en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 336 subscribers, ranking 5 643 in the Religion & Spirituality category and 2 190 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 336 subscribers.

According to the latest data from 13 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -75 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 22.35%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.54% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 428 views. Within the first day, a publication typically gains 1 616 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 25.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 14 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 336
Subscribers
+224 hours
-47 days
-7530 days
Posts Archive
#ለየካቲት_12_መዳረሻ፥ #ለየካቲት_23_መነሻ፥ #ለሚያዝያ_27_ማስታወሻ የአውሮፓ ኃያላን ሃገር ነን ብለው ራሳቸውን የሰየሙ አፍሪካን ሊቀራመቱ በተስማሙት መሠረት ጣሊያን ኢትዮጵያን ልትቀራመት ወሰኑ፡፡ ለዚህም ውሳኔ ያደረሳቸው ከሚስዮኖቿ አንዱና ተኩላው አባ ማስያስን(የጣሊያ ንጉሥ የቪክቶሪ ንስሐ አባትን ቀድሞ በትንሹ ራስ ዐሊ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የገባው) በአፄ ቴዎድሮስ ተባሮ፤ እንደገና በአፄ ዮሐንስ ዘመን ወደ ሃገራችን ገብቶ ነበር፤ አሁንም መልሰው አፄ ዮሐንስ ሲያብርሩት ለጣሊያን መንግሥት የኢትዮጵያን ልዩ መልክአ ምድሮችና በዓለም ላይ ልዩ ሃገር መሆኗን 2ት መጻሕፍት ጽፎ ለጣሊያን መንግሥት በማስረከቡ በዚሁ መሠረት ጣሊያኖች በመቋመጣቸው ነው፡፡ #የመጀመሪያው_ወረራና_ጦርነት መጀመሪያ በ1861ዓ.ም. እግሯን ወደ ኢትዮጵያ በአሰብ በኩል አስገባች፤ በ17ዓመታት ቆይታ(እስከ 1878ዓ.ም.) ምጽዋን፣ የዳህላክ ደሴቶችንና የኤርትራን ቀይ ባሕር ያዘች፡፡ ምጽዋን በያዘ በ3ት ዓመታት ኤርትራን ያዘች፤ ኤርትራን በያዘች በ7 ዓመት መረብን ተሻግራ ወደ ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመግባት ጦርነት ከፈተች፡፡ ከኤርትራ ሲሻገሩ መጀመሪያ ጦርነት ያደረጉት በ1887ዓ.ም. በወርኃ ጥር በዶጋሊ ከአጼ ዮሐንስ ጦር አበጋዝና ከሐማሴኑ ባላባት ከጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋ ጋር ነው፡፡ ጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋም ጠላትን ድል በማድረግ ወደ ምጽዋ መልሰውታል፡፡ ለራስ አሉላ አባ ነጋም እንዲህ ተብሎ ተግጠሞላቸዋል፡፡ ‹‹የአሉላ ፈረስ የረገጣቸው፤ እስካሁን ድረስ አለ ቊስላቸው፡፡ የአሉላ ፈረስ ተስቦ ወርዶ፤ ያንን ነጭ ገብስ አረገው ነዶ፡፡›› ይህ አልሆን ሲላቸው በተወካያቸው በአንቶኔሊ በሚያዝያ 25/1881ዓ.ም. በውጫሌ (ወሎ ቦሩ ሜዳ የምትገኝ) ላይ የተፈረመውን የውል ስምምንት አንቀጽ 17 በአማርኛና በጣሊያንኛ ቅጂው የተሳሰተ  (የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከውጭ ሃገራት ጋር የሚያደርገውንግንኙነት በኢጣልያ በኩል ማድረግ ይገባዋል!!፡፡›› በማድረግ በየካቲት 1885ዓ.ም. ዐጤ ምኒልክ የውጫሌ ውል እንደማይሠራ ለአውሮፓ መንግሥታት ደብዳቤ ጻፉ፡፡ በዶጋሊ የተሸነፉትና በውጫሌ ውል አልሆን ያላቸው ጣሊያን በኅዳር 29/1888ዓ.ም. ጦርነት ከፈቱ ጀግኖች ኢትዮጵያኖችም ሻለቃ ቶዘሊንና ሌሎች ፋሽስቶችን እንደ ነፋስ ትቢያ አድርጎ በተናቸው፡፡ ቀጥለውም በየካቲት 23/1888ዓ.ም. ጠዋት 12 ሰዐት አመሻሽ 12 ሰዐት ባለቀው፤ እንኳን ለኢትዮጵያውይን ይቅርና ለአፍሪካውያን ኩራትና የጀግንነት ተምሳሌት የሆነው የአድዋ /የሶሎዳ ተራራ/ ጦርነት በጀግናው መሪ በዐጤ ምኒልክ ድል አድራጊት ተጠናቀቀ፤ ጣሊያንም የሽነፈት ጽዋዋን ጠጥታ ተመለሰች፡፡፡ዐጤ ምኒልክም ሚያዝያ 15/1889ዓ.ም. ወደ መናገሻ ከተማቸው ሲመለሱ የማረኳቸወን ጣሊያኖች ዛሬ ‹‹ጣሊያን ሰፈር›› በሚባለው ቦታ አኖሯቸው፡፡ ‹‹የአዲስ አበባ ውል›› ተብሎ በሚጠራው በኢትዮጵያና በጣሊያን በተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ ምርኮኞቹን እንድትፈታ፤ የውጫሌ ውል መሠረዙና፣ ኢጣሊያ በኢትዮጵያ ላይ ጣልቅ እንዳትገባ፤ የኤርትራ ድበር እስኪከለል ጣሊያን ከጦርነቱ በፊት ባለችበት እንድትረጋ በሚል ተከናወነ፡፡ #ሁለተኛው_ወረራና_ጦርነት ሁለተኛው ጦርነት ከ1929ዓ.ም.-1933ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ (ለዚህ ጦርነት ደግሞ መሠረቱ ጣሊያን የቀድሞ ሽንፈቷ ቂም በመያዟ ነው)፡፡ የተጀመረውም በኅዳር 26/1927ዓ.ም. በወልወል (የኢትዮጵያ ሶማሌ ክፍለ ሃገር በኦጋዴን ውስጥ በዋርዴር አውራጃ አካባቢ የምትገኝ ወረዳ ስትሆን ንጹሕ የከርሠ ምድር ውኃ የሚገኝባትም ነች፤ አጼ ዘርዓ ያዕቆብ 350 ጥልቅ የውኃ ጕድጓድ አስቆፍረውላታል) ላይ ጣሊያን ባንዲራዋን በመትከሏ ምክንያት ነው፡፡ በዚሁም ምክንያጥ የአውራጃው ገዢ ፋውራሪ ዓለማየሁ ከጣሊያኑ ጦር አዛዥ ካፒቴን ችማሩታ ጋር ጦርነት ገጠመዋል፤ በጦርነቱም ጀግናው ፊታውራሪ ዓለማየሁ በፋሽስታዊ ታንክ ነጂ በገዛ ታንኩ ላይ ላይ ተወርውረው በመውጣት ሰይፈውታል፤ ብዙ የጀግንንት ሥራንም አከናውነዋል፤ ቆይቶ ግን ለሃገራቸው በጀግንነት እየተዋጉ ሣለ ከሌሎች 107 ኢትዮጵያውያን ጋር አርፈዋል፡፡ በዚህ ውጊያ ላይ አብዛኞቹ ሙስሊሞች ባንዳ በመሆን ለሃገራችን ጠላት ቢሆኑም (ለምሳሌ ሡልጣን ኢብራሂም አሰብን ለሮማ ልዑካን ሸጥኩላቸው የሚለውና፣ የአዳል ባላባት የራሄታ ሡልጣን ሐሰን ሙሐመድለሮማ ሚስዮናውያን የኢትዮጵያን ወደቦች እነሸጣለን ብሎ የመከረ)፤ ለሃገራቸው ሲሉ የተዋጉ የሙስሊም አርበኞችም ነበሩ፤ ዋነኞቹም ኑር ሑሴንና ደጃዝማች ዑመር ሰመትር ይጠቀሳሉ፡፡ በዚሁም ጣሊያን ‹‹ጅራፍ ረሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል›› እንደሚሉት ኢትዮጵያ ዜጎቹን ገድላብኛለችና 200 ሺህ ሊሬ ካሳ ትክፈለን ብለው ለመንግሥታቱ ማኅበር ከሰሱ፡፡ ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በድርድር ያልቃል ብላ ስትጠብቅ በጎን ግን ኢጣሊያ ለጦርነት ስትዘጋጅ ቆየች፤ በኅዳር 1927ዓ.ም የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስቴር ፒየር ላቫል ኢጣሊያ ከጀርመን ሂትለር ጎን እንዳትሰለፍ በማሰብ ኢትዮጵያን ብትወርር እንደማትቃወም አሳወቅ፤ ጦርነቱን የተቃመወችው ሩሲያ ብቻ ነበረች፡፡በመስከረም 22/1928ዓ.ም. ኢጣሊያ የመረብን ወንዝ ተሸግራ ጦሯን በ3ት መስመር አሰልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ገባች፡፡ ያገኘችውንም እያጠፋች እንትጮንና አዲግራትን በያዝ ዓድዋ ደረሰች፤ ለዚሁም አስተዋጽዖ ያደረጉላት ለግል ጥቅማቸው ያደሩ የኢትዮጵያ ጠላት የሆኑ ባንዳዎች ነበሩ ለአብነትም ዋነኞቹ (ደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ፣ ደጃዝማች ሀብተ ማርያም፣ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው) ናቸው፡፡ ባንዳ ደጃዝማች እጅጉ አያሌው የጎንደርን ሕዝብ አሳምኖ ለኢጣሊያ ተገዢ ለማድረግ መንቀሳቀሱን ጀግናው አርበኛ ደጃዝማች ታደሰ ይማም ወንድይራድ ሲሰማ ያለበት ድረስ ደርሶ ድባቅ መትቶታል፤ ባንዳው እጅጉ በጣና ሐይቅ በታንኳ ተሸግሮ አምልጦ ወሎ ተደበቀ፤ ይህንንም ታላቁ አርበኛ ደጃዝማች  ታደሰ ወሎ ድረስ ዘምቶና ከበባ አድርጎ ሃገሩን ለሸጠ ምሕረት አይገባውምና እንደ በግ አርደውታል፡፡ ጣሊያኖች በባንዳዎች በመታገዝ ጭምር በመርዝ ጋዝ ታግዘው በየካቲት 27 ከራስ ሙሉጌታ ጋር በተደረገው ውጊያ የራስ ሙሉጌታ ጦርን በመደምሰሳቸው በሐበሾች ዘንድ የሞራል ውደቀት አስከትሏል፡፡ ነገር ግን ጀግኖች አርበኞች እምቢ ለሃገሬ በማለት በተንቤን፣ በእንደርታ፣ በሽሬ፣ በአሸንጌ ላይ ተዋጉ፡፡ በአሸንጌው ጦርነት ጠላት ጣሊያን ከላይ በአውሮፕላን ጠላት ባንዳ ደግሞ ከታች በመሆን 8ሺህ የሚጠጉ አርበኞቻችን ላይ ጉዳት አደረሱ፡፡ በመጋቢት 24 ለ13 ሰዐታት በተካሄደው የማይቸው ጦርነት ላይ ኢትዮጵያውያን ድል አድረገው ጦርነቱ ማብቂያ ላይ የመርዝ ጋዝና የቦንብ ውርጅብኝ ከአውሮፕላን ላይ በማዝነብ ጀግኖች አርበኞቻችን አብዛኞች አለቁ፤ ከማይጨው የተረፉና በአሸንጌ ላይ የነበሩትን ጀግኖች አርበኞችን 150አውሮፕላን ደርሰው ደብደቡት በመትረየስም ፈጁት፡፡ (ጣሊያኖች ዚሁ ወረራቸው በሰሜን 300፣ በደቡብ 150 አውሮፕላን አዝምተዋል፡፡)

“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ”   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !! በሀገር ውስጥና በልዩ ልዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ፡- በመዋዕለ ጾሙ ሰይጣንንና መስሓቲ ተግባሩን ድል በማድረግ ድል እንድንነሣ ያደረገን ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ኣርብዓ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!   ‹‹ወልበሱ ወልታ እግዚአብሔር በዘትክሉ ተቃውሞቶ ለመናግንተ ሰይጣን፤   የሰይጣንን ሽንገላ መቃወም ትችሉ ዘንድ የእግዚአብሔርን ጋሻ ልበሱ›› (ኤፌ.፮፥፲፩)፤ እኛ ሰዎች ቀዋሚና ምሕረት የለሽ ጠላት እንዳለን እናውቃለን፤ ይህ ጠላት ሰይጣን፣ ዲያብሎስ፣ክፉ መንፈስ፣ ርኩስ መንፈስ ተብሎ እንደሚጠራም ቅዱስ መጽሓፍ ነግሮናል፤ዲያብሎስ ከጥንት ጀምሮ በክፉ ሽንገላው ሰዎችን ሲጥል ኖሮኣል፤ አሁንም ከዚህ ክፉ ተግባሩ ኣልታቀበም፤ ለወደፊቱም ይታቀባል ተብሎ አይጠበቅም፤ ጌታችን በዚህ ዓለም በሥጋ በተገለጠ ጊዜም ይህ ክፉና ርኩስ መንፈስ በሽንገላ ቃሉ ጌታችንን ሊጥል ያልተሳካ ሙከራ አድርጎኣል፡፡ ርኩሱ መንፈስ ጾም መንፈሳዊ ኃይልን እንደሚያቀዳጅ ያውቃልና፣ ጌታችን ምንም ሳይበላና ሳይጠጣ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት መጾሙን ተመልክቶ፣ በሽንገላ ቃሉ ሊጥለው ሙከራ አድርጎኣል፤ ይህንን ያደረገበት ዋና ምክንያትም ጾም መንፈሳዊ ኃይል መሆኑን በውል ያውቃልና በጾም ኃይል ከእጄ ያመልጣል ብሎ በማሰቡ ነው፤ ይሁን እንጂ ሰይጣን የሰውን ደካማ ጠባይ በመጠቀም ያስለመደው ሽንገላ፣በተዋሕዶ ሰውም አምላክም በሆነው ጌታችን ላይ ሊሳካለት ባለመቻሉ ተሸንፎና ተስፋ ቆርጦ ሊሄድ ችሎአል፡፡   የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን! የጌታችን ድል አድራጊነት ያስተማረን ብዙ ነገር አለ፤በዚህ ተግባራዊ ትምህርቱ እኛ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስን ድል የምናደርግባቸው ሁለት መሣሪያዎችን በዋናነት አሳይቶናል፤ እነሱም የእግዚአብሔርን ጋሻ መልበስና በጾም መንፈሳዊ ኃይልን መቀዳጀት ናቸው፡፡ ሁሌም እንደምንማረው በውስጣችን ሁለት ተቃራኒ ነገሮች ኣሉ፤ እነሱም ፍትወተ ሥጋና ፍትወተ መንፈስ ናቸው፤ እነኝህ ሁለት ነገሮች ኣንዱ ላንዱ ፍጹም ተቃራኒ መሆናቸውን ቅዱስ መጽሓፍ እንዲህ በማለት ያስረዳል፡-‹‹ እስመ ሥጋኒ ይፈቱ ዘኢይፈቱ መንፈስ፤ ወመንፈስኒ ይፈቱ ዘኢይፈቱ ሥጋ፤ ወይትኣበዩ በበይናቲሆሙ ከመ ኢትግበሩ ዘትፈቅዱ፤ ወባሕቱ እብለክሙ በመንፈስ ሑሩ ወፍትወተ ሥጋክሙ ኢትግበሩ፣ማለትም ሥጋ መንፈስ የማይወደውን ይወዳል፤ መንፈስም ሥጋ የማይወደውን ይወዳል፤ እርስ በርሳቸውም ይቀዋወማሉ፤ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ ኣትችሉም፤ ነገር ግን እላለሁ በመንፈስ ተመላለሱ የሥጋን ምኞት ግን ከቶ አትፈጽሙ››(ገላ.፭÷፲፮‐፲፰)፡፡ እነኝህ የውስጣችን ጠባዮች በዚህ ደረጃ እርስ በርስ የሚቃረኑ መሆናቸው ለምናስተውላቸው በግልጽ የሚታወቁ ናቸው፤ ከዚህ አንጻር ሰይጣን ይህንን ክፍተት ተጠቅሞ የሥጋችንን ፍላጎት እንድንከተል ይገፋፋናል፤ መሳሪያዎቹ ደግሞ ፍቅረ መባልዕት፣ ፍቅረ ንዋይና ፍቅረ ሢመት ናቸው፤ ይህም በመሆኑ ነው ሰይጣን፣  በነዚህ ጌታችንን ሊሸነግለው የሞከረ፤ይሁንና ጌታችን እነኝህን የሽንገላ መሣሪያዎች ሰባብሮ ጥሎኣቸዋል፤የጣላቸውም በጾምና በእግዚአብሔር ቃል ነው፤ ጾም መጾም ማለት ከፍቅረ መባልዕት፣ ከፍቅረ ንዋይና ከፍቅረ ሢመት ፍላጎት ጨርሶ መራቅ ማለት ነው፤ ይህንን ኣደረግን ማለት ደግሞ ሥጋችን የማይወደውን፣መንፈሳችን ግን የሚወደውን ነገር ኣደረግን ማለት ነው፤ ይህ ሲሆን ሰይጣን ከሰረ፤ ድልም ሆነ ማለት ነው፤ በዚህ መንፈሳዊ ኃይል ዲያብሎስ ተሸንፎና ተስፋ ቆርጦ ይሄዳል፡፡ ከዚህ ኣኳያ እኛም በቃለ እግዚአብሔር እየተመራን የምንጾምበት ምክንያት የሥጋችንን ፍላጎት በመግራት ለነፍሳችን ፍላጎት ለማደርና በዚህ ኃይለ መንፈስ ሰይጣንን በማሸነፍ የእግዚአብሔር ቤተ ሰብ ለመሆን ነው፡፡            የተከበራችሁ ሕዝበ ክርስቲያን ልጆቻችን! የጾም ዋና ዓላማ ሥጋዊ ፍላጎትን መግራት፣ በምትኩ ደግሞ መንፈሳዊ ፍላጎትን ማጐልበት እንደሆነ ተነግሮናል፤ በመሆኑም ይህንን መርሕ ጠብቀን መጾም ግዴታችን ይሆናል፤ ዛሬ ባለንበት ዓለም ሥጋዊ ፍላጎታችን ያየለበት፣መንፈሳዊ ፍላጎታችን ግን የተዳከመበት ዘመን ላይ እንገኛለን፤ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ፣ ከኣንድነት ይልቅ መለያየት፣ ከመራራት ይልቅ ጭካኔ፣ ከእምነት ይልቅ ክሕደትና ኣስመሳይነት በዓለማችን ላይ የበላይነቱን ይዞ መገኘቱ ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ ይሁንና ዓለም ቢሰማም ባይሰማም፣ ሓቁም ጠቃሚውም የመንፈስን ፍላጎት ማጐልበት ስለሆነ የመንፈስ ፍሬዎች የሆኑትን ማለትም፣ ፍቅርን ሰላምን፣ ኣንድነትን፣ ርኅራኄንና፣ ሃይማኖትን፣ ማስፈን ምርጫችን ልናደርግ ይገባል፤ ቤተክርስቲያንም እንድንጾም የምታስተምረን እነዚህን ለመተግበር ጾም ፍቱን መሳሪያ ሆኖ ስለሚገኝ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የጾም ዓላማውና ግቡ ጽኑዕ ሃይማኖትን፣ እውነተኛ ፍቅርን፣ ዘላቂ ሰላምን፣ ልባዊ ኣንድነትን፣ የማይናወጽ ፍትሕንና እኩልነትን፣ ወሰን የሌለው ርኅራኄን በውስጣችን፣ ብሎም በዓለማችን ማሥረጽ እንደሆነ በውል ተገንዝበን ጾሙን መጾም ይገባል፤ልንለብሳቸው የሚገቡ እነዚህ የመንፈስ ፍሬዎች የእግዚአብሔር ጋሻዎች ናቸውና፡፡ ይህንን ካደረግን እንደ ጌታችን የሰይጣንን ሽንገላ በጣጥሰን በመጣል በኣስተማማኝ ሁኔታ ድል ማድረግ እንችላለን፤ የተጠራነውም ለዚሁ ነው፡፡ በመጨረሻም፡- የሕዝባችንና የሀገራችን የራስ ምታት ሆኖ የሚገኘውን ያለመግባባት ዝንባሌ ለመቅረፍ ከልብ በመጸለይ፣ እንደዚሁም የተራቡትን በማጒረስ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የተጣሉትን በማስታረቅ፣ ፍትሕ ለተነፈጉትም እውነተኛ ፍትሕን በመስጠት፣ መዋዕለ ጾሙን እንድንጾመው በእግዚአብሔር ስም ኣባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን። “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ”   ወስብሓት ለእግዚአብሔር     አሜን!                         አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፡፡                             የካቲት ፱ ቀን ፳፻፲፰          አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

#ዘወረደ_ወይም_ሕርቃል_ወይም_ሙሴኒ     ጾም ማለት፤ ፨ ከእህልና ከውኃ እንዲሁም ከሥጋ ፈቃድ ጾሙ እስኪፈጸም ድረስ መተው ማለት ነው። ፨ ጾም ማለት በጾም ወቅት ሥጋ ነክ ምግቦችንም ሆነ ወተትን፤ ቅቤን የመሳሰሉትን የምግብ እና የመጠጥ ዓይነቶችን ጥሉላትነት በሌላቸው ምግቦች መለወጥ ብቻ ሳይሆን የምንወደውን የሥጋ ፍላጎት ስለ እግዚአብሔር ብለን መተው ማለት ነው። ራስን መግዛት በክርስቲያናዊ ሕይወት ውስጥ ትልቅ ዋጋ እንዳለው ሁሉ አንድ ሰው የሥጋ ፍላጎቱን ወይም የዓለም ምኞቱን ትቶ እግዚአብሔርን እያሰበ የሚጾም ከሆነ በፈጣሪው ዘንድ ጾሙ ተቀባይነት አለው። ፨ ጾም ለእግዚአብሔር ያለንን ታዛዥነት የምንገልጽበት የፍቅር መገለጫ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን ዐቢይ ጾም ስንጾምም፤ ዐይናችን ትጹም (ክፉ ከማየት)፤ ጆሮም ትጹም (ክፉ ከመስማት ወይም ሰውን ከማማት እንታቀብ)፤ አፋችን ትጹም (ከመሳደብ ሆነ ክፉ ከማውራት)፤ እጅም ትጹም (ከመስረቅም ሆነ ሰውን ከመደብደብ)፤ አግርም ትጹም (ወደ ኀጢአት ቦታዎች ከመሄድ ምሳሌ ከጭፈራ ወይም ዳንኪራ ቤቶች)፤ ….. ሁላችንም በተሰበረ ልብ ሆነን እንጹም። ዐቢይ ጾም ማለት ታላቅ ጾም ማለት ነው። ታላቅ ጾም የተሰኘበት ምክንያት ለ55 ቀናት መጾሙና ከሌሎች አጽዋማት ጋር ሲነጻጸር በቊጥር መብለጡ ብቻ ሳይሆን ፍጥረታትን የፈጠረ አምላክ፤ ስለ ሰው ልጅ ፍቅር ሲል ከዙፋኑ ወርዶ ከእመቤታችን ተወልዶ፤ መጾም ሳይገባው ለእኛ አርአያ ለመሆን ሲል በገዳመ ቆሮንጦስ የጾመው ጾም ነው። የዐቢይ ጾም  የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ ወይም ጾመ ሕርቃል በተጨማሪም ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፤ ለምን እንደተባለ በዝርዝር ስንመከለከታቸው፤ ፩ኛ. #ዘወረደ_ይባላል፤ ‹‹ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ፤ ወሚመ ኢያእመሩ፤ እግዚአ ኵሉ ዘየሐዩ በቃሉ፡፡›› ‹‹ዘወረደ እምላዕሉ እመልዕልተ ኵሉ››፡፡ «ዘወረደ» ማለትም በቀጥታ፣ ቃል በቃል ሲተረጐም «የወረደ» ማለት ነው፡፡ ይህም በምሥጢሩ አምላክ፥ ወልደ አምላክ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤዛ ዓለም፥ እኛን  ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን፤ በፈቃዱ ሰው ሆኖ ከሰማየ ሰማያት ከባሕርይ ልዕልናው በትሕትና መውረዱን፥ ከድንግል ማርያም መወለዱን፥ የእኛን ሥጋ መዋሐዱን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ ይህ እንዲታወስበት፣ እንዲወሳበት የዐቢይ ጾም የመጀመሪያውን ሳምንትን ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ ‹‹ዘወረደ›› ብሎ ሰይሞታል፡፡ /ዮሐ.3፥13፣ ጾመ ድጓ፡፡/       ፪ኛ. #ጾመ_ሕርቃል_ይባላል፡፡ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ሌላ መጠሪያ ስሙ ‹‹ጾመ ሕርቃል›› ነው፡፡ ሕርቃል ማን ነው? ለምንስ በስሙ ተሰየመ? በ614 ዓ.ም. ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር ጥቃት አደረሰ፡፡ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው ቤተመቅደስ ውስጥ ንግሥቲቷ በክብር አስቀምጣው የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡ ቢነካው አቃጠለው ካህናትን አሸክሞ፥ ሌላውን ንዋያተ ቅድሳት ዘርፎ፥ 60ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ፥ 3ሺ የሚሆኑትን ማርኮ፥ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን ይመለሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ14 ዓመት በኋላ በ628 ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲያኑ የሮም ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፤ እርሱም ሐዋርያት ሰውን የገደለ እድሜውን በሙሉ ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርግ? አላቸው; እኛ የአንተን እድሜ ተከፋፍለን እንጾማለን ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው ጾሙን ፩ ሱባኤ ጾመውታል፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና የተማረኩ ክርስቲያኖችን ለመመለስ ሕርቃል ጦር መዝዞ በኪርዮስ ላይ ተነሳበት ድል ለሕርቃል ሆነና መስቀሉ ያለበትን አጥቶ ሲቸገር ኪርዮስ መስቀሉን ሲቀብርና ዲያቆናቱን ሲያስገድል በመስኮት ሆና ያየችው ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ ቊስጥንጥንያ ተመለሰ፤ የተማረኩት በሙሉ ነጻ ወጡ፤ ይህንን ለማሰብ፥ ለማስታወስ የምንጾመው ሲሆን፤ ዛሬም እኛ በመስቀልህ ከምርኮ እንደተመለሰ እኛንም ከኃጢአት ምርኮ መልሰን እያልን፥ ለሕርቃል በጠላቶቹ ላይ ድል መንሳትንና በጠላቶቹ ላይ ኃይልን እንደሰጠኸው ለእኛም በኃጢአት ላይ ድል መንሳትን፥ መንፈሳዊ ኃይልን እንዲበዛልን እንጾመዋለን፡፡ በጌታ ጾም ላይ እንዲጾም የሆነበት ምክንያት ጾሙ የጌታ ጾም በሚጾምበት ወቅት ላይ ስለተጾመ ቤተክርስቲያናችን አብራ ደንግጋዋለች፡፡ የእኛ ጠላት የጨለማ ገዥ የሆነው ዲያቢሎስ ነውና እሱን ደግሞ በጾም እንደምናሸንፈው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡    ፫ኛ. #ሙሴኒ የመጀመሪያው ሳምንት ሙሴኒ የተባለበት ምክንያትም፤ በዚሁ ሳምንት መጀመሪያ የሰኞ ዕዝል «ከመዝ ይቤ ሙሴ ፀዓቱ እምትእይንት (ሙሴ ከከተማ መውጣቱ እንደዚህ ነው አለ») ስለሚል እንደዚሁም የዚሁ ዕለት ማለት የሰኞ አቡን «ሙሴኒ ይቤ በውስተ ኦሪት ምድር ሰናይት» እያለ የሙሴን ታሪክ ስለሚጠቃቅስ ሳምንቱ ሙሴኒ ተባለ፡፡ ነቢያትም አርባ አርባ ቀን ጾመው ካለፉ በኋላ የሙሴ ሕግና ትንቢተ ነቢያት ፈጻሚ የሆነው አምላካችን እንደ እነሱ 40 ቀንና 40 ሌሊት መጾሙን  የሚያስታውስ ነው፡፡  /ዘፀ.24፥18፤  1ኛ.ነገ.19፥8፤  ማቴ.4፥1-4/፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

እንኳን ለዐቢይ ጾም አደረሳችሁ! ጾሙ የካቲት 9 ይገባል #የዐቢይ_ጾም_ሳምንታት_ስያሜዎች ፩ኛ)የመጀመሪያው እሑድ(ሳምንት)፥ #ዘወረደ (ሙሴኒ፣ ጾመ ሕርቃል) ይባላል፡፡ አምላክ ከሰማይ መውረዱን፣ ሰው መሆኑንና ነገረ መስቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡ ፪ኛ. የሁለተኛው እሑድ፥ #ቅድስት ይባላል፤ ስለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው ፫ኛ. የሦስተኛው እሑድ፥ #ምኲራብ ይባላል፤ በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኲራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ ፬ኛ. ዐራተኛው እሑድ፥ #መፃጉዕ ይባላል፤ ድውያንን መፈወሱን፣ ዕውራንን ማብራቱን፣ የሚያነሣ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ፭. አምስተኛው እሑድ፥  #ደብረ_ዘይት ይባላል፡፡ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሁኖ ያስተማረው ትምህርት፥ የዳግም ምጽአትን ነገር የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ፮. ስድስተኛው እሑድ፥ #ገብርኄር ይባላል፡፡ የጌታውን ብር ተቀብሎ ያተረፈበት፣ በጌታውም ፊት ምስጋናን ያገኘው ሰው ታሪክ ይዘመርበታል፡፡ ፯. ሰባተኛው እሑድ፥ #ኒቆዲሞስ ይባላል፡፡ በሌሊት ወደ ጌታ እየመጣ ይማር የነበረውን የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ፰. ስምንተኛው እሑድ፥ #ሆሣዕና ነው፡፡ ጌታ በአሕያ ውርንጭላ ሆኖ ሆሣዕና በአርያም እየተባለ ወደ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት መታሰቢያ ነው፡፡ ፨ ከሠርክ ሆሣዕና እስከ ትንሣኤ ያለው ሰባት ቀን #ሕማማት ይባላል:- የጌታን መከራና ስቃይ እንዲሁም ሞት የምናስታውስበት ሳምንት ነው ፡፡ #የዐቢይ_ጾም_ሌሎች_መጠሪያ_ስያሜዎች ፩. ዐቢይ ጾም ይባላል፤ ፪. ጾመ ሁዳዴ ይባላል፤ ፫. የካሣ ጾም ይባላል፤ ፬. የድል ጾም ይባላል፤ ፭. የመሸጋገሪያ ጾም ይባላል፤ ፮. ጾመ አስተምህሮ ይባላል፤ ፯. የቀድሶተ ገዳም ጾም፤ ፰. የመዘጋጃ ጾም ይባላል፤ ፱. የሥራ መጀመሪያ ጾም፤ ፲. ጾመ አርብዓ ይባላል፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

"ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ ፡-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ስምዖን አረጋዊ #የካቲት_8  ፤ የጌታችን  ከከበርች ልደት በኋላ  ወደ ቤተመቅደስ የገባበት ዕለት ኾነ ፡፡ በዓሉ ከጌታችን ንዑስ በዓሎች መኻከል አንዱ ነው ፡፡ ++++ የካቲት 8 ፤ ልደተ ስምዖን አረጋዊው  ፣ ካህን ፣ ጻድቅ ፣ ነቢይ ፡፡ + በዓሉ የመድኀኔዓለም ቢሆንም ስምዖን አረጋዊ አማናዊ ድኅነት አግኝቶበታልና ፣  በእርጅና ምክንያት ከአልጋ ላይ ተጣብቆ ሲኖር ታድሶበታልና እንደ 30 ዓመት ጎልማሳም ዘሏልና  በዓሉ ይከብራል ። ስምዖን ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ሁሉ የድኅነት ባለቤት ኾኖበታልና በዓሉ ይከብራል ። ++++ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በተወለደ በ40 ቀኑ የኦሪትን ሕግ ለመፈጸም ወደ ቤተ መቅደስ ገባ ። ይህም ሕግን ሊፈጽም እንጂ ሊያፈርስ አለመምጣቱን በቃልም ፣ በግብርም የገለጠበት በዓል መኾኑን ያስረዳናል። ሥርዓቱን ለመፈጸም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ጌታቸውን ይዘው፣ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ ጨምረው ወደ ቤተ መቅደስ ሔዱ ። ++++ የስምዖን አረጋዊ ነገርም እንዲኽ ነው .. ዓለም በተፈጠረ በ5,200 ዓመታት በጥሊሞስ የተባለ ንጉሥ በግሪክ ነግሦ ነበር። ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጦ፣ እንደ ገል ቀጥቅጦ የገዛው መሆኑን ገልጦ፣ የቀረው ነገር አለመኖሩን ሲናገር ባለሟሎቹ በእሥራኤል ጥበብ የመላባቸው 46 መጻሕፍት ስላሉ እነርሱን አላስተረጎምክም አሉት። እስራኤልን አስገብሮ ስለነበር 46ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ72 የአይሁድ ሊቃውንት ጋር አስመጣ። አይሁድ ተንኮለኛ መኾናቸውን ስለሚያውቅ 36 ድንኳን እንዲዘጋጅ አድርጎ ኹለት ኹለቱን መድቦ፣ የየድንኳኑን ሊቃውንት የሚቆጣጠሯቸው አንዳንድ ጠባቂዎች ጨምሮ  እንዲተረጕሙ አዘዛቸው። በዚህ ምክንያት በ284 ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት 46ቱ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ወደ ልሳነ ጽርዕ (ግሪክ) በ70ው ሊቃናት ተተረጐሙ። ከ70 ሊቃናት በመኻከል አንዱ የነበረው #ስምዖን ምሁረ ኦሪት ነበር። ይተረጕም ዘንድ መጽሐፈ ኢሳይያስ ደረሰው። ታዲያ ይህ ሊቅ የትንቢቱን መጽሐፍ እየተረጎመ ሳለ ምዕራፍ ፯ ላይ ሲደርስ የሕይወቱን አቅጣጫ ወደ ዘላለማዊ በረከት የሚያሳድግ ልዩ ገጸ ንባብ ገጠመው ።  እርሱም “ ስለዚኽ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነኾ ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” ኢሳ 7፥14 የሚል ነበር። ስምዖንም "እንዴት ድንግል ትፀንሳለች?" ብሎ "ድንግል" የሚለውን "ሴት" ብሎ ቀይሮ " ሴት ትፀንሳለች " ብሎ ለማረም ይሞክርና አመሻሽ ላይ ስለነበር እንቅልፍ ሸለብ አድርጎት ሲነቃ የቀየረው ተቀይሮበት " ድንግል ትጸንሳለች" የሚል ሁኖ ያገኘዋል።  ተሳስቼ ነው ብሎ አሁንም ሊያበላሽ ሲሞክር መልአኩ ሦስት ጊዜ አርሞበት  በሦስተኛው መልአኩ ራሱ ተገልጦለት "ይህችን ድንግል ሳታይና ልጇንም ታቅፈህ ሳትባረክ አትሞትም" ( የተጠራጠርከውን ሳታይ አትሞትም ብሎ ብሎ ነግሮት )  ተሰወረ። አረጋዊ ስምዖንም ከዚያች ዕለት ጀምሮ መድኅን ክርስቶስ እስከሚወለድ ለ284 ዓመታት ከአልጋ ጋር ተጣብቆ ኖረ። አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም በተወለደ በ40 ቀኑ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ወጡ ። በዕለቱም መልአከ እግዚአብሔር አረጋዊ ስምዖንን ቀስቅሶ ተስፋ የሚያደርገው አዳኝ ክርስቶስ መምጣቱን ነገረው። በዚህ ጊዜ አረጋዊ ስምዖን አካሉ ታድሶ፣ እንደ 30 ዓመት ወጣት እምር ብሎ ከአልጋው ተነሣ። በፍጥነትም ወደ መቅደስ ገባ። መድኀኔዓለምን ከድንግል ማርያም ተቀብሎ በመታቀፍ "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ፡-አቤቱ ባሪያህን እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" (" ጌታ ሆይ፥ አን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና፤ ይኽም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን ለሕዝብህም ፳ኤል ክብር ነው።" (ሉቃ 2÷29-32)  ) በማለት ጸለየ።  አምላኩም ጸሎቱን ሰምቶት በዛሬው ዕለት ዐረፈ። ከበዓሉ በረከት ይክፈለን። አሜን!! የሊቁ ስምዖን  አረጋዊ በረከት እና ምልጃ አይለየን ! በዓለ ስምዖን በዐይቢይነት  ሜላት ደብረ ገነተ ኢየሱስ  ይከብራል  ፡፡ ጐንደር   -- › አንዳቤቴ ወረደ   -- › ገነተ ኢየሱስ   በ13ኛ መቶ ክፍለ  ዘመን በአጼ ሰይፈ አርዕድ ዘመነ መንግስት ልዕልት ሜላተ ወርቅ ያሰተከለችው ደብር ነው ፡፡ +++ በዓሉ በኢየሱስ ስም የተሰየሙ አድባራትና ገዳማት ላይ ይከበራል ! /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#የበረሃው_መልአክ፤ #የገዳማት_ኮከብ፤ #የመናንያን_አባት፤ #በሊቃውንት_የተወደሰው #የአባ_ጳውሊ_ዕረፍት ፨ የካቲት 2 በዚህች ቀን በግብጽ በርሃ ታላቅ አምድ ወደቀ፤ ይህም የባህታውያን ሁሉ አለቃቸው የሆነ አባ ጳውሊ  ነው። ይኽ ጳውሊ በ227 ዓ.ም የተወለደ ሲኾን ዕረፍቱ በ341 ዓ.ም. ነው፤ ስርዓተ ብሕትውና በጳውሊ ስርዓተ ምንኩስና በእንጦኒ ተጀምሯል ይላል። ጳውሊ አባቱ ባለጸጋ ነበር ሲሞት ለታላቅ ወንድሙ በጴጥሮስ እጅ አድርጎ ኃላ አካለ መጠን ሲያደርስ ከፍለህ ስጠው ብሎት ተናዞ አረፈ፤ አባ ጳውሊ አካለ መጠን ሲደርስ “ ደረስሁ ልጅ ፈላሁ ጠጅ ” የአባቴን ገንዘብ ከፍለህ ስጠኝ አለው አይሆንም አልሰጥህም አለው ምነው ቢለው ልጅ ነህ ታጠፋዋለህ ብዬ ነው ይለዋል አላጠፋውም ስጠኝ ይለዋል ግድማ ካልኸኝ ብሎ ብዙውን አስቀርቶ ጥቂቱን፤ መልካሙን አስቀርቶ ተራ ተራውን ሰጠው አባ ጳውሊ በዚህ ተበሳጭቶ ዳኛ ጋር ሄደ በመንገድ ላይ አንድ ባለጸጋ ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት አየ አባቴ ባለጸጋ ነበር ሞተ ይሄም ባለጸጋ ነበር ሞተ እኔስ ነገ እሞት የለምን ብሎ ወደ ወንድሙ ተመልሶ ወንድሜ ገንዘቡ ላንተ ይሁን ትቼልሃለው ብሎ ከቤት ወጣ፤ መጀመሪያ ለ 3 ቀን ከመቃብር ቤት ገብቶ ጸለየ በ3ኛው ቀን ከሰማይ ግማሽ ህብስት ወረደለት፤ ገረመው፤ #ከዓለም ፈጽሞ ሳይለዩ እንዲህ ከሆነማ ፈጽሞ ቢለዩማ እንደምን ያለ ተአምር በተደረገ ብሎ አናብስት አናምርት አካይስት አቃርብት ካሉበት ነቃዐ ማይ ልምላሜ ዕፅ ከሌለበት ድሩክ ለተአቅቦ ይለዋል ዘር ተክል ከማይገኝበት ከጽኑ በርሃ ገባ፤ የሰው ፊት ሳያይ ለ 80 ዓመት በተጋድሎ ኖሯል። ምግቡን ግማሽ ህብስት በየቀኑ የሚያመጣለት ቁራ ነበር። የእረፍቱ ቀኑ ሲደርስ ከአባ እንጦንስ ጋር በእግዚያብሔር ፈቃድ ተገናኝተው ብዙ ነገር ተጨዋወቱ በተለይም በኃለኛው ዘመን ስለሚነሱት መነኮሳትና፤ ግብጽ በሙስሊሞች እንደምትወረር ብዙ ሚስጢር አወሩ ብዙ ትንቢትም ተናገሩ። ከዚህ በኃላ አባ ጳውሊ አስኬማ መልአክ አምጣልኝ ብሎ ይልከዋል፤ አባ እንጦስ ወደ ገዳሙ ሄደ የ 2 ቀን ጎዳና ነው ሲመለስ በርሃው ላይ ሰማያውያን መልአክ ሰፍረውበት ሲዘምሩ ሲያመሰግኑ አየ፤ ልብን የሚመስጥ የእጣን መዓዛም አሸተተ፤ ምንድር ነው ? ብሎ አንዱን መልአክ ይጠይቀዋል አባ ጳውሊ ሞቶ ነፍሱን እያሳረግን ነው ይለዋል ይሄን አስኬማ አምጣልኝ ብሎኝ ነበር ምን ላድርገው ? ይለዋል፤ ጸሎት አድርሰህ አድርግለት፤ ደግሞም መቃብሩን የሚቆፍሩ አንበሶች ይመጣሉ ቦታውን ለክተህ ስጣቸው አለው፤ ወደ ገዳሙ ሲገባ እጁን መስቀልኛ እንደዘረጋ ሞቶ አገኘው የሚጸልይ እንጂ የሞተ አይመስልም ነበር አስኬማውን አድርጎለት ሲያበቃ ከራስጌው ቆሞ ኤልያስ ልበልህ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ልበልህ እያለ አለቀሰለት፤ ሁለት አንበሶች መቃብሩን ቆፈሩለት ገንዞ ቀበረው። 80 ዘመን ሙሉ ለብሶት የኖረው የሰሌን ልብስ ነበረችው ወስዶ ለሊቀ ጳጳሱ ለአባ አትናቴዎስ ሰጠው፤ በዚህች ልብስ አባ አትናቴዎስ ብዙ ተአምራትን ሰረቶበታል ይልቁንም ሙት አስነስቶበታል።  ቅዱስ አትናቴዎስ ዜናውን ሰምቶ እጅግ በመደሰት፤ ዐጽፉንም በከበረ በልደት፣ በጥምቀትና በትንሣኤ በዓል በቅዳሴ ላይ ይለብሳት ነበር፡፡ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከአባ ጳውሊ በረከት ያሳትፈን። ፨ ኢትዮጵያዊው ሊቅ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ጳውሊን ነገር፡- “ሰላም ለጳውሊ በውሳጤ ገዳም ዘተፀምደ እንዘ ኢይሬኢ እምሰብእ መነሀ አሐደ ጻመወ ብዙኀ ወተጋደለ ፈድፋደ ድኅረ ሞቱሂ ከመ በሕይወቱ ለመደ ለእግዚአብሔር ተረክበ ከዊኖ ስጉደ” (ከሰው ወገን ማንንም ማን አንድ ሳያይ በገዳም ውስጥ የተጠመደ ለኾነ ለጳውሊ ሰላምታ ይገባል፤ በብዙ ወገን ደክሞ በብዙ ወገንም ተጋደለ፤ ከሞቱም በኋላ በሕይወቱ እንደለመደው ለእግዚአብሔር የሰገደ ኾኖ ተገኘ) በማለት ታላቁን ተጋድሎውን መስክሯል፡፡) ፨ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፡- “ሰላም ለአባ ጳውሊ ዘንጉሥ ወዓሊ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ ርእሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም” (በበረሓ ላሉ ባሕታውያን (መናንያን) አለቃቸው፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል) በማለት አወድሶታል፡፡ የቅዱስ አባ ጳውሊ በረከት ይደርብን፡፡) ፨ በፎቶ ላይ የምትመለከቱት ገዳም ገዳመ ቅዱስ ጳውሊ ወይም (ዴር አባ ቦላ/ቡላ) ሲሆን ይህ ገዳም  በምስራቅ በቀይ ባህር ተራራ አጠገብ የሚገኝ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ገዳም ነው።  ከካይሮ በስተደቡብ ምስራቅ 155 ኪሜ (96 ማይል) ይርቃል።  ገዳሙ #የነብሮች_ገዳም በመባልም ይታወቃል። ገዳሙ የተመሠረተው 4ኛው ክፍለ ዘመን ነው። /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

#በአዲስ_አበባ_በብቸኝነት_እንደ_ደብረ_ሊባኖስ_ገዳም_በየቀኑ_ውዳሴ_ማርያም_በዜማ፥#ክስተተ_አርያም_በዜማ፤#መስተጋብዕ_በዜማ_የሚያደርሰው_ደብራችን_ደብረ_ሰላም_የዜማ_ትምህርት_የተጀመረበትን_ ፴፫ኛ #ዓመት_ጥር_18 (ጥር 30) 2018 ዓ.ም. አክብሯል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን የምታስምራቸውን ትምህርቶች በዘርፍ በዘርፍ ከፍላ ነው የምታስተምረው፤ እነዚህም የፊደል ቤት፣ የንባብ ቤት፣ የዜማ ቤት (ከሰላም ለኪ ዜማ ጀምሮ ውዳሴ ማርያም፣ ሰዐታት፣ ቅዳሴያት፣ ምዕራፍ፣ ድጓ፣ ዝማሬ፣ መዋስዕት፣ አቋቋም፣….)፣ የቅኔ ቤት፣ የትርጓሜ ቤት፣ የቊጥር (የአቡሻኽር) ቤት ብላ በመክፈል ነው፤ ከእነዚህ ትምህርቶችም አብዛኞቹ በደብራችን የሚሰጡ ቢኾንም፤ የዓለማዊ (የአስኳላ) ትምህርት በእጅጉ እየተስፋፋ በመጣባቸው ዘመናት (ከ1960-1980 ተማሪዎች በቀኑ መርሐ ግብር የዓለማዊ (የአስኳላ) ትምህርት ስለሚማሩ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የሚማሩበት ጊዜ አጥተው፤ ደብራችንም በአዲስ አበባ ከሚገኙ አድባራትና ገዳማት ሰፊ አጥቢያን የሚያቅፍና የብዙ ሊቃውንት መኖሪያ እንደመኾኑ መጠን ከአጥቢያው የሚወለዱ ተተኪ እንደሚፈለገው መጠን ሳይኾን እስከ 1985ዓ.ም. ዘልቆ ነበር፡፡ ይህንን ችግር በውል የተረዱት ቄሰ ገበዝ መርሐ ጽድቅ ኃ/ጊዮርጊስ በቀኑ መርሐ ግብር የአስኳላ ትምህርታቸውን ለሚማሩ ተማሪዎች በማታው መርሐ ግብር የንባብና የዜማ ትምህርትን በራሳቸው ተነሳሽነት ‹‹ዘነሳእክሙ በጸጋ፥ ሀቡ በጸጋ›› የሚለውን ሲማሩ ያደጉትን የወንጌል ቃልና፤ ቀደሞውንም የተማሩት ከታላቁ ሊቅ አለቃ መርዓዊ ሣህለ ሚካኤል በመኾኑ፤ የወንጌልን ቃልና የመመህራቸውን አሠረ ፍኖት ተከትለው ያለምንም ደመወዝ በመቃብር ቤት ማስተማር ጀመሩ፤ እነኾ ዘንድሮም ማስተማር ከጀመሩ 26 ዓመታትን አስቈጠሩ፤ በእነዚህ ዓመታትም ከ850 በላይ ተማሪዎችን ሲያስተምሩ አብዛኞችንም እስከ ዲቁናና ቅስና ማዕርግ ያበቁ ትጉህና ታታሪ መምህር ናቸው፤ ማታ ማታ ከ12፡30-3፡00 ለ33 ዓመታትም ተማሪዎቼን ማስተማር ይበልጥብኛል ብለው ብዙ ነገሮችን (ማኅበራዊ ጉዳዮችን ሳይቀር) ትተው እያስተማሩ ያሉ ታላቅ መምህራችንም አባታችንም ናቸው፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤታችንም ላፈራቻቸው ዲያቆናትና ቀሳውስት ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት እኒሁ መምህር ናቸው፡፡ ስለ መምህራችንም የቱን ተናግረን እንዘልቀዋለን!! ወደፊት የእርሳቸውን የሕይወት ልምድ፣ ምክር ይዘን የምንቀርብ መኾኑን እንገለጽን፤ የዜማ ትምህርቱ ከዛሬ ከ33 ዓመታት በፊት በ1985ዓ.ም. በመቃብር ቤት በመመህራችን በቄሰ ገበዝ መርሐጽድቅ ኃ/ጊዮርጊስ (ከ10-15 በሚጠጉ ተማሪዎች /ለአብነትም ሸዋረጋ አዳነ፣ ሚሊዮን ከበደ፣ አዲስ ወርቅ ደበበ፣ ደረጀ ተክሌ፣ በላይ አዳነ፣ መሳፍንት አለማየሁ፣ …./ ተነሳሽነት የተጀመረ ነው፡፡ በመቀጠልም ተማሪው እየበዛ በመምጣቱ የዜማ መማሪያ ቦታው (መቃብር ቤቱ) ባለመቻሉ ወደ ደወል ቤት መጣ በቅቱም ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በግምት 120-125 ይጠጉ ነበር (በወቅቱ ይማሩ ከነበሩት ውስጥም ለአብነት ያህል ቴዎድሮስ አዳነ፣ ዮሐንስ ደምሴ፣ ወንድይፍራው ጌታቸው፣ ፍስሐ አዱኛ፣ ተፈሪ ተስፋዬ፣ ሰብስቤ ተክለማርያም፣ ዘለዓለም ተረፈ፣ ዘካርያስ አለማየሁ፣ መልአኩ ገብረሥላሴ፣ (አቡሽ) ገብረሥላሴ፣ ቃልአብ አለማየሁ፣ ሔኖክ አለማየሁ፣ ሚሊዮን እሸቱ፣ ዐሥራት ለይኩን፣ ሚሊዮን ለይኩን፣ ተክሉ ተዋበ፣ ፣ ተስፋዬ ገብረሥላሴ፣ ደሳለኝ ገብረ ሥላሴ፣ ምሕረቱ አዳነ፣ በልሁ ሰሎሞን፣ ጥበቡ መኮንን፣ ከተማ ወርቅአለማሁ፣ ቡሩክ አድማሱ፣ ደርብ ወርቁ፣ ዐሥራት ማሙዬ፣ ዐቢይ አለማየሁ፣ ግሩም መልአኩ፣ አበባየሁ ዕንቈ፣ ጌትዬ ዕንቈ፣ ዳንኤል ገብረ ሥላሴ፣ ካሣ ፍቅሩ፣ አፈወርቅ ማሞ፣ ጸጋ ዘአብ ማሞ፣ ስንሻው ውብአየሁ፣ ይስሐቅ ውብአየሁ፣ ስዩም አስቻለው፣ ናርዶስ ንጉሤ፣ አቡሽ ጌታቸው፣ ………… ይገኙበታል፤ አብዛኛው ተማሪዎችም የማርገጃ አካባቢ ልጆች ነበሩ፤ በአብዛኛው የአካባቢ ተወላጆች ዲያቆናትን ደብሩ ያፈራበት ዘመን ነበር፤ ለዚህም የዜማ ትምህርቱ ከፍተኛውን ሚና ተጫውቷል፡፡ ከደወል ቤት ቀጥሎ የመማሪያ ቦታው ወደ ወንዶች መጠለያ (ገረገራ)ና በመሃል ላይ ወደ ደብሩ የአብነት ትምህርት ቤት እየተዘዋወረ ትምህርቱ ሲሰጥ ቆይቷል፤ በዚህ ወቅትም ከ105-110 የሚጠጉ ተማሪዎች ሲኾኑ፤ በወቅቱ ከተማሩ ተማሪዎች መካከልም መስፍን ለገሠ፣ ስመኘው ጌትዬ፣ ዮሐንስ ጌትዬ፣ ዘካርያስ ጌትዬ፣ ሱራፌል አውግቸው፣ ወንድወሰን ሺፈራው፣ ኢሳይያስ ቦጋለ፣ ያሬድ እንደሻው፣ ….. ይገኙበታል፤ በዚህ ወቅትም ከማርገጃ አካባቢ በተጨማሪ ከሌሎች የደብሩ አጥቢያዎች (ከቀጨኔ፣ ከሰሜን፣ ከችሎት፣ ከ20ቀበሌና ከመነን) መጥተው ተማሪዎች መማር የጀምሩበት ነበር፡፡ አሁን ባለንበት ጊዜ ደግሞ በቋሚነት በወንዶች መጠለያ (ገረገራ) ትምህርቱ እየተሰጠ ይገኛል፤  በአሁኑ ወቅትም በፊት ወንድሞች ይማሩ የነበረው ይህ የማታ የዜማ ትምህርት እኅቶችንም ያካተተ ሁኗል፡፡ አሁን ባለበት የዜማ ትምህርት ሒደት ከምሽቱ 12፡30 ላይ ውዳሴ ማርያም በዜማ፥ ክስተተ አርያም በዜማ፤ እንዲሁም መስተጋብዕ በዜማ ከደረሰ በኋላ የትምህርቱ መርሐ ግብር እስከ ምሽቱ 2፡30 ድረስ ይካሔዳል፤ ከ32 ዓመታት በፊት የዜማ ትምህርቱ በተጀመረበት ወቅት ግን መርሐ ግብሩ ላይ ይደርሱ የነበሩት የዜማ ይዘቶች አሁን የሚደርሱት እንዳሉ ሁኖ ሌሎች የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶችም የሚጨምር ነበር፡፡ ይህ የዜማ ትምህርት ከቀድሞ የወረሰውን የፍልሰታ ልዩ የሱባኤ የጸሎት መርሐ ግብር እና የደብረ ታቦር ዝክርን፤ አሁንም ሳይቋረጥ አሁን በመማር ላይ ያሉ፣ ከዚህ በፊት የተማሩና የደብሩ ማኅበረ ካህናትና ዲያቆናት በአንድነት በመኾን ሱባኤውንና የደብረ ታቦር ዝክሩን አጠናክረው የቀጠሉበት ኹኔታ ነው ያለው፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958

3. ከድንጋይ ላይ ሁኖ ወርቅ ዘንግ ወርውሮ ያፈለቀው ማየ ጸሎት ማየ ዮርዳኖስ ብሎ የሰየመው 4. ቁመት ጨምራ ከመሬት ተነስታ እንደ ሰው አፍ አውጥታ የመሰከረችው ዋንጫ 5. ጻድቃኑ ይወቅጡበት የነበረ የድንጋይ ሙቀጫ 6. በማኅበራቸው ጊዜ ሲደግሱባቸው የነበሩ የድንጋይ ገበታዎች 7. ከሀገራቸው ከሮም ያመጡት ባለመስታወት ቋሚ ዕፀ መስቀል፡፡ 8. ርዕሰ ዮሐንስ የሚባል ነገሥታት ከነዘውዳቸው፥ ጳጳሳት ከነአክሊላቸውና ከነመስቀላቸው በዚያን ጊዜ      የተሳሉበት ስዕል፡፡ 9. ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በማህበረ ፃድቃን ዴጌውን ሆኖ ያስተማረበትና የጠመቀበትን በስዕል የሚያሳይ፡፡ 10. ይህ ገዳም በአፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት እንደተገደመና ገዳሙ ራሳቸው የገደሙት የራሳቸው መሆኑን በአክሱም መጽሐፍ ክብረ ነገሥት ላይ ተጽፎ ይገኛል፡፡ መልክኦሙ ለጻድቃን ዘዴጎ፤ ሰላም ለዝክረ ስምክሙ ዘሐዋዝ ጥቀ፤ ለዘይሰምእ በእዝኑ ወበኅሊናሁ ጥንቁቀ:: ጻድቃን ዘዴጎ እበይክሙ ተአውቀ፤ እመ በትህትና ማእከሌክሙ ረፈቀ፤ ሊቀ ጠቢባን ክርስቶስ ዘይሜህር ጽድቀ፡፡ (ምንጭ፤ በዋሊ ጉዞ ላይ የገዳሙ አባቶች በቃል ያስረዱን፣ የብሥራት ዕይታ፣ ማኅበረ ዴጎ የምትል ትንሽ መጽሔት) /#ዋልድባ_ዋሊ/