en
Feedback
𝙞𝙢𝙖𝙜𝙞𝙣𝙖𝙩𝙞𝙤𝙣

𝙞𝙢𝙖𝙜𝙞𝙣𝙖𝙩𝙞𝙤𝙣

Open in Telegram

D𝚊𝚛𝚔 🌃 % S𝚞𝚗𝚜𝚎𝚝 🎴

Show more
7 794
Subscribers
+624 hours
+597 days
+18330 days
Posts Archive
+1
Sometimes, you just need to step back for a little while. I've met some really good people here, shared thoughts, laughs, random conversations, and a lot of little moments that made this place feel less like a screen and more like a small part of life. I might be a little quiet for a while. Nothing dramatic sometimes life just calls for a little distance, a little silence, and some time to yourself. I'm grateful for everyone I've crossed paths with here. For the conversations, the jokes, the kindness, and even the disagreements 😊 u've all added something to this journey in one way or another. So, if you don't see me around as much, don't worry about it. I'm probably just somewhere enjoying a little peace and getting my thoughts together. Take care of yourselves, keep doing your thing, and hopefully I'll see you around again soon. 🥂 https://t.me/Imagination_officially

“For God gave us a spirit not of fear but of power love and self-control.” ፦2 Timothy 1:7 ``እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈ
“For God gave us a spirit not of fear but of power love and self-control.”                              ፦2 Timothy 1:7 ``እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንምና።``                              ፦2ኛ ጢሞቴዎስ 1፡7

የአዲስ አበባ ልጅ መሆን እና ከተጣሉ ባል እና ሚስት መሃል መሆን አንድ ነው፤ የሚጎዳው ልጁ ነው! 😐 @Armemo_offical
የአዲስ አበባ ልጅ መሆን እና ከተጣሉ ባል እና ሚስት መሃል መሆን አንድ ነው፤ የሚጎዳው ልጁ ነው! 😐                         @Armemo_offical

«ማንኛውንም ሥነ-ጽሑፍ መረጋጋት አይሰጠንም፤ ይልቅስ በመጨረሻ የሚረዳን ሰው አገኝን የሚል ስሜት ይፈጥርብናል!።» —ጆርጅ ኦርዌ @Imagination_officially
«ማንኛውንም ሥነ-ጽሑፍ መረጋጋት አይሰጠንም፤ ይልቅስ በመጨረሻ የሚረዳን ሰው አገኝን የሚል ስሜት ይፈጥርብናል!።»               —ጆርጅ ኦርዌ          @Imagination_officially

Voice message03:12

Voice message02:46

የድንግል ማርያም ፍቅር በአፌ መሃላ ብቻ ሆኖ ቀርቷል፤ በልቤም የድሮን ያህል አይደለም። የሚገርመው ግን ከደሜ እስከዛሬ ድረስ ሊወጣ አለመቻሉ ነው!፤ በእናቴ ማህፀን ውስጥ የሰራኝ ስጋ የእሷ ምህረት
የድንግል ማርያም ፍቅር በአፌ መሃላ ብቻ ሆኖ ቀርቷል፤ በልቤም የድሮን ያህል አይደለም። የሚገርመው ግን ከደሜ እስከዛሬ ድረስ ሊወጣ አለመቻሉ ነው!፤ በእናቴ ማህፀን ውስጥ የሰራኝ ስጋ የእሷ ምህረት ይሁን አላውቅም!። ብዙ የፍልስፍና አግኖስቲክና ፓጋን ጽሁፎች ለሰባት አመት ጠልፈው ወስደውኝ ጨክኜ እንዳልቀር የሚያደርገኝ አንድ ስም አለ። ማርያም ነባቢት፣ ልባዊት፣ ህያዊት፤ ማርያምን ማርያምን እወዳታለሁ❤‍🩹

ዴመን፦«የሆነ እኔን የሚጠላኝን ሰው እያዳንኩ ነው» ስቴቨን፦«የትኛውን ይሆን? ብዙ ናቸው!» 📽️ The vampire diaries @Mid_Cinema
     
ዴመን፦«የሆነ እኔን የሚጠላኝን ሰው እያዳንኩ ነው» ስቴቨን፦«የትኛውን ይሆን? ብዙ ናቸው!»            
📽️ The vampire diaries  @Mid_Cinema

እኛ በልጅነት ጽድቃችን የምንኖር ክፉ አዋቂዎች ነን!።

የአብዛኛው ተቀጣሪ ትልቁ ፍላጎት ቀለል ያለ በሽታ ቢይዘኝ ብሎ መመኘት ነው። በሽታው ካንሰር እና አስፈሪ አደጋ አይሁን እንጂ  እንደጉንፋን፣ ብርድ ወይም መጠነኛ ትኩሳት ብቻ ለሶስት ቀናት እቤቱ የሚያርፍበት የሲክሊፍ ፈቃድ ማግኘት ነው ዋናው እቅዱ። እነሆ ክብሯን ሆይ ይሄ የሰው ልጅ ሙሉ ለሙሉ የወደቀበት ጊዜ ማሳያ ነው። ልጅ እያለን ካመመን ትምህርት ቤት ከመቅረት ጀምሮ በቤተሰብ ትኩረት እስከ ማግኘት የተለያየ እንክብካቤ ውስጥ እንገባለን። ከአመታት በኋላ አድገን እራሱ ይህ ባህሪ አለቀቀንም። ብቻ ዘመኑ ዘመነኛውን ሰው መስሏል። ዛሬ ላይ ህመም ከጤና የበለጠ ማራኪ እየሆነ መጥቷል። ምክንያቱም ጤነኛ መሆን ማለት ጠዋት ሁለት ሰዓት ላይ ስራ ቦታ መገኘት አለብህ የሚል ማስጠንቀቂያም ጭምር ነው። ያ ሰው በስራ ቦታ ተገኝቶ ለ9 እና 10 ሰዓታት ደፋ ቀና ማለቱ ምንም አይነት አዲስ ነገር እያመጣለት አይደለም። በርግጥ ሰራተኛው መታመም ሳይሆን በወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የጥፋተኝነት ስሜት ሳይሰማው አልጋው ላይ የመቆየት መብት እንዳለው የሚያረጋግጥበት ወረቀት ነው የሚፈልገው። በትንሹም ሰዋዊ አስተሳሰባችንን መቀየር ያልቻልን እንደምኞታን ቢደረግለን የፈጠነ የምንጠፋ ፍጡሮች ነን። ለነገሩ ዘመናዊው የሥራ ሥርዓት እራሱ ዕረፍትን ለታካሚው ብቻ የሚገባ ልዩ መብት አድርጎ አጽድቆታል። ጤነኛው ግን በየቀኑ ወዝና ላቡ እስከመጨረሻው መታለብ፣ ጊዜው እና ጉልበቱን ማባከኑን ማረጋገጥ አለበት። ታድያ ግን በዚህ አካሄድ ህይወቱን ለገንዘብ መስዋት አድርጎ ቢያልፍ፤ ቀሪ ህይወቱ ግን ያለገንዘብ ጡረተኛ ሆኖ የሚያበቃበት ሌላኛው የኪሳራ ጅማሮ ነው። አብዛኛው የኢትዮጲያ ሰራተኛ ህመም ሲሰማው «በዚህ ስራ እንዲህ ተጨናንቄ እስከመቼ?» ከማለት ይልቅ ለእራሱ በሹክሹክታ እንዲህ ማለት ይቀናዋል፦«ነገ የፈጠነ ሃኪም ቤት ሄጄ ሲክሊፍ አጽፋለሁ። ከዛ ምርጥ የሆነ ቀን በቤቴ ማሳለፍ ነው!» 🤦🏽 @Imagination_officially

የሳራ እና የሳምሶን ምኞት
የሳራ እና የሳምሶን ምኞት

የግጥሜ አርዕስት (አንጎቨር) ኸረ ወይኔ!😑

የሃገሬ ሰው "ሰላም አደርክ ፣ ሰላም ዋልክ እና ሰላም ነህ?" ለሚለው ጥያቄ አንድ መልስ ብቻ ነው ያለው፦«እግዚአብሔር ይመስገን»             እውነታው ግን፦🌱🥃🚬😢🪦 @Imagination_officially

በመጨረሻም ጦርነትም ያበቃል፣ ወታደሩ ያልቃል፣ ሕዝቡ ደብሮታል!😑

በምድረበዳ ምንጭ ፍለጋ መኳተኔን ትቼ መብረር ተመኘው። ምንአልባት ከሰማይ ደመና የተቋጠረ ውሃ ካገኘው በሚል የእግር ሰንሰለቴን እስከነእግሬ በጥሼ ጥዬ ወደላይ በረርኩ። አሁን እግር ባይኖረኝም ትልቅ ክንፍ አለኝ። ታድያ በሰማይ ስበር ከንፋስ ጋር የሚያፏጨው ነፋሻማ ዓየር የአጥንቴን አውታሮች ነቀነቃቸው። በድንገት ቀለለኝ። ነፃ ሆንኩኝ ከእሰራቴ። ቢሆንም ግን ልክ እንደካህሊል ጅብራን፦«ጭንብሎቼን የሰረቁ ሌቦች ለዘላለም ይባረኩ ይባረኩ!» አላስባለኝም። ይልቅስ እራስን ከማጥፋት ቡናም ካለመጠጣት መካከል እንደቦንሪዳ አህያ ያለምርጫ ደርቄ ቀረሁ። በረርኩ፤ በጣም በረርኩ። የማርፍበት እግር አልባ ቢጤነቴ በሰማይም የሚጨበጥ አንዳችን እንኳን አሳጣኝ!። ለካ ነፃነት የምናርፍበት መሬት እና የሚያስጠጋን ግድግዳ ከሌለ ትርጉም አልባ አቅጣጫ ነው። እየው ከዚያ ቀን ጀምሮ ከሰንሰለቴ ነፃ ሆኜ ከማያልቀው ሰማይ በታች እጓዛለሁ። በጠፋ ካርታ ላይ እጄን የሚይዘኝ አጥቼ በማያበቃ  ፍጻሜ መጨረሻዬን አጣደፍኩ። የተዘጉ በሮች በጠቅላላ ክፍት ቢሆኑልኝም በረከት አጣውባቸው። ለካ እያንዳንዱ ክፍት በሮች ከነበርንበት የመጥፊያ መንገዳችን ነበሩ። በፊት ላይ ነፃነት ክንፍን መቀናጀት ነው ብለው ሰብከውኛል። ማንም ግን ባለክንፉ መሬት እንደሚናፍቀው አልነገረኝም ነበር። አሁን በማያልቀው አጥናፈ ሰማይ ያለመዳረሻ እየተጓዝኩ ነው። ይህ መሄጃዬን አለማወቅ ብቻ አልነበረም፤ ይልቅስ መቆም ከሁሉም የከፋውን እውነት እንድቀበል ስለሚያስገድደኝም ጭምር ነበር። የማርፍበት እግሬ ተሰብሯል፣ የምመለስበት ቦታ እርቋል፣ ለካ የሰው ልጅ የሚጠፋው መንገዱን ባለማወቁ ሳይሆን የነበረበትን ቦታ በመርሳቱ  ነው። እኔም ዛሬ ነፃ ሆኛለሁ። ሰማይን ያህል ግዛት የእኔ ነው፣ በሮቼ ሁሉ ክፍት ናቸው፣ ጎዳናው በጠቅላላ በፊቴ ተዘርግተዋል። ነገር ግን ከእነዚህ ሁሉ ማግኘች መካከል አንድ ነገር ብቻ ጠፍቶብኛል፤ ያም እኔ ነበርኩ!። ነፃ ነኝ ለዛም ነው የጠፋውት። እውነትም የሰው ልጅ ሊያጣው ከሚችለው የከፋው ማጣት እራሱን ማጣት ነው!። I am free. And somewhere between all these open doors, I lost my way back to myself until, one day, I realized that the stranger I had been searching for was the person I had become..              @Imagination_officially

«I am free, and that is why I am lost» —Franz Kafka
«I am free, and that is why I am lost»   —Franz Kafka

ከዚህ በኋላ በዚህ ልክ ማስተዋቂያ አላበዛም። አንድ ድርጅት ነው። አልሞላ ሲል ተደጋጋሚ የለቀኩት። እኔ ደግሞ የሜምበሩን ሰላም ይበልጥብኛል። እስከዛሬ ከሌሎች የቴሌግራም ቻናሎች ጋር እርስ በእርስ ማስታወቂያ ያልሰራውት ይህን ስብስብ ላለመበትን ነው። እናም ይቅርታ 🙏🏼

ጥቂት ነው የሚቀረው°° ለ500 ሰው ሰዓቱ እየየረሰ ነው። ስምምነ ትብብረ 😑
ጥቂት ነው የሚቀረው°° ለ500 ሰው ሰዓቱ እየየረሰ ነው። ስምምነ ትብብረ 😑