en
Feedback
ጣና ሚዲያ Tana Media

ጣና ሚዲያ Tana Media

Open in Telegram

ጣናዊነት አዳማዊነት ኖኃዊነት!!! https://telega.io/channels

Show more
2 355
Subscribers
No data24 hours
-87 days
+430 days
Posts Archive
🔓 PRIVATE CHANNEL now OPEN +$154.382 per day raised by Jack subs⚡️ 👉 https://t.me/+qRKP9TmigCwxM2Iy Don’t miss signals and
🔓 PRIVATE CHANNEL now OPEN +$154.382 per day raised by Jack subs⚡️ 👉 https://t.me/+qRKP9TmigCwxM2Iy Don’t miss signals and start make money 🔥

ይሄ የወያኔ ቡጥቡጥ ብዙ ነገር አሳይቶናል። ሁሉም ግልጥልጥ እያለ ነው። ከብቸኛ ቀሪ ሚስጢሮቻቸው መካከል አንዷ የጌታቸው አሰፋ ምስል ነበረች። እሷም ይሄው ተሰጣች 😂 ጌታቸው አሰፋ ማለት በቀይ የ
ይሄ የወያኔ ቡጥቡጥ ብዙ ነገር አሳይቶናል። ሁሉም ግልጥልጥ እያለ ነው። ከብቸኛ ቀሪ ሚስጢሮቻቸው መካከል አንዷ የጌታቸው አሰፋ ምስል ነበረች። እሷም ይሄው ተሰጣች 😂 ጌታቸው አሰፋ ማለት በቀይ የተከበበው ሰውዬ ነው አሉ ! (እኔስ ምኑም ሊገባኝ አልቻልም። አቅርባችሁ እዩት እስኪ 😂 ) #wlkayi

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋዛን እንቆጣጠራለን ማለታቸውን ተከትሎ እስራኤል በጋዛ አዲስ የምድር ጦርነት መክፈቷን ገለፀች‼️ የእስራኤል መከላከያ ኃይል ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል ኤፊ ዴፍሪን እንደተናገሩት ዘመቻው ከዚህ ቀደም ከነበሩት ጥቃቶች በተለየ መልኩ ሐማስ እንደገና ቁጥጥር እንዳያገኝ ግዛትን በማስጠበቅ ላይ ያተኩራል። "እየገፋን ነው፤ እና እኛን ሊያቆመን የሚችለው ብቸኛው ነገር የታጋቾቹ ወደ ቤታቸው መመለስ ብቻ ነው" ብለዋል። ባለሥልጣኑ ንፁሀን ሰዎች ወደ "አስተማማኝ ቦታዎች" እንደሚላኩ ገልፀዋል። እስራኤል ለሁለት ወራት ያህል ምንም ዓይነት የሰብዓዊ እርዳታ እንዳይገባ ከከለከልች በኋላ እሁድ እለት "ወታደራዊ ዘመቻዎችን ማስፋት አስፈላጊ" በመሆኑ ምክንያት የጋዛ ነዋሪዎች "መሠረታዊ የምግብ መጠን" እንደሚያገኙ አስታውቃለች።

በማግስቱ ባለቤቱ እና የቅርብ ቤተሰቦቹ አዲስ አበባን ሲያካልሉ ውለው ማታ አዲስ አበባ ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ አገኙት። በምን ጠርጥረው እንዳሰሩትም እርሱም አላወቀም። ከሁለት ቀን በኋላ ከ14 ተጠርጣሪዎች ጋር ወደ አፋር ክልል ሰመራ ጉዞ ተጀመረ። ሰመራ ከተማ መግቢያው አካባቢ አንድ የግለሰብ ግቢ ውስጥ እንዲገቡ ተደርገው በዕለቱ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት እስረኞቹ በየተራ እየተጠሩ በመርማሪዎች ይጠየቃሉ። "የኢሳያስ ተራ ደረሰ" ይላል ከኢሳያስ ጋር አብሮ የነበረ ስሙን እንዳይገለፅ የጠየቀን አንድ ወጣት። እኔ ይላል ይሄው ወጣት "አራት መርማሪዎች በየተራ እየተነሱ እውነቱን ተናገር እያሉ በጥፊ እና በእርግጫ እየደበደቡ አድክመውኛል፣ በዛ ላይ እጅግ ይሞቃል። መቆም አቅቶኝ ተዝለፍልፌ ወድቂያለሁ። እጅ እና እግሬን ይዘው በሩ ላይ ጣሉኝ። ኢሳያስን ይዘውት ሲመጡ ይታየኛል። ሊቢያ ውስጥ በአሸባሪዎች እንደ ታረዱት ወጣቶች ጀርባውን ጨምድደው ወደ ታች ደፍቀው ይዘውት ገቡ። እጁን ወደ ኋላ አዙረው በካቴና አስረውታል። ወደ ግርግዳው ፊትህን አዙር ሲሉት ይሰማኛል" በማለት የሚያስታውሰውን ምልልስ እንዲህ ያስረዳል። "ማነው ስምህ?" "ኢሳያስ በላይ" "የት ነው የተወለድከው?" "ጎንደር" "ለምን እንደ ታሰርክ ታውቃለህ?" "አላውቅም" "ምን አባህ ሆነህ ነው የማታውቀው?" ሌሎቹ እየደበደቡት አንዱ ይጠይቃል: "ለምንድን ነው የማታውቀው?" "አላውቅም! ከቤቴ ነው ይዘውኝ የመጡት" "ከፋኖዎች ጋር ምን ነበር ስታወራ የነበረው?" "ከማንም ጋር አውርቼ አላውቅም?" "ስልካችሁ እንዳይጠለፍ ምን አድርጉ ነው ስትላቸው የነበረው?" አሁንም የእርግጫ እና የጥፊ ድምፅ ይሰማኛል። "ይናገራል ቆይ" ሲል አንዱ ገልጋይ ሆኖ ተከሰተ። "በሕይወት መኖር ከፈለግህ ተናገር ካልሆነ አስከሬንህን እዚህ ነው በእሳት የምናቃጥለው" የእሱ ድምፅ አይሰማኝም "ልጆች አሉህ አይደል?" "ተናገር እንጂ!" እንዲናገር ተንጫጩበት፣ የእሱ ድምፅ አሁንም አይሰማም። አንዱ በምን እንደ መታው ባላውቅም ኢሳያስ "አአአአአአአአ ..... ብሎ ሲወድቅ ተሰማኝ። ከወደቀበት በእግራቸው ሲደበድቡት አንደኛው "አሁን ይናገራል ተውት" ብሎ አስቆማቸው። ኢሳያስ መሬት ላይ እንደ ተኛ ያቃስት ነበር። "ለፋኖ ስልካችሁ እንዳይጠለፍ ምን አድርጉ ብለህ እንደ ተናገርህ ካላወጣህ አስከሬንህን ለጅብ ነው የምንሰጠው፣ ልጆችህን ድጋሜ አታያቸውም" ሁለቱ መርማሪዎች የክፍሉን ሙቀት መቋቋም ያቃታቸው ይመስላል። ሲወጡ እኔ መኖሬንም ረስተው "ይሄን ነው በደንብ ጠይቁት ያለው ኮማንደር" ሲል ሰማሁት። "ማን ነበር ስሙ?" አንደኛው ጠየቀ "ኢሳያስ" አለው ሌላኛው አንደኛው መርማሪ የእስረኞቹን ክፍል ከፍቶ ሁለት እስረኞችን ይዞ መጣና "ይዛችሁት ግቡ" ብሎ አንጠልጥለው ክፍሌ ውስጥ አስገቡኝ። ኢሳያስ በላይ ምርመራ ክፍል ውስጥ አድሮ ጧት እንደ ጨርቅ ሰውነቱ ልሞ በእስረኞች ተደግፎ መጣ። ሙቀቱ እሳት ነው። የሚሰጠን ውሃ በቀን ግማሽ ሊትር ከአንድ ዳቦ ጋር ነው። ሁላችንም ተዳከምን። ወደ መጨረሻው ቀን ኢሳያስን እና እኔን በመኪና ራቅ ያለ ቦታ ይዘውን ሄዱ። እልም ያለ በረሀ ነው። ከመኪና አስወርደው ሁለት እጅ እና እግራችንን በካቴና አስረው "እዚህ በረሀ ላይ ጅብ ነው የሚበላችሁ። ማንም አይደርስላችሁም። እውነቱን ብትነግሩን ይሻላል" ሲል አንዱ መርማሪ ጠየቀን። እኔ ከማንም ጋር ተገናኝቼ እንደማላውቅ ነገርኩት። ኢሳያስ ደካክሞ ስለነበር የሚለው አይሰማም። እኔን መልሰው መኪናው ላይ አንስተው ጫኑኝ። ኢሳያስን ትተነው ሄድን። የተወሰነ ርቀት ከተጓዝን በኋላ እኔንም አውርደው ጥለውኝ ሄዱ። ሁለት እግሮቼ እና ሁለት እጆቼ በካቴና የታሰሩ በመሆናቸው በፍፁም መንቀሳቀስ አልችልም። ለመገላበጥ አያመችም እንጂ ከምርመራ ግቢው የተሻለ አየር አገኘሁ። ነፃነትም ተሰማኝ። ነገር ግን አውሬ ቢተናኮለኝ መከላከል እንደማልችል ሳስብ ደግሞ ስጋት ገባኝ። በግምት ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት አካባቢ ሲሆን የመኪና ድምፅ ቀሰቀሰኝ። አንድ በማስክ እስከ አፍንጫው ድረስ የተሸፈነ መርማሪ ጋቢና ውስጥ ብቅ ብሎ በተኛሁበት ቁልቁል እየተመለከተ፣ "ጅብ አልበላህም?" ሲል አብሮት ያለው ሹፌር ሳቀ። ሁለት ፈርጠም ፈርጠም ያሉ ፖሊሶች አንስተው ማታ ከጣለችን ሽፍን ወታደራዊ ተሽከርካሪ ውስጥ ጣሉኝ። ትንሽ ከተጓዝን በኋላ ኢሳያስን አገኘነው። "ይሄም ሰውዬ አለ። የዚህ አገር ጅብ ምን ነካው? በአፉ እንድናጎርሰው ፈልጎ ነው?" ሲል ሰማሁት ለቃቅመው ወደ ምርመራ ካምፕ መለሱን። ከቀኑ 10:00 ሰዓት ሲሆን መርማሪዎቹ ኢሳያስን ጠርተውታል። እስረኛው ስለተዳከመ እና አቅም ስላነሰው እንደ በፊቱ አንዱ አንዱን ደግፎ መሄድ አልቻለም። ራሳቸው ፖሊሶች ሰቅስቀው አንስተው ይወስዱናል። ኢሳያስንም እንደዚሁ አድርገው ወደ ምርመራ ክፍል አስገቡት። ምርመራ ክፍል አስር ሰዓት ገብቶ 12:00 ላይ ይዘውት ወጡ። እሱ ከምርመራ ክፍል ሲወጣ እኛ ለሽንት ወጥተን ተገናኘን። ሆዱ አካባቢ ደም በደም ሆኗል። ከላዩ ላይ ውሃ የተደፋበትም ይመስለኛል። ልብሱ ሁሉ በስብሷል። እስከ ሱሪው ድረስ በደም ተነክሯል። ደም እና ውሃ ከሰውነቱ ይወርዳል። ፖሊሶቹ በር ላይ ስለጣሉት ዝልፍልፍ ብሎ ተኛ። ጠጋ ብዬ ሳየው ሆዱ ተቀዶ የውስጥ ክፍሉ ይታያል። ጠጋ ብዬ በእሱ በኩል አለፍኩ። መራመድ አቃተኝ። ኢሳያስ አልኩት። አልመለሰልኝም። የሚደበድቡን በተቆረጠ የፌሮ ብረት ነው። ብረቱ ጫፉ ላይ ሲቆረጥ ትንሽ ሰየፍ ያለ በመሆኑ እሱ ሁላችንንም ብዙ ቦታ እየቆረጠን ደም ፈሶናል። ብዙ ደም ስለፈሰሰን ሰውነታችን ገርጥቷል። ኢሳያስንም ያገኘው ይሄው ብረት ነው። ብረቱ ጫፉ ላይ ስለት እንዳለው ስለሚያውቁ የሚመቱን በስለቱ በኩል ነው። በኋላ መርመሪዎቹ ከምርመራ ክፍል ወጥተው ወደ ህክምና ልንወስደው ነው ገንዘብ አዋጡ አሉን። ከቤታችን ስንያዝ ኪሳችን ውስጥ የነበረችውን በሙሉ አሰባስበን ሰጠን። ይዘውት ወጡ። በማግስቱ እኛንም ወደ አዲስ አበባ ይዘውን ተመለሱ" ሲል የደረሰባቸውን ግፍ ለመሠረት ሚዲያ ተናግሯል። መርማሪዎቹ የኢሳያስን አስከሬን ለቤተሰቦቹ ሲያስረክቡ "ለማንም ቢሆን ታስሮ እንደነበር እንዳትናገሩ" ብለው የዛሬ ዓመት ግንቦት 7 ቀን አስከሬኑን አስረከቧቸው። ኢሳያስ በላይ የሁለት ልጆች አባትና ባለ ትዳር ነበር። መረጃን ከመሠረት!

ኢሳያስ በላይ የወታደራዊ ሬዲዮ ትስስሮች እንዲሁ በቀላሉ የሚከወኑ አይደለም። በዘርፉ ልምድ ያላቸው አለም አቀፍ ተቋማት ተወዳድረው በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚጠይቁበት ስራ ነው። አገርን ለከፍተኛ ወጪ የዳረገ የሬዲዮ ግንኙነት መረብ እንዲሁ በቀላሉ የይለፍ ቃሉ ተሰብሮ ሚስጥሮች የሚባክኑ ከሆነ ደግሞ ሌላ የአገራዊ ደኅንነት ስጋት ነው። ይህ ስጋት በ2014 ዓ/ም በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የሰላም እና ደኅንነት የሬዲዮ መገናኛ ላይ በግልፅ ታየ። ችግሩ እንዴት ይቀረፍ? በሚል ኢንሳ መፍትሄ ሲያፈላልግ ኢሳያስ በላይ በተቋሙ ውስጥ ያገኘውን አለም አቀፍ ልምድ በመውሰድ የክልሉን የሬዲዮ አውታር እንደ አዲስ ለማቀናጀት ሀሳቡን አቀረበ። ኢንሳ ሰባት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን አዋቅሮ ኢሳያስን የቡድኑ መሪ አድርጎ ወደ አማራ ክልል ሸኘው። ቡድኑን በማስተባበር የአማራ ክልልን ከወረዳ ጀምሮ እስከ ዋናው ቢሮ ድረስ ያለውን የሬዲዮ ትስስር በዘመናዊ መልኩ አቀናጅቶ ለክልሉ መንግስት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ አስረክቧል። ኢሳያስ ዛሬ በሕይወት ባይኖርም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን እና የሰላምና ደኅንነት ቢሮ እስከ ወረዳ ድረስ የሚጠቀሙበት የሬዲዮ መገናኛ መረብ በዚህ ድንቅ ወጣት የተሳሰረ ነው። ኢሳያስ በላይ ለምን ተገደለ? የአማራ ክልልን የሬዲዮ መገናኛ አውታር አቀናጅቶ ከተመለሰ ከሁለት ወር በኋላ አንድ ቀን ጧት 4:00 ሰዓት ላይ ቢሮ ከመግባቱ የኢንሳ የውስጥ ደኅንነት እና ጥበቃ ኃላፊ የኢሳያስን መታወቂያ ቀማው። በኢንሳ ተቋም ውስጥ የውስጥ ደኅንነት እና የጥበቃ አባል የሰራተኞችን መታወቂያ ቀምቶ ከወሰደ ቢሮ መግባት የተከለከለ ነው። ኢሳያስም ለምን መታወቂያው እንደተወሰደበት ቢሮ ገብቶ ኃላፊውን መጠየቅ አልቻለም። ከስራ እንዳሰናበቱት ቆጥሮ ሌላ ስራ ማፈላለግ ያዘ። ከወራት በኋላ አማራ ባንክ ተቀጥሮ ለሁለት አመታት ያህል በሙያው እየሰራ ባለበት ወቅት ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 2:30 የፌደራል ፖሊሶች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ትፈለጋለህ በሚል ይዘውት ወጡ።

ልክ የዛሬ አመት በዚህ ወር በምርመራ ክፍል ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ስለተገደለው ኢሳያስ በላይ የተሰራ የምርመራ ዘገባ (መሠረት ሚድያ)- ኢሳያስ በላይ ማነው ? ለስድስት አመታት ያህል በኢንፎርሜሽን
ልክ የዛሬ አመት በዚህ ወር በምርመራ ክፍል ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ስለተገደለው ኢሳያስ በላይ የተሰራ የምርመራ ዘገባ (መሠረት ሚድያ)- ኢሳያስ በላይ ማነው ? ለስድስት አመታት ያህል በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) ውስጥ ከፍተኛ የሳይበር ደኅንነት ባለሙያ ሆኖ አገልግሏል። በ2014 ዓ/ም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የክልሉ ሰላምና ደኅንነት የሚጠቀምበት ወታደራዊ ሬዲዮ የመለያ ኮዱ በቀላሉ ተጋላጭ ሆኖ ተገኘ። ይህንን የሬዲዮ ትስስር እንደ አዲስ ማስተሳሰር ግድም ሆነ።

አዲስ የተመረጡት የሮማ ካቶሊክ ሊቀጳጳስ ሊዮ 14ኛ ኢትዮጵያን ጨምሮ ጦርነት ባለባቸው አገራት ‹‹ለማደራደር ዝግጁ ነኝ›› አሉ‼️ አዲሱ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ሊዮ 14ተኛ በአለማችን ላይ
አዲስ የተመረጡት የሮማ ካቶሊክ ሊቀጳጳስ ሊዮ 14ኛ ኢትዮጵያን ጨምሮ ጦርነት ባለባቸው አገራት ‹‹ለማደራደር ዝግጁ ነኝ›› አሉ‼️ አዲሱ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ሊዮ 14ተኛ በአለማችን ላይ ያሉ ግጭቶችን ለመሸምገል ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ የምስራቅ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ኢዩቤልዩን በማስመልከት ዛሬ ባደረጉት ንግግር ‹‹ከቅድስት አገር እስከ ዩክሬይን፣ ከሊባኖስ እስከ ሶሪያ፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ እስከ ካካኦስ ድረስ ጦርነት ተስፋፍቶ ይገኛል፡፡ እኔም ተፋላሚዎችን ለማግኘትና እርስ በእርሳቸው ተነጋግረው ለህዝባቸው ተስፋ እንዲሰጡ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ፡፡ ሰላም እንዲሰፍን የቻልኩትን ሁሉ አደርጋለሁ›› ብለዋል፡፡

ባልታሸጉ የወተት ምርቶች ውስጥ ለአደገኛ በሽታዎች የሚያጋልጡ ባክቴርያዎች ተገኙ‼️ በአልታሸጉ የወተት ምርቶች ለአደገኛ በሽታዎች የሚያጋልጡ አራት የባክቴሪያ ዓይነቶች መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለፀ፡፡ በኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ነክ በሽታዎች ምርምር ዲቪዥን ኃላፊና የጸረ ተህዋስያን መድኃኒቶች ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ይመር ሙሉጌታ ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ማኅበረሰቡ እየተጠቀመባቸው ያሉ ያልታሸጉ ወተቶች ንጹህ ቢመስሉም በተለያየ ደረጃ ችግሮች ያሉባቸው መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ማኅበረሰቡ እየተጠቀመባቸው በሚገኙ የወተት ምርቶች አራት የባክቴሪያ አይነቶች ተገኝቶባቸዋል ብለዋል፡፡ ባክቴሪያዎቹ የኩላሊት፣ የሽንት መተላለፊያ እና የቆዳ በሽታን የሚያስከትሉ መሆናቸውን ተናግረዋል። ባክቴሪያዎቹ ኩላሊትንና የሽንት መተላለፊያዎችን በእጅጉ የሚጎዱ ከመሆናቸውም ባሻገር  የቆዳ በሽታን የሚያስከትሉ፤ የሳምባ ምች፣ የደም ዝዉዉር እና የቁስል ኢንፌክሽኖች እና ታይፎይድን የመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎችን በብዛት የሚፈጥሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ ጥናቱ የተሠራው በማህበረሰቡ ጥቅም ላይ እየዋሉ ከሚገኙ የወተት ምርቶች ናሙና ተወስዶ እንደሆነ የጠቆሙት ተመራማሪው፤ ለጥናቱ ከፍተኛ ወተት አምራች የሆኑ ስድስት ክልሎች ናሙና መወሰዱን ተናግረዋል። የተሰራው ጥናት በፋብሪካ የተቀነባበሩትን የወተት ተዋዕጾዎችን ያካተተ እንዳልሆነ ጠቁመዋል። አምራቾች፣ ነጋዴዎች እና በግብርናና በጤና ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች እና የስራ ኃላፊዎች ከምንጊዜውም በላይ ተናበው ለመፍትሄው መረባረብ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡ #GazettePlus

【DPK-AI ትሬዲንግ】 አውቶማቲክ መጠናዊ ስርዓቱ ዝቅተኛውን የዲጂታል ገንዘቦች መሸጫ ዋጋ እንደ BTC፣ ETH፣ USDT ወዘተ በዋና ልውውጦች ላይ መፈለግ እና በሰከንዶች ውስጥ በፍጥነት መግዛት ይ
+1
【DPK-AI ትሬዲንግ】 አውቶማቲክ መጠናዊ ስርዓቱ ዝቅተኛውን የዲጂታል ገንዘቦች መሸጫ ዋጋ እንደ BTC፣ ETH፣ USDT ወዘተ በዋና ልውውጦች ላይ መፈለግ እና በሰከንዶች ውስጥ በፍጥነት መግዛት ይችላል። 1.DPKAI-quantitative, ፈንዶች ተቀማጭ እና ማውጣት በራስ-ሰር ወደ መለያው ገቢ ይደረጋል. 2. VIP1-VIP11፣ መጠናዊ ተመላሾች 20% -35%. 3. ከ 25% ወደ 40% በመጨመር ብዙ ምንዛሬዎችን እና ብልጥ የኢንቨስትመንት ገቢን ይደግፉ. 4. መጠኗ በየ24 ሰዓቱ እንደገና ይጀመራል፣ እና እያንዳንዱ ሰው በቀን አንድ ጊዜ በመጠን የገቢ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ይችላል። 5. የሶስተኛ ደረጃ ወኪል ግብዣ ሽልማቶችን ጠቁም። ብዙ ግብዣዎች ባደረጉ ቁጥር፣ የበለጠ ሽልማቶችን ያገኛሉ። ምንም ከፍተኛ ገደብ የለም [አንድ ሽልማት 10%, B ሽልማት 5%, C ሽልማት 3% = 18% ሽልማት]. እንደ ቲክቶክ፣ ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ዩቲዩብ፣ ኢንስታግራም፣ የዋትስአፕ ቡድን፣ የቴሌግራም ቡድን፣ ወዘተ ባሉ ማህበራዊ ሶፍትዌሮችዎ ላይ ለማጋራት የግብዣ ሊንኩን ይላኩ። 【DPK-AI ትሬዲንግ】 የምዝገባ አገናኝ፡ https://dpk-ai.com/#/register?ref=281171 【DPK-AI ትሬዲንግ】 የመስመር ላይ የደንበኞች አገልግሎት፡ https://chat.ssrchat.com/service/gomw2j

አቶ ታየ ደንደዓ ስለትላንቱ የአገዛዙ የድጋፍ ሰልፍ ትዝብት! “የመጋቢት 24 አከባበር ... ለምን በነጠላ? ከበርካታ አከባቢዎች ተጨባጭ መረጃዎች ተሰብስቧል። በከተሞች እስከ ስድስት ሰዓት ሱቁን የ
አቶ ታየ ደንደዓ ስለትላንቱ የአገዛዙ የድጋፍ ሰልፍ ትዝብት! “የመጋቢት 24 አከባበር ... ለምን በነጠላ? ከበርካታ አከባቢዎች ተጨባጭ መረጃዎች ተሰብስቧል። በከተሞች እስከ ስድስት ሰዓት ሱቁን የከፈተ የሚቀጣ መሆኑ ታዉቋል:: ለማንኛዉም የዛሬ ሰባት ዓመት በሁሉም ኢትዮጵያውያን እጅግ የተወደደዉ "ለውጥ" ሰባተኛ ዓመቱ ትላንት በመላዉ ኦሮሚያ በግዴታ ሰልፍ ሲደገፍ ዉሏል። የብልፅግና ደሴት ነዋሪዎች ከፊት ሆነዉ ሲጨፍሩ ህዝቡ እያለቀሰና እያዘነ ከኋላ አጅቧል። መጠነኛ ሠልፍ በአሶሳና በወላይታ ሶዶ ከመታየቱ ባሻገር ትይዕንቱ በዋናነት በኦሮሚያ ተወስኗል። አንድ ክልል "ሀገራዊ" የተባለዉን አጀንዳ ብቻዉን ለምን እንደወሰደ ያጠያይቃል። ይሁንና 7ኛዉ ትላንት በብዙ ክልሎች ሳይታወስ ቀርቷል።  ሁሉም ዜጎች በጋራ የደገፉት ጉዳይ አድማሱ ጠቧል። ከሁለት ምክንያቶች በአንዱ ወይም በድምር ሊሆን ይችላል። አንደኛዉ ከለውጡ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ ተገዶ የሚሰለፍ ህዝብ ከኦሮሚያ ውጭ አለመኖሩን  ያሳያል። ኦሮሞ ማሳዉን በኪሳራ ስንዴ ለመዝራትና ምርቱንም ከገበያ ዋጋ በታች ለመሸጥ የሚገደድ ከመሆኑም በላይ ለብልፅግና ቀልድ በግድ ሲሰለፍ ከራርሟል። ሁለተኛዉ ደግሞ ከመቸዉም ግዜ በላይ በመከራ የተዘፈቀዉንና  የሞተ ዘመዱን እንኳ ለመቅበር የተቸገረዉን ኦሮሞ ልዩ የስርዓቱ ተጠቃሚ ለማስመሰልና ከወንድሞቹ ጋር የማቃቃር ድራማ መሆኑ ይገመታል። ፖለቲካ ቁማር መሆኑ በአደባባይ ከመነገሩና በተግባርም ከመፈፀሙ አንፃር ይህም ሚዛን ያነሳል። ምን ይመስላችኋል?” -ታየ ደንደዓ አርዶ #Amhara #Ethiopia

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት  እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው‼️ ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ። ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሆነበትን መንስዔ በተመለከተ በቀረበ ጥናት ላይ  ውይይት ሲደረግ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ ስለተያዘው እቅድ አብራርተዋል። ላለፉት ዓመታት(እሳቸው  በኃላፊነት ከተሾሙ ጀምሮ)፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት በከፍተኛ ደረጃ ዝቅተኛ  እንዲሆን ካደረጉ መንስዔዎች መካከል፣ የመምህራን ብቃትና የተነሳሽነት ማነስ ተጠቃሽ መሆናቸው ጠቁመዋል። ችግሩን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲቻል የተለያዩ ተግበራት እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል። ''የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ'' የሚል መጠሪያ የተሰጠው አሠራር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ዕቅድ የተያዘ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ "በአራት ዓመት የሚመረቅ ተማሪ፣ የሦስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማረው ማኅበረሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ይሰጥና (ማኅበረሰቡን እንዲያገለግል ይደረግና) እንዲመረቅ ይደረጋል"ሲሉ ተናግረዋል። ይህም ሲሆን የተማሪዎቹ መሠረታዊ ወጪ የሚሸፈን እንደሚሆንም አክለዋል። ይህ አሰራር ለተማሪዎች ለራሳቸው የተግባር ትምህርት እንደሚሆንና የበለጠ እንዲበስሉ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል። ተማሪዎች የመምህርነትን ሙያ ተላብሰው በዚያው ወደ ሙያው እንዲያመሩ ዕድል በመፍጠር ለጊዜውም ቢሆን በዘርፉ እየቀነሰ የመጣውን ወደ ሙያው የሚገባ የአስተማሪን ቁጥር ለማሳግ እንደሚረዳም ሚንስትሩ አብራርተዋል። በቅርቡ በመምህራን ላይ በተደረገ ግምገማ ፣ 100,000 የሚደርስ የመምህራን ዕጥረት መኖሩ መታወቁን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሰራሩ በከፍተኛ ደረጃ ያለውን የመምህራን ዕጥረት እንዲቀንስ የበኩልን እንደሚወጣ አስረድተዋል። ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎችን ክፍተት ለማስተካከል ከተያዙ ዘርፈ ብዙ የማትጊያ ሥርዓቶች አንዱ፣ መምህራን በአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸውና የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድረግ፣ "የመምህራን ባንክ" ማቋቋም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል። ባንኩ "በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባዋል ብለን እንጠብቃለን" ያሉት ሚኒስትሩ፣ በ2019 ዓ.ም ደግም በእርግጠኝነት ወደ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ አሰራር እንደሚገባ ጠቁመዋል። Via_reporter

አገዛዙ የ"7 አመት ትሩፋቶች" በሚል ከሰማይ መና አውረድን ማለት እስኪቀራቸው ድረስ መግለጫቸውን ሲያዥጎደጉደው ውሏል። በአንፃሩ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በአገዛዙ ላይ ያመፁ ኃይሎች መሳሪያቸውን
አገዛዙ የ"7 አመት ትሩፋቶች" በሚል ከሰማይ መና አውረድን ማለት እስኪቀራቸው ድረስ መግለጫቸውን ሲያዥጎደጉደው ውሏል። በአንፃሩ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በአገዛዙ ላይ ያመፁ ኃይሎች መሳሪያቸውን እየወለወሉ ነው። የሱማሌው የኦጋዴን ነፃ አውጪ ቡድን ትላንት በይፋ የትጥቅ ትግል ማወጁን ለደጋፊዎቹ ትላንት አሳውቋል።

የገነት አራጌ ስቃይና የብርሃኑ ነጋ ጭካኔ ! ! ምስሏን የምታዩት ወጣት ገነት አራጌ ትባላላች። የኢዜማ አባልና ከፍተኛ አመራርም ነበረች ። ኢዜማን ከተቀላቀሉ ብሩህ አይምሮ ከነበራቸው በርካታ ወጣት ሴቶች መሃከል አንዷ ነበረች። እንደሌሎቹም ወጣት ሴቶች በኢዜማ ላይ የነበራቸው ተስፋና ለኢዜማ የነበራቸው ፍቅር ገደብ አልነበረውም። ዛሬ ከእነዚህ ወጣት ሴቶች መሃከል አንዳቸውም በኢዜማ ውስጥ የሉም። ከኢዜማ ጋር እንዲፋቱ ያደረጋቸው ዋናው ምክንያት፣ ኢዜማ ሁነኛ የተቃዋሚ ፖለቲካ ሚና በመጫወት የአብይ አህመድን ገደብ ያጡ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ፣ የደህንነትና የውጭ ግንኙነት ቀውስ ጠማቂ እርምጃዎች በመቃወምና አገዛዙን ተጠያቂ ከማድረግ ፋንታ የብልጽግና ፓርቲ የቤት ውስጥ ባሪያ መሆኑ ነው። በዚህ ላይ የአብይ አህመድ አገዛዝ ምንም አይነት ማስመሰያ ምክንያት ወይም ሰበብ ሳይኖረው፣ የአማራን ህዝብ ቅስም ለመስበር ያወጀው ጦርነት፣ አማራ የሆኑትን የኢዜማ ወጣቶች ያስቆጣና ድርጅቱን በገፍ ለቀው እነዲወጡ ያደረገ ነው። ገነት አራጌ ከእነዚህ ወጣቶች አንዷ ነች።  በአማራ ህዝብ ላይ የመከራ ዶፍ ከሚያወርደው የአብይ አገዛዝ ጋር በአጋርነት ተጣብቆ የሚሰራውን የቀድሞ ድርጅቷን ትጠየፋለች። ገነት፣ የአብይ አህመድን “ትጥቅና ቀበቶ እናስፈታለን” የሚል እብሪት ለማስተንፈስ መላው የአማራ ክልል ህዝብ “ሆ” ብሎ በተነሳበት ወቅት ባህርዳር ነበረች። በዛ ወቅት፣ በደርግ ዘመን ይደረግ እንደነበረው የቀይ ሽብር እርምጃ፣ የአብይ አህመደ ጭራቅ ወታደሮች፣  የባህር ዳር ወጣቶችን፣ በለሌት ከየቤታቸው እየጎተቱ እያወጡ፣  በደጃፋቸውና በወላጆቻቸው ፊት በጭካኔ ሲረሸኑ በአይኗ አይታለች ። ይህን የአይን ምስከርነቷን ለኢዜማ አመራሮች፣ ለብርሃኑ ነጋ ተናግራለች። ብርሃኑ ነጋ በቀይ ሽብር ዘመን፣ ህይወቷ የጠፋ ብሩህ አይምሮ የነበራት፣ ከመለስ ዜናዊ ጋር የህክምና ትምህርቷን ስትከታተል የነበረች፣ እህት እንደነበረቸው ስለምታውቅ፣ አብይ አህመድ ለሚረሸናቸው የአማራ ወጣቶች “ቁጭትና ሃዘን ይሰማዋል” ብላ ነበር የጠበቀችው። የብርሃኑ ነጋ ምላሽ “እዚህ ውስጥ ሲገቡ ይህ እንደሚመጣ አያውቁም ነበር ወይ?” የሚል ጥያቄ ነበር። ገነት አራጌ “እነዚህ ሰዎች ጠመንጃ ይዘው እየተዋጉ አልነበረም። መሳሪያ በጃቸው በቤታቸው አልተገኘም። “ማህበረሰቡን ለማሸበር” በሚል እሳቤ ነው ከቤታቸው አውጥተው የረሸኗቸው። አንተ እንደምትለው የገቡበት ነገር” የለም።“ ብላ ለብርሃኑ ነጋ የሰጠችው ምላሽ፤ የአማራ ጥላቻና የስልጣን ጥም ልቡን ላደነደነው የሰው ጉድ ትርጉም አልነበረውም። ገነት አራጌን ጨመሮ ዶ/ጫኔና ሌሎችም በገፍ የተሳሩ የቀድሞ የኢዜማ አባላት ሌላ ምንም ወንጀል የለባቸውም። የታሰሩትና የሚታሰሩት አማራ በመሆናቸው ብቻ ነው። በአማራ ላይ ያነጣጠረን የብርሃኑ ነጋን እና የአብይ አህመድን እርኩስ ጋብቻ ስለተቃወሙ ብቻ ነው። እነዚህ የቀድሞ የኢዜማ አባላት እየተሳሩ ያለውም፤ በዶ/ር ጫኔ እስራት ወቅት ኢዜማ ካወጣው መግለጫ በመነሳት “በኢዜማ ጠቋሚነትና ተባባሪነት ነው” ብል እያጋነንኩ አይደለም። ለዚህ ክሴ የሰንድ መሳረጃ ማቅረብ አያስፈልገኝም። ዜጎችን፣ ልብ በሉልኝ አማሮችን አላልኩም፣ የራሱን የኢዜማን ቋንቋ ነው የምጠቀመው፤ በጅምላ በድሮን እና በከባድ መሳሪያ ከሚጨፈጭፍ፣ ዜጎችን በጅምላ ከሚያስር፣ ፍትህን መቀለጃ ካደረገ፣ ሃገርን ከመቼውም ዘመን በላይ ከሚዘርፍ ጨካኝ አገዛዝ ጋር ተባብሮ የሚሰራ ኢዜማ ከአብይ እኩል ተጠያቂ የማይሆንበት ምንም ምክንያት አይኖርም። ገነት አራጊ በታጣቂዎች ከቤቷ ከተወሰደች 45 ቀናት አልፏታል። ቤተሰቦቿ በህይወት ትኑር አትኑር የሚያውቁት ነገር የለም። በከተማው ውስጥ በሚገኙ እስርቤቶችና ማጎሪያዎች ተዘዋውረው ሊያገኛት አልቻሉም። ከዚህ ቀደም ታስራ በነበረበት ወቅት ከባድ ድብደባ ተፈጽሞባት ነበር። አካላዊ ቁመናዋ የአብይን አህመድ ባለጌ አፋኞች ጡቻና እርግጫ መቋቋም የሚችል አይደለም። ምን አድርገዋት ይሆን? ወላጆቿን ብቻ ሳይሆን  የምናውቃትን ሁሉ የሚያሳስብ ነው። ጌታው ብርሃኑ ነጋ ሆይ! የዚች ወጣት ሴት ቤተሰቦች ለአንተ ክብር በቤታቸው በደገሱት ድግስ ላይ እኔም ታድሜ ፍቅራቸውን የገለጹበትን ምሽት አስታውሰዋለሁ። የገነትን ጉዳይ እንደተለመደው “እዚህ ውስጥ ስትገባ ይህን እንደሚከተል አታውቅም ነበር ወይ” በሚለው ራስን መሸንገያ አመክኖህ ስቃይዋን እያወቅህ እንዳላየህ እለፈው። ግድ የለም። ሌላው ቢቀር እነዛ እንደዛ ያከበሩህና ፍቅራቸውን የገለጹልህ ወላጆች፣ ለ45 ቀናት ልጃቸው የት እንደወደቀች ባለማወቃቸው የሚያነቡት የደም እምባ ግድ አይልህም? ጌታው ብርሃኑ! ሁሉ ነገር ይቅር። ሰው እንዴት ያለማስረጃ ይታሰራል የሚል ጥያቄው ይቅር? ሰው እንዴት ፍርድ ቤት ሳይቀርብ 48ሰአት፣ አንድ ሳምንትና 14 ቀናት ያልፋሉ የሚለው የቅንጦት ጥያቄ ይቅር። "ገነት ታስራ ሰቆቃ ለምን ይፈጸምባታል" የሚል ቁጭት ይቅር። ሆኖም ግን ለእነዛ እንግዳ ተቀባይና አከባሪ ወላጆቿ ስትል፣  ጌታህን አብይ ወይም አሽከሮቹን ጠይቀህ፣ “ልጃችሁ እዚህ ነው ያለችው” የምትል ትንሽ መልእክት ማስተላለፍ እስኪያስቸግር ድረስ ነወይ ስብእናህ ተንጠፍጠፎ ያለቀው? ምን አይነት ክፉ ዘመን መጣ? ለገነት አራጌ፣ ከገነት አራጌ ጋር ከየቤታቸው ለታፈኑትና ለሌሎችም አማራ ብቻ በመሆናቸው ብቻ በግፍ ታስረው ለሚማቅቁት ወገኖቻችን ድምጻችንን እናሰማ ይህን ጽሁፍ በማጋራት ተባበሩ

photo content

ሩስያ ሆን ብላ የራሷን ግድብ አወደመች ሩስያ በዩክሬይን ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የራሷን ግድብ ማውደሟ ተሰማ። ሩስያ ግድቡን ያወደመችው የዩክሬይን ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎችን ለማገድ ነው ተብሏል። የጀርመን ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ሩስያ ግድቡን የደረመሰችው ሦስት ቶን ይመዝናል በተባለ የጦር አውሮፕላን ቦምብ ነው። ግድቡ ከዩክሬይን ድንበር በጥቂት መቶ ኪሎ ሜትሮች በምትገኘው ፖፖቭካ በተባለች መንደር አቅራቢያ ነው። ዩክሬይን በቤልጎሮድ ዞን የማጥቃት እርምጃዋን እያጠናከረች እንደሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ። የዩክሬይን ጦር ግን በጉዳዩ ላይ እስከ አሁን ያለው ነገር እንደሌለ ዜናው አመልክቷል። Via አዲስ Magazine

ይህ የራሄል እንባ ነው ቀይ ባህርን በሙሴ የከፈለ። ይህ የናዚ ጀርመን በትር ያረፈበት የግፍ አሻራ ውጤት ነው እስራኤልን አንድ ሁነው ስለማንነታቸው እንዲቆሙ የመሰብሰቢያ ደወል ሁኖ ለማንነት ከሩቅ
ይህ የራሄል እንባ ነው ቀይ ባህርን በሙሴ የከፈለ። ይህ የናዚ ጀርመን በትር ያረፈበት የግፍ አሻራ ውጤት ነው እስራኤልን አንድ ሁነው ስለማንነታቸው እንዲቆሙ የመሰብሰቢያ ደወል ሁኖ ለማንነት ከሩቅ የሚሰማ የአንድነት ጥሪ ። ይህ ቤተእስራኤላውያን ትግል ማቀጣጠያ ጋዝ ነው በልብ የሚታተም ብሶት፣ መበደልና መገፋት የወለደው ትግል ። ይህ ንፅፅር የቤተ አማራ መበደል ትልቅ ቤተሙከራ ነው ለነገ የማይባል አንድ የመሆን ጥሪ ፤ ደህንነት የሚጠብቅ ሞሳድ። ይህ የግፈኛ ስርዓት መገለጫ ምህዋር ነው ። ነገ ለአማራ ህዝብ ብሩህ ቀጣዩ ጊዜ የትንሣኤ ወቅት ነው ። የነገ ሰው ይበልን‼️