.com/AAAEKERA Corporate -Email - info@aaae.gov.et

Show more
298
Subscribers
-124 hours
-27 days
No data30 days
Posts Archive
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል በድርጅቱ ዉስጥ ያሉ ሰራተኞች የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ላለፉት ተከታታይ ቀናት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታዉቋል
+2
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል በድርጅቱ ዉስጥ ያሉ ሰራተኞች የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ላለፉት ተከታታይ ቀናት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታዉቋል

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል በድርጅቱ ዉስጥ ያሉ ሰራተኞች የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ላለፉት ተከታታይ ቀናት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታዉቋል
+3
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል በድርጅቱ ዉስጥ ያሉ ሰራተኞች የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ላለፉት ተከታታይ ቀናት እያከናወነ እንደሚገኝ አስታዉቋል

ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የቀረበ የጥንቃቄ መልዕክት ሰሞኑን የተለያዩ የዲጂታል ሚዲያዎችን በመጠቀም ሽልማቶችን ለመሸለም በሚመስል መልኩ የኢትዮ-ቴሌኮ ነጻ የዳታ ሽልማት ለሁሉም አሮጌ ሲም ካርድ ተጠቃሚዎች በሚል መልዕክቶች ወደተለያዩ ግለሰቦች እየተላኩ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ማረጋገጥ ችሏል። ይህ መልዕክትም የግለሰቦችን ሚስጥራዊ መረጃዎች የማጥመድ ጥቃት (Phishing Attack) መሆኑን ማረጋገጥ ችሏል። በጥቃት አድራሾቹ ለተጠቃሚዎች አጓጊ የሚመስሉ ሆነዉ ከኋላቸዉ የሳይበር ጥቃት የያዙ ሲሆን የተጠቃሚዎችን ቀልብ ለመሳብ የኢትዮ ቴሌኮም ረጂም ጊዜ ተጠቃሚ በሚል በሲም ካርድ የቆይታ ጊዜ የሚል ዘዴዎችን እየተጠቀሙ ሲሆን ከእነዚህ መካከል፡ • 6 ወር የቆየ ሲም- 10GB • 1 አመት እና ከዚያ በላይ- 20GB • 5 አመት እና ከዚያ በላይ- 50GB እንሽልማለን የሚሉ ናቸዉ። ነገር ግን ያቀረቡት ማታለያ እንጂ ምንም አይነት ሽልማት እንደማይሰጡ ማህበረሰቡ እንዲያዉቅና ሊንክ ተጠቃሚዎችን ለማጥመድ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ በፍጹም ሊንኩን እንዳይከፍቱ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ለማሳሰብ ይወዳል። እንደዚህ አይነት የማጭበርበር ሁኔታዎች በበዓል ወቅቶች በስፋት የሚከሰቱ በመሆኑ ማህበረሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ እያካሄደ መሆኑን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል ገለፀ፡፡ መስከረም 15 ፤ቀን 2017 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ም
+2
የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ እያካሄደ መሆኑን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል ገለፀ፡፡ መስከረም 15 ፤ቀን 2017 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ክፍል የሰራተኞችን ሃብት መመዝገብ መጀመሩን ገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሃብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 የተዘጋጀ ማኑዋልንና ሃብት ምዝገባን በተመለከተ የተሰጠውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰረት በማድረግ በድርጅቱ የሚገኙ ሰራተኞች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ድረስ ሃብታቸውን ማስመዝገብ እንዳለባቸው ተጠቁሟል። በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሃብቱን ያላስመዘገበ አካል 1000 ብር ቅጣት ከፍሎ በ5 ቀናት ውስጥ ማስመዝገብ የሚችል ሲሆን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው በወንጀል የሚጠየቅና በድርጅቱ ደንብ መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰድበታል ሲሉ የድርጅቱ የስነ - ምግባርና ፀረ-ሙስና የስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ አባተ ገልፀዋል። ሰራተኞች ለተጨማሪ ወጪና ቅጣት እንዳይዳረጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ በስነምግባርና ፀረ-ሙስና ክፍል በመገኘት ሃብታቸውን እንዲያስመዘግቡ በማለት ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።

ለ2017 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዓል የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከ 6ሺ በላይ የእንስሳት እርድ አከናወነ! መስከረም 3 ፤ቀን 2017 ዓ.ም በዓሉን ምክንያት በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን ከፍተኛ የስጋ ፍላጎት ለሟሟላት የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከ 6ሺ በላይ የእንስሳት እርድ በማከናወን እና ስጋውን ለደንበኞች በማሰራጨት ንፅህናውን የጠበቀ እንዲህም የተመረመረ ስጋ በማቅረብ በአራቱም የከተማዋ ማዕዘናት ተደራሽ ማድረጉ ተገልጿል፡፡ የድርጅቱ የእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት በለጠ በ 2017 ዓ.ም ዘመን መለወጫ በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው 3,595 የዳልጋ ከብት 2,894 ትናንሽ እንስሳት /በግ እና ፍየል/ በጥቅሉ 6,489 የእንስሳት እርድ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡ ስራው ውጤታማ እና የተሳካ እንዲሆን አመራሩን ከሰራተኛው የሚያገኛኝ የመወያያ መድረክ በማዘጋጀት በሰራተኞቹ መካከል የስራ ተነሳሽነትና የስነ ልቦና ዝግጅት እንዲፈጠርና፣የተሽከርካሪ፣የእርድ መሳሪያዎችና የተለየያዩ ለስራው አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በሟሟላት የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ የበዓል ስራው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእንስሳት እርድ መጠን 2% ጭማሪ የታየበት መሆኑ፤ ሰራው በታሰበለት ጊዜ ፣በጥራትና በፍጥነት መጠናቀቁ እንዲሁም ምንም አይነት የደንበኞች ቅሬታ ያልተስተናገደበትና የተሻለ የስራ ክንውን የተመዘገበበት ነው ሲሉ ዳይሬክተሯ ጨምረው ገልፀዋል፡ ፡ ስራው በስኬት ለመጠናቀቁ ቁልፍ ምክኒያት በቅንጅት መስራታችን ነውና ለተገኘዉ ዉጤት ለድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊ የስራ ሂደቶች እንዲሁም ለስራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱት ለእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ሰራተኞች በሙሉ እንዲሁም ህገ ወጥ እርድን በመጠየፍ ሁሌም ከአንጋፋው ድርጅታችን ከአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅትን ጎን በመሆን አገልግሎታችንን ለሚጠቀሙ ለክቡራን የእርድ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ልባዊ ምስጋናቸውን ሃላፊዋ አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም አዲሱ ዓመት የሰላም፣የስኬትና የብልፅግና እንዲሆን በመመኘት በህገ ወጥ እርድ የተገኘ ስጋ የህብረተሰቡን ጤና ስለሚጎዳ እንዲሁም የሀገርን ኢኮኖሚ የሚያቀጭጭ በመሆኑ ህብረተሰቡ ይህንን በመረዳት ጤናማነቱ በህክምና ባለሙያ የተረጋገጠ በቄራ ብቻ የታረደ ስጋን በመመገብ ሀላፊነቱን እንዲወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላፈዋል፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለዘመን መለወጫ በዓል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለፀ! ጳጉሜ 4፤ቀን 2016 ዓ.ም በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከ 5 ሺ እስከ 6 ሺ የሚሆን የእንስሳት ዕርድ ይከናወናል ተብ
+1
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለዘመን መለወጫ በዓል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለፀ! ጳጉሜ 4፤ቀን 2016 ዓ.ም በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከ 5 ሺ እስከ 6 ሺ የሚሆን የእንስሳት ዕርድ ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ የድርጅቱ የኢንፎርሜሽንና ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አታክልቲ ገ/ሚካኤል በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ገልፀዋል። ለኅብረተሰቡ ንፅህናውን የጠበቀ የእርድ አገልግሎት በፍጥነት እና በቅልጥፍና ለማቅረብ የእርድ መሳሪያዎች እንዲሁም የስጋ መጓጓዣ መኪናዎች ዝግጁ መሆናቸውን ሃላፊው ተናግረዋል፡፡ በዕለቱ የሰው ኃይል እጥረት እንዳያጋጥምም ድርጅቱ ከ 200 በላይ ጊዜያዊ ሰራተኞች መቅጠሩን ሀላፊው ጨምረው ገልፀዋል። በመዲናዋ የሚከሰቱ ሕገ-ወጥ የእንስሳት እርድን ለመከላከል ከደንብ ማስከበርና ከፖሊስ ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ ጠቅሰው ኅብረተሰቡም ጥቆማ በማድረግ እንዲተባበር ጥሪ አቅርበዋል። በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር የበዓል ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡ በከተማዋ የሚገኙ ልኳንዳ ቤቶች በተመመጣጣኝ ዋጋ በቂ የስጋ አቅርቦት እንደሚኖር የገለፁት የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር ስራ አስኪያድ አቶ አየለ ሳህሌ ህብረተሰቡ ከበዓሉ እለት ጀምሮ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል ተነግሯል። በቤትና በተለያዩ አካባቢዎች የሚከናወኑ እርዶች ከእንስሳት ወደ ሰው ለሚተላለፉ በሽታዎች ተጋላጭ ስለሚያደርጉ፥ ህብረተሰቡ በቄራ ብቻ የታረደ ስጋ በመመገብ የራሱን እና የቤተሰብን ጤና እንዲጠብቅ በማለት ጥሪ ቀርቧል።

ጳጉሜ 1 የመሻገር ቀን!!!
ጳጉሜ 1 የመሻገር ቀን!!!

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ሠራተኞች የ2016 ዓ.ም አብይ አፈጻጸም እና የ2017 ዓ.ም እቅድ እንዲሁም የሪፎርም ስራዎችን በተመለከተ ግምገማ አከናዉነዋል! ነሀሴ 21፤ቀን 2016 ዓ.ም በመድረኩ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎችን በተመለከተ በሰው ሀይል ልማት አስተዳደር የስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ደመቀ ኪሮስ የሪፎርም ስራዎችን የሚዳስስ ሰነድ ለድርጅቱ ሰራተኞች ቀርቦ የጋራ ተደርጓል፡፡ የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች ላይ በድርጅቱ ም/ክ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ድሪብሳ ለሰራተኞች ተጨማሪ ሃሳብና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም የ2016 ዓ.ም አብይ አፈጻጸም እና የ2017 ዋና ዋና የእቅድ ሪፖርት ለድርጅቱ ሰራተኞች የቀረበ ሲሆን በበጀት አመቱ በዋናዉና ቅርንጫፍ ቄራዉ ከእርድ አገልግሎት 405,481 ለማረድ ታቅዶ 357,690 የእንስሳት እርድ በማከናወን የእቅዱን 88% መፈጸሙ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከእርድ አገልግሎት፣ከምርትና ሽያጭ እንዲሁም ከቆዳና ሌጦ በገቢ ደረጃ ከ96% በላይ አፈጻጸም መመዝገብ መቻሉን በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡ በጥምረት ከሌሎች ተቋማት ጋር በመስራት ህገወጥ እርድ ቁጥጥር ላይ ግብረሀይል በማሰማራት በሁለት ዙር በአጠቃላይ 2,406 ቤቶች ላይ ፍተሻ ተደርጎ 303 ቤቶች ህገወጥ የሆነ ስጋ ሙሉ በሙሉና በከፊል የተገኘባቸው መሆኑን በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡ በህገወጥ እርድ ቁጥጥር የተገኙ በድምሩ 23,157 ኪሎ ስጋ ተወገደ ሲሆን 478 ቆዳና ሌጦ ለቆዳ ፋብሪካዎች እንዲሸጡ መደረጉን በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡ መድረኩን የመሩት የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ሰኢድ እንድሪስ ተቋሙ በአጠቃላይ በ2016 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 256 ሚሊየን ብር በማትረፍ ከእቅዱ በላይ ማሳካት መቻሉን ገልጸዉ ለዚህ ዉጤት መመዝገብ የሁሉም ሰራተኛ የላቀ አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ለሰራተኛዉ የሶስት ወር ቦነስ እንዲሁም የሶስት እርከን የደሞዝ ጭማሪ እንደተደረገ ለተቋሙ ሰራተኞች አብስረዋል፡፡ለተገኘዉ ስኬት ለድርጅቱ ስራ አመራር ቦርድ ለተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች ላበረከቱት ጉልህ ሚና ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡ በቀጣይም የታቀዱ እቅዶችን ከግብ ለማድረስ በተለይም የእርድ አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ቅሬታዎችን በመቀነስ በፍጥነት፣በቅልጥፍና እንዲሁም የሚስተዋሉ የስራ ላይ ክፍተቶችን በማረም ደንበኞቻችን የሚረኩበትን አገልግሎት በማቅረብ የተገኘውን ውጤት ማስቀጠል ይኖርብናል በማለት የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰኢድ እንድሪስ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

በአንድ መንፈስ በመላዉ ኢትዮጵያ አሻራችንን እናኑር፡፡ አንድ ከሆን ከዚህም በላይ እንችላለን በሚል መሪ ቃል 600 መቶ ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀንበር የመትከል መረሃ ግብር አካል በሆነዉ የችግኝ ተከላ ላይ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አመራርና ሰራተኞች የችግኝ ተከላ በእንጦጦ ፓርክ አከናዉነዋል ፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለፍልሰታ ፆም ፍቺ ከ 4000 በላይ የእንስሳት እርድ ማከናወኑ ተገለፀ!! ነሀሴ 16፤ቀን 2016 ዓ.ም በዘንድሮ የፍልሰታ ፆም ፍቺ ትላልቅ እንስሳት 3‚060 ትናንሽ
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለፍልሰታ ፆም ፍቺ ከ 4000 በላይ የእንስሳት እርድ ማከናወኑ ተገለፀ!! ነሀሴ 16፤ቀን 2016 ዓ.ም በዘንድሮ የፍልሰታ ፆም ፍቺ ትላልቅ እንስሳት 3‚060 ትናንሽ እንስሳት ማለትም በግ እና ፍየል 1‚125 እርድ የተከናወነ ሲሆን በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው በጥቅሉ 4‚185 የእንስሳት እርድ መከናወኑን የእርድ አገልግሎት እና የስጋ ስርጭት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ይፍሩ ጌታቸው ገልጸዋል ፡፡ የፍልሰታ ፆም ፍቺ በበጀት ዓመቱ ክፍተኛ የእርድ ቁጥር ከሚመዘገብባቸው የበዓላት ስራዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ስራው ውጤታማ እና የተሳካ እንዲሆን አመራሩን ከሰራተኛው የሚያገኛኝ የመወያያ መድረክ በማዘጋጀት ሰራተኞቹን በስነ ልቦና ዝግጁ በማድረግ ፣አስፈላጊውን የሰው ሀይል በማዘጋጀት እና ግብዓቶችን በበቂ ሁኔታ በሟሟላት የቅድመ ዝግጅት ስራ ተወካይ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ስራው በስኬት ለመጠናቀቁ ቁልፍ ምክኒያት በቅንጅት መስራታችን ነውና ለተገኘዉ ዉጤት ለድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊ የስራ ሂደቶች፣ ለክቡራን ደንበኞቻችን እንዲሁም ለስራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱት ለእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ሰራተኞች በሙሉ እንዲሁም በተከታታይ ሁለት ቀናት በነበረዉ ከባድ ስራ ወቅት ያላሰለሰ ድጋፍ ሲያደርጉ ለነበሩት የድርጅቱ የቴክኒክና ጥገና የስራ ሂደት ሰራተኞች ላቅ ያለ ልባዊ ምስጋናቸውን ሃላፊዉ አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም ህብረተሰቡ ህገ ወጥ እርድን በመከላከል ጤናማነቱ በህክምና ባለሙያ የተረጋገጠ በቄራ ብቻ የታረደ ስጋን በመመገብ ሀላፊነቱን እንዲወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ለፍልሰታ ፆም ቅበላ ከ 8 ሺ በላይ የእንስሳት እርድ ማከናወኑን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ገለፀ! ነሃሴ 1፤ቀን 2016 ዓ.ም የፍልሰታ ፆም ቅበላ በበጀት ዓመቱ በተቋማችን ከፍተኛ የእርድ ቁጥር ከሚመዘገብባቸው የበዓላት ስራዎች መካከል አንዱ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በዘንድሮ የፍልሰታ ፆም ቅበላ ትላልቅ እንስሳት 6,456 ትናንሽ እንስሳት ማለትም በግ እና ፍየል 2‚470 እርድ የተከናወነ ሲሆን በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው በጥቅሉ በተከታታይ አራት ቀናት ውስጥ 8‚926 የእንስሳት እርድ መከናወኑን የእርድ አገልግሎት እና የስጋ ስርጭት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ይፍሩ ጌታቸው ገልፀዋል፡፡ የፆም ቀናቶች ባለመኖራቸው የእንስሳት እርዱ በተከታታይ አራት ቀናት ውስጥ የተከናወነ ሲሆን በዚህም ክፍተኛ የእርድ መጠን ሊመዘገብ ተችሏል በማለት አጠቃላይ የእርድ አፈፃፀሙ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ60% ጭማሪ እንዳለው ተወካይ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ስራው ውጤታማ እና የተሳካ እንዲሆን አመራሩን ከሰራተኛው የሚያገኛኝ የመወያያ መድረክ በማዘጋጀት በሰራተኞቹ መካከል ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቦና ዝግጅት እንዲፈጠር የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ተወካይ ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡ የታረደውን ስጋ ለደንበኞቻችን በአግባቡ እና በሰዓቱ ለማድረስ ከ35 በላይ የሚሆኑ የስጋ ስርጭት መኪናዎችን በማዘጋጀት በቀንም በማታም አገልግሎት በመስጠት የስርጭት ስራውን ቀልጣፋና የተሳለጠ በማድረግ ስራውን ያለምንም የደንበኞች ቅሬታ ማጠናቀቅ ተችሏል ሲሉ ተወካዩ ተናግረዋል፡፡ ስራው በስኬት ለመጠናቀቁ ቁልፍ ምክኒያት በቅንጅት መስራታችን ነውና ለተገኘዉ ዉጤት ለድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮችና ደጋፊ የስራ ሂደቶች፣ ለክቡራን ደንበኞቻችን እንዲሁም ለስራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፆ ላበረከቱት ለእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ሰራተኞች በሙሉ ምስጋና ይገባቹሃል በማለት ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም መልካም የፆም ወቅት እንዲሆን በመመኘት ህብረተሰቡ ህገ ወጥ እርድን በመከላከል ጤናማነቱ በህክምና ባለሙያ የተረጋገጠ በቄራ ብቻ የታረደ ስጋን በመመገብ ሀላፊነቱን እንዲወጣ በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

#ፕሬስ_ሪሊዝ ሀምሌ 26 ቀን፤2016 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት በ2016 ዓ.ም ለፍልሰታ ፆም ቅበላ በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው ከ 8ሺ በላይ የእንስሳት እርድ ያከናውናል ተብሎ ይጠበቃል
+2
#ፕሬስ_ሪሊዝ ሀምሌ 26 ቀን፤2016 ዓ.ም የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት በ2016 ዓ.ም ለፍልሰታ ፆም ቅበላ በዋናው እና በቅርንጫፍ ቄራው ከ 8ሺ በላይ የእንስሳት እርድ ያከናውናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የቅበላ ስራው ከዛሬ ጀምሮ የፆም ቀናቶች ባለመኖራቸው በተከታታይ አራት ቀናት ውስጥ የሚከናወን ሲሆን 5 ሺ ትላልቅ እንስሳት እንዲሁም 4 ሺ ትናንሽ እንስሳት/ በግና ፍየል/ በጥቅሉ 8ሺ ጤንነቱ በእንስሳት ሀኪም የተረጋገጠ የእንስሳት እርድ ለፆም ቅበላው ይከናወናል ተብሎ እንደሚታሰብ የድርጅቱ የእርድ አገልግሎትና የስጋ ስርጭት የስራ ሂደት ዳሬክተር ተወካይ አቶ ይፍሩ ጌታቸው ገልፀዋል፡፡ የቅበላ ስራው የተሳካ እንዲሆን በቂ የሰው ሃይል፣የእርድ መሳሪያዎች እንዲሁም የታረደውን ስጋ ለኅብረተሰቡ በፍጥነት እና በቅልጥፍና ለማሰራጨት 37 የስጋ መጓጓዣ መኪናዎች ዝግጁ መሆናቸው በተወካዩ ተገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ካቢኔ በ3ኛ ዓመት 15ኛ መደበኛ ስብሰባው የከተማ አስተዳደሩ እየተገበረ ያለውን የተቋማት ሪፎርም ተከትሎ ለከተማው ነዋሪ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ የተለያዩ አዳዲስ እና ነባር ደንቦችን ለማሻሻል የቀረቡ ረቂቆችን መርምሮ አፅድቋል:: በዚህም መሰረት:- 1. የመኖሪያ ቤቶች ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር መመሪያ 2. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሠራተኛ የስራ ልብስ አለባበስና እና ጌጣጌጥ አጠቃቀም የአፈጻጸም ደንብ ፣ 3. የመስሪያ ቦታ ልማትና አስተዳደር ደንብ 4. የህብረት ስራ ማህበራ አደረጃጀትና አሰራር ደንብ 5. የህብረት ስራ ማህበራት የፋይናንስ ፣ ግዥና የንብረት አስተዳደር ደንብ 6. የሲኒማ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እንደገና ማቋቋሚያ ደንብ 7. የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት እንደገና ለማቋቋም በተዘጋጀ ደንብ 8. የኤግዚብሽን ማዕከልና የገበያ ልማት ድርጅት እንደገና ማቋቋሚያ ደንብ 9. የከነማ መድኃኒትና የህክምና መሳሪያ አቅራቢ ድርጅት እንደገና መቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል::

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የ 10 ዓመት  ፍኖተ ካርታ ለማዘጋጀት  ከባለድርሻ አካለት ጋር ውይይት ተካሄደ::ለውይይት መነሻ ሃሳብ ያቀረበው E.E.S   የተባለ አማካሪ ድርጅት ሲሆን   ከመንግስትና ከግል ጅርጅቶች የመጡ ባለ ድርሻ አካለት ተገኝትዋል::  በዝግጅት ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የ10 ዓመት ፍኖተ ካርታ የሚውል  በርካታ ግብአቶች ከመድረኩ እንደተገኙ ለማወቅ ተችልዋል::በውይይቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ማኔጂንግ ዳሬከተር አቶ ሰይድ እንድሪስ ይህ  ፍኖተ ካርታ ያስፈለገው  ከከተማዋ አድገት ጋር  አብሮ  የሚሄድ ዘመናዊ  ቄራ በማስፈለጉ ነው ብልዋል::