cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Ethio247 Media_(ኢትዮ247_ሚዲያ)

አብራችሁን ቆዩ!! የኢትዮጱያዊያን !!!

Show more
Ethiopia1 812Amharic1 458The category is not specified
Advertising posts
11 600
Subscribers
-324 hours
-427 days
-28930 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

በአዲስ አበባ ልዩ ኦፕሬሽን ሰርተው በመንግስት ሀይሎች የተወሰደው ፋኖ ናሁሰናይ አንዳርጌ በህይወት መኖሩን ለኢትዮ247 ሚዲያ መረጃው የደረሰን ሲሆን ከወደ ጳውሎስ ያለው እርግጥ መረጃ ከሁለቱ አንዱ በህይወት መኖሩን ነው። ጳውሉስ ሁለት ቦታ የፅኑ ሕሙማን ማከምያ ሆስፒታል አለው አንዱ ዮሐንስ ጋ የሚባለው እና ሁለተኛው ደሞ ነባሩ ሆስፒታል ነው። ዮሃንስ ጋር ባለው የፅኑ ህሙማን ማከሚያ ያለው ውጥረትና ከፍተኛ ጥበቃ፣ እንዲሁም ከታማኝ ምንጭ እኢትዮ247 ሚዲያ ባገኘው መረጃ መሰረትም ከሁለቱ አንዱ በህይወት እንዳሉና ክትትል ውስጥ መሆናቸውን ነው። በአንፑላንስ ላይ ሆኖ የፖሊስ ዶክሜንትሪው ላይ የታየው ፋኖ ናሁሰናይ በመሆኑም የመትረፍ እድል ግምቱ ለፋኖ ናሁሰናይ የሚሰጥ መስሏል። በመሆኑም ልጁ እንዳይገደል ለአለም ህዝብ መረጃ እብዲደርስም ጥሪ ቀርቧል፡፡
Show all...
Show all...
በአዲስአበባ ጳውሎስ ሆስፒታል ፋኖ ናሁሰናይ በህይወት መኖሩ ተረጋገጠ | በአዳሩ የተሠሩ ኦፕሬሽኖች በጎጃም በሽዋ እና በጎንደር | ሚያዚያ 10 2016 ዓ.ም

የዘመቻ ናሁሰናይ ጅማሮ   ዘመቻ ናሁሰናይ በጎንደር ግዛት በድል ታጅቦ እየተካሄደ መሆኑን የፋኖ አመራሮች ገለጹ ዘመቻ ናሁሰናይ መታወጁን ተከትሎ በአማራ ፋኖ በጎንደር የአድዋ ክፍለጦር በስብሰባ ላይ በነበሩ የአገዛዙ ወታደሮችና አድማ ብተናዎች ላይ እርምጃ ወስዷል፡፡ የአማራ ፋኖ በጎንደር ምክትል ወታደራዊ አዛዥ እና የአድዋ ክፍለጦር አዛዥ አርበኛ ሳሙኤል ባለድል በሻውራ ወረዳ በክፍለ ጦሩ ስር ንጋት ጮራ ክፍለጦር ጋዝጌ ቀበሌ ላይ የመከላከያ አባላት ከአድማ ብተና እና ሚሊሻው ጋር ውይይት በሚያደርጉበት ወቅት መብረቃዊ ጥቃት መፈጸማቸውን ገልጿል፡፡ በዚህ ልዩ ዘመቻም በስብሰባ ላይ የነበሩ የመከላከያና የአድማ ብተና አመራሮች መገደላቸውን የፋኖ አመራሩ ተናግሯል፡፡ የፋኖ አዛዡ በዚህ ጥቃት ከዚህ ቀደም እጃቸውን ሰጥተው የተለቀቁ ሆድ አደሮች ጭምር መደምሰሳቸውን የተናገረ ሲሆን፣ ካሁን በኋላ ለሆድ አደሮች ቦታ የለንም ብሏል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከትናንት በስቲያ ወደ ሸዋ ማጀቴ አርብ ገበያ የገባው የብልጽግና ሃይል ያሰበው ሳይሳካለት በሸዋ አናብስቶች ክፉኛ ተመትቶ መመለሱ ታውቋል፡፡ ይህን አስመልክቶ ምላሽ የሰጠው የአማራ ፋኖ በሸዋ እዝ ምክትል ቃል አቀባይ ፋኖ ንጋቱ ይታፈሩ ከፍተኛ ድል ማግኘታቸውን ተናግሯል፡፡ ከትናንት በስቲያ የተጀመረው ውጊያ እስከ ትናንት እኩለ ቀን መቀጠሉን እና በመጨረሻም የብልጽግና ጦር አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ ወደ መጣበት ከሚሴና መንዝ ተመልሷል ብሏል ፋኖ ንጋቱ፡፡
Show all...
የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል‼ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ13 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል አደጋው ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ከ 30 ከዋቻ ወደ ቦንጋ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሸከርካሪ እና ከሚዛን ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ሲኖ ትራክ ተሸከርካሪ በጨና ወረዳ ቦባ በላ ቀበሌ በመጋጨታቸው የደረሰ ነው ተብሏል። የአደጋው መንስኤ ይጣራል ሲባል ቦታው በተደጋጋሚ ጊዜ አደጋ የሚደርስበት ስፍራ በመሆኑ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተጠይቋል። =============
Show all...
መረጃ መሀል ሳይንት ..‼️‼️ በመሀል ሳይንት ወረዳ 036 (ወዠድ) ቀበሌ ማዕከል ውስጥ መሽጎ የነበረውን ባንዳ መከላከያ ሚሊሻና ፖሊስ ጀግናው የሳይንት ፋኖ አትሮንስ ብርጌድ ዛሬ ማለትም በቀን 20 ለ21 አጥቢያ ከሌሊቱ 8_11 ሰአት ባደረገው ኦፕሬሽን ሙትና ቁስለኛ አድርጎት አድሯል ። በዚህም ውጊያ ለጊዜው ቁጥሩ ያልተረጋገጠ ወራሪ ሀይል የተመታ ሲሆን 1 ባንዳ ሚሊሻ ወደ ሲኦል ሲሸኝ 1 ባንዳ ደግሞ የማይተፍ ሆነ ለመሄድ መንገድ ላይ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል። ብዙ ቁስለኛም እንዳለ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። በተጨማሪ በትናንትናው እለት መሀል ሳይንት ደንሳ ከተማ አንድን ወጣት ፋኖ ነህ በማለት ሊደበድቡት ሲሞክሩ በያዘው ሳንጃ አንድኛውን መከላከያ ሆዱን ለሁለት ሰንጥቆታል ። via ashara media
Show all...
ለየት ያለ መረጃ ነው❗👇 የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ ታካሚ ሆድ ዉስጥ  ሚስማር ፣ መርፌ ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕዳን ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን ገለጸ‼️ የወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከአንድ የ28 አመት ወጣት ሆድ ዉስጥ ሚስማር ፣ መርፌ ፣ ሽቦና የጥርስ መፋቂያን ጨምሮ 15 ባዕዳን ነገሮችን በቀዶ ህክምና ማዉጣቱን አስታውቋል። የቀዶ ህክምናዉ ቡድን መሪ ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ ለኦቢኤን እንደተናገሩት ከታካሚዉ የሆድ ክፍል ሶስት ሚስማሮች ፣ሁለት ቀጫጭን ሽቦዎች ፣ አንድ መርፌ ፣ 9 የእንጨት ጥርስ መፋቂያዎችና ሌሎች ባዕዳን ነገሮች አንድ ሰአት በፈጀ ቀዶ ህክምና መዉጣት መቻሉን አስታዉቀዋል። ታካሚዉ  በአዕምሮ ህመም ምክንያት የህክምና ክትትል ሲያደርግና መድኃኒት ሲጠቀም እንደነበረ የሆስፒታሉ ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ አብራርተዋል። ነዋሪነቱን በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ ወረዳ ያደረገዉ ይህ ታካሚ ከአንድ በፊት በአዕምሮ ህመም ምክንያት ሲከታተል የነበረዉን ህክምናና መድሃኒት አቋርጧል። ታካሚዉ ክትትሉን ከማቋረጡም በላይ አሁን በቀዶ ህክምና ከሆዱ የወጣዉ ባዕድ ነገር ይኖራል ብሎ ያሰበም ሆነ ተገቢዉን ምርመራ ያደረገ አካል አለመኖሩን ተናግረዋል። ዶ/ር ኤሊያስ ሰኝ እንደተናገሩት መሠል ክስተቶች ሊፈጠሩ ስለሚችሉ ማህበረሰቡ የአእምሮ ህመም ያለባቸዉን ግለሰቦች  ከተለመደዉ  ክትትል በዘለለ በጤና ተቋማትና በሰለጠነ ባለሙያ ድጋፍ ሊያደርጉላቸዉ እንደሚገባ መክረዋል።
Show all...
ፖሊስ እየወሰዳት ነው! በወሎ ዪኒቨርስቲ ለ12 አመታት በማስተማርና በምርምር የካበተ ልምድ ያላት መምህርት ችግር ላይ መውደቋን ገልጻ የኢትዮጵያ ህዝብ እገዛ እንዲያደርግላት ለልመና አደባባይ ብትወጣም ከመገናኝ በፖሊሶች ተይዛ ተወስዳለች፡፡ ወዴት እንደሚወስዷት የታወቀ ነገር የለም፡፡
Show all...
ደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ! በዩኒቨርስቲው ይሰጡ የነበሩ ከ18 በላይ የአማርኛ ትምህርት ክፍሎች እንዲዘጉ ያደረገው የደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በፋኖዎች ታግቶ ተወስዷል።
Show all...
ከምስራቅ አማራ ፋኖ የተሰጠ መግለጫ አማራን በጅምላ እንደ ጠላት ፈርጆ ማጥላላቱም ሆነ ይፋዊ የሕግ ሽፋን በተሰጠው ሁለንተናዊ መዋቅራዊ ጥቃት ሰለባ ማድረጉ በቂ ያልመሰለው ኦህዴድ መራሹ ብልፅግና ስልጣን ከያዘ ማግስት ጸረ-አማራ ጥቃቱን ወደ ለየለት ብሔር-ተኮር የጅምላ ጭፍጨፋ ከፍ ያደረገው መሆኑ ዛሬ ዛሬ ዋቢ የማይሻ ጥሬ ሀቅ ሆኗል። በአጠቃላይ በብልፅግና ስር በወደቀችው ኢትዮጵያ አማራ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ሊፈፀም  ቀርቶ ሊታሰብ የማይችል የጭካኔና የግፍ አይነት መሞከሪያ ተድርጓል ብሎ መደምደም ይቻላል። አብይ መራሹ ፋሽስታዊ መንግስት አማራን እንደ ህዝብ ለማጥቃት በተለያየ የዳቦ ስም በሚጠራቸው ቡድኖች በየክልሉ የማያቋርጥ የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ማፈናቀልና እገታ ሰለባ ማድረግ ሳይበቃውና ለተከታታይ ይፋዊ ወረራና ጭፍጨፋ ማጋለጡ ሳያረካው ያለውን ሙሉ የጥፋት አቅም አሟጦ በመጠቀም በአማራ ሕዝብ ላይ ይፋዊ ጦርነት ከከፈተ እነሆ ውሎ አድሯል። ይሁንና የአማራ ህዝብና ከአብራኩ የወጡት ፋኖ ልጆቹ  ፋሽስታዊው መንግስት በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ የሚፈፅማቸውንና የሚያጽፈፅማቸውን የግፍ ወረራወች ለመመከት ብቻ ሳይሆን ለመቀልበስ ታግሏል፣እየታገለም ይገኛል። በአማራ ሕዝብ ላይ የተቃጣውን የእጅ አዙርም ሆነ  ቀጥተኛ ወረራና ግፍ ለመመከትና ለመቀልበስ በግንባር ቀደምትነት ተደራጅተው ከታገሉና ከሚታገሉ የፋኖ አደረጃጀቶች መካከል የምስራቅ አማራ ፋኖ አንዱ ነው። ምስራቅ አማራ ፋኖ ከምስረታው ጀምሮ በደል እና ሰቆቃ አምጦ በወለዳቸው ታማኝ ሀቀኛ እና ጀግና መሪዎቹ እየተመራ በብዙ እንቁ ወጣቶች ጓዶች መስዕዋትነት እዚህ ደርሷል። ትላንትም ዛሬም የወገኑ መከታነቱን አሳይቷል። ፋሽስታዊው መንግስት የሚፈፅመውን ግፍና ጭፍጨፋ ወደ ይፋና ቀጥተኛ ወረራ ከቀየረው ወዲህ ደግሞ በወታደራዊ አቅሙም ሆነ በትጥቁ ግዙፍ የሆነው ምስራቅ አማራ ፋኖ የሚያደርገው ትግልም ሆነ ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት  ወደሚመጥን አደረጃጀት በፍጥነት ቀይሮ  እነሆ ራሱን ወደቻለ ዕዝ  አሳድጎ አሁን በሚገኝበት ቁመና ላይ ይገኛል። ይህ ሁሉ ያለ አማራ ሕዝብ ሁለንተናዊ ድጋፍ፣ ያለ አማራውና ፍትህ ወዳዱ በውጭ ሀገራት ነዋሪ ወገን ድጋፍ እውን አልሆነም። የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ ከኦህዴድ ወራሪ  ሰራዊት ጋር በየአውደ ውጊያው በእየዕለቱ  በሚያደርገው ትንቅንቅ ከሚከፍለው መስዋዕትነት  በላይ በሲቪሉ ህዝባችን ላይ የሚደርሰው ግፍና በደል በእጅጉ ያመዋል። ሴት እህቶቻችንና እናቶች በአገዛዙ ወታደሮች በግፍ ይደፈራሉ።የአማራ ወጣቶች እና ምሁራን የጅምላ ጭፍጨፋና እስር ሰለባ መደረጋቸው የዕለት ተዕለት ክስተት ነው። በአብይ ዙፋን አስተባቂ ወራሪ ሰራዊት አዛውንት ያለ ጧሪ፣ ልጆች ያለወላጅ፣እህቶቻችን ያለ አባወራ ቀርተዋል። ዛሬ የጤናና የትምህርት  ተቅዋማት ሥራ፣የንግድ፣የፋይናንስና የግብርና ሥራ በአማራ ምድር ላይ የለም።እናቶችና ሕፃናት በሕክምና እጦት እንደቅጠል እየረገፉ ነው። ህዝባችን ድርቅ ባስከተለው ረሃብ ይረግፋል። ይህን ሁሉ የህዝባችን ሰቆቃና እልቂት የአብይ አህመድ  ፋሽታዊ አገዛዝ አማራን ለማጥፋት እንደ ዋነኛ ግብዓት የሚያየውና የሚጠቀምበት መሆኑ ሊሰመርበትና ዓለም ሊያውቀው ይገባል። አማራ እንደ ሕዝብ ሕልው ሆኖ እንዳይኖር የተከፈተበትን ዘርፈ ብዙ ጥቃት ለመመከት የሚደረገው ሁለንተናዊ ትግል  ከምንጊዜውም የበለጠ ትብብርና ሁለንተናዊ ድጋፍ ይሻል። በጋራ ወገናችን ላይ  የሚፈፀመውን ዘርፈ- ብዙ፣ተከታታይነት ያለው፣መዋቅራዊና ስልታ እልቂትና ሰቆቃ ለማስቆም ዛሬም እንደትናንቱ የሁላችንንም ትብብርና መስዋዕትነት ይጠይቃል።የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ ህዝባችንና ለሕዝባችን የሚደረገው ትግል የገጠሙት ችግሮች ጊዜ የማይሰጡ መሆናቸውን በመገንዘብ ትብብርና ርብርብ ለማድረግ እንዲረዳ በሚል ወደፊት በጋራ እንደ አንድ አማራየጋራ አደረጃጀት እስከሚፈጠር ድረስ ጊዚያዊ የአስቸኳይ ጊዜ ፋይናንስ አሰባሳቢ ግብረሃይል እንዲመሰረት ያደረገ ሲሆን በውጭ ሃገራት የምትገኙ የአማራ ሕዝብ አብራክ ክፋዮችና የአማራ ሕዝብ የሚያደርገውን ፍትሃዊ ትግል የምትደግፉ ወገኖቻችን ግብረ ኃይሉ የሚያደርገውን ጥሪ ተከትሎ በሚደረጉ የፋይናንስ ማሰባሰቢያ መረሃግብሮች በመሳተፍ ወገናዊ ድጋፋችሁን እንድታደርጉ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። የህልውና ትግሉ በአማራ ሕዝብ ድል ይደመደማል!!
Show all...