en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 333 subscribers, ranking 5 639 in the Religion & Spirituality category and 2 190 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 333 subscribers.

According to the latest data from 15 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -80 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 22.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.47% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 409 views. Within the first day, a publication typically gains 1 605 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 22.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 16 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 333
Subscribers
-124 hours
-117 days
-8030 days
Posts Archive
#በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም #መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚነግሡት ዓመታዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ ነሐሴ ፳፬ ቀን የሚከብሩት የጻድቁ አባታችን አቡነ #ተክ
#በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም #መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚነግሡት ዓመታዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ ነሐሴ ፳፬ ቀን የሚከብሩት የጻድቁ አባታችን አቡነ #ተክለ_ሃይማኖት፣ የቅድስት እናታችን #ክርስቶስሠምራ እና የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ በዓለ ንግሥ ነው፡፡ በደብራችን ታቦታተ ሕጉን በማውጣት መከበር የተጀመረው #በ፲፱፻፹፪(1982) ዓ.ም እንደሆነ አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡አሁንም የአባቶቻችንን ፈለግ የተከተልን እኛ ከቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ለማግኘት በየዓመቱ በድምቀት እናከብረዋለን፡፡ ✤✤✤ ነሐሴ ፳፬(24) ቀን የሦስቱም ቅዱሳን በዓለ እረፍታቸው ነው አቡነ #ተክለሃይማኖት ወቅድስት #ክርስቶስ ሠምራ እንዲሁም አርዮስን መልስ ለመስጠት በቅርጫርት ውስጥ ተጉዞ ለሄደው እና ከ 318 ሊቃውንት አንዱ የሆንው የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ ነው።

የመርዓስ ኤጵስ ቆጶስ የነበረው አባት አባ ቶማስ ክርስቶስን በማመን በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊት በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የሚኖር ነበር። በዚህ ፅናቱ የክብር ባለቤት ጌታችን መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ዘንድ መንጋውንም ይጠብቅ ዘንድ መረጠው አባታችን ቶማስም ሐዋርያዊ ተልዕኮውን እየፈፀመ፣ ሕዝቡን እየመራ ሳለ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በሱ ላይ፣ በአጠቃላይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ላይም ተነሳባቸው፣ ክርስቲያኖችንም ያሰቃያቸው ጀመር በአንድ ወቅት ከመኳንንቶች አንዱ የነበረው፣ ቅዱስ ቶማስን ወደ እርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ እነርሱም እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ ወሰዱት ደሙም እንደ ውኃ ፈሰሰ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት «እኔ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ ጣኦታት አልሰግድም ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና» በዚህም ጊዜ መኮንንኑ በጣም ተቆጥቶ እጅግ የበዛ ስቃይን አሰቃየው የነዳጅ ድፍድፍን አፍልተው በላዩ በአፉና በአፍንጫው እስከመጨመርም ደረሱ ልባቸው እንደ ድንጋያ የፀና ስለ ነበር ቅዱስ ቶማስን ገድለው ቶሎ ማሣረፍ አልፈለጉም ይልቁንም የስቃዩን ዘመን አስረዘሙ እንጂ እርሱም ስለ ስህተታቸው ይዘልፋቸው ነበር፣ እንደ ማይመልስም ሲገባቸው በጨለማ ቦታ ጣሉት በየዓመቱም ወደ እርሱ እየሄዱ ከሕዋሳቱ አንድ፣ አንዱን ይቆርጡ ነበር፡፡ በዚህም ለሃያ ሁለት(፳፪) ዓመት ቆየ ሲቆይ ግን አፍንጫውን፣ ከንፈሮቹን፣ ጆሮዎቹን፣ እጆቹንና እግሮቹን ቆርጠው ነበር፤ በዚህም ምክንያት የአገሬው ሰው ሞቷል ብለው አስበው በየዓመቱ መታሰቢያ ያደርጉለት ነበር ይህ ለምን ሳይሞት ቢሉ ጊዜው ሲረዝም ቢሞት ነው እንጂ እስካሁንማ ይመጣ ነበር ብለው ስላሰቡ ነበር፤ ነገር ግን ከሕዋሳቶቹ አብዛኛው ክፍል ቆርጠው ቢጥሉትም አካሉ ግን ተቆራርጦ ሲጣል አንዲት ሴት አየችው፣ ይህችም ሴት በሌሊት ወደርሱ ተሠውራ በመሔድ ትመግበው ነበር፡፡ ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከገለጥ ድረስ እንዲህ ሲሰቃይ ኖረ፡፡ #ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ስለክርስቶስ በመታመን የታሠሩ እስረኞች ሁሉ እንዲፈቱ በማዘዙ ሁሉም ተፈቱ፡፡ ቅዱስ ቶማስ ግን የተጣለበት ቦታ፤ በሕይወት ያለም ስላልመሠላቸው አላወጡትም ነበር፤ ነገር ግን ይህን አዋጅ ትመግበው የነበረችው ሴት ሰምታ ነበርና ወደ ካህናቱ ዘንድ ሄዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ሃያ ሁለት ዓመት በዚያ ስለመኖሩ ነገረቻቸው ቦታውንም አመለከተቻቸው እነርሱም ባገኙት ጊዜ አንስተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑም ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደስ ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱንም ይሳለሙ ነበር፡፡ ከቦታ ቦታ ይዘዋወር የነበረውም በቅርጫት ኹኖ በዘህያ ላይ ተጭኖ ነው፡፡ ✤ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ የከበሩ ፫፻፲፰ ኤጲስ ቆጶሳትን (ሠለስቱ ምዕት) የአንድነት ጕባኤን በኒቂያ አገር በሰበሰበ ጊዜ ይህ አባት (ቅዱስ ቶማስ) ከሠለስቱ ምዕት አንዱ ነበር፤ ወደ ኒቅያ ጕባኤ በቅርጫት ሁኖ በአህያ ተጭኖ እየሄደ መሆኑን አርዮሳውያን ሲሰሙ፤ ቶማስማ በጕባኤው ከተገኘ ተከራክሮ ይረታናል አንችለውም በማለት መንገድ ላይ ባደረበት ይዘውት ይጓዙት የነበሩትን አህዮች በጨለማ በሰይፍ መተዋቸዋል፤ ነገር ግን ሌሊት ሊነጋጋ ሲል ለመንገድ ሲነሱ ቶማስ በተዓምራት አግልጋይ ረድኡን የተቆረጡትን የአህያዎቹን አንገታቸውን ከሰውነታቸው አጋጥመው ይነሳሉ ብሎ ሲያዘው የአንዱን አህያ ከሌላኛው አህያ ቢያጋጥመውም ቅሉ አህዮቹ ሕይወት አግኝተው ጕባኤ ኒቅያ አድርሰውታል፤ በዚያም አርዮስን መልስ እስኪያጣ ድረስ በጽናት ሲከራከረውና መልስ ሲያሳጠው የጕባኤው ሊቀ መንበር ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እስኪደነቅ ድረስ በማየቱ ሃይመኖትስ የእነ ቶማስ ዘመርዓስ ነች ብሎ አጽንቶ ወስኗል፡፡ በጕባኤውም አርዮስን ተከራክረው ከረቱ በኋላ አውግዘው ለይተውታል፤ ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ፤ ሕግና ሥርዐትን ሥጋዊና፤ መንፈሳዊ ፍርድንም ሰሩ። ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ከተመለሰ በኋላ ካህናቱና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲያስተውሉት እንዲጠበቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው፡፡ ይህ አባት ለ፵ ዓመት ያህል በሢመቱ አገልግሎ በነሐሴ ፳፬ ቀን አርፋል። /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

✤✤✤ #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ ✤✤✤ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትውልድ ሀገሯ #ሸዋ_ቡልጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ቅዱስ ጌየ ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ደጋግ ወላጆቿ ከአባተቷ ቅዱስ ደረሳኒ ከእናቷ ከቅድስት ዕሌኒ በግንቦት 12 ቀን ተወለደች፡፡ እነርሱም ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ከወለዱ በኋላ በደም ግባቷና በጠባይዋ እየተደሰቱ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በማስተማር ስላሳደጓት ከልጅነቷ ጀምራ በሥነ ምግባር፣ በሃይማኖት የታነጸች በመልኳም እጅግ ውብና ያማረች ሆነች፡፡ ባደገችም ጊዜ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ የንጉሥ ባለሟል ለሆነ ስሙ ሠምረ ጊዮርጊስ ለተባለ ደግ ሰው በሕግ አጋቧት፡፡ ከሕግ ባሏ ከሠምረ ጊዮርጊስም ዐሥራ ሁለት ልጆችን ወለደች፡፡ ከእነዚህም መካከል አስሩ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች ነበሩ፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዐፄ #ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት የነበረች ኢትዮጵያዊት ጻድቅ ስለነበረች ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ገብረ መስቀል በትዳሯ፣ በሥነ ምግሯና በሃይማኖቷ በሁለመናዋ የተመሰገነች መሆኗን ዝናዋን ስለሰማ ‹‹#በጸሎትሽ አስቢኝ›› በማለት ከአገልጋዮቹ ውስጥ እርሷን እንዲያገለግሏት፣ 174 አገልጋዮቸን ላከላት፡፡ ብዙ ፈረስና በቅሎ እንዲሁም ለነገሥታት ሚስቶች የሚገባ ከሐርና ከወርቅ የተሠራ ልብስና የወርቅ ጫማም ላከላት፡፡ ነገር ግን እሷ ይህን ሁሉ ክብር አልፈለገችም ይልቁንም ‹‹ለዓላማዬ እንቅፋትና ውዳሴ ከንቱ ይሆንብኛል እንደዚሁም ወርቁ ጌጡ ተሸጦ ለነዳያን ይመጸወታል ነገር ግን እነዚህን አገልጋዮች ምን አደርጋቸዋለው?›› እያለች ወደ እግዚአብሔር አመለከተች፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ #ሚካኤል ፊቱ እንደ ፀሐይ እያበራ ሦስት ኅብስት በእጁ ይዞ መጥቶ ‹‹የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! እነሆ ይህን #ኅብስት ተመገቢ እግዚአብሔር በቸርነቱ ብዛት ሰጥቶሻል›› አላት፡፡ እርሷም ፈጣሪዋን አመስግና ኅብስቱን ከመልአኩ እጅ ተቀብላ ተመገበች፣ መዓዛ ጣዕሙም ሰውነቷን አለመለመው፡፡ በዚህም የተነሳ እስከ ሦስት ቀን እህል ሳትበላ ውኃ ሳትጠጣ ቆየች ኃይለ መንፈስ ቅዱስ በሰውነቷ አድሮባታልና፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን እንዲህ ሆነ፡- ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ የከፋ ነበርና በጣም ስላበሳጨቻት በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት፡፡ ያም የእሳት ትንታግ እስከ ጉሮሮዋ ዘለቀና አገልጋይዋን ገደላት፡፡ በዚህ ጊዜ ብጽዕት ክርስቶስ ሠምራ ደንግጣ ወደ ሌላ ክፍል ገባችና ኃጢአቷን ለእግዚአብሔር እየተናዘዘች እጅግ በጣም አዝና ጥፋቷ እንደ ጸጸታትና እግዚአብሔር አምላክም በእጇ የሞተችውን አገልጋይዋን ከሥጋዋ አዋሕዶ ቢያሥነሳላት ያላትን ገንዘብና ሀብት ትታ ባላት ዘመኗ ሁሉ አገልጋዩ እንደምትሆን ብጽዓት (ስዕለት) አደረገች፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቷን ሰምቶ አገልጋይዋን ከሞት አሥነሳለት፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ‹‹ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከእኔ ከባሪያው ያላራቀ አምላክ ይክበር ይመስገን›› ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔርን ካመሰገነች በኋላ አስቀድማ የገባችውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኩስናዋን አዘጋጀች፡፡ ሕፃን ልጅዋንም ይዛ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደች፡፡ ስትሄድም በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግሯ ከመንገዱ ብዛት ከእንቅፋቱም የተነሳ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሟ መሬት ለመሬት እየፈሰሰ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ደረሰችና አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኩስናዋን ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ይዛው የተሰደደችውን ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከደጅ ላይ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ ሲያለቅስ ከመነኮሳቱ አንዲቷ ሕፃኑ ሲያለቅስ ከሚያድር ብላ ወደ በአዓቷ ልታስገባው ስትል የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፡፡ ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በ 3 ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ብፁዓን ገባ፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል ካለችበት በዓት አውጥቶ በክንፉ ተሸክሞ ከጣና ደሴት አደረሳት፡፡ ከዚያም ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ሳትወጣ ባሕሩ ውስጥ ዐሥራ ሁለት ዓመት ቆማ ስትጸልይ ኖረች፡፡ ከዐሥራ ሁለት ዓመት በኋላም ጌታችን ተገልጦላት #ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ከዚህ በኋላ ሕይወቷን በሙሉ በታላቅ ተጋድሎ ስታሳልፍ ጌታችንም ከቅድስት እናቱ ጋር ሆኖ በየጊዜው ይጎበኛት ነበር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልንም የሁልጊዜ ጠባቂዋ አድጎ ሰጥቷታል፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብሔረ ብፁዓን እየሄደች ከዚያ ከሚኖሩ ቅዱሳን ጋር እስከ ሰባት ቀን ድረስ ስትነጋገር ትቆይ ነበር፡፡ #ሄኖክና #ኤልያስ ወዳሉበት ወደ ብሔረ ሕያዋንም እየሄደች ትመለስ ነበር፡፡ ✤✣✤ ከዕለታት አንድ ቀን በጣና ማዶ መዕቀበ እግዚእ የሚባል አንድ ሰው ነበረና መልአከ ጽልመት ወደ እርሱ ዘንድ መጥቶ ‹‹ፈጣሪውን ክደህ ይህን ዕፅ በሰውነትህ ብትቀብር ሞትና እርጅና አያገኝህም›› አለው፡፡ እርሱም ለዚህ ክፉ ሀሳቡ ፈቃደኝነቱን ስለገለጠለት መልአከ ጽልመት በሰውነቱ ውስጥ ዕፁን ቀብሮለት ሄደ፡፡ መዕቀበ እግዚእም ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዘንድ መጥቶ ‹‹ሰላም እልሻለው በጸሎትሽም ተማጽኛለሁ፣ የፈጠረኝን እግዚአብሔርን እስከ መካድ ደርሼ ብዙ ኃጢአት ሰርቻለውና›› አላት፡፡ ቅድስት እናታችንም በዚያን ጊዜ ፈጥና ተነሥታ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደችና ስለዚህ ሰው በፍጹም ኀዘን በመሆን ወደ ፈጣሪዋ አመለከተች፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን መጥቶ ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ለዚህ ሰው ምሕረት አይገባውም፣ የምገድል የማድን የምቀስፍ ይቅር የምል አምላክ እኔ እያለሁ ፈጣሪውን ክዶ በሰይጣን ምክር ተማምኖአልና›› አላት፡፡ በዚህ ጊዜ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጌታችንን እግሩ ሥር ተደፍታ ‹‹አንተ መዓትህ የራቀ ምህረትህ የበዛ ፈጣሪ ሆይ! ማርልኝ ሁሉ ይቻልሃልና…›› ስትል አጥብቃ ለመነችው፡፡ ሁሉን የፈጠረ ጌታችንም ‹‹ስለ አንቺ ፍቅር ምሬልሻለው›› አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ማዕቀበ እግዚእን ጠርታ ‹‹ኃጢአትህን ይቅር ብሎሃል›› አለችው፡፡ ከዚህ በኋላ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ የተቀበረውን ዕፅ ሰውነቱን ፍቃ ስታወጣለት ደሙ እንደ ቦይ ውኃ ወረደ፤ በዚያው ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ከማኅበረ ሰማዕታት ጋር አንድ ሆነች፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ #ስድስት ክንፎችን ሰጥቷታል፡፡ በበዓለ ጥምቀት ወቅት ሙሴ፣ ኤልያስና መጥመወቁ ዮሐንስ ጌታ የተጠመቀበትን የዮርዳኖስን ውኃ አምጥተው ሙሴ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ቀኝ እጇን፣ ኤልያስ ግራ እጇን ይዘዋት ዮሐንስ ውኃውን በራሷዋ ላይ አፍስሶ አጥምቀዋታል፡፡ ከጌታችን ጥምቀት በኋላ እንደዚህ ዓይነት መንገድ የተጠመቀ ማንም የለም፡፡ እነርሱም ጓንጉት በምትባል ገዳም ውስጥ የገዳም አስተዳዳሪ እንደምትሆንና እጅግ ብዙ ተከታዮች እንደሚኖሯት ትንቢት ነግረዋት ወደ ሰማይ ዐርገዋል፡፡ የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ምልጃና ጸሎት አይለየን +++ ✤✤✤ #ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ ✤✤✤

#በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም #መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚነግሡት ዓመታዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ ነሐሴ ፳፬ ቀን የሚከብሩት የጻድቁ አባታችን አቡነ #ተክለ_ሃይማኖት፣ የቅድስት እናታችን #ክርስቶስሠምራ እና የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ በዓለ ንግሥ ነው(ታሪኩን ከታች ይመልከቱ) ፡፡ በደብራችን ታቦታተ ሕጉን በማውጣት መከበር የተጀመረው #በ፲፱፻፹፪(1982) ዓ.ም እንደሆነ አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡አሁንም የአባቶቻችንን ፈለግ የተከተልን እኛ ከቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ለማግኘት በየዓመቱ በድምቀት እናከብረዋለን፡፡ ✤✤✤ ነሐሴ ፳፬(24) ቀን የሦስቱም ቅዱሳን በዓለ እረፍታቸው ነው ታሪከ አቡነ #ተክለሃይማኖት ወቅድስት #ክርስቶስ ሠምራ እንዲሁም አርዮስን መልስ ለመስጠት በቅርጫርት ውስጥ ተጉዞ ለሄደው እና ከ 318 ሊቃውንት አንዱ የሆንው የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ ታሪክ:: ✤✤✤ ✤✤✤ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ✤✤✤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት #እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው«አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለውሥላሴ ን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በአሥራ አምስት ዓመታቸው ከ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያ ውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ኃሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም የኃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡ አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ /ገድለ ተክለ ሃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫/ ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡ አባታችን በዳዊት ፀሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም 10፣ 10 ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡ በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው (አወጣቸው) ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበረን “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አጥነዋል ፡፡ በሐይቅ 10 ዓመት በደብረዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡ ለ22 ዓመት ቆመው በመፀለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው #ለ7 ዓመት በፀሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በፀሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ አባታችን ባረፉ 54 ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም ለአባታችን ለአቡነ #ሕዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ# ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል ፡፡ በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ለእኚህ ዕረፍታቸው በእግዚአብሔር ፊት ለከበረና ብዙ ክብር ለተሰጣቸው ለጻድቁ ተክለ ሃይማኖት በየዓመቱ በነሐሴ ፳፬ ቀን በዓለ ዕረፍታቸውን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ እኛንም ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/ ✤✤✤

• ይህን ችግር ለመቅረፍ የተነሡት የዘመኑ ፓትርያርክ ከሀቢብ ጊዮርጊስና ከሌሎች ሁለት ምእመናን ጋር በመሆን ሐዋሪያዊ ጉዞ አደረጉ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር ሀቢብ በውጪ የሚገኙ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ወጣቶችን የሚሰበስብበትን ዘዴዎች መመልከት የቻለው፡፡ ወዲያውኑ ከጉዞው መልስም ህጻናትና ወጣቶች ተሰብስበው የሚመሩባቸውን ሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማደራጀትና የሚመጥናቸውን ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረጽ መንፈሳዊ መዝሙራትንም ለማዘጋጀት አቅዶ ሥራውን ጀመረ፡፡ በዚህ ሥራውም በሌላ እምነት ተማርከው የነበሩትን መመለስ ችሏል፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ #ጸሐፊነትን፣ #አስተዳዳሪነትን እና #ሰባኪነትን በእኩል ደረጃ አሳክቶ መያዝ የቻለ ሰው ነው፡፡ በአጠቃላይ #ሠላሳ_መጽሐፍትን አዘጋጅቷል፡፡ በመጨረሻ ዕድሜው ሲገፋ #ጤናውም_እየታወከ_መጣ፤ ቤቱም በደቀ መዛሙርቱ መሞላት ጀመረ፡፡ ለእርሱም የነበራቸውን ፍቅር ለመግለጽ መኝታን ከበው አብረውት ጸሎት በማድረግ ራሱ የደረሳቸውን #መዝሙራትም_ይዘምሩለት ነበር፡፡ በመጨረሻ ሀቢብ ጊዮርጊስ ነሐሴ 15 ቀን 1943 ዓ.ም (በ75 ዓመቱ) አረፈ፡፡ ዜና እረፍቱም በሀገረ ግብፅ ከዳር እስከ ዳር ተሰማ፡፡ ቀብሩም በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት መስከረም 17 ቀን 1944 ዓ.ም ተፈጸመ፡ ምንጭ፡-ሊቀ ዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስ እና ሥራዎቹ፣ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#ሊቀ_ዲያቆናት_ሀቢብ_ጊዮርጊስ #ለግብጽ_ቤተ_ክርስቲያን_የንጋት_ጎህ (ነሐሴ 15 እረፍቱ) #ሀቢብ_ጊዮርጊስ_ማነው? ሀቢብ ጊዮርጊስ በ1868 ዓም #በካይሮ_ከተማ ተወለደ፡፡ አባቱ በሕጻንነቱ ስለሞተበት እናቱ ለብቻዋ በፍቅረ ቤተ ክርስቲያን አንጻ አሳደገችው፡፡ ትምህርቱን የተከታተለው አቡነ ቄርሎስ አምስተኛ በመሠረቱት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው፡፡ በዚያውም #ዲቁና ተቀብሎ ማገልገል ሲጀምር ዕድሜው #አሥራ_ሰባት ብቻ ነበር፡፡ በወቅቱ ፓትሪያርኩም በኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን የተከሰቱትንና የቤተክስቲያኒቱን አገልግሎት እጅጉን የጎዱ እንቅፋቶች በማስወገድ ወደ ለውጥ መንቀሳቀስ የጀመሩበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ደግሞ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ሆኖ የተገኘው #የሰለጠኑ_ካህናትን_የሚያፈራ_ተቋም_መክፈት ስለነበር ለዚህ ወሰኝ ተልዕኮ የሚመጥን ይሆናል የሚሉትን ሰው ሲፈልጉ ምርጫቸው ያረፈው በወጣቱን አገልጋይ ሀቢብ ጊዮርጊስ ላይ ሆነ፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ ኃላፊነቱን እንደተቀበለ ትኩረቱን ያደረገው ለተቋሙ ግንባታ የሚያስፈልገውን ገቢ ማሰባሰብ ላይ ነበር፡፡ በውጤቱም ከሀገር ሀገር እየተዘዋወረ ባደረገው ቅስቀሳ የምእመኑን የታመቀ ፍቅር ማቀጣጠል የቻለ ሲሆን በጥቂት ቀናት ውስጥ የተገኘው ድጋፍም በቂ ሆኖ ስለተገኘ ኮሌጁ እንደታሰበው ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል፡፡ ኮሌጁ ተከፍቶ ማስተማር ሲጀምር ደግሞ ሀቢብ ጊዮርጊስም ከመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች አንዱ ለመሆን የቻለ ሲሆን በወቅቱ የተከሰተውን የመምህራን እጥረት መቅረፍ ግድ ሲሆን ደግሞ ተማሪ በሆነበት ዓመታት መምህርነትንም ደርቦ ያዘ፡፡ የሀቢብ አስደናቂ አገልግሎት በስፋት የተገለጠው ከተመረቀ በኋላ ሲሆን በሰባኪነት ተሰማርቶ የሰበካቸው ስብከቶች በወቅቱ ሰማዕያኑን የመሰጡ ብቻ ሆነው አልቀሩም፡፡ ይልቁንም ብዙዎች ከሞተ በኋላ እንኳ ሳይቀር የሚያስተውሷቸው እንዲሁም ታትመው የብዙዎችን ሕይወት ሲለውጡ የሚኖሩ ሆነዋል፡፡ ለመሠረተው ኮሌጅ ማደግ ከፍተኛ ራእይ የነበረው ሀቢብ ጊዮርጊስ በዚያ ወቅት ከሠራቸው ሥራዎች መሀከልም ጉልህ የነበረው በኮሌጁ ዙሪያ የነበሩ ቦታዎችን ባገኘበት አጋጣሚ ሁሉ በግል ገንዘቡ እየገዛ ለኮሌጁ ማስፋፊያ ይሆን ዘንድ ማበርከቱ ይጠቀሳል፡፡ በዚህና መሰል ወደር የለሽ ተግባራቱና ከፍ ያለ ትጋቱ የተደሰቱት ፓትሪያርኩ አቡነ ቄርሎስ #የሊቀ_ዲያቆንነት_ማዕረግን_ሰጡት፡፡ የሀቢብ ጊዮርጊስ ቀጣይ የአገልግሎት ምዕራፍ የኮሌጁ ርዕሰ መምህር በሞት በተለየ ጊዜ እርሱን በመተካት የርዕሰ መምህርነትን ኃላፊነት ሲጨምር የሚጀምረው ነው፡፡ በዚህ ወቅት ከሠራቸው ተግባራት መሀከልም ዋነኛው ኮሌጁን ከውጪ ተጽእኖ የተጠበቀ እንዲሆነ ማድረጉ የመጀመሪያው ሲሆን በመከላከል ብቻ ላይም ሳይወሰን ተቋሙ #የኦርቶዶክሳዊት_ቤተ_ክርስቲያንን_ትምህርት_በምልዓት_የሚያንጸባርቅ መብራት ማድረግ መቻሉ ደግሞ ሌላው ዘለዓለማዊ ስኬቱ ነው፡፡ በተለይ ኦርቶዶክሳዊያን ደቀመዛሙርት ወደ አንግሊካን የትምህርት ተቋማት ሄደው የከፍተኛ ትምህርት እንዲከታተሉ የሚል ግፊት ሲነሳና እንዲሁም የአንግሊካን ምሁራን በኮፕቲክ የሥነ መለኮት ኮሌጅ እንዲያስተምሩ ሐሳብ ሲመጣ ይህን በመቃወም ግፊቱ ከሐሳብ አልፎ በተግባር እንዳይውል ማድረግ መቻሉ ነበር፡፡ የሀቢብ ልዩ ችሎታ የነበረው በመቃወምና በመከላከል ላይ ብቻ አለመወሰኑ ይልቁንም ከተቃወመው ሐሳብ የተሻለ አማራጭ እንዲኖር መሥራቱ ነው፡፡ በዚህም የተነሣ በኦርቶዶክሳዊው የትምህርት ተቋም ውሰጥ የአንግሊካን ሊቃውንት እንዳያስተምሩ በማለት አጥብቆ ሲቃወም በምትኩ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊውያን አስተምህሮ በጥልቀት የተረዱ ቀሳውስት እንዲኖሩ አጥብቆ ይሠራ ነበር፡፡ ሌላው የሀቢብ ጊዮርጊስ ጅምር የነበረውና ባለፉት ቅርብ ዓመታት ውሰጥ ለግብጽ ቤተ ክርስቲያን መነቃቃት መንስኤ የሆነው ተግባር ደግሞ ኮሌጁ የማታ የትምህርት መርሐ ግብር እንዲጀምር ማድረጉ ነው፡፡ የዚህ አዲስ መርሐ ግብር መከፈት በርካታ ምሁራንና ወጣቶች ወደ ቤተክርስቲያን እንዲመጡና በትምህርተ ሃይማኖት እንዲታነጹ እድል ከመስጠቱም በላይ በዚህ ምክንያትነት #የግብጽ_የትምህርት_ሚኒስቴር_ለኮሌጁ_እውቅና_ሊሰጠው_ችሏል፡፡ በማታው መርሐ ግብር ተካፍለው ከነበሩ ወጣት ምሁራን መካከል #ፖፕ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ አንዱ ናቸው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ለኮሌጁ እድገት ዕድሜውን ሁሉ የተጋው ሀቢብ ጊዮርጊስ ኮሌጁን በማሳደግ ዓለም አቀፍ ደረጃውን እንዲጠብቅ ማድረግ የቻለ ሲሆን መደበኛው የሥነ መለኮት ትምህርት በፍልስፍናና በሥነ ልሳን ትምህርቶች የታጀበ እንዲሆንና እንዲሁም በብቁ መምህራን የተሞላ በማድረግ የምርጥ አገልጋዮች መፍለቂያ እንዲሆን ስላደረገው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በቤተ ክርስቲያን ክህነት የሚቀበሉ ሁሉ የኮሌጁ ዲፕሎማ እንዲኖራቸው የሚያስገድድ ሕግ ተሠራ፡፡ ሀቢብ ጊዮርጊስ በሕይወት ኖሮ የኮሌጁን አርባኛ ዓመት ለማክበር የበቃ ሲሆን በዚያው ዓመትም ‹‹#የነገረ_መለኮት_ኮሌጅ_ትናንትናና_ዛሬ›› የሚለውን መጽሐፉን ለሕትመት አብቅቷል፡፡ #የሰንበት_ትምህርት_ቤት_ጅማሮ ሀቢብ ጊዮርጊስ የመጀመሪያውን ሰንበት ትምህርት ቤት በማቋቋም ሥራውን ሲጀምር የ24 ዓመት ወጣት ነበር፡፡ ጊዜውም 1892 ዓም ቦታው ካይሮ ከተማ ውስጥ በሚገኙ የኮፕቲክ አብያተ ክርስቲያናት፡፡ ጅማሮው ሕጻናትን ሰብስቦ በማስተማር ነበር፡፡ በእግዚአብሔር ቸርነት አገልግሎቱ ተባርኮለት ሥርዓተ ትምህርት ለመቅረጽ ማዕከላዊ ኮሚቴ አቋቋመ፡፡ ይህም ውጥን በሀገሪቱ በሞላ ተስፋፍቶ አገልጋዮች እጅግ የበዙ ሆኑ፡፡ በሀቢብ ጊዮርጊስ የተቋቋሙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በወጣቶች ልቡና ውስጥ መተከል እንዲችል ሕያው ምስክር ሆኑ፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ በግብጽ የመጻሕፍትና የበራሪ ጽሑፎች ስርጭት፣ ዐውደ ርእያት፣ ሴሚናሮች፣ ኮንፈረንሶች፣ ወደ አብያተ ክርስቲያናትና ወደ ገዳማት የሚደረጉ መንፈሳዊ ጉዞዎችንና የመሳሰሉ እንቅስቃሴዎች የመነጩት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ነው፡፡ #የሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_መስፋት_ምን_ጠቀመ? ሀቢብ ጊዮርጊስ የመሠረተው የሰንበት ትምርት ቤት እንቅስቃሴ ከተስፋፋ በኋላ በወቅቱ ቤተ ክርስቲያንን ይፈታተኑ የነበሩ ችግሮችን በእግዚአብሔር እርዳታ መፍታት የሚችል ሊሆን በቅቷል፡፡ ከነዚህም መሀከል የሚከተሉት ዐበይት ተግባራት አይዘነጉም፡፡ • መጽሔቶችን በማሳተም ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት ሥራ በብዛት የተሠራው በዚህ ዘመን ነው፡፡ • ወደ ቤተ ክርስቲያን ሳይመጡ የቀሩ ወጣቶች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲቀርቡ አድርጓል፡፡ • በዘመኑ የነበሩ እንግሊዛውያን ሚስዮናውያን የቅኝ ገዢዎችን አካሄድ በመከተል ኦርቶዶሳውያንን ከእምነት ለማስወጣት ይጥሩ ነበር፡፡ • ሚስዮናውያኑ በተለይ የትምህርት ዕድል በመስጠትና በመሳሰሉ ዘዴዎች በመጠቀም ወጣቶችን ለማማለል ይሞክራሉ፡፡ ቤት ለቤት እየዞሩ ማራኪነት ባላው ጽሑፎችና ባሸበረቁ ሥዕላት ያዘጋጁዋቸውን ብሮሹሮች በመበተን የሚሠሩት የቅሰጣ ተግባር አልበቃ ብሏቸው የእናት ቤተ ክርስቲያንን ስም ጥላሸት እስከ መቀባት ደርሰው ነበር፡፡ በዚህም ተግባራቸው ብዙዎች ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠፍተዋል፡፡

የ2018 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በጃንሜዳ አዘጋጅ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ .... 1) ልብሰ ተክህኖ በሙካሽ እና በግሪክ ጨርቅ 2) የታቦተ ህጉ መጎናጸፊ
የ2018 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በጃንሜዳ አዘጋጅ  የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ .... 1) ልብሰ ተክህኖ በሙካሽ እና በግሪክ ጨርቅ 2) የታቦተ ህጉ መጎናጸፊያ በሙካሽ 3) የመቀደሻ ንዋይ ቅድሳት 4) የሊቃውንት አባቶች ጥንድ ድርብ እና ልዩ ካባ 5) የሊቃውንት አባቶች የብር መቋሚያ እና ጽናጽል 6) የሰ/ትምህርት ቤት ዩኒፎርም እና ጥንድ ድርብ 7) የሰ/ት/ት ቤት ጽናጽል እና መቋሚያ እና የመሳሰሉት ንዋየ ቅድሳትን ለማሟላት ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ለዚሁ በዓል ገቢ ማሰባሰቢያ በተከፈተው የኮሚቴው አካውንት አስተዋጽዎ ያድርጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000636620991