አምልኮ ለጌታ ብቻ(WORSHIP FOR GOD)
1,ይህ ቻናል አላማው ጌታን በስነ-ፅሑፍ ማገልገል 2,የጌታን ወንጌል ለአለም ሁሉ ማድረስ 3,የተለየ የፀጋ ስጦታ ያላቸውን ልጆች በመዝሙር ና በግጥም እንዲሁም የጌታን ቃል በማስተማር ማሳተፍ 4,የተለዩ አስተማሪ የሆኑ ፅሁፎችን አዘግልጅቶ ማቅረብ ♦♥♣የተለያዩ የኮንፍረንስ እና ሎሎች ማስታወቂያዎች እናስተዋውቃለን በዚህ አናግሩን። @Boyzk @chrstiyanochbot
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
4 336
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
✍የእግዚአብሔር ክብር
***********************
እስጢፋኖስ...........❝መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት #የእግዚአብሔርን_ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፦እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ።❞
— ሐዋርያት 7 ፥ 55-56
♥♥♥የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!
❝በመንፈስም ወደ ታላቅና ወደ ረጅም ተራራ ወሰደኝ፥ #የእግዚአብሔርም_ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ፤ ብርሃንዋም እጅግ እንደ ከበረ ድንጋይ እንደ ኢያሰጲድ ድንጋይ ሆኖ እንደ ብርሌ የጠራ ነበረ፤❞
— ራእይ 21 ፥ 10-11
♥♥♥የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!
❝ለከተማይቱም #የእግዚአብሔር_ክብር ስለሚያበራላት መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ፥ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጓትም ነበር።❞
— ራእይ 21 ፥ 23
♥♥♥የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!
✍የእግዚአብሔር ክብር ሁሌም በእኔ ውስጥ ይኖራል፡፡ላፍታ እንኳን አይለየኝም!!
✍የእግዚአብሔር ክብር ተአምራቱ አይደለም ፤ አጋንንት መጮሁ አይደለም፡፡የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!
ሙሴ ብዙ ተአምራትን ካደረገ በሗላ እግዚአብሔርን እባክህ ክብርህን አሳየኝ አለው፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ መለሰለት፦❝ደግሞም፦ ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻልህም አለ።❞
— ዘጸአት 33 ፥ 20
✍የእግዚአብሔር ክብር የሆነው ኢየሱስ በሙሴ ውስጥ አላደረም!!በእኛ ውስጥ ግን አድሯል!!በደሙ ቀድሶን ማደሪያዎቹ ሆነናል!!
እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው?
✍ኢየሱስን ይዞ እባክህ ክብርህን አሳየኝ ፈጽሞ አይባልም!!
✍ሙሴ እግዚአብሔርን ክብርህን አሳየኝ ብሎ የጠየቀው ኢየሱስን ለማየት ነው፡፡
መጽሐፍ እንደሚል.........
ዕብራውያን 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ሙሴ ካደገ በኋላ የፈርዖን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ፤
²⁵-²⁶ ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ #ስለ_ክርስቶስ_መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።
✍ሙሴ ከግብፅ ብዙ ገንዘብ ይልቅ እጅግ የሚበልጥ ባለጠግነት እንደሆነ ያሰበው #ስለ_ክርስቶስ መነቀፍን ነው!!
✍እኛ እንደሙሴ አይደለንም!!
መጽሐፍ እንደሚል.............
❝ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተሞልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው #ክብሩን_አየን።❞
— ዮሐንስ 1 ፥ 14
ክብርህን አሳየኝ = ኢየሱስን አሳየኝ!!
እኛ ክብሩን አይተነዋል!!
★የእግዚአብሔር ክብር ኢየሱስ ነው!!
#ሄኖክ_አሸብር
https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7
#የቀራንዮ_የፍቅር_ጭማቂ
የግጥም መድብል ምረቃ
በሄኖክ አሸብር
ቦታ፦ ሐዋሳ ኬራዊ ኢንተርናሽናል ሆቴል
ቀን፦ ቅዳሜ ሰኔ 5
ሰአት፦ ከ10:00 ጀምሮ
አገልጋዮች
👉 ፓስተር ዳዊት ጥላሁን
👉 ዘማሪ ጥላሁን
👉 ገጣሚ ሰላም ታምሩ
👉 ገጣሚ ያብስራ መስፍን
👉 ገጣሚ ኤደን መሀመድ
👉 ሌሎች ተጋባዥ ገጣሚያን
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!
0906114984 ሄኖክ አሸብር
https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7
✍ ያወቀኝ ጌታ
*************
ያ ያላወቁት ፣ የክብር ጌታ
ያ ያላወቁት ፣ ያወቀኝ ጌታ
መሞትን ፈቅዶ ፣ ተንጠለጠለ
አንድ ገላው ላይ ፣ ሁሉን ሰቀለ
ያላወቁት ጌታ.......
ከሰማይ የመጣ ፣ አንድ የስንዴ ቅንጣት
ብቻውን ሊቀበል ፣ የሁሉንም ቅጣት
ገ'ለነዋል ሲሉ ፣ ተዘራሁኝ አለ
ዘሩን አበዛና ፣ እልፍ ሆኖ በቀለ
ያ ያወቀኝ ጌታ
እኔን ይዞ
አንቺን ይዞ
አንተን ይዞ
ያስታረቀን ፣ ደሙ ፈሶ
ያስቀመጠን ፣ ከእርሱ ጋራ
አሳርፎን ፣ በእርሱ ስፍራ
አንዴ ሰርቶ ፣ ለዘላለም
ልጅ ሆነናል ፣ ባባት አለም
https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7
#ሄኖክ_አሸብር
#የቀራንዮ_የፍቅር_ጭማቂ
የግጥም መድብል ምረቃ
በሄኖክ አሸብር
ቦታ፦ ሐዋሳ ኬራዊ ኢንተርናሽናል ሆቴል
ቀን፦ ቅዳሜ ሰኔ 5
ሰአት፦ ከ10:00 ጀምሮ
አገልጋዮች
👉 ፓስተር ዳዊት ጥላሁን
👉 ዘማሪ ጥላሁን
👉 ገጣሚ ሰላም ታምሩ
👉 ገጣሚ ያብስራ መስፍን
👉 ገጣሚ ኤደን መሀመድ
👉 ሌሎች ተጋባዥ ገጣሚያን
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!
https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7
#የቀራንዮ_የፍቅር_ጭማቂ
የግጥም መድብል ምረቃ
በሄኖክ አሸብር
ቦታ፦ ሐዋሳ ኬራዊ ኢንተርናሽናል ሆቴል
ቀን፦ ቅዳሜ ሰኔ 5
ሰአት፦ ከ10:00 ጀምሮ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!
✍ መቼ?.....አሁን!!
***************
አሁን!!
አሁን!!
አሁን!!
እስኪ በሚከተሉት ጥቅሶች ላይ አሁን የሚለውን ቃል በማስተዋል እንመልከት
✍ “ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ #አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው።”
— ሮሜ 3፥26
📌 “ይልቁንስ እንግዲህ #አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።”
— ሮሜ 5፥9
✍ “ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን #አሁን መታረቁን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ እንመካለን።”
— ሮሜ 5፥11
📌 “#አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው።”
— ሮሜ 6፥22
✍ “እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት #አሁን ኵነኔ የለባቸውም።”
— ሮሜ 8፥1
📌 “እንግዲህ እንደ ወንጌሌ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስም እንደ ተሰበከ፥ ከዘላለም ዘመንም የተሰወረው #አሁን ግን የታየው በነቢያትም መጻሕፍት የዘላለም እግዚአብሔር እንደ አዘዘ ለእምነት መታዘዝ ይሆን ዘንድ ለአሕዛብ ሁሉ የታወቀው ምሥጢር እንደ ተገለጠ መጠን ሊያበረታችሁ ለሚችለው፥”
— ሮሜ 16፥25-26
✍ “በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት #አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን #አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2
📌 “ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም #አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ #አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።”
— ገላትያ 2፥20
✍ “#አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።”
— ኤፌሶን 2፥13
📌 “ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ #አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤”
— ኤፌሶን 5፥8
✍ “ይህም ቃል ከዘላለምና ከትውልዶች ጀምሮ ተሰውሮ የነበረ ምሥጢር ነው፥ #አሁን ግን ለቅዱሳኑ ተገልጦአል፤”
— ቆላስይስ 1፥26
📌 “#አሁን ግን በሚሻል ተስፋ ቃል በተመሠረተ በሚሻል ኪዳን ደግሞ መካከለኛ እንደሚሆን በዚያ ልክ እጅግ የሚሻል አገልግሎት አግኝቶአል።”
— ዕብራውያን 8፥6
✍ “ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ #አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ።”
— ዕብራውያን 9፥24
📌 “እንዲህ ቢሆንስ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር፤ #አሁን ግን በዓለም ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል።”
— ዕብራውያን 9፥26
✍ “እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም #አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም #አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥10
📌 “እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ #አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥25
✍ “ወዳጆች ሆይ፥ #አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን።”
— 1ኛ ዮሐንስ 3፥2
#አሁን_በክርስቶስ!!
#ሄኖክ_አሸብር
Show all...
#Kegni ena gira #ቀኝ እና ግራ #መንፈሳዊ ግጥም
Henok Ashebir (@henokashebir5) has created a short video on TikTok with music feeling. | #Kegni ena gira #ቀኝ እና ግራ #መንፈሳዊ ግጥም
Show all...
#voiceeffects | with Music feeling - Official Sound Studio
Henok Ashebir (@henokashebir5) has created a short video on TikTok with music feeling. | #voiceeffects
❤ከስራ አይደለም!!❤
ኤፌሶን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥
⁵ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥
⁶-⁷ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
@proverbs_tube
@proverbs_tube
"የቀራንዮ የፍቅር ጭማቂ" የግጥም መድብልን ማግኘት ለምትፈልጉ
አድራሻ፦
👉 ሐዋሳ ሄሴድ አለምአቀፍ ቤተክርስቲያን.....አዲሱ ስታዲየም ፊት ለፊት ከላቭያጆው ጀርባ
👉 ሐዋሳ ብርሃን ባንክ መናኸሪያ ቅርንጫፍ አጠገብ ሻሎም ጀነራል ትሬዲንግ
👉 ሐዋሳ ኬራዊ ኢንተርናሽናል ሆቴል ፊት ለፊት ፖል ጫማ ቤት
ስልክ፦ 0906114984 ሄኖክ አሸብር
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.