en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 396 subscribers, ranking 5 567 in the Religion & Spirituality category and 2 182 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 396 subscribers.

According to the latest data from 28 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 15 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.32%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 282 views. Within the first day, a publication typically gains 1 576 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 396
Subscribers
+524 hours
+287 days
+1530 days
Posts Archive
ይህ በዓል ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተዳድሩ የቆዩ አባቶቻችን ጌታንና ደቀ መዛሙርቱን አብነት በማድረግ በጋራ በመሰባሰብ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተቀላጠፈ አገልግሎት እንደዚሁም ለምእመናን አንድነትና መንፈሳዊ ዕድገት የሚበጁ መንፈሳውያን መመሪያዎችን የሚያስተላልፉበት እለት ነው፡፡ ይህንን የጌታችን ትእዛዝና የሐዋርያትን ሥልጣነ ክህነት መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጉባኤ ያደርጋል፤ ፩ኛ. የመጀመሪያው ጉባኤ ጥቅምት ፲፪ ቀን (የቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍት) ሲሆን፣ ፪ኛ. የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን የሚደረገው ይህ ርክበ ካህናት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ቅዱስ ሲኖዶስ በሚያደርገው ጕባኤ የሚተላለፉ መመሪያዎችና የሚጸድቁ ውሳኔዎች ለቤተ ክርስቲያን ዕድገት፣ ለምእመናን አንድነት፣ ለአገር ሰላምና ደኅንነት የሚጠቅሙ ይሆኑ ዘንድ ሁላችንም በጾም በጸሎት እግዚአብሔርን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ አምላካችን ቤተ ክርስቲያናችንንና አባቶቻችንን ይጠብቅልን፤ እኛንም ለአባቶች የሚታዘዝ ልቡና፣ ሓላፊነታችንን የምንወጣበትን ጥበብና ማስተዋሉን ያድለን፡፡ ፠ጉባኤው በትላንትናው ዕለት ግንቦት 9 ተጀምራል መንፈስ ቅዱስ ይህንን ታላቅ ጉባኤ ይባርክ ይምራ፤ እኛንም ይጎብኘን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

#ርክብ_ካህናት (#ዕለተ_ጥብርያዶስ፤ #ዳግሚት_ዕለተ_አግብኦተ_ግብር፤ የሃገራችን የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ ቀን)፤ ግንቦት በቤተክርስቲያን ሊቃውንት ፤ ጉባኤያት በ8 ይከፍላሉ ከእነርሱ ውስትም ‹‹ቋሚ ሲኖዶስ (Synode of Residents ) ››አንዱ ነው፡፡ አሁን ያለው የቤ.ክርስቲያነችን (የኦ.ኦ.ተ.ቤ.ክ) ሲኖዶሳዊ ደግሞ ጉባኤ ሦስት ዓይነት ነው ፡፡ 1. ዓመታዊ ፣ 2. ቋሚና 3. ድንገተኛ ጉባኤ ፡፡ ዓመታዊው ጉባኤ ጥቅምት 12 እና ትንሣኤ በዋለ በ25ኛው ቀን(በአራተኛው ሳምንት ) የሚካሄድው የግንቦት ርክበ ካህናት ይባላል፡፡ ርክበ ካህናት የሁለት ቃላት ጥምረት ሲኾን እነዚህም፤ ረክብ የሚለው ቃል ተራከበ ተገናኘ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጕሙም ማግኛ፣ መገኛ፣ መገናኛ ማለት ነው፡፡ /አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፰፴፩/፡፡ ክህነት የሚለው ቃል ደግሞ ከዲቁና ጀምሮ እስከ ከጵጵስና ድረስ ያሉትን መዓርጋት (በጥቅሉ ዲያቆናትን፣ ቀሳውስትንም ኾነ ጳጳሳትን) የሚያጠቃልል ስያሜ ነው፤ ካህን (ነጠላ ቍጥር) ሲኾን ካህናት ደግሞ (ብዙ ቍጥር) ነው፤ ብዙ ጊዜ ግን ይህን ባለማወቅ ካህናት የሚለውን ለቀሳውስት ብቻ መጠሪያ ሲኾን እናያለን፤ አለማወቅ ነው (ለምሳሌ በቅዳሴ መጨረሻ ጊዜ ዲያቆኑ በእደ … ካህን ይባርከነ ቢል ለኹሉም ያስኬዳል ሰዋስዉም ያዛል ሥርዐቱም ይኸው ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ዛሬ በእደ … ካህን ይባርከነ በማለት ፈንታ ፠( በእደ ብፁዕ ፓትርያርክ፣ በእደ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ፣ በእደ ቆሞስ…. ሲባል ይታያል፤ መስተካከል ያለበት ጉዳይ ነው፡፡)፠ ርክበ ካህናት ማለትም የአባቶች ካህናት (ማለትም በጵጵስና ማዕረግ ያሉ /ኤጲስ ቆጶሳት፣ ጳጳሳት፣ ሊቃነ ጳጳሳትና ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስን ያጠቃለለ (የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት) ጕባኤ፤ የካህናት መገኛ መገናኛ ጉባኤ (መሰባሰቢያ፣ መወያያ) ማለት ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን ሁልጊዜ በዕለተ ረቡዕ ይውላል፤ ወሩና የሚውልበት ቀን ግን በኢየዓርግና በኢይወርድ (በባሕረ ሓሳብ የበዓላትንና የአጽዋማትን ቀመር ተከትሎ) የሚወጣ ስለኾነ ከፍና ዝቅ ይላል፡፡ የአጽዋማትና የበዓላት ቀመር በቅዱስ ድሜጥሮስ አማካኝነት ከመዘጋጀቱ በፊት (ዐቢይ ጾም ሰኞ፣ ስቅለት ዓርብ፣ ትንሣኤ እሑድ፣ ርክበ ካህናት ረቡዕ፣ ዕርገት ሐሙስ፣ ጰራቅሊጦስ እሑድ እንዲሆን ከመደረጉ በፊት( መሉ ማብራራይ ሰሙነ ሕማማት የጻፍናን ይመልከቱ ) ርክበ ካህናት በየዓመቱ ግንቦት ፳፩ ቀን ይውል ነበር /መጽሐፈ ግጻዌ ግንቦት ፳፩/፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጐ ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ በየጸጋቸው መጠን እየተገለጠ ያጽናናቸው፥ ያጸናቸው፥ ያስተምራቸው፥ ይባርካቸውም ነበር፤ ጌታችን እስከ ዕርገቱ ባሉ ፵ ቀናትም መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን፣ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን አስተምሯቸዋል፤ በልቡናቸውም አሳድርድሮባቸዋል:: በመጽሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል ከዕርገቱ አስቀድሞ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ፫ ጊዜ በጉባኤ መገለጡ ተዘግቦ ይገኛል፡፡ እነዚህም፤ 1. የትንሳኤ (ዮሐ. 20፥19) 2. የአግብኦተ ግብር (ዳግም ትንሳኤ) /ዮሐ. 20፥:26/ 3. የጥብርያዶስ፤ (ዮሐ. 21፥1) ፡፡ ለድንግል ማርያም ግን በኹሉም እለታት መገለጡን አበው ያስተምራሉ፡፡ በጥብርያዶስ ባሕርም ከዐሥራ አንዱ ቅዱሳን ሐዋርያት ጋር ምሳ በልቷል፡፡ የርክበ ካህናት በዓል መነሻም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከተገለጠበት ከጥብርያዶስ ባሕር ካለው ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህች ዕለት በቅዱስ ጴጥሮስ መሪነት ሐዋርያቱ ወደ ጥብርያዶስ ባሕር ሔዱ፡፡ ዓሶችን ሊያጠምዱም በብዙ ደከሙ፤ ነገር ግን ጌታችን በረድኤት አብሯቸው አልነበረምና አንዳች አሣ በመረባቸው ሊገባ አልቻለም፡፡ ማጥመድ (አስተምሮ ከክህደት ወደ ሃይማኖት፤ ከኀጢአት ወደ ጽድቅ መመለስ) የሚቻለው በረድኤተ እግዚአብሔር እንጂ በእውቀት ብዛት ወይም በአንደበተ ርቱዕነት ብቻ አይደለምና፡፡ ሲነጋ ግን መድኀኒታችን ወደ ቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻም ቆሞ ታያቸው፤ ከሚወደው ደቀ መዝሙሩ ከቅዱስ_ዮሐንስ በቀር የለየው ግን አልነበረም፡፡ ቸሩ አባት "ልጆቼ! አንዳች የሚበላ ነገር አላችሁ?" ሲል ጠየቀ፤ "ጌታ ሆይ! የለም" አሉት፡፡ "የለንም" ብሎ የሌለንን ነገር በጌታ ፊት ማመኑ እጅግ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ያጣነውን ነገር ያን ጊዜ ሊጠቁመን ቸርነቱ ብዙ ነውና፡፡ ያን ጊዜ ሐዋርያቱን መረባቸው በመርከብ ቀኝ እንዲጥሉ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም በደስታ ጣሉ፤ በአግራሞት እስኪሞሉ ድረስ መረባቸውን መሳብ አቅቷቸው ሊቀደድ እስኪደርስ ድረስ 153 ዓሦች ተያዙላቸው፡፡ ያን ጊዜም የሚወደው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችን መኾኑን ለቅዱስ ዼጥሮስ "ጌታ እኮ ነው" አለው፤ ሽማግሌው ቅዱስ ግን ራቁቱን ነበርና ወደ ባሕሩ ተወረወረ፡፡ ከአፍታ በኋላም ጌታችን ከሐዋርያቱ ጋር በድጋሚ (ለ፪ኛ ጊዜ) ለምሳ ተቀመጠ፤ ባርኮ ሰጥቶ ልባቸውን ሊያጸና አብሯቸው በላ፡፡ በዚያች ሰዓት ቅዱስ ጴጥሮስን ፫ ጊዜ "ትወደኛለህን?" ሲል ጠየቀው፤ ቅዱሱ አረጋዊም እየደጋገመ "ለሊከ ተአምር ከመ አነ አፈቅረከ (እንድወድህ አንተ ታውቃለህ)" ሲል መለሰ፡፡ ጌታም በበጐች ሐዋርያት (ካህናት)፤ በጠቦቶች አርድእት (ዲያቆናት)፤ በአባግዕት ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት (ምዕመናን ወምዕመናት) ላይ ሁሉ እረኛ እንዲሆን ሾመው፡፡ ይህ ምሥጢር ለጊዜው ጌታችን ሐዋርያትን፣ ሰብዐ አርድእትንና ሠላሳ ስድስቱን ቅዱሳት አንስት በአጠቃላይ መቶ ሃያውን ቤተሰብ እንዲጠብቅና እንዲከባከብ ቅዱስ ጴጥሮስን ማስጠንቀቁን፤ ፍጻሜው ግን የቤተ ክርስቲያን አባቶች (ጳጳሳት) መምህራንንና መላው ሕዝበ ክርስቲያንን እንዲጠብቁና እንዲያስተዳድሩ በእግዚአብሔር መሾማቸውን የሚያስረዳ ትርጕም አለው /ዮሐ.፳፩፥፩-፲፯ (አንድምታ ትርጓሜ)/፡፡ ቀጥሎም የቅዱስ ጴጥሮስን የሰማዕትነቱን ምሥጢር ገልጦለት "ተከተለኝ" (ለጊዜው በእግር፤ በኋላ ግን በግብር ምሰለኝ) ብሎታል፡፡ ወልደ ነጐድጓድ ወፍቊረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስም ሞትን እንደማይቀምስ እንዲሁ ተናግሮለታል:: ጌታ ለሐዋርያት በአንድነት የተገለጠባትን ይህች ቀን እነዚህ ሁሉ ተግባራት የተከናወኑባት ናትና (የትንሣኤ በዓል ፳፭ኛ ቀን) መሠረት በማድረግ፤ የኋላ ሊቃውንት በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን በሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት የሚሰበሰቡበት የካህናት መገናኛ ቀን ርክበ ካህናት ይሁን ብለው ወስነዋል፡፡ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብም ‹‹ሐዋርያት ሃይማኖትን ለማጽናት ከፋሲካ በኋላ በሃያ አምስተኛው ቀን እና በጥቅምት ዐሥራ ሁለት ቀን ጉባኤ እንዲካሄድ በሲኖዶሳቸው እንዳዘዙት እኔም አዝዥለሁ ›› ይላል ፡፡ መጽሐፈ ብርሃን ገጽ 185 መጽሐፍ ሲኖዶስ ላይም ‹‹ ቀኖና በእንተ ጉባኤ ›› ተብሎ ተደንግጎ እናገኝዋለን(አንቀጽ 37) ከዚህ በኋላ ርክበ ካህናት በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ፳፭ኛው ቀን፣ በበዓለ ሃምሳ እኩሌታ በዕለተ ረቡዕ ይዘከራል፤ በያዝነው ዓመት በ፳፻፲፬ ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ከተከበረበት ዕለት (ሚያዝያ 16 ቀን) ጀምሮ ብንቈጥር ፳፭ኛው ቀን ግንቦት ፱ ቀን ይኾናል፡፡ በመኾኑም የዘንድሮው ርክበ ካህናት ግንቦት 9 ቀን በዕለተ ረቡዕ ይውላል(ውሏል) ማለት ነው፡፡

ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደብረ ብርሃን፡፡ ፲፬ኛ). #ድሬዳዋ_ደብረ_ሰላም_መድኀኔ_ዓለም፤ (በዚህ ደብር ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) አድራሻው፤ ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት፥ ድሬ ዳዋ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቃሊቲ አውቶቡስ ተራ → ድሬዳዋ፡፡ ፲፭ኛ). #ጀርመን_ክሮምበርግ_ቅዱስ_ዑራኤልና_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ፤ (በጀርመን ሃገር በክሮምበርግ ከተማ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያናችን ነው፡፡) አድራሻው፤ ጀርመን ሀገረ ስብከት፥ ክሮምበርግ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → ጀርመን፡፡ ፲፮ኛ). #ዋሽንግተን_ዲሲ_ኆኅተ_ምሥራቅ_ኪዳነ_ምሕረት_ቤ/ክ፤ (በአሜሪካ ሃገር ዋሽንግተን ዲሲ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ስትኾን፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) አድራሻው፤ ዋሽንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት፥ ዲሲ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → አሜሪካ፤ ዋሽንግተን ዲሲ፡፡ ፲፯ኛ). #ርዕሰ_አድባራት_ዱባይ_ሻርጃ_አጅማን_ሰአሊተ_ምሕረት_ቅድስት_ማርያም_ቤ/ክ፤ (በዱባይ ሃገር ሻርጃ አጅማን የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ናት፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) አድራሻው፤ የባበሩት ዐረብ ኤምሬትስ ሀገረ ስብከት፥ ዱባይ ሻርጃ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → ዱባይ፡፡ ፲፰ኛ). #ደቡብ_አፍሪካ_የቅድስት_ሥላሴና_የቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (በደቡብ አፍሪካ የሚገኝ፡፡) አድራሻው፤ ደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት፥ ደቡብ አፍሪካ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → ደቡብ አፍሪካ፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ አሳውቁን) አቅጣጫ ምንጭ ዋሊ ገጽ፤

#በአዲስ_አበባ_የሚከብርበት_ #፩_ብቸኛው_ደብር፡፡ ፩ኛ). #አዲስ_አበባ_ደብረ_ይባቤ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ (ወ/ሮ ደስታ ሞላ በሚባሉ እናት በ1948 የተሠራ፤ ፈዋሽ ጠበልም አለው፡፡) አድራሻው፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ መስቀል ፍላወር (ጎተራ /አጎና ሲኒማ/፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ቦሌ/መገናኛ) → ሳሪስ በሚለው ታክሲ መስቀል ፍላወር ጋራ፤ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፲፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩ኛ). #ደብረ_ሐዊ_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (እመቤታችን በስደቷ ወቅት ያረፈችበት፤ ጃንደረባው ባኮስ የተሠወረበት፤ ቅዱስ ያሬድ ለ22 ዓመታት የመነነበት፥ ያስተማረበትና የተሠወረበት፤ በሀገራችን ትልቁ የሱባዔ መግቢያ ቅዱስ መካን፤ በዓለም ላይ በሃገራችን ብቻ፤ ከሀገራችንም በአብዛኛው በሰሜን ተራሮች ላይ ብርቅዬ ኾነው የሚገኙት ዋልያና ጭላዳ በአብዛኛው የሚገኙበት ቦታም ነው፡፡ በዚህ ቦታ ቅዱስ ያሬድ ያስተማረበትና የተማሪዎቹ ወንበር ጕባኤ ቦታና የደንጊያ ወንበር፤ ጽዮንን ከሩቅ እያየ ያለቀሰበት ቦታ ላይ የፈለቀ ጠበልና በዘንጉ ያፈለቀው ፈዋሽ ጠበል፤ የተሠወረበት የዋሻ ቤተ ክርስቲያን፣ እንዲሁም አበውና እማት የሚኖሩበት ገዳም ይገኛል፡፡) አድራሻው፤ ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጸለምት፥ በየዳ ወረዳ፤ ራስ ደጀን ተራራ አጠገብ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → ደባርቅ → በየዳ (ባኂት/ አርቋዝዬ/ጭሮ ለባ/) → በእግር፡፡ ፪ኛ). #በየዳ_ደብረ_ገነት_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ፤ (በደብረ ሐዊ ተራራ በስተጀርባ የሚገኝ ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ በደብረ ሐዊ በምናኔ እንደመኖሩ መጠን በተራራው ጀርባ በገጠሩ መንደር የሚገኙ ምዕመናን እኛም ቅዱስ ያሬድን ልንዘክረው ይገባል፤ የቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ደብረ ሐዊ ላይ ብቻ ሳይኾን በኹሉም ቦታ መኖር ይገበዋል በሚል መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሣሥተው የሠሩት ነው፡፡) አድራሻው፤ ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጸለምት፥ በየዳ ወረዳ፤ ራስ ደጀን ተራራ አጠገብ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → ደባርቅ → በየዳ (ባኂት/ አርቋዝዬ/ጭሮ ለባ/) → በእግር፡፡ ፫ኛ). #ጣና_ቂርቆስና_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ (ከፎገራ ከመንገዱ የ3 ሰዓት መንገድ እንደተጓዙ፤ በመርከብ ደግሞ ከባሕር ዳር፣ ከጎርጎራ፣ ከደልጊ፣ ከቁንዝላ ተሣፍረው ከጣና ክርስቶስ ሠምራ አጠገብ የሚያገኙት ታላቅ ገዳም ነው፤ መስዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፤ ታቦተ ጽዮን ለበርካታ ዓመታት ያረፈችበት፤ ቅዱስ ያሬድ ምልክት ያለውን ድጓ የጻፈበት ቦታ ነው) አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጸለምት፥ ፎገራ፤ ጣና ዳር፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር → ፎገራ፡፡ ወይም ከባሕር ዳር /በመርከብ/ ጣና ቂርቆስ፡፡ ፬ኛ). #ወገራ_ደልደሊት_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ፤ (በሰሜን ጎንደር ወገራ አውራጃ አምባ ጊዮርጊስ ወረዳ የሚገኝ ሲኾን፤ በቅዱስ ያሬድ ዜማ ከብቶች ሁሉ ተመስጠው ሳያርሱ በመቆማቸው ምክንያት ቅዱስ ያሬድ የተገረፈበት ቦታ ነው) አድራሻው፤ ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ወገራ፥ አምባ ጊዮርጊስ ወረዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → አምባ ጊዮርጊስ፡፡ ፭ኛ). #ደረስጌ_ወረዳ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ፤ አድራሻው፤ ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ስሜን፥ መካነ ሰላም /ደረስጌ/፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → መካነ ሰላም፡፡ ፮ኛ). #አኵሱም_ደብረ_ዝማሬ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ፤ (ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ አጠገብ የሚገኝ ሲኾን፤ የአኵሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዴት ቅዱስ ያሬድ ተወልዶ ባደገባት፥ ተምሮ ባስተማረባት፤ ሰማያዊ ምሥጢራትና በተገለጡለት፤ የተሰዓቱ ቅዱሳንን የበርካታ ቅዱሳን መናኸሪያ በኾነችው፤ የገዳማትና የአድባራት ራስ፤ የምዕመናን ሁሉ አምባ መጠጊያ በኾነችው ከተማ እንዴት መታሰቢያ ቤተ ከርስቲያን ሳይሠራለት እስካሁን ቀረ ብለው በመንፈሳዊ መነሣሣት በአጭር ጊዜ ውስጥ በዕሥራ ምዕት ማግሥት ያሠሩት ቤተ ክርስቲያን ነው) አድራሻው፤ ማዕከላዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ አኵስም ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → አኵስም፡፡ ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → በአዲዓርቃይ (በዳንሻ ሁመራ) → ሽረ → አኵሰም፡፡ ፯ኛ). #አኵሱም_ማይኪራህ_ደብረ_መድኀኒት_ወፈለገ_ጥበብ_ቅዱስ_ያሬድ_ቤ/ክ፤ (ከአኵሱም ከተማ በ4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በቅዱስ ያሬድ የትውልድ ቦታ አጠገብ በዋናው መንገድ ዳር የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ነው፤ ቅዱስ ያሬድ ከትሏ መውደቅና መነሳት በመመልከት ማስተዋልን የተማረባት ቦታ ስትሆን ሾላዋ እስካሁንም ድረስ እየተካች ትገኛለች፤ ከሾላው ሥር የሚፈልቅ ፈዋሽ ጠበልም አለ፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን የተሠራው የአኵሱም ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የደብረ ዝማሬን ቤተ ክርስቲያን ሲሰሩ የሃገሬው ሰው ተመልክቶ እንዴት የትውልድ ቦታው ላይ እኛ ቤተ ክርስቲያን ሳንሠራ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቀድመውን ሠሩ በሚል መንፈሳዊ ቅንዓት ተነሣሥጠው በተፋጠነ ሁኔታ ያነጹት ነው፡፡) አድራሻው፤ ማዕከላዊ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ አኵስም ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → አኵስም፡፡ ወይም፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር → በአዲዓርቃይ (በዳንሻ ሁመራ) → ሽረ → አኵሰም፡፡ ፰ኛ). #ጎንደር_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሩፋኤል_ወአቡነ_ሐራ_ድንግል_ቤ/ክ፤ (ይህ ቤተ ክርስቲያን በጎንደር ከተማ የሚገኝ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ ሲኾን፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፱ኛ). #ጎንደር_ጎሐ_ተራራ_ቅዱስ_ያሬድ_ገዳም፤ አድራሻው፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፥ አራዳ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲ኛ). #ባሕር_ዳር_ፈለገ_ጥበብ_ቅዱስ_ማርቆስና_ቅዱስ_ያሬድ ቤ/ክ፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ይባብ ካምፓስ አጠገብ የሚገኝ፡፡ አድራሻው፤ ምዕራብ ጎጃም (ባሕር ዳር) ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር፡፡ ፲፩ኛ). #ዳንግላ_ደብረ_ሣህል_ቅዱስ_ሚካኤል_ቤ/ክ፤ (በአዊ ሃገረ ስብከት የሚገኝ ሲሆን በዚህ ደብር ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ከ8/10/2008 ዓ.ም. ጀምሮ በድርብነት ይከበራል)፡፡ አድራሻው፤ አዊ ሀገረ ስብከት፥ ምዕራብ ጎጃም፥ ዳንግላ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → በባሕር ዳር መስመር /ዳንግላ/፡፡ ፲፪ኛ). #ሐይቅ_ደብረ_ኅሪት_ቅሌንሳ_ማርያም_፤ (ከሐይቅ እስጢፋኖስ ባሻገር የምትገኝና፤ የቅዱስ ላሊበላ አያት መሶበ ወርቅ ያነጸቻት ጥንታዊ ደብር)፡፡ አድራሻው፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሐይቅ ከተማ፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → ሐይቅ፡፡ ፲፫ኛ). #ደብረ_ብርሃን_አንሳስ_ማርያም_ቤ/ክ፤ (በደብረ ብርሃን ከተማ የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ስትኾን ፈዋሽ ጠበል ያለባትና፤ የአቋቋሙ ሊቅ፣ የቅዳሴና የሌሎች ዜማ ትምህርቶች መምህር የኾኑት የመምህር አባ ናሁ ሠናይ /መምህር ለምኔ/ ማስተማሪያ ደብር ነች፤ በዚህ ቦታ ታቦተ ቅዱስ ያሬድ ያሬድ በድርብነት ይከበራል) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ደብረ ብርሃን ከተማ፤

ይህ በዓል ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተዳድሩ የቆዩ አባቶቻችን ጌታንና ደቀ መዛሙርቱን አብነት በማድረግ በጋራ በመሰባሰብ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተቀላጠፈ አገልግሎት እንደዚሁም ለምእመናን አንድነትና መንፈሳዊ ዕድገት የሚበጁ መንፈሳውያን መመሪያዎችን የሚያስተላልፉበት እለት ነው፡፡ ይህንን የጌታችን ትእዛዝና የሐዋርያትን ሥልጣነ ክህነት መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ጉባኤ ያደርጋል፤ ፩ኛ. የመጀመሪያው ጉባኤ ጥቅምት ፲፪ ቀን (የቅዱስ ማቴዎስ በዓለ ዕረፍት) ሲሆን፣ ፪ኛ. የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን የሚደረገው ይህ ርክበ ካህናት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ቅዱስ ሲኖዶስ በሚያደርገው ጕባኤ የሚተላለፉ መመሪያዎችና የሚጸድቁ ውሳኔዎች ለቤተ ክርስቲያን ዕድገት፣ ለምእመናን አንድነት፣ ለአገር ሰላምና ደኅንነት የሚጠቅሙ ይሆኑ ዘንድ ሁላችንም በጾም በጸሎት እግዚአብሔርን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ አምላካችን ቤተ ክርስቲያናችንንና አባቶቻችንን ይጠብቅልን፤ እኛንም ለአባቶች የሚታዘዝ ልቡና፣ ሓላፊነታችንን የምንወጣበትን ጥበብና ማስተዋሉን ያድለን፡፡ ፠ጉባኤው በትላንትናው ዕለት ግንቦት 9 ተጀምራል መንፈስ ቅዱስ ይህንን ታላቅ ጉባኤ ይባርክ ይምራ፤ እኛንም ይጎብኘን፡፡ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot .YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w www.finotehiwotsundayschool.com ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

#ርክብ_ካህናት (#ዕለተ_ጥብርያዶስ፤ #ዳግሚት_ዕለተ_አግብኦተ_ግብር፤ የሃገራችን የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ ቀን)፤ ግንቦት በቤተክርስቲያን ሊቃውንት ፤ ጉባኤያት በ8 ይከፍላሉ ከእነርሱ ውስትም ‹‹ቋሚ ሲኖዶስ (Synode of Residents ) ››አንዱ ነው፡፡ አሁን ያለው የቤ.ክርስቲያነችን (የኦ.ኦ.ተ.ቤ.ክ) ሲኖዶሳዊ ደግሞ ጉባኤ ሦስት ዓይነት ነው ፡፡ 1. ዓመታዊ ፣ 2. ቋሚና 3. ድንገተኛ ጉባኤ ፡፡ ዓመታዊው ጉባኤ ጥቅምት 12 እና ትንሣኤ በዋለ በ25ኛው ቀን(በአራተኛው ሳምንት ) የሚካሄድው የግንቦት ርክበ ካህናት ይባላል፡፡ ርክበ ካህናት የሁለት ቃላት ጥምረት ሲኾን እነዚህም፤ ረክብ የሚለው ቃል ተራከበ ተገናኘ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጕሙም ማግኛ፣ መገኛ፣ መገናኛ ማለት ነው፡፡ /አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፰፴፩/፡፡ ክህነት የሚለው ቃል ደግሞ ከዲቁና ጀምሮ እስከ ከጵጵስና ድረስ ያሉትን መዓርጋት (በጥቅሉ ዲያቆናትን፣ ቀሳውስትንም ኾነ ጳጳሳትን) የሚያጠቃልል ስያሜ ነው፤ ካህን (ነጠላ ቍጥር) ሲኾን ካህናት ደግሞ (ብዙ ቍጥር) ነው፤ ብዙ ጊዜ ግን ይህን ባለማወቅ ካህናት የሚለውን ለቀሳውስት ብቻ መጠሪያ ሲኾን እናያለን፤ አለማወቅ ነው (ለምሳሌ በቅዳሴ መጨረሻ ጊዜ ዲያቆኑ በእደ … ካህን ይባርከነ ቢል ለኹሉም ያስኬዳል ሰዋስዉም ያዛል ሥርዐቱም ይኸው ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ዛሬ በእደ … ካህን ይባርከነ በማለት ፈንታ ፠( በእደ ብፁዕ ፓትርያርክ፣ በእደ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ፣ በእደ ቆሞስ…. ሲባል ይታያል፤ መስተካከል ያለበት ጉዳይ ነው፡፡)፠ ርክበ ካህናት ማለትም የአባቶች ካህናት (ማለትም በጵጵስና ማዕረግ ያሉ /ኤጲስ ቆጶሳት፣ ጳጳሳት፣ ሊቃነ ጳጳሳትና ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስን ያጠቃለለ (የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት) ጕባኤ፤ የካህናት መገኛ መገናኛ ጉባኤ (መሰባሰቢያ፣ መወያያ) ማለት ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን ሁልጊዜ በዕለተ ረቡዕ ይውላል፤ ወሩና የሚውልበት ቀን ግን በኢየዓርግና በኢይወርድ (በባሕረ ሓሳብ የበዓላትንና የአጽዋማትን ቀመር ተከትሎ) የሚወጣ ስለኾነ ከፍና ዝቅ ይላል፡፡ የአጽዋማትና የበዓላት ቀመር በቅዱስ ድሜጥሮስ አማካኝነት ከመዘጋጀቱ በፊት (ዐቢይ ጾም ሰኞ፣ ስቅለት ዓርብ፣ ትንሣኤ እሑድ፣ ርክበ ካህናት ረቡዕ፣ ዕርገት ሐሙስ፣ ጰራቅሊጦስ እሑድ እንዲሆን ከመደረጉ በፊት( መሉ ማብራራይ ሰሙነ ሕማማት የጻፍናን ይመልከቱ ) ርክበ ካህናት በየዓመቱ ግንቦት ፳፩ ቀን ይውል ነበር /መጽሐፈ ግጻዌ ግንቦት ፳፩/፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጐ ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ በየጸጋቸው መጠን እየተገለጠ ያጽናናቸው፥ ያጸናቸው፥ ያስተምራቸው፥ ይባርካቸውም ነበር፤ ጌታችን እስከ ዕርገቱ ባሉ ፵ ቀናትም መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን፣ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን አስተምሯቸዋል፤ በልቡናቸውም አሳድርድሮባቸዋል:: በመጽሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል ከዕርገቱ አስቀድሞ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ፫ ጊዜ በጉባኤ መገለጡ ተዘግቦ ይገኛል፡፡ እነዚህም፤ 1. የትንሳኤ (ዮሐ. 20፥19) 2. የአግብኦተ ግብር (ዳግም ትንሳኤ) /ዮሐ. 20፥:26/ 3. የጥብርያዶስ፤ (ዮሐ. 21፥1) ፡፡ ለድንግል ማርያም ግን በኹሉም እለታት መገለጡን አበው ያስተምራሉ፡፡ በጥብርያዶስ ባሕርም ከዐሥራ አንዱ ቅዱሳን ሐዋርያት ጋር ምሳ በልቷል፡፡ የርክበ ካህናት በዓል መነሻም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከተገለጠበት ከጥብርያዶስ ባሕር ካለው ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህች ዕለት በቅዱስ ጴጥሮስ መሪነት ሐዋርያቱ ወደ ጥብርያዶስ ባሕር ሔዱ፡፡ ዓሶችን ሊያጠምዱም በብዙ ደከሙ፤ ነገር ግን ጌታችን በረድኤት አብሯቸው አልነበረምና አንዳች አሣ በመረባቸው ሊገባ አልቻለም፡፡ ማጥመድ (አስተምሮ ከክህደት ወደ ሃይማኖት፤ ከኀጢአት ወደ ጽድቅ መመለስ) የሚቻለው በረድኤተ እግዚአብሔር እንጂ በእውቀት ብዛት ወይም በአንደበተ ርቱዕነት ብቻ አይደለምና፡፡ ሲነጋ ግን መድኀኒታችን ወደ ቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻም ቆሞ ታያቸው፤ ከሚወደው ደቀ መዝሙሩ ከቅዱስ_ዮሐንስ በቀር የለየው ግን አልነበረም፡፡ ቸሩ አባት "ልጆቼ! አንዳች የሚበላ ነገር አላችሁ?" ሲል ጠየቀ፤ "ጌታ ሆይ! የለም" አሉት፡፡ "የለንም" ብሎ የሌለንን ነገር በጌታ ፊት ማመኑ እጅግ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ያጣነውን ነገር ያን ጊዜ ሊጠቁመን ቸርነቱ ብዙ ነውና፡፡ ያን ጊዜ ሐዋርያቱን መረባቸው በመርከብ ቀኝ እንዲጥሉ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም በደስታ ጣሉ፤ በአግራሞት እስኪሞሉ ድረስ መረባቸውን መሳብ አቅቷቸው ሊቀደድ እስኪደርስ ድረስ 153 ዓሦች ተያዙላቸው፡፡ ያን ጊዜም የሚወደው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችን መኾኑን ለቅዱስ ዼጥሮስ "ጌታ እኮ ነው" አለው፤ ሽማግሌው ቅዱስ ግን ራቁቱን ነበርና ወደ ባሕሩ ተወረወረ፡፡ ከአፍታ በኋላም ጌታችን ከሐዋርያቱ ጋር በድጋሚ (ለ፪ኛ ጊዜ) ለምሳ ተቀመጠ፤ ባርኮ ሰጥቶ ልባቸውን ሊያጸና አብሯቸው በላ፡፡ በዚያች ሰዓት ቅዱስ ጴጥሮስን ፫ ጊዜ "ትወደኛለህን?" ሲል ጠየቀው፤ ቅዱሱ አረጋዊም እየደጋገመ "ለሊከ ተአምር ከመ አነ አፈቅረከ (እንድወድህ አንተ ታውቃለህ)" ሲል መለሰ፡፡ ጌታም በበጐች ሐዋርያት (ካህናት)፤ በጠቦቶች አርድእት (ዲያቆናት)፤ በአባግዕት ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት (ምዕመናን ወምዕመናት) ላይ ሁሉ እረኛ እንዲሆን ሾመው፡፡ ይህ ምሥጢር ለጊዜው ጌታችን ሐዋርያትን፣ ሰብዐ አርድእትንና ሠላሳ ስድስቱን ቅዱሳት አንስት በአጠቃላይ መቶ ሃያውን ቤተሰብ እንዲጠብቅና እንዲከባከብ ቅዱስ ጴጥሮስን ማስጠንቀቁን፤ ፍጻሜው ግን የቤተ ክርስቲያን አባቶች (ጳጳሳት) መምህራንንና መላው ሕዝበ ክርስቲያንን እንዲጠብቁና እንዲያስተዳድሩ በእግዚአብሔር መሾማቸውን የሚያስረዳ ትርጕም አለው /ዮሐ.፳፩፥፩-፲፯ (አንድምታ ትርጓሜ)/፡፡ ቀጥሎም የቅዱስ ጴጥሮስን የሰማዕትነቱን ምሥጢር ገልጦለት "ተከተለኝ" (ለጊዜው በእግር፤ በኋላ ግን በግብር ምሰለኝ) ብሎታል፡፡ ወልደ ነጐድጓድ ወፍቊረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስም ሞትን እንደማይቀምስ እንዲሁ ተናግሮለታል:: ጌታ ለሐዋርያት በአንድነት የተገለጠባትን ይህች ቀን እነዚህ ሁሉ ተግባራት የተከናወኑባት ናትና (የትንሣኤ በዓል ፳፭ኛ ቀን) መሠረት በማድረግ፤ የኋላ ሊቃውንት በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን በሁሉም ሊቃነ ጳጳሳት የሚሰበሰቡበት የካህናት መገናኛ ቀን ርክበ ካህናት ይሁን ብለው ወስነዋል፡፡ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብም ‹‹ሐዋርያት ሃይማኖትን ለማጽናት ከፋሲካ በኋላ በሃያ አምስተኛው ቀን እና በጥቅምት ዐሥራ ሁለት ቀን ጉባኤ እንዲካሄድ በሲኖዶሳቸው እንዳዘዙት እኔም አዝዥለሁ ›› ይላል ፡፡ መጽሐፈ ብርሃን ገጽ 185 መጽሐፍ ሲኖዶስ ላይም ‹‹ ቀኖና በእንተ ጉባኤ ›› ተብሎ ተደንግጎ እናገኝዋለን(አንቀጽ 37) ከዚህ በኋላ ርክበ ካህናት በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ፳፭ኛው ቀን፣ በበዓለ ሃምሳ እኩሌታ በዕለተ ረቡዕ ይዘከራል፤ በያዝነው ዓመት በ፳፻፲፬ ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ከተከበረበት ዕለት (ሚያዝያ 16 ቀን) ጀምሮ ብንቈጥር ፳፭ኛው ቀን ግንቦት ፱ ቀን ይኾናል፡፡ በመኾኑም የዘንድሮው ርክበ ካህናት ግንቦት 9 ቀን በዕለተ ረቡዕ ይውላል(ውሏል) ማለት ነው፡፡

መ. የቅዱስ ያሬድ ዜማ ጥቅም ሀ. የቤተ ክርስቲያንን አንድነት በመጠበቅ፤ በየትኛውም አካባቢ የምትኖር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አንድ ዓይነት መዝሙር፣ አንድ ዓይነት ቅዳሴ፣ አንድ ዓይነት ማኅሌት፣ አንድ ዐይነት ሥርዐት በአንድ ዓይነት ጊዜ በአንድ ቀን ማቅረብና መፈጸም እንድትችል አስችሏታል፡፡ ለ. በነገረ መለኮት ትምህርት፤ ሊቁ የትርጓሜ መምህር ስለሆነ ከብዙ መጻሕፍት ስለሚጠቅስና የሃይማኖት ትምህርቱትንም በዜማ አቀነባብሮ መድረሱ በጣም ተወዳጅ ትምህርት እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ሐ. በሥርዓተ ጸሎት፤ ከዓመት እስከ ዓመት ለሚከናወኑ (የዘመናትና የሳምንታትን ጨምሮ) ማንኛውም ሥርዐተ ጸሎት ዋና መሪው የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ነው፡፡ ማኅሌቱ፣ ቅዳሴው፣ ፍትሐቱ፣ ጥምቀተ ክርስትናው ሁሉ በዜማው መሪነት የሚከናወኑ አገልግሎቶች ናቸው፡፡ መ. ለቱሪዝም ሀብት (መስህብነት)፤ ክርስቲያናችን በየወሩና በየዓመቱ ከምታከብራቸው በዓላት ላይ ከሚቀርቡት ዝግጅቶች አብዛኛውን ክፍል የሚይዘው በቅዱስ ያሬድ ዜማ የሚቀርበው የዝማሬና የቅዳሴ አገልግሎት ነው፡፡፠፠፠፠ ከታች በፍቶ የምትመለከቷቻ አድባራትናደ ገዳማት በዓሉ የሚከብርባቸው ናቸው /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ፤ ትምሕርት ዋና ክፍል ፥ ንዑስ ክፍል /ሕትመት እና ሚዲያ/ የተዘጋጀ :: #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት .

#የቅዱስ_ያሬድ_አስደናቂ_ነገሮች ፠#ከጌዴዎን ዘንድ ትምህርቱን አቋርጦ ሄደ ስንል፤ በአንድ ሾላ ዛፍ ላይ በትል አማካይነት ትዕግስትንና ማስተዋልን ቀስሞ፤ ወደ አጎቱ ተመልሶ ተምሮና ትምህርትን አምላክ ገልጾለት መምህረ መምህራን ሁኖ እንገኘዋለን፤ /እግዚአብሔር አምላክ ለቅዱስ ያሬድ ያንን ኹሉ ጥበብ ቶሎ ያልገለጸለት በቀላሉ ቢያገኘው ኋላ እንዳይታበይ ብሎ ነው፤ የሐዊራ ብስድር እስክንድራን ታሪክ ልብ ይሏል) ፠#መምህር ነው ስንል፤ መናኝ ባሕታዊ ኾኖ እናገኘዋለን፤ /በደብረ ሐዊ ለ22ዓመታት መመኑን ልብ ይሏል/ ፠#መናኝ ነው ስንል የተለያዩ የሃገራችንን ክፍሎች ገዳማትና አድባራት ሲጎበኝ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ሲጓዝ እንገኘዋለን፤ /ጣና ቂርቆስ፤ ዙር አባ አቡነ አረጋዊ፣ …. ሌላውንም ልብ ይሏል) ፠#ወደ ገዳማትና አድባራት ይጓዛል ስንል፤ ወደ ደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ በደመና ተጭኖ ሂዶ ምሽቱን ወደ በዓቱ ሲመለስ እንገኘዋለን፡፡ ፠#በሃገራችን በዋና ከተማ አኵሱም ተወልዶ ያደገ ነው ስንል፤ ሰው ሊኖርበት በማይችለው፥ በረድ በሚፈላበት፥ የነፋስ እሩምታ በሚያይልበት፥ ቅዝቃዜው አጥንት በሚሰነጥቅበት፥ ውርጩ እጅጉን በሚቀዘቅዝበት፥ ደመና በሚፈስስበት በራስ ደጀን ተራራ አጠገብ በደብረ ሐዊ መንኖ እናገኘዋለን፡፡ ፠#ከሰዎች ጋር አብሮ ኑሯል ስንል፤ ከሰው የማይቀርቡና በዐለማችን ላይ ብርቅዬ ኾነው በሃገራችን የሚገኙ ከሃገራችን ኢትዮጵያም በሰሜን ተራሮች በአብዛኛው ከሚገኙት ዋልያ ጋር አብሮ ሲኖር፤ ዋልያዎችንም እንደ መጓጓዣና እንደ መጫኛ ሲያገለግሉት እንገኛለን፡፡ ፠#በሙራደ ቃል የመላእክት ዜማ ተገልጾለት ተማረ ስንል፤ የግእዝ ቋንቋ ምሁርና ጠበብት ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ለተሰዓቱ ቅዱሳን መምህር መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#የዜማ ጀማሪ አባት ነው ስንል ባለቅኔ ኾኖ እንገኘዋለን (ሕንፄሃ ወሡራሬሃ …. የሚለው ቅኔውን ልብ ይሏል)፤ ፠#ባለቅኔ ነው ስንል መተርጕም ኾኖ እንገኘዋለን፤ (ድጓው የብሉይና የሐዲስ ትርጓሜ መሆኑን ልብ ይሏል) ፠#መተርጕም ነው ስንል ባለታሪክ፥ የታሪክ ምሁር ኹኖ እናገኘዋለን፤ ፠#የታሪክ ምሁር ነው ስንል፤ የመርሐ አዝማን ሊቅ ኹኖ እናገኘዋለን፤ (ዓመቱን በሚገርም ሁኔታ ከወቅታቱ ጋራ አገናዝቦ መሠየሙን ልብ ይሏል) ፠#የመርሐ አዝማን ሊቅ ነው ስንል ቅዱስ ኾኖ እንገኘዋለን፤ የቅዱሳንም ጓደኛ ኹኖ እንገኘዋለን፡፡ /የአቡነ አረጋዊ፣ የአጼ ገብረ መስቀልን ታሪክ ልብ ይሏል፡፡/ ፠#ነቢይ ነው ሰንል ሐዋርያ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ (ስለ ዳግም ምጽአት፣ ስለ መንግሥተ ሰማያትና …. ሌሎችንም ልብ ይሏል) ፠#ሐዋርያ ነው ስንል ሰማዕት ኹኖ እናገኘዋለን፡፡ (እግሩን በጦር መወጋቱን ልብ ይሏል)፤ ሌላም ሌላም …. ፠#በአጠቃላይ ምድራዊ ነው ስንል ሰማያዊ፤ ሰማያዊ ነው ስንል ምድራዊ (ብእሲ ሰማያዊ ወመልአክ ምድራዊ) ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ #ዜማውን በግዕዝ ዕዝል አራራይ የዜማ ስልት የደረሰ፤ #በዓለም ደረጃ የዜማ ምልክቶች ባልታወቁበት ጊዜ ዜማዎቹን በምልክት የቀመረ፤ #የዜማ ሥርዓትን በመንደፍ የዓመቱን ቀለም ያዘጋጀ፤ #ዜማውን በ4ት ዘመናት ከፋፍሎ፤ ዘመናቱን በንዑሳን ዘመናት ከፋፍሎ ለወራቱና ለሰሙኑ ለእለቱ የሚገባውን ቀምሮ የደረሰ፤ #እንኳን በእርሱ ዘመን ዛሬ እንኳን ብዙ ነገሮች ተሰባስበዋል በተባለበት ዘመን ሊሠራ አይደለም ሊታሠብ በማይችሉ መልኩ መጽሕፍትን እንደ ንብ እየቀሰመ፤ እንደ ወይን እየጨመቀ፤ እንደ አረቂ እያጣራ፤ እየተረጐመ ላሰበው ድርሠት ያዋለ፤ … ስለ ቅዱሱ ምኑን ተናግረን እንጨርሰዋለን፡፡ … ##.. ይኼማ ኢትዮጵያዊ ሊኾን አይችልም ብለው ብዙ የውጭ ሃገራት ወደ ራሳቸው ለመውሰድ የሚዳዳቸው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ የቅዱስ ያሬድ የዜማው ይዘት ፤ የዜማውጠባያት_፤ ከሌሎች ዓለማዊ ዜማዎች የሚለይበት ጠባይና የዜማው ጥቅም ሀ የቅዱስ ያሬድ የዜማው ይዘት ፠ቅዱስ ያሬድ ዜማውን ያዘጋጀው ከብሉያት፣ ከሐዲሳት፣ ከሊቃውንት መጻሕፍት እየመረጠ ለምስጋናና ለጸሎት እንዲኾኑ አድርጎ ነው፡፡ ፠ዜማው ምስጢሩ የማይጠገብ፥ቃሉ የሚያረካ፥ አነጋገሩ የተሳካ፥ ጣዕመ ቃሉና ኀይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ፥ ልብን የሚነካ ነው፡፡ ፠በይዘቱም የሥነ ፍጥረት ውበትን በማድነቅና የሥነ ፍጥረት አስገኝ የኾነውን እግዚአብሔርን በማመስገን ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ፠በአጠቃላይ የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ጌታ ለሰው ልጆች ሲል በዚህ ዓለም የፈጸመውን የማዳን ሥራ ሁሉ ገልጦ የሚያስረዳ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያምን፣ የቅዱሳን መላእክትን፣ የነቢያትን፣ የሐዋርያትን፣ የጻድቃንና የሰማዕታትን ክብርና ቅድስና በማውሳት በስማቸው መማፀንና መጸለይ የሚያስገኘውን ጥቅም የሚያስረዳ ታላቅ ዜማዊ ሀብት ነው፡፡ ፠ከእርሱ በፊት የነበሩና በእርሱ ዘመን የተጻፉ የቅዱሳን ገድላትና ድርሳናትን እንዲሁም የበዓላትን ጥንታዊ አመሠራረት ውስጠ ምሥጢር በማስረዳት በዜማ ድርሰቱ አካቷል፡፡ ፠ምስጋናውንም ለአራቱ ክፍላተ ዘመን ለክረምት፣ ለመፀው (ለጥቢ)፣ ለሐጋይ (ለበጋ)፣ ለጸደይ (ለበልግ) እንዲኾን አዘጋጅቶታል፡፡ ለ የዜማው ጠባያት ፨የቅዱስ ያሬድ ዜማ ሰማያዊ በመኾኑ ኅሊናን የመመሠጥ፣ ሥጋዊ ደስታንና ኀጢአትን ከማሰብ የመጠበቅ፣ ሰማያዊውን ድንቅ የምስጋና ምስጢር የማሳወቅ ኀይል አለው፡፡ ፨ከእግዚአብሔር የተገኘ ስጦታም በመኾኑ ብልየት (እርጅና)፣ ውላጤ (መለወጥ) የማይታይበት ዘወትር ሕያው የኾነ ብቸኛ ዜማ ነው፡፡ ፨የመንፈስ ቅዱስ ስጦታም በመኾኑ ዘወትር አዲስና የማያልቅ ጥልቅ ምንጭ ያለው ሕይወትን የሚያለመልም ነው፡፡ ፨ዜማውም ሰማያዊና መንፈሳዊ፣ ከእግዚአብሔር የተገኘ ለመኾኑ ማስረጃ የሚኾነን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ውጪ ያሉ ሰዎች ዜማውን ለተለያየ ዐላማ ይመኙታል፤ ነገር ግን ለመያዝም ኾነ ለመወሰን አይችሉም፡፡ ምክንያቱም በምድራዊ ጥበብና ፍልስፍና የሚያዝ የሚወሰን ሳይኾን ታላቅ መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ፣ ሌት ተቀን ልቡናን ለሥላሴ ሰጥተው ከእግዚአብሔር የሚያገኙት በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያጸኑት፣ የሚማሩትና የሚያዜሙት እንጂ በገንዘብ የማይገዛ ታላቅ ጸጋ መኾኑ ነው፡፡ ሐ.የቅዱስ ያሬድ ዜማ ከሌሎች ዓለማዊ ዜማዎች የሚለይበት ጠባይ፤ ዜማው አሳብን የሚገዛ፣ ከሥጋ ይልቅ በመንፈስ መመላለስን የሚያስተምር በመኾኑ፤ በአቀራረቡም የተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ያለው በመኾኑ፤ ዜማው በአዝማናት ተለይቶ በወቅት ተከፋፍሎ የሚዜም መኾኑ፤ ማንኛውም ሰው ከተወሰነ የዜማ ስልትና ቀመር ውጪ በራሱ ፍላጎት የድምፅ ቅላጼውን ለማሳመር ስለፈለገ የሚያሻሽለው ወይም የሚለውጠው አለመኾኑ፤ ዜማው በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ምሥጢር የተሞላ መኾኑና የዜማው ምልክቶችና ዐይነቶች ጥልቅ ምሳሌና ምስጢር ያላቸው መኾናቸው ነው፡፡

#ማሕሌቱን_ለማሕሌት_አባት_እናቅርብለት:: ግንቦት 11 በዓለ ሥዋሬው ለቅዱስ ያሬድ በዚህችም ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተሰወረበት ቀን ነው። የቅዱስ ያሬድ መጠሪያ ስሞች ሥርዐተ ማኅሌት ዘግንቦት ፲፩ ፠የቅዱስ ያሬድ ልደትና የስሙ ትርጓሜ ፠የቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች፤ ፠የቅዱስ ያሬድ አስደናቂ ነገሮች ፠የቅዱስ ያሬድ የዜማው ይዘት ፤ የዜማው ጠባያት ፤ ከሌሎች ዓለማዊ ዜማዎች የሚለይበት ጠባይና የዜማው ጥቅም ፠፠፠፠፠የቅዱስ ያሬድ ሌሎች መጠሪያ ስሞች ፠፠፠ ጥዑመ ልሳን፤ ፠ የሱራፌል አምሳያ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤ ፠ መዓርዒረ ዜማ፤ ፠ ካህን (ካህነ ስብሐት) ፠ ማኅሌታይ፤ ፠ መዘምር ዘበድርሳን፤ ፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት) ፠ ዓርከ ሊቃውንት፤ ፠ ደራሲ፤ ፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ) ፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤ ፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ ፠ ልዑለ ስብከት፤ ፠ ሰማዕት፤ ፠ ባሕታዊ፤ ፠ መናኝ ፠ የዜማ አባት፤ ፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡ ፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ:: ፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ ፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ:: ፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ:: ፠ አእምሮው የመጠቀ፤ ፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤ ፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …... #ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘግንቦት_፲፩ /ማኅሌቱን በአ.አ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ የምትቆሙ በደብረ ይባቤ የሚለውንና በሰማየዊ ቀለም የተቀባውን እየመረጣችሁ መጠቀም ስትችሉ፤ በሌሎች አድባራት ግን ሰማያዊ ቀለም የሌለበትን (በቢጫና እንዲሁ ያለቀለም የተቀመጠውን) እየመረጣችሁ መጠቀም ትችላላችሁ፡፡/ #የቅዱስ_ያሬድ_ልደትና_የስሙ_ትርጓሜ ꔰ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ሚያዚያ 5 ቀን በ505 ዓ.ም. ከአባቱ ይስሐቅ(አብድዩ) ከእናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) በአኵሱም ከተማ ተወለደ፡፡ (አንዳንዶች ልደቱን 493 ዓ.ም. ነው ይላሉ፤ እንዲሁም አባቱ ኖኅ ነው ይሉና መሪጌታ ይስሐቅ የቀለም አባቱ /መምህሩ/ ነው ይላሉ፡፡) ꔰ የስሙም ትርጓሜም ያሬድ ማለት እንዚራ፣ በገና፣ መሰንቆ ማለት ነው ፡፡ እነዚህ መሣሪያዎች በስልት በስልት ሲመቱ ለሚሰማቸው ደስ እንዲያሰኙ የያሬድም ዜማ በንጉሠ ነገሥቱ ክርስቶስ አደባባይ በቤተ ክርስቲያን ሲሰማ መላእክትን፥ ሰውንና እንስሳትን ደስ ያሰኛልና፡፡ አንድም ያሬድ ርደት፣ ወሪድ፤ መውረድ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ሰማያዊውን ልዩ ጣዕመ ዜማ ወደ ኢትዮጵያ አውርዷልና፡፡ * አንድም ያሬድ ማለት ንብ ማለት ነው፤ ንብ የማይቀስመው አበባ እንደሌለ ሁሉ ቅዱስ ያሬድም ከመጻሕፍት የማይጠቅሰው የማይቀሰመው የለም፤ አንድም ያሬድ ማለት ረአዬ ምሥጢር፥ ነጻሬ ኅቡአት ማለት ነው፤ የመላእክት ምሥጢራት የነበሩትን ጸዋትወ ዜማ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯልና፣ ነጻሬ ኅቡአት አለ፥ ኅቡእ (ስውር) የሆነ የጻድቃን፣ የሰማዕታት የነቢያት የሐዋርያትን ገድል አምልቶ አስፍቶም ይናገራልና፡፡ *** አፄ ካሌብ ቤተ እስራኤል፣ ገብረክርስቶስና ገብረ መስቀል የሚባሉ ልጆች ነበሩት፤ ቅዱስ ያሬድ የተነሳው ከእነዚህ ውስጥ በአፄ ገብረመስቀል ዘመን ነው፡፡ #የቅዱስ_ያሬድ_ድርሰቶች፤ ** ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ፤ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ፤ በከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ፡፡ #፩ኛ) ምዕራፍ (ውዳሴ ማርያም በዜማን፣ መስተጋብዕ፣ አርባዕት፣ አርያም፣ ሠለስት፣ ክስተተ አርያምን) ያጠቃልላል፡፡ ፠ የውዳሴ ማርያም ዜማ ቅዱስ ኤፍሬም ሦርያዊ የደረሰውን ለቅዱስ ያሬድ እየነገረው ልብን የሚመስጥ ዜማ ደርሶለታል፡፡ ፠ መስተጋብዕ፤ ስብስብ ማለት ሲኾን፡፡ ከዳዊት መዝሙር (ከ180ው የመስተጋብእ ድርሰት 1ድ ድርሰት በስተቀር) ለጸሎትና ለዝማሬ ተስማሚ የኾነው እየተውጣጣ ለመዝሙር ተስማሚ የኾነው የተቀመረ ነው፡፡ መስተጋብዕ ሲጀምር ‹‹ወለቡ ጽራኅየ (ጩኸቴን ልብ አድርግ›› ብሎ ነው፡፡ በዐቢይ ጾም ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ጠዋት ይዘመራል፤ የቀድሞ መምህራን በፍልሠታም ይዘምሩት ነበር፤ ዜማው በዋነኛነት በግዕዝና በዕዝል ሲኾን በአራራይ ከሐሙስ ‹‹አንተሰ እግዚኦ ለዓለም›› የሚለውና ከቅማዴ ‹‹መንግሠትከሰ መንግሥት›› የሚለው ይገኙበታል፡፡ በየእለቱ እንዲደርስ (ከእሑድ በስተቀር) አድርጎ የደረሰው ነው፤ ፠ አርባዕት፤ አራት አራተኛ ማለት ሲን በዳዊት መዝሙር በአራተኛው መሥመር ውስጥ እየገባ የሚዘመር ነው፤ ‹‹ቃልየ አጽምእ እግዚኦ ወለቡ ጽራኅየ፤ ወአጽምአኒ ቃለ ስእለትየ፤ ንጉሥየኒ ወአምላኪየኒ፡፡ ከፈጸመ በኋላ አርባዕት ይገባል፡፡ አርባዕት ሲጀመር ‹‹ቃልየ፤ ከመ ያፈቅርለ ጐሥዓ፤ ዐቢይ፤ ተሣሃለኒ›› ብሎ ነው (በዳዊት መዝሙር ጀምሮ ቀጥሎ በቅዱስ ያሬድ ድርሠት በኾነው በአርባዕት ያጠናቅቃል፡፡አብዛኛው በግጥም መልክ የተቀመረ ሲኾን አልፎ አልፎም በስድ ንባብ መልክ ይገኛል፡፡ ግእዝ ዕዝልና አራራይ ዜማ አለው፡፡ ፠ አርያም፤ አርያም ልዑል፥ ከፍተኛ ማለት ሲኾን፤ ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ሰምቶ ‹‹ቀዳሚ ዜማ፤ አንድም ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ›› ስላመጣው ነው፡፡ ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብሎ የግጥም መል ባለው አእያም በተባለው ይጀምራል፡፡ በግጥም መልክና በስድ ንባብ ሲገኝ የግጠም አገጣጠሙ ከፍ ያለ የግጥም አገጣጠምን የተከተለነው፡፡ የሚባልበት ጊዜ በጾም ጊዜ በጾመ ድጓው እየገባ፣ በተለይ ደግሞ በክብረ በዓል ክሥተተ አርያም ሲደርስ ይዘመራል፡፡ ሠለስት፤ ስምዐኒ ብሎ የሚጀምር ባለ ብዙ ሃሌታ ያለው፤ በዳዊት መዝሙር በሦስተኛው መሥመር እየገባ የሚዘመር፤ አንድም 3 መዝሙሮች ብቻ የሚዘመሩለት ብዙውን ጊዜ በግጥም የሚቀርብ ሲኾን፤ ይኽ ዜማ የሚደርሰው በክብረ በዓላት ዋይዜማ፤ በስብሐተ ነግህ፣ በአርያም፣ በጾመ ድጓ ውሎ፣ በአርያም፣ በሰንበት፣ በፍትሐት ጊዜ ነው፡፡ ክስተተ አርያም፤ የሰማይ መከፈት ማለት ሲኾን በታላላቅ በዓል ቀን እንዲሁም ታላላቅ? ሰዎች ሲሞቱ የሚዘመር ነው፤ ክስተትን ቅዱስ ያሬድ ያዘጋጀው ከዳዊት መዝሙራት፥ ከጸሎተ ነቢያትና ከራሱም ጭምር ኀይለ ቃል ያላቸውን ባለሁለት መስመሮች ሐረግ በመውሰድ ሲኾን ዜማው እጅጉን ነፍስና ሥጋን፥ ልብንና ኅሊናን የሚመስጥ ነው፡፡ ፪ኛ) ጾመ_ድጓ፤ በዐቢይ ጾም የሚባል ነው፡፡ ፫ኛ) ድጓ፤ በ4ት ክፍላተ ዘመናት የተቀመረና ጾመ ድጓን በውስጡ የሚያካትት ነው፡፡ ፬ኛ) ዝማሬ፤ ቅዱስ ቊርባን ድርገት ሲወርድ ለቅዱስ ቊርባን ክብር የሚዘመር ነው፡፡ ፭ኛ) መዋሥዕት፤ ሰው ሥጋው ከነፍ ስትለይ ፍትሐት የሚደረግበት ጸሎት ነው፡፡ ፮ኛ) የ፲፬ቱ ቅዳሴያት ዜማ፤ 14ቱን ቅዳሴያት 14ት አባቶች የደረሷቸው ቢሆንም ዜማ የደረሰላቸው ግን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ፯ኛ) አንቀጸ ብርሃንን፤ ድርሰቱ ነው፡፡ /ይቀጥላል……/ በተጨማሪም ደግሞ፤ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ዐይነቶች ግእዝ፣ ዕዝልና ዓራራይ በመባል ይታወቃል፡፡እነዚህ የዜማ ዐይነቶች የአንዱ ድምፅ ከሌላኛው ድምፅ ያልተደባለቀ፣ ወጥ የሆነ ድምፅ አላቸው፡፡ በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ትርጉም ያላቸው በሆኑ የዜማ ምልክቶች (ድፋት፤ ሂደት፤ ቅናት፤ ይዘት፤ ቁርጥ፤ ጭረት፤ ርክርክና ደረት) ደርሷል፡፡ የቅኔ ጀማሪም ነው፡፡ ‹‹ሕንፄሃ …›› የሚለውን ቤት መምቻ ያለውን ቅኔ ልብ ይሏል፤ አንድ ባለቅኔ ግን ይህን ሳይረዳ ‹‹ተትሕተ ያሬድ …›› የሚል ቅኔን ተቀኝቷል፡፡

ሰላመ ዕብል ለመልክአክሙ መክብበ ፤ እንተ ይሠረጉ ላህበ፡፡ አርባዕቱ እንስሳ ዘትሰመዩ ኪሩበ፤ ጸሎትየ በቅድሜክሙ እመ ሞገሰ ረከበ ፤ ኑኃ መዋዕል ጽግወኒ አስበ፡፡ https://youtu.be/KrUaSIJ9_98

https://youtu.be/KrUaSIJ9_9 ..... ፰...... በዓለ ኪሩብል (አርባዕቱ እንስሳ) ሰላመ ዕብል ለመልክአክሙ መክብበ ፤ እንተ ይሠረጉ ላህበ፡፡ አርባዕቱ እንስሳ ዘትሰመዩ ኪሩበ፤ ጸሎትየ በቅድሜክሙ እመ ሞገሰ ረከበ ፤ ኑኃ መዋዕል ጽግወኒ አስበ፡፡ #share Contact: https://t.me/finotehiwot1927 .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) Telegram (https://t.me/finotehiwot1927) ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት.ቤት https://youtu.be/KrUaSIJ9_9

የእርዳታ ጥሪ ደ/ነ/ቅ/ዮሐንስ እና መ/ጎ/ቅ/ማርያም ቤ/ክ የፍቁረ እግዚእ ሰ/ት/ ቤት አገልጋይ የሆነችው አባይነሽ አበበ ወልደ በደረሰባት የጡት ካንሰር ህመም ምክንያት በአስቸኳይ የጨረር ህክምና መግኘት እንዳለባት የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እርዳታ ማግኝት እንዳለባት የአስታውቋል፡፡ በዚህ ሰዓትም ለጨረር ህክምናው አቅም ስለሌላት የተቻላቹሁን ያክል እንድትረዷት ቅዱስ ዮሐንስ ስም እንጠይቃለን፡፡ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000183883457 | አባይነሽ አበበ ጎሹ ስልክ ቁጥር | 0910 59 86 23 https://youtu.be/lTV_LiajQTk