en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 334 subscribers, ranking 5 646 in the Religion & Spirituality category and 2 192 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 334 subscribers.

According to the latest data from 18 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -95 over the last 30 days and by 11 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.81%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.33% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 344 views. Within the first day, a publication typically gains 1 430 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 22.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 19 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 334
Subscribers
+1124 hours
-67 days
-9530 days
Posts Archive
ሥርዐተ ማኅሌት ዘኅዳር ፲፫ በዓለ አዕላፍ መላእክት ልዩ አዋጅ ዘኅዳር አእላፍ መላእክት የኅዳር አዕላፍ መላእክት የማኅሌቱ ሥርዐት በዋነኝነት ‹‹የመልክአ አዕላፍን›› የሚከተል ነው፡፡ ነገር ግን እንደ አዲስ አበባ ደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ያሉት ደግሞ ‹‹መልክአ እግዚአብሔር አብን›› ይከተላሉ። በዚህ ሥርዓተ ማኅሌት ውስጥ ‹‹የመልክአ አእላፍ››ን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ያስቀደምን ሲሆን በመቀጠልም የአዲስ አበባ ደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያንን ሥርዓተ ማኅሌት አያይዘን አስቀምጠናል። ‹‹የመልክአ አዕላፍ››ን ቁመት የሚቆሙ አድባራት እንደ አጣጣሚ ሚካኤል እና ፊት ሚካኤል ያሉትን ከነዚቆቻቸው አስቀምጠንላችኋል። ✤ መልካም በዓል ይሁንላችሁ✤

#ኅዳር_13_በዓለ_እግዚአብሔር_አብ_ወአእላፍ_መላእክት፤ በደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ካቴድራል የዚህ ደብር ታሪክ እነዲህ ነው፤ በደብሩ የሚገኝው የእግዚአብሔር አብ ታቦት #በደብራችን_በቀጨኔ_ደብረ_ሰላም ይገኝ ነበር፡፡ በታላላቅ አባቶችም ይህ ታቦት ወጥቶ ወደ አሁኑ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ ሥፍራ እንደሚሄድ #የበቁ_አባቶች_ይናገሩ_ነበር፡፡ እንደተናሩትም ሐምሌ 29፤ 1969 ዓ.ም ታቦተ ሕጉ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወጥቶ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ቤት አረፈ፣ ቤተhርስቲያኑም እራሱን ችሎ እስኪቆም ድረስ የደብራችን የቀጨኔ ደብረ ሰላም  መድኀኔዓለም አገልጋዮች #በቅዳሴ_በማኀሌት_በሰዓታት ያገለግሉ ነበር :: ከዚህም በኃላ ጥር 19 ቀን 1971 ዓ.ም የመጀመሪያው ቤተከርስቲያን አልቆ ተመርቋል፡ የቤተክርስቲያኑ ዲያቆናት ፣ ቀሳውስት እና መሪጌቶችም በጊዜያዊነት ተቀጠርው ነበር ሆኖም የአገልግሎት ፍቅር ያደረባቸው የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቃውንት አልግሎታቸውን አላቆሙም ነበር። ታላቁ ሊቅ አለቃ ኤልያስ ነቢየ ልዑል ከመኖርያ ቤታቸው ቀጨኔ ድረስ በምጣት ለደብሩ ታላቅ አሰተዋጽዖ አድርገዋል። እሁን ያለው ሕንፃ ቤ.ክ የደብተራ ኦሪት እና የኖኀ መርከብን ቅርጽ ይዞ በቅድስቱ አካባቢ ያለው አሠራር ደግሞ ክቧን ቤ.ክ ሆኖ ተሰረቶ በ2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ተመረቋል፡፡ የቅዱስ እግዚአብሔር አብ ታቦትም ኅዳር 13 እልፍ አእላፋት መላእክት በሚከሩበት ዕለት ይከብረል። በዚሁ ደብር ኅዳር 25 #የሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ በዓልም ይከበራል ( ታቦቱ በድርብነት አለ) የእግዚአብሔር ቸርነት የአእላፍ መላእክት ተራዳኢነት አይለየን! • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#አንኳን_ለቅዱስ_አግዚአብሔር አብ በዓልና_ለአእላፍ_መላእክት_በዓለ_ሢመት  እንዲሁም #ቅዱስ_ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 ጀምሮ እስከ 13 ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን ለሚለምንበት)  በዓል በሰላም አደረሳቹህ፡፡ ፨ ፨ ፨ #ኀዳር_13  ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሊቃውንት #አእላፍ መላእክት እየተባለ ይጠራል ፤ 99ኙ ነገደ መላእክት በአንድ ላይ የሚከብሩብት ቀን ነው እንዚህም ሥጋ የሌለቸው ረቂቃንና ለዓለም ሁሉ የሚማልዱ ናቸው ፡፡       #Share ያድርጉ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ 100 በክፍለ ነገድ 10 አድርጓቸዋል ፡፡ በ3 ሰማያትና በ10 ዓለማት ላይም ይገኛሉ፡፡ መላእክት ያሉባቸው ከተሞች #ኢዮር #ራማ #ኤረር ይባላሉ ፡፡ አሥሩ ነገዶች ከነአለቆቻቸው አንዲህ ናቸው 1.  #አጋዕዝት (ቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል የነበረ ፤ አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ስር ናቸው) 2.  #ኪሩቤል (አለቃቸው ቅዱስ #ኪሩብ ፤ ለበለጠ ኀዳር 7 የጻፍነውን  ይመልከቱ) 3.  #ሱራፌል (አለቃችወ ቅዱስ #ሲራፊ ፤ ለበለጠ ኀዳር 24 ይጠብቁን) 4.  #ኃይላት (አለቃቸው ቅዱስ #ሚካኤል  ) 5.  #አርባብ (አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ) 6.  #መናብርት (አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል) 7.  #ሥልጣናት (አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ) 8.  #መኳንንት (አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ) 9.  #ሊቃናት (አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል) 10.  #መላእክት (አለቃቸው ቅድስ አናንኤል) ናችው፡፡ ከእነዚህም  ፨ አጋዕዝት ፣ኪሩቤል ፣ ሱራፌልና ኃይላት መኖርያቸው በኢዮር(3ኛው ሰማይ ) ነው ፡፡  ፨አርባብ ፣መናብርትን ሥልጣናት መኖርያቸው በራማ ነው ፡፡  ፨መኳንንት ፣ሊቃናት ፣ መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር ነው (1ኛው ሰማይ ) ———- (ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤  #ሚካኤል_ወገብርኤል፥ #ሱራፌልወኪሩቤል/፬ቱ እንስሳ/፥  #ዑር(ራ)ኤል_ወሩፋኤል /፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ/፥ #ሱርያል_ወፋኑኤል፥ #አፍኒን_ወራጕኤል፥ #ሳቁኤል_ወአቅናኤል፥ #ብርናኤል_ወሱባኤል፥ #ፍናኤል_ወሰላታኤል፥ #ሰዳካኤል_ወኤልናኤል፥ #አናንኤል_ወኢየሩማኤል፥ #ግርማኤል_ወድርማኤል ፥  #ድማህኤል_ወአድማኤል፥ #ሙራኤል_/ምናቴር_አብያቴር/፥ #ሱታ(ስቱ)ኤል_ወሱርያል፤ ……. ፨ ፨ ፨ ፨   የመላእክት ተፈጥሮ እመኀበ አልቦ ኀበ ቦ (ካለመኖር ወደመኖር ) ነው ፡፡ አይራቡም አይጠሙም ፤አይዋለደሙ ፣ አይሞቱም ፣ ዕረፍት የላቸውም ፤ምስጋናቸው  እረፍታቸው ፤እረፍታቸው ምስጋናችው ነው አንጂ(አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ) እንዲል፡፡  ተፈጥሯቸው እጅግ ረቂቅ ነው፡፡ ተግባረቸውም ዘውተር እግዚአብሄርን  ማመስገን ነው፡፡ —— #መላአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም ፤ ለመዓትም ይላካሉ፡፡ ምሕረትን ያወረዳሉ ፡፡ ልመናን ያሳርጋሉ  ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ አንዲዚሁም ሁሉ ወቅትንም የሚቆጣጠሩ አሉ ፤ ስለ ሰው ልጆች ይማልዳሉ (ዘካ 1÷12 ) ምሥጢርም የሚገልፁም አሉ(ዳን 9÷21) መላእክት ተራዳኢም ናቸው  (ኢያ 5÷13)፣ እነዳንሰናክል ይጠብቁናል (መዝ 90÷11 ) ፣ያድናሉ ( መዝ 33÷7 ) ፣የፀጋ ስግደትም ይገባቸዋል (መሳ 13÷20)   በፍርድ ቀንም ኀጥአንን ከጻድቃን ያለያያሉ (ማቴ 25 ÷31) እነሆ እግዚአብሄር ይፈርድዘንድ ቅዱሳን መላእክቶቹን አስከትሎ ይመጣል እንዲል ፡፡ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት  ፨፨፨ እልፍ አእላፋት ወትእልፊት ቅዱሳን ንጹሐን መላእክት ቆሙ በአገልግሎት ጸንተው በአንድነት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አምላክ በማለት፡፡ ምልጃቸው እና ጠብቆታቸው አይለየን አሜን ፡፡ —————— ኀዳር 13  ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹ፤ ከፎቶ ጋር  …. 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤ 2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤ 3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን (በሰሜን ሸዋ)፤ 4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (አዲስ አበባ)፤ 5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) 6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ስዕለት_ሰሚዋ_ፉሪ_መንበረ_ንግሥት_ቅድስት_ሐና_ቤተክርስቲያን_አጭር_ታሪክ ✝ የተተከለችው በ1920ዓ.ም ነው። ✝ ተካይዋም #ግርማዊት_እቴጌ_መነን ናቸው። ቦታውም ከመላው ፉሪ እና አካባቢው ጋር የእናታቸው የወይዘሮ ስኂን መሬት ነበር፤ የሰጧቸውም #ዳግማዊ_አፄ_ምኒልክ ነበሩ። ✝ ቤተክርስቲያኒቱ የተተከለችው የአካባቢውን ሕዝብ መንፈሳዊ እና ሐዋሪያዊ ችግር ለማቃለል ለባለርስቷ እናታቸው ወይዘሮ ስኂን #መታሰቢያ ነው። ✝ ታቦተ ሕጉ የመጣው ከታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ነው። ታቦቱን ያስገቡት ሊቀ ሊቃውንት ገብረ አብ፥ የኋላው #አቡነ_ፊልጶስ ናቸው። ✝ እቴጌ መነን በበዓታ ለማርያም ገዳም ስር እንድትተዳደር አስበው የነበረ ቢሆንም በዓታ ብዙ ቅፈፍ ስለነበራት በጊቢ ገብርኤል ሥር ስትተዳደር ቆይታለች። ✝ መንበረ ንግሥት ሰበካዋ ሰፊ ነበር፤ አሁን ግን በሰበካዋ ላይ ከሃያ በላይ አቢያተ ክርስቲያናት ተተክለዋል። ✝ አስተዳደሯም በቤተክህነቱ ተጠባባቂነት ተጠቃሎ በሕዝበ ክርስቲያን ትከሻ ላይ አርፏል። ምንጭ፦ የቤተክርስቲያን መረጃዎች፤ ዳንኤል ክብረት ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ፲፩ ኅዳር ፳፲፯ ዓ.ም ከእናታችን ቅድስት ሐና ረድኤት በረከቷን ያሳድርብን፤ በምልጃዋ ትጠብቀን ✝

#የክርስቶስ_አያት #ቅድስት_ሐና ኀዳር 11 በዚህችም ቀን ፀሐይን እና ጨረቃን ለሚገዛ፣ ሰውን በአርያውን በመልኩ ለፈጠረ ፈጣሪያችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ #አያት የሆነች፤ ለእመቤታችን ለቅድስት ቅዱሳን ድንግል ማርያምም #እናቷ የሆነች የተመሰገነች እና የከበረች #ቅድስተ_ሐና ዕረፋቷ ነው፡፡ #ቅድስት_ሐና በኢየሩሳሌም ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሚልኪ ልጅ ለሆነው ማጣት ለተባለ ሰው ልጁ ናት፡፡ #ማጣትም 3 ልጆች አሉት፤ እነርሱም፦ 1) #የመጀመሪያይቱ ስሟ ማርያም ነው፤ አዋላጅ የነበረች ስትሆን ቅድስት ሰሎሜን ወልዳለች፤ ሰሎሜም እመቤታችን መድኃኒታችንን ከወለደችው ጀምሮ በስደቷም ወራት ከአረጋዊ ዮሴፍ ጋር እመቤታችንን ያገለገለቻት ናት፡፡ 2) #ሁለተኛይቱ ስሟ ሶፍያ ነዉ ፤ ይህቺ ቅድስተ ለመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እናት የሆነችውን ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች፡፡ 3) #ሦስተኛይቱም ስሟ ሐና ነው፤ ይህች ቅድስት ሐናም የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደቻት፡፡ ቅድስት ሰሎሜ፣ ቅድስት ኤልሳቤጥ እና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእኀትማማች ልጆች ናቸው፡፡  የሐና ወላጆች ልጃቸውን በሥርዓት አሳደጓት፡፡ ለአካለ መጠን ስትደርስም ከይሁዳ ነገድ ለሆነ ጻድቅ ስሙም ኢያቄም የተባለውን ጻድቅ ሰው አጋቧት፡፡ ሐና ግን ልጅ መውለድ አልቻለችም ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀንም ቅድስት ሐና ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲጫወቱ ተመልክታ «ፈጣሪ ሆይ! የእንስሳትን ማኅፀን የምትከፍት ዕፅዋትንም ከባሕርያቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ እውነትም ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?» ስትል አለቀሰች። ቅዱስ ኢያቄምም ወደ ተራራ ወጥቶ ለዐርባ ቀናት አለቀሰ። ይህ ሲሆን ሁለቱም አርጅተው ነበር። ፈጣሪ ልጅ ከሰጣቸው ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ እንዲሆን ለመስጠት ስእለት ተሳሉ፡፡ በሐምሌ ፴ ቀን ኢያቄም ለሐና ራእይ አየ፤ ነጭ ርግብ ፯ቱን ሰማያት ሰንጥቃ ወርዳ በራሷ ስታርፍ በቀኝ ጆሮዋ ገብታ በማኅፀኗ ስታድር አየ፤ ሐናም ለኢያቄም ፀምር ሲያስታጥቁህ መቋሚያህ አብባ አፍርታ ፍጥረት ሁሉ ሲመገባት አየሁ ብላ» ነገረችው፡፡ ከዚህም በኋላ በነሐሴ ፯ በዕለተ እሑድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፀንሰቻት፤ ይህም ለእነርሱም ለወገኖቻቸውም ታላቅ ተድላ ሆነ። ብፅዕት ሐና ግን ፈጣሪዋን ታከብረው ዘንድ በጐነትንና ንጽሕናን አበዛች። ፀንሳ ሳለም ዕውራንን አበራች፤ ድውያንን ፈወሰች። የጦሊቅ ልጅ በሞተ ጊዜም እያለቀሰች ስትዞረው ጥላዋ ቢያርፍበት አፈፍ ብሎ ተነሥቶ፦ «ሰላም ለኪ እሙ ለፀሐየ ጽድቅ» ብሎ ድንግል ማርያምን «ወሰላም ለኪ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ» ብሎ ቅድስት ሐናን አመስግኗል። ትርጉሙም ድንግልን «የፀሐየ ጽድቅ እናቱ» ሐናን «ሰማይና ምድርን ለፈጠረ አያቱ» ማለት ነው። ይህንን ያዩ አይሁድ ቅድስት ሐናን ሊገድሉ ብዙ ጊዜ ሞክረዋል። ነገር ግን መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል አልፈቀደላቸውም። ቅድስት ሐናም እመቤታችን ቅድስት ማርያምን በፀነሰች በ፱ኛው ወር ግንቦት ፩ ቀን ነቢያት የተናገሩ ትንቢት ይፈጸም ዘንድ በአምስት ሺህ አራት መቶ ሰማንያ አምስት ዓመተ ዓለም በፈቃደ እግዚአብሔር ወለደቻት። ይህችም ቅድስት ሰማይና ምድርን ለፈጠረ ማደሪያ ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር አምላክ ለመረጣት ከፍጥረት ሁሉ የተለየችና የከበረች ቅድስት ድንግል ማርያምን ለመውለድ የተገባች ሆናለች፡፡ ቅድስት ሐናና ልጇ ሦስቱ ዓመታት እስኪሆናት ከክንዷ አውርዳት አታውቅም ነበር። አንድ ጊዜም መላእክት ወስደውባት ፍጹም አልቅሳለች። ከዚህም ግን መልሰውላታል። ነገር ግን ስእለታቸውን የሚሰጡበት ጊዜ በደረሰ ጊዜ ሳይሰስቱ ለእግዚአብሔር ቤት እንድታገለግል ሰጧት፤ ቅድስት ሐናም ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ ከገባች በኋላ የእናትነት ፍቅሯ እያገበራት ለአምስት ዓመታት እየተመላለሰች ትጐበኛት ትስማትም ነበር። እመቤታችን ስምንት ዓመት በሞላት ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ጥሪ ወደ ቅድስት ሐና ደረሰ። ከክርስቶስ ልደት ስምንት ዓመታት አስቀድማ ብፅዕት እናት ቅድስት ሐና በኅዳር ፲፩ ቀን ዐረፈች። ጌታ የዘር ሐረግ ውስጥ የተቆጠሩ ሁሉ ክቡራን ናቸው የመጨረሻዎቹ አያቶቹ ደግሞ የመጨረሻው ክብር ይገባቸዋል እነርሱም ሐና እና ኢያቄብ ናቸው፤ አምላካችንን የልጅ ልጅቻችን ነው ለማለት ተገብተዋልና። ቅድስት ሐና ከሴቶች ሁሉ የምትከብርና የምትበልጥ መሆኗን አምላክን ለወለደችልን ለቅድስት እናታችን ድንግል ማርያም እናት ሆና አይተናል፤ ከሴቶች ሁሉ የሚበልጥ ትሩፋትና ተጋድሎ ባይኖራት ይህ ጸጋ ባልተገባት ነበር፡፡ አባቶችም ታጋድሎዋ እጅግ ብዙ እንድሆነ ነግረውናል፡፡ ---ምልጃዋ አይለየን፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን፤ አሜን! ሃገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን እና ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን ትጠብቅልን አሜን!      አርኬ ሰላም ለኪ ለጸሎተ ኵሉ ምዕራጋ፡፡ ከመ አስካለ ወይን ዲበ ሐረጋ፡፡ ሐና ብፅዕት ተፈሥሒ እንበለ ንትጋ፡፡ እስመ ረከብኪ ምገሰ ወአድማዕኪ ጸጋ፡፡ እምሔውተ አምላክ ትኵኒ በሥጋ፡፡ 👇በቦታው ሄዳቹ በዓሉን ማክበር ለምትፈልጉ👇 (ፎቶዎቹ፤ በአዲስ አበባ እና በሌሎች የሚገኙ የቅድስት ሐና አብያተ ክርስቲያናት ...) 👉 ኮተቤ መካነ ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ቤ/ክ ፡ 👉 ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና:: 👉 በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በደብረ መንክራት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በደባልነት ትገኛለች 👉 ደብረ ንግስት መንዝ ቅድስት ሐና ሌሎች በዓሉ የሚከብሩባቸውን ቦታዎች  ኮሜንት ላይ ያጋሩን /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ/ #share .Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot      www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፬. ሸኖ ጎልባ ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሚካኤል ደብር፤ (በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰኖ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ሸኖ፡፡ ፭. መላሃይዘንጊ ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ8ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፮. ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ የታነፀ፥ ከ11ዱ የላስታ ላሊበላ ፍልፍል ሕንጻዎች አንዱ) አድራሻው፤ ላስታ ሀገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡ ፯. ገርዓልታ ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል፤ አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ገርዓልታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ገርዓልታ፡፡ ፰. ሚካኤል ዓምባ፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ውቅሮ፥ (በመቀለና በአዲግራት መሃል)፥ አጽቢ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ውቅሮ → አጽቢ፤ ፱. ባሕር ዳር ሽምብጥ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ13ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13 ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር ከተማ → ሆስፒታል በሚል ታክሲ (ዲፖ ጋር)፡፡ ፲. እስቴ አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ፤ (በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በልጃቸው በአቡነ ፊልሞና የተሠራ ታሪካዊ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ ወረዳ፥ ደስኳ አጋማች ቀበሌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፩. በሮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ በ16ኛው መ/ክ/ዘመን መጨረሻ የተመሠረተ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሳይንት ወረዳ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → አማራ ሳይንት፡፡ ወይም፤ ከጎጃም በመርጠሉ ማርያም → አማራ ሳይንት ፲፪. ጎንደር ፊት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት ተመሠረተ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፫. ጎንደር አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፬. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፭. አጃና ቅዱስ ሚካኤል፤ (በቀስተ ደመና ጠበል አጥማቂው) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ አጃና፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ → አጃና፡፡ ፲፮. ቦንብ አርግፍ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት፤ የጁ ወልዲያ) ፲፯. ቦረዳ ቅዱስ ሚካኤል ፲፰. ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ ኢቲሳ) ፲፱. አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፵፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ 1.. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ ሚካኤል ጎሚስታው ሚካኤል (ትግራይ) እንዳ ቅዱስ ሚካኤል (ትግራይ) መቀለ ቅዱስ ሚካኤል 5. ጾረና ቅዱስ ሚካኤል (ኤርትራ) ዓለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ዘይት /ቢሾፍቱ/ ደብረ አሚን ቅዱስ ሚካኤል ዱከም ቅዱስ ሚካኤል ናዝሬት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 10. ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል ጭሮ አሰበ ተፈሪ ቅዱስ ሚካኤል (ድሬዳዋ፥ አሰበ ተፈሪ) ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል አርባ ምንጭ ላከ ኢየሱስና ሚካኤል ዲላ ቅዱስ ሚካኤል 15. አሰላ ደብረ ሰላም ቅድስ ሚካኤል ጂጂጋ ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ቴፒ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ቦንጋ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ኢሉባቦር ሌንቃ ቅዱስ ሚካኤል 20. እነሞርና ኤነር ወረዳ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራጌ ሀ/ስብከት) አሰቦት ደብረ ወገግ ቅዱስ ሚካኤል (ምሥ. ሀረርጌ ሀ/ስብከት) ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ኩክ የለሽ ዛሪያ ቅዱስ ሚካኤል ጅሩ ሞቶሎኒ ቅዱስ ሚካኤል (ጅሩ አርሴማ ውስጥ) 25. መንዝ ይገም ቅዱስ ሚካኤል መሐል ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የሲጠር ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ) ወንጪት ቅዱስ ሚካኤል (በነብር የሚጠበቅ) ሸዋሮቢት ጫሬ ቅዱስ ሚካኤል 30. ወልዲያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል ደሴ ጢጣ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ራያ ቆቦ ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ማርቆስ ዋሻው ቅዱስ ሚካኤል 35. ደብረ ማርቆስ አጠገብ ብዕርና ቅዱስ ሚካኤል ደምበጫ ቅዱስ ሚካኤል መርዓዊ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ባሕር ዳር ድባንቄ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል አዘዞ አይራ ቅዱስ ሚካኤል 40. ዛራ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ ሐሙሲት) ጉመር ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ሚካኤል ካምባ ቅዱስ ሚካኤል ሳንቃ ወይራ ቅዱስ ሚካኤል ዳስ ዓምባ ቅዱስ ሚካኤል 45. ላሐ ቅዱስ ሚካኤል 46. ጊራራ ቅዱስ ሚካኤል 47. መለኮዛ ቅዱስ ሚካኤል 48. ዋይሎ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል

አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 10 ከጉራራ ከፍ ብሎ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ጉራራ፡፡ ፲፮. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩዋንዳ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ወረገኑ፡፡ ፲፯. ቃሊቲ ሰፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፲፰. ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሃራብሳ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ንቡ ሚካኤል፡፡ ፲፱. ጀሞ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ #እንዲሁም_በአንድነት_በተሠሩ_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳. ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ጎላ (ኢምግሬሽን ጀርባ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል (ኢምግሬሽን)፡፡ ፳፩. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ዮሴፍ፥ ደጃዝማች መርዕድ መንገድ፥ ቀለበት መንገድ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ከላጋር (ከፒያሣ) (ከ4 ኪሎ) (ከቦሌ)(ከመገናኛ) → ቃሊቲ መናኸሪያ /በቀለበት መንገድ/ ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፳፪. ጀሞ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ፳፫. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፳፬. ኮተቤ ማኅደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሎቄ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሎቄ፡፡ ፳፭. ፉሪ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡ ፳፮. ቂሊንጦ መካነ ፍስሐ ቅዱስ ሚካኤልና በዓታ ለማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ አደባባይ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፳፯. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ ኬላ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቱሉዲምቱ፡፡ #እንዲሁም_በድርብነት_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳፰. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ → 6 ኪሎ (ማርቆስ)፡፡ ፳፱. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቦሌ በሚል ታክሲ → መስቀል ዐደባባይ፡፡ ፴. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች በሚለው ታክሲ → ልደታ፡፡ ፴፩. ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አረዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ (አርበኞች መንገድ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → በዊንጌት አስኮ /ሩፋኤል ፊንሐስ/ ታክሲ →  ዮሐንስ፡፡ ፴፪. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ፥ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት፡፡ ፴፫. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ልኳንዳ፥ ፈጥኖ ደራሽ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ → ልኳንዳ → (በስተግራ ባለው አስፓልት በእግር 5 ደቂቃ ፈጥኖ ደራሽ ማሰልጠኛ)፡፡ ፴፬. ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተ ማርያም ወቅድስት ልደታ ወቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻው፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ ካኦ ጄጄ ዱቄት ፋብሪካ፥ ቃሌ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → አስኮ፤ ፴፭. ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → የሺ ደበሌ፡፡ ፴፮. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ ፴፯. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ (ካራ) ፴፰. ረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ቆሬ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → አለም ባንክ → ካራቆሬ (ረጲ)፡፡ ፴፱. ፉሪ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጋራ ኦዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጋራ ኦዳ፡፡ ፵. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ወርቁ ሰፈር፡፡ ፵፩. ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሰፈረ ገነት፡፡ ፵፪. ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባና ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም (ኮንዶሚኒየም)→ ወደ ላይ በአስፓልቱ የ5 ደቂቃ የእግር መንግድ፡፡ ወይም፤ ከቦሌ መድኃኔ ዓለም → ቡልቡላ (በአዲሱ መንገድ) ፵፫. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ፥ ጋራው መድኃኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡ ፵፬. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሣሎ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፲፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #እየላ_ቅዱስ_ሚካኤል፤ (#የ3 #ሺህ_ዓመታት_ባለታሪክ፤ ከታቦተ ጽዮን ጋራ በ980 ከክ.ል.በ. ታቦቱ የመጣ፤ መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መጥቶ የባረከው) ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ግዳን (እየላ)፡፡ ፪. ሰሜን ትግራይ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል፤ (መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) አድራሻው፤ ሰሜን ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ሰሜን ትግራይ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፫. ጎሐ ጽዮን ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተሠራ)

ኅዳር 12 ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡ (እንኳን አደረሳችሁ) በዓለ ሢመቱ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ በእለተ እሁድ ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ሲሆን እርሱም የነገደ ኃይላት አለቃቸው ነው በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የአጋእዝትን ነገድም በአለቅነት ደርቦ የያዘ ሲኾን፡፡ ለ100ውም(99ኙም) ነገደ መላእክት አለቃቸውም ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (በዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ 13 (የአእላድ መላእክት) በዓል ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን የሚለምንበት ነው፡፡ በዚህ ቀን የሚከበረው እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እያመራቸው ማውጣቱን ለማዘከር ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ በ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ በ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ ፈርኦን በግብፅ ነገሠ፡፡  እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው ፍርድ አጓደለባቸው፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ 430 ዘመን በባርነት ከቆዩ በኋላ ከእብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ እንዲያሳርፉዋት ጠየቀች ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል ርገጭ  አሉዋት፡፡ ከመሐጸኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች፡፡ ራሔልም አለቀሰች ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡ የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባ የሕዝበ እስራኤል ሁሉ ጩኸት እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 (ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ) በማድርግ ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡  ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ንሴብሆ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ ጠላታቸውን የመታላቸውን እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መና ከሰማይ እያወረደላቸው ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ቀኑን በደመና ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጉዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓን ገብተዋል፡፡ /ዘጸ 15/ ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡ ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡ ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቢ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን፤ ከበዓሉ በረከት ይክፈለን፡፡                               #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_ #፵፬ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በኦሪት ዘመን መሥዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፥ ዋሻ ቤተ ክርስቲያኑ በ4ኛው ክ/ዘመን በአብሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ መገናኛ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ፤ ፪. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ራስ ካሳ ሚካኤል) (ጭቁኑ)፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ራስ ካሳ ታክሲ፤ ከ4ኪሎ(ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ፡፡ ፫. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (አዲሱ ሚካኤል) አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ አውቶቡስ ተራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → አውቶቡስ ተራ፡፡ ፬. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ወህኒ ቤት) (ከርቸሌ) አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ ቡልጋርያ (ከርቸሌ) (አፍሪካ ኅብረት)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ቄራ፡፡ ፭. ኮተቤ (ሲኤምሲ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲኤምሲ) አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሲኤምሲ፡፡ ፮. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፯. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፰. ቤተል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፱. ኤረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ፒያሳ) → ጎሮ፡፡ ፲. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቀጨኔ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ)(ከአዲሱ ገበያ) → ቀጨኔ፡፡ ፲፩. አያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፪. ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፫. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ሚካኤል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቦሌ ሚካኤል፡፡ ፲፬. የካ አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፭. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤

#እንኳን ለበዓለ ‹‹ኪሩቤል›› አርባዕቱ እንስሳ  በሰላም  አደረሳቹህ::   ኅዳር ፰፤ አርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) | አራት ኪሎ ቤ.ክ በዓሉ በድምቀት ይከብራል :: *በኢትዮጵያ ሀገራችን የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) ዓመታዊ ክብረ በዓል የሚከበሩባቸው አድባራትና ገዳማት በጥቂቱ:-  ከታች ይመልከቱ ::   #share  ያድርጉ ----- ከእግዚአብሔር በቀር የሚቆጥራቸው የሌለ የብዙ ሠራዊተ መላእክት በሰማይ ያሉ ሲሆን በዙውን አንድ እያልን  በነገዳቸው እንቆጥራል፡፡ ስንቆጥርም የመጀሪያዎቹ ኪሩቤል (አርባዕቱ እንሳሣ )ናቸው ፨  ኪሩቤል ቃሉ ከአካድ/ጥንት ባቢሎናውያን ቋንቋ / የተወረሰ ሲሆን ትርጉሙም አማላጅ፣ኃያል፣ታላቅ ማለት ነው፡፡በአራቱ እንስሣ አምሳል የተገለጹ ጸውርተ መንበሩ  ኪሩቤል ናቸው ፡፡ #ኪሩቤል የብዙ ቁጥር ሲሆን በነጠላ #ኪሩብ ይባላል፡፡ ፨  መላእክት ሆነው ሳለ ‹‹አርባዕቱ እንስሳ›› የተባሉበት ምክንያት ለቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በእንስሳት አምሳል በመገለጻቸው ነው፡፡ ፨  ኪሩቤል ከመቶው ነገድ መላእክት የአስሩ ነገድ መጠሪያ ስም ነው ፨  ከ3ቱም ሰማየ መላእክት በመጀመሪያይቱ በኢዮር ላይ ከአጋዕዝት በታች በ2ኛይቱ ከተማ የሰፈሩ ናቸው፡፡ ፨  ከእግር እስከ ራሳቸው በዓይን ተሸልመዋል  - ዓይናቸውን እንደ ነብር ለምድ ዥንጉርጉር  ነው፤አንድም እንደ መስታወት ስድ ነው ፤ ይኸውም ኪሩቤል ኃላፊያትንና መጻእያትን የማወቅ ክሂል ከልዑል አምላክ መቸራቸውን ያሳየናል ፤ ይህም የእግዚአብሔር ስራ ገደብ የማይጣልለት የቸርነት ሥራ ነው፡፡ መዝ 87፥ 35 ፨ነቢዩ ሕዝቅኤል እንደተመለከታቸወ ‹‹ ኪሩባውያን አፍራሱ ፤ ፈረሶቹ ናቸው ሲል ይገልጻቸዋል፡፡ ግብራቸውም  ዙፋኑን ተሸክመው ሥላሴ ለወደዱት መገለጽ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ዙፋኑን ተሸክመው ይዘዋወራሉ  ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሔር መገለጽ ሲፈልግ  ዙፋኑን በዘፈቀደ ተሸክመው ስለሚታዩ ነው ፡፡ ፨ከአራቱ ኪሩቤል አንዱ ‹‹  ባራ ማራ  ›› የሚባል ነው አንደኛነቱ የቁጥር እንጂ የክብር መበላለጥ አይደልም፡፡ ትርጕሙም ባራ ማለት በራ ማለት ነው ፡፡ በተፈጥሮ በራነት እንዳለ በመሸከምም  በራነት ይኖራል ፡፡ ጸዋሬ መንበርነቱን ሲመለከትም ‹‹ ባራ ማራ መሊጦን ›› ብሎ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በምድራዊ ግሥ  ገልጾታል፡፡ ፊቱም በአንበሣ ምስል ይገለጻል፤ ‹‹ ወቀዳሚ ይመስል አንበሳ ፤ የመጀመሪያው አንበሣን ይመስላል ›› እንዲል ራዕ 4፡፡ አንበሣ የአራዊት ንጉሥ ነውና በአለቃቸው ተመሰለ፡፡በአንበሣ መገለጹ ኃያልነቱን ሲያሳይ ነው ፍጻሜው ግን ‹‹ ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ›› የተበላው ክርስቶስ ይገለጣል ነው፡፡  ግብሩ ለአራዊት መለመን ሲሆን  በሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ መመሰሉም የጌታን ሃያልነት ገልጾ  ከማስተማሩ ጋር እና በአምሳለ አንበሳ የተሰሩ የግብፅ ጣዖታትን ቀጥቅጦ በማጥፋቱ ነው ፡፡ ፨‹‹መሊጦን መልአክ ›› ይህ ደሞ ሁለተኛው ሲሆን ሁለተኝነቱ የቁጥር እንጂ የክብረ መበላለጥ አይደልም፡፡ ትርጉሙም ዓምዳዊ ዘዐምድ እንደማለት ነው ዙፋኑን ተሸክሞ ‹‹ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ›› ብሎ ማመስገኑን ያሳያል ይህም መላእክት የሰማይ አምድ ናቸው  ማለት ሳይሆን ግብራቸውን ያሳያል ፡፡ ቅዱስ ያሬድም ባራ ማራ .. መሊጦን ሲል ያዜማል፡፡‹‹ወካልዑ ይመስል ከመ ላሕም ››ሁለተኛውም ላም ይመስላል እንዲል ›› ራዕ እንዲል በላሕም ተመስሏል፡፡ በዚህም የተመሰለው ሉቃስ ሲጽፍ ‹ ‹ያን ላም አምጡት አርደን አወራርደን እንብላው ››  ሉቃ 15 ሲል ምሥጢረ ቁርባንን ጸፏል ፤ መሰየሙም ለዚህ ምክንያት ነው ፡፡ ፨‹‹እግረ ማጣ›› መልአክ ደግሞ አንዱ ነው ፡፡ቅዱስ ያሬድ ጸወርተ መንበር ብሎ በአንድነት ገልጻቸዋል፡፡ አምላካችንን በንጉሥ ፣ መንበረ ምንግሥቱን በኮር ፣ ሰማይ ውዱድን በአልጋ ፣ ኪሩቤልን በአራቱ እግሮቹ መስሎ ነው ፡፡ ይህ ከኪሩቤል አንዱ የሆነው መልአከ ፊቱ የሰው ልጅን ይመስላል ‹‹ወሣልሱ ይመስል ከመ ገጸ እጓለ እመ ሕያው ›› እንዲል   ራእ 4 ፡፡ ይህ የሰው ፊት ያለው በማቴዎስ ይመሰላል ማቴዎስ ከአብርሃም ጀመሮ እስከ እመቤታችን ድረስ ልደተ አበውን ጸፏልና ፡፡ ፨‹‹ሱርትዮን መልአክ››   ይህ ደግሞ ትርጓሜው አገልጋይ ማለት ነው ፡፡ እሱም ዙፋኑን ተሸክሞ  ሲያመሰግን  ይኖራል ፡፡ገጹም ገጸ ንሥር ነው፤፤ ‹‹ወራቡዑ ይመስል ከመ ገጸ ንሥር›› እንዲል ራዕ 4፡፡ይህም ወንጌላዊውን ዮሐንስ የሚመስል ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌሉን ሲጽፍ አመሣጥሮ ስለሚጽፍ ንሥር ደግሞ ከፍ ብላ ሌሎች አዕዋፍ የማይደርሱበትን ሰለምታይ እሱም እንዲሁ በ ንሥር ተመስሏል ፡፡ ፨ኪሩቤል (4ቱ እንሰሳ ) ለተወከሉበት መልክእ ቅድም እግዚአብሔር ጸሎት ያደርጋሉ #የሰው መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹እግረ ማጣ›› #ለሰው ልጅ፣ #የአንበሳ መልክ ያለው ኪሩብ‹‹  ባራ ማራ  ››#ለአራዊት፣ #የላሕም መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹መሊጦን መልአክ ›› #ለቤት እንስሳት፣#የንስር መልክ ያለው ኪሩብ ‹‹ሱርትዮን›› ደግሞ #ለአእዋፍ ሁሉ እየጸለየ ሲጠብቃቸው ይኖራል፡፡ ይህ ማለት ግን ምልጃቸው ገደብ አለው ማለት አይደለም አንዱ ለሌላኛው አንዱም ለሌላው መጸለይ መለመን ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ፨የሰው ፊት ያለው ዕውቀታቸውን ፣ የአንበሣ ፊት ያለው ግርማ ሞገሳቸውን ፣ የንስር ፊት ያለው ተመሥአቸውን ( ሲመሰጡ ሰማየ ሰማያት ይደርሳሉ )፡፡ ትህትናቸው የፍርሃት ምልክት ሲሆን ምድር ምድር የመለከታሉ ይህም ፊቱን ማየት ባሕርዩን መመርመር አይቻለንም ሲሉ ነው ፡፡ ግርማቸው ነበልባል ሲሆን እንደ እሳት ለተልእኮ ይፋጠናሉ ፡፡ አእምሮአቸው ግሩም ሲሆን በእውቀት ከሁሉ በላይ ናቸው ፡፡ አራት ፊትም ስላላቸው ለተልዕኮ አቅጣጫ አይቀይሩም ያለምንም ተፋልሶ ባለቡት ይቀጥላሉ እንጂ ‹‹ ሕዝ 1›› ለእያንዳንዳቸው አራት ክንፍ አላቸው ይህም በአጠቃላይ 16 ይሆናል ፡፡ ክንፋቸውስ 6 ነበር ነገር ግን በሰው አምሳል  ስለተገለጡ ሁሉቱ እጃቸው ነበር ፡፡ እንጂ ያው ስድስት ክንፍ ነው ያላቸው ፡፡ ሁለቱ  ክንፋቸውን ፊታቸውን ይሸፍኑበታል( ባህሪያን መመርምር አይቻለንም ሲሉ ) ሁለቱን ደግሞ እግራቸውን ይሸፍኑበታል( ከፊትህ ጸንቶ መቆም አይቻለንም ሲሉ )  ፣ ሁለቱን ደግሞ አንዱን ወደ ታች አንዱን ወደ ላይ ይዘረጋሉ( ቢወጡ ቢወረዱ አትመረመርም ሲሉ )  ፡፡ ፨የክንፋቸውም ጅግጅታ እንደ ፏፏቴ ከሩቅ ይሰማል ፡፡ ለመላእክት 6 ክንፍ ሲኖራቸው ለእንያንዳንዳቸው ኪሩቤል 16 ክንፍ በጠቅላላው 64 ክንፍ አላቸው ፡፡ ከዚኅ ጋርም ተያይዞ ‹‹ ከኪሩቤል እና ከሱራፌልም እሳ ትበልጣለች ›› የተባለቸው እመቤታችን እንዲዚህ መባሏ አንድም  ኪሩቤል በክንፋቸው ጋርደው አምላከ ምሕረት ክርስቶስን ሲያመሰግኑባት አይቶ ነው ፡፡ ምልጃቸው አይለየን ፡፡ አሜን ! ---- በቅዱስ በዓለ ወልድ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 http://tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ኅዳር 7 ( ፯ ) የሊቀ ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅዳሴ ቤቱ ነው ። ፠ኅዳር 7  ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨ ------- መክብበ ሰማዕት ፥ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ኰከበ ልዳ፥ ፀሐየ ፋርስ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ የኢትዮጵያ ገበዝ፤ ከአውሎ ነፋስ ይልቅ ፈጥኖ የሚደርስ ፈጥኖ ደራሽ ሰማዕት፤ እንደ እናቱ (እኅቱ) ቅድስት ማርያም ርኁሩህ የኾነ፡፡ ኅዳር 7 ቅዳሴ ቤቱ (ለመጀመሪያ ጊዜ የተሠራው ቤ.ክ የተመረቀበትና ቅዳሴ የተከናወነበት ክብረ በዓል) ነው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሚያዚያ 23 ቀን በሰማዕትነት ከሞተ በኃላ አጋልጋዮቹ እጅግ የከበሩ ልብሶችና ያማሩ ሽቶዎች አዘጋጁ በከበረ አገናነዝም ገነዙት በመርከብም ጭነው ወደ ትውልድ አገሩ ልዳ አመጡት ነገር ግን ቤተሰቦቹ በሙሉ ማለትም አባቱ ዘሮንቶስ እናቱ ቴዎብስታ እህቶቹ ማርታና እስያ እንዲሁም አጭተውለት የነበረች እጮኛው ሁሉም ሞተው አገኙዋቸው፤ እንድርያስ የሚባል አጎት ነበረው ስጋውን ተቀበላቸው አገሬው ተሰበሰበ የእየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳስ አባ ቴዎድሮስ ተጠርቶ መጣ ቤተክርስቲያኑን አነጹለት ስጋውንም በዚያ በክብር አኖሩት፤ በዚህች ቀን እጅግ ብዙ የሆነ ድንቅ ታአምራትና ታላላቅ ኃይላት ተደረጉ፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቤተክርስቲያን ይህንን ቀን ታከብረዋለች። ታላቁ  ንጉሳችን እምዬ ምኒሊክ አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ሲሰሩ ከዚሁ ከልዳ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ካለበት አፈሩን በመርከብ ከዚያም በበቅሎ አስጭነው አምጥተው ለቤተክርስቲያኑ መሰረት እንዳደረጉት እና ቅጥሩን ዙርያውንም እንደነሰነሱት መጻሕፍት ይናገራሉ ፡፡     ፠ ፠ በዓሉ በድምቀት በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ (በአራዳ ጊዮርጊስ) ይከበራል ———- ፨ ኅዳር ፯፤ (የአቡነ ገብረ እንድያስ በዓለ ዕረፍትና ነው)፨ ፠ ዕፁብ ድንቅ የኾነ ተዓምራትን የሚሠሩት እንጨቱ ጸበላቸው_=ውስጥ ሲገባ መቊጠሪያ የሚያደርጉት ፤ (በፎቶ የምታዩት)፤ ፠ በጠበላቸው ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተዓምራትን የሚያደርጉት ፠ ፻ ትውልድ የሚያስምሩት፤ ፠ በደንጊያ ሠረገላነት የሚጓጓዙት፤ ፠ ከ፯ቱ ቅዱሳን ዘጋሥጫ አንዱ የኾኑት፤ #አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_በዓለ_ዕረፍታቸው_ነው፨ ቦታቸውን ክርስቲያን የኾነ ኹሉ ሊያየው የሚገባ የተዓምራት ቦታ ነው፤ ✤✣✤ #ጻድቁ_አቡነ_ገብረ_እንድርያስ_ዘወለቃ_ወዘደብረ_ቆዘት_፤ ✤አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ፥ እናታቸው አርሴማ ሲባሉ፥ የትውልድ ሀገራቸው ወሎ፥ ቦረና፥ ጋሥጫ ሲኾን፤ የቀድሞ ስማቸው ንፍታሊም ይባል ነበር። ✤ ለትምህርት ሲሄዱ መምህራቸው ብዙኃኑን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት የተናገሩላቸው ሲኾን፤ የመጻሕፍትን ትርጓሜ በደንብ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሊም ይባል የነበረውን የቀድሞ ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው። ✤ ጻድቁ በአቡነ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል፤ ብዙ አባቶች ሱባኤ በሚይዙበት በስኮሩ ሥላሴ ቤተክርስትያን ጸሎት ሲያደርጉ ቅዱስ ዑር(ራ)ኤል በወርቅ ጽዋ ማየ ሕይወት አጠጥቷቸዋል። ✤ ጻድቁ አባታችን ሙታንን በማስነሳትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። ✤ ጻድቁ ዐርብ ፥ ዐርብ የጌታችንን ቅዱስ ሥጋውን ና ክቡር ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበረው በአየር ላይ ድንጋዩን እንደ ሰረገላ ፥ ዋርካውን እንደ ጥላ እየተጠቀሙበት ነበር። ይህ ሰረገላ የሆነው ድንጋይ በገዳማቸው ዛሬ ድረስ ይገኛል። (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ጻድቁ አባታችን እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ርቀት ወንዝ ከተሰኘው ቦታ በአንገታቸው ላይ በጣም ትልቅ ድንጋይ እየተሽከሙ ይጸልዩ ነበር። በዚህም ይጸልዩበት በነበረው ወንዝ ውስጥ በተአምራት መቊጠርያ የሚሰራ ጸበል ፈለቀላቸው፤ ጠበላቸው ውስጥም እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት መቊጠርያ ሆኖ ይወጣል፤ ይኸውም መቊጠሪያ ለብዙ ሕመሞች መድኀኒት ነው፡፡ (ፎቶውን ይመልከቱ) ✤ ✤ ✤ አቡነ ገብረ እንድርያስና ሊቀ ሰማዕቱ ስለ ሃገራችን በተቀበሉት ቃል ኪዳን ሰላምና ጤና ያውርዱልን፤ ጠላታችንን ከሃገራችን ያባርሩልን፨ • Facebook 👉 https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 https://t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 http://tiktok.com/@finotehiwot • YouTube 👉 https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w