en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 380 subscribers, ranking 5 573 in the Religion & Spirituality category and 2 194 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 380 subscribers.

According to the latest data from 06 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 32 over the last 30 days and by -4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 22.44%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.50% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 449 views. Within the first day, a publication typically gains 1 461 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 20.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 380
Subscribers
-424 hours
-257 days
+3230 days
Posts Archive
ዛሬ በደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቆራቢዎች እንዳይገቡ፤ የምሕረት በሩን እንኳን እንዳይሳለሙ ሲደረግ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ መጀመሪያ ያወጣው አዋጅና ባለፈው ሳምንት ባወጣው መመሪያም ሆነ መ
ዛሬ በደብራችን ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ቆራቢዎች እንዳይገቡ፤ የምሕረት በሩን እንኳን እንዳይሳለሙ ሲደረግ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ መጀመሪያ ያወጣው አዋጅና ባለፈው ሳምንት ባወጣው መመሪያም ሆነ መንግሥት ባወጣው አዋጅና ደንብ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያንን የውጭ በር ዝጉ፤ በአደባባይዋም ምዕመኗ ዝር እንዳይል፤ ፠ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያንን በር አይሳለሙ፤ ፠ ካህናትን መስቀል አይሳሙ ፥ አይሳልሙ፤ ፠ ቅዱሳትን መጻሕፍትን አይሳሙ ፥ አይሳልሙ፤ ፠ በስግደት ጊዜ ሰው ርቀቱን ጠብቆ አይስገድ፤ የሚል ነገር የለውም፡፡ ፖሊስ ከየት አምጥቶ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያንን በር የሚዘጋው ጥያቄ የሚያስነሳ ብቻ ሳይሆን የሚያስጠረጥርም ነው!!!!!

#ከሌሎች ቤተ እምነቶች እኩል ቤተ ክርስቲያንን ማየት የለብንም፡፡ ምክንያቱም፤ * የየትኛው ቤተ እምነት እምነት (አፈር) ነው እርኵስ መንፈስ ሲነካው የሚፈወስው፤ * የየትኛው ቤተ እምነት ነው በሩን ተሳልሞና ተሸሽቶ የሚፈወሰው፤ * የየትኛው ቤተ እምነት ነው በዕለታት የተቀመረ የጸሎት ሥርዐት ያለው (ምናልባት ሰሞኑን መቅረብ የነበረበት ጸሎት ምናልባት ቀኑና የዕለቱ ቊጥር ሲገጥመው ከ7ት ዓመታት በኋላ የሚቀርብ ነው) * የየትኛው ቤተ እምነት ነው በካህናት መስቀል የሚፈውሰው፤ (አንድ ርኵስ መንፈስ መንገድ ላይ የጣለውን ሰው አንድ ካህን በመስቀሉ ቢዳስሰው ይፈውሰዋል፤ የዓለም ላይ ቊጥር አንድ ባለሀብት ግን መስቀል ይዞ መጥቶ ውጣ ቢለው፤ አንተ ደግሞ ማነህ ብሎ ያሾፍበታል እንጂ አይፈወስም፡፡) **መስቀሉ እኮ መለኮት የተዋሐደው፤ ደሙ የፈሰሰበት ነው፡፡ ….. ለነገሩ፤ ፠ ዓይናማ ዓይናማ፤ ከሊቅም ሊቅ፤ የሊቃውንት ሁሉ ዋልታ የሆኑት መምህራን እንዳይናገሩና እንዳያስተምሩ፤ ዋሾና ቀጣፊ በዝቶበት በየት በኩል ይናገሩ፤ ድምፃቸው ታግቶ ነው የሚገኘውና እንርሱን መስማት ለአሁንም ሆነ ለወደፊት ችግር ይበዛል፡፡ ፠ የምሕረትና የፈውስ ደጅ (ደጀ ሰላም) የሆነውን የቤተ ክርስቲያን በር ስንሳለም ኮሮና ይይዘን ይሆንን እያልን የምንሳለም ሰዎች እያለን እግዚአብሔርስ እንዴት የቤቱን በር አያዘጋብን፡፡ አሁንም ቢሆን በእምነት እንለመለስ፤ የእኛ ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች ከምትለይባቸው ነገሮች አንዱ እምነት ነው፤ እምነት የማያደርገው ነገር የለምና ልብ ልንል ያስፈልጋል፡፡ ፠ ተጠራጣሪ እምነት ያለን እምነታችንን እንዲሞላልን ልክ ሌሎች ነገሮችን እንደምንጠይቀው መድኀኔ ዓለምን ልንጠይቀው ይገባል፡፡ ፠ ኢትዐፀዉ አናቅጽኪ /ደጆችሽ አይዘጉ/ እንዲል ነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ በመጽሐፍ ቅዱስ/፡፡ ፠ ቤተ ክርስቲያን ሐኪም ቤት ነች /ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ ቤተ ክርስቲያን ሐኪም ቤት ነች /ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ ቤተ ክርስቲያን ሐኪም ቤት ነች /ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/

#ቤተ_ክርስቲያን_ሐኪም_ቤት_አይደለችምን!!!!? (SHAREE, LIKEEEEE) #ኮሮናንስ_አትፈውስምን!!? #ሰሞነኛ_ሕግጋትን_በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ መጀመሪያ ያወጣው አዋጅና ባለፈው ሳምንት ባወጣው መመሪያም ሆነ መንግሥት ባወጣው አዋጅና ደንብ፤ ፠ የቤተ ክርስቲያንን የውጭ በር ዝጉ፤ በአደባባይዋም ምዕመኗ ዝር እንዳይል፤ ፠ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያንን በር አይሳለሙ፤ ፠ ካህናትን መስቀል አይሳሙ ፥ አይሳልሙ፤ ፠ ቅዱሳትን መጻሕፍትን አይሳሙ ፥ አይሳልሙ፤ ፠ በስግደት ጊዜ ሰው ርቀቱን ጠብቆ አይስገድ፤ የሚል ነገር የለውም፡፡ #እሺ፤ ዐርብ ስቅለት ላይ ጥብጣብ (የስግደት ቀኖና ይሰጣል) በቴሌቪዥን ይሆናልን???? #ቅዳሜ የሚደረገውስ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ በቴሌቪዥን ይሆናልን??? #በጸሎተ ኀሙስ፣ በትንሣኤና ከዚያም በኋላ ባሉ ቀናት ቅዱስ ቊርባን በቴሌቪዥን ይሆናልን??? #በሽታ_ከቤት_አይገባም_እንዴ፤ #ዘበኛና_ፖሊስም_አይከለክለውም፡፡ የቤተ ክርስቲያንን በር ዘግቶ ሌሎችን የውጭ በረራና ጉምሩክን ሳይቀር የሕዝብ መገናኛ ቦታዎች ፈቅዶ እንዴት ነው ነገሩ!!! ሌላ ነገር አስመሰለሳ!!!!!!! *ይልቁንም አዋጁ ርቀትን እንጠብቅ፤ እንዲሁም መንግሥት ያወጣው አዋጅም ደግሞ 4ት ሰው ሆኖ አይሰብሰብ ይላል እንጂ ቤተ ክርስቲያን ላይ አትሳለሙ አይልም፡፡ ስለ ቤተ እምነትም ያለው ነገር የለም፡፡ ፠ ቤተ ክርስቲያናችንም ያወጣችው መመሪያ አገልጋዮች በቤታቸው፣ በአገልግሎት ጊዜና ከአግልግሎት በኋላ ምን ማድረግ እንዳለባቸው በሰፊው ይተነትናል እንጂ ለቤተ ክርስቲያን ዐምድ የሆኑትን ምዕመናን በተወሰነ መልኩ ከማየት ይልቅ በስፋት እንደ አገልጋዮች በደንብ አያያቸውም፤ (የቤተ ክርስቲያናችን ትልቁ ችግር ብዙ ጊዜ ምዕመናንን ተገቢውን ቦታ ያለመስጠት ነው)፡፡ ፠ ጌታችን የዓለም መድኀኒት ከሚከተለው ከ5ቱ ገበያ ሕዝብ መርጦ 12ቱ አባቶችን ለሐዋርያነት፤ 72ቱ ወጣቶችን ለተልዕኮ ለርድዕትነት፤ 36ቱ ቅዱሳት እናቶችን ለተልዕኮነት የመረጠው ከሕዝብ እንጂ ከመንግሥት አካል ወይም ከካህናት ወገን አይደለም /የሐዋ. ሥራ 6/ ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው በሕዝብ ላይ ነው እንጂ በመንግሥት ላይ አይደለም፡፡ ይህንን ቤተ ክርስቲያን መዘንጋት የለባትም!!!፡፡ ፠ ልጆቼ ሥርዐቴንና ሕጌን ባይጠብቁ እንደ ቁንጥጫ እገርፋቸዋለሁ፤ ያለ ጌታ ከሥርዐቱ ፈቀቅ ብንል በሽታ አምጥቶብናል፡፡ ይህንንም መዘንጋት የለብንም፡፡ ፠ መንግሥት በተናገረ ጊዜ ቤተ ክስቲያን መናወጥ ፥ ሃይማኖት መሸርሸር የለበትም፡፡ ፠ በሽታና ፈተና አዲስ አይደለም (የሚርቀው በስገደት፣ በምሕላ፣ በጾም ነው፡፡) ፠ እውነተኛ አባትም አሁን ነው የሚታየው ዘኢፆረ መስቀለ ሞትየ ኢይጸመደኒ (መስቀሌን ያልተሸከመ፤ የእኔን ነገር የማይከተል የእኔ ሊባል አይገባውምና ይላል፡፡) ….. ስም ሌላ፥ ልብስ ሌለ፥ መመሪያ ሌላ ከሆነ፤ እግዚአብሔር ነገሮችን እንዳልሆኑ ያደርገቸዋል፡፡ ፠ በየቤተ ክርስቲያኑ ለበሽታው መከላለከል የተቋቋሙት ልዑካን ከፖሊስ እንደወረደ ቤተ ክርስቲያን በሯን ዝጉ ሲባሉ እንደወረደ መዝጋት ነው ወይስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና ታሳቢ አድርገው ነው መፈጸም ያለባቸው!!!፡፡ ፠ የቤተ ክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ፓትርያርኩ ለጠቅላይ ሚንስቴር ረቡዕ ሚያዝያ 7/2012ዓ.ም. በጻፉት ደብዳቤም እኛ መጀመሪያ መንግሥት ያወጣውን ዐዋጅ ተግባራዊ ስናደርግ በሽታውን ከመከላከል አንጻር ትክክል ነው ብለን ነበረ፤ አሁን ግን ስናየው በከተማው ባንኩ፣ ገበያው፣ ትራንስፖርቱ ሁሉ በሰው ተሞልቶ በሥነ ሥርዐት አካላዊ ርቀትን ጠብቆ ሥርዓተ አምልኮ መፈጸም አይቻልም፤ ከበር ላይ መሳለም አይቻለም መባሉ ነገርየውን በሌላ መልክ እንድናየው እያደረገን ነው ብለዋል፡፡ #የፖሊስ_አካላትን_በተመለከተ፤ *የፖሊስ አካላትም ባልተጻፈ መመሪያ ለምን ቤተ ክርስቲያንን ዘጉ!!!!!??፤ *የሃገራችን ሕዝብ ባለፉት ወራት ሲረግፍ ፖሊስ ምን ሲሰራ ነበር፤ *22 ቀበሌ ቤተ ክርስቲያን ስትፈርስ ፖሊስ የት ነበር፤ *ሰው ቁልቁሊት ተሰቅሎ ያም አልበቃ ብሎ ሲቃጠል የት ነበር ፖሊስ፤ ፠*፠ ቆይ ለመሆኑ ፖሊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲሆን ልዩ አመለካከት የሚኖው ለምንድን ነው?፤ *ፖሊስ በየአካባቢው የመንግሥት አዋጅ የከለከላቸውና ከ4ት ሰዎች በላይ ሰዎች የሚሰባሰቡባቸውን በርካታ ቦታዎች መከልከል አይሻለውምን፤ *መንግሥትስ ቢሆን የበሽታው ዋና መግቢያ የሆነውን አየር መንገድና ጉሙሩክ እስካሁንም ድረስ በተወሰነ መልኩ ሳያቆም የምሕረት ደጅ የሆነች ቤተ ክርስቲያንን ለምን ስትዘጋ ዝም ይላል፡፡ * በፌደራል ደረጃ የወጣ አዋጅስ የሚፈጸመው አዲስ አበባ ላይ ባሉ ገዳማትና አድባራት ላይ ብቻ ነውን? #ቤተ_ክርስቲያን_ሐኪም_ቤት_ናት /ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ ፠ ስግዱ ለእግዚአብሔር በዐፀደ መቅደሱ (በመቅደሱ ስገዱ አለ እንጂ በቤታችሁ ስገዱ አላለም!!) (ስገዱ እንጂ አትስገዱ አላለም)፡፡ ወንሰግድ ውስተ መካን ኀበ ቆመ እግረ እግዚእነ፤ (የጌታችን እግር በቆመበት እንሰግዳለን)፤ ወረከብናሁ ውስተ ኦመ ገዳም ንብእ እንከሰ ውስተ አብያቲሁ ለእግዚአብሔር፡፡ ፠ ኦሪትን ወንጌልን የሚጠብቅ ሕዝብ ይገባ ዘንድ በሩን ክፈተው አለ እንጂ በሩን ዝጋው አላላም፡፡ ፠ ሥርዐቷና ትምህርተቷ ሰማያዊ ነውና፤ ያመነ ይድናል /ማር. 16/፡፡ ፠ በሽታውን ያመጣውም የሚፈውሰውም እግዚአብሔር ነው፡፡ ፠ እምነት ያለው ሰው ገብቶ እንዳይጸልይ መከልከል የለበትም፡፡ *አንድ ሰው አደጋ ደርሶበት (ታሞ) ደም እየፈሰሰውም ቢሆን የሚያምርና ለመርገጥ የሚያሳሳ ሐኪም ቤት እንኳን ቢሆን መዳኑ ስለሚያስፈልገው፤ ደሙ የሐኪም ቤቱን ወለል ቢያጨማልቀውም እንኳን ገብቶ መታከሙን አያቆምም፤ እስኪድን ድረስ፡፡ በነፍስና በሥጋ ጭምር ድኅነትን የምትሰጥ ቤተ ክርስቲያን በኮሮና ምክንያት መዘጋቷ እኮ ለምንድን ነው፤ እርሷ እንኳን በማይክሮስኮፕ የሚታይ የቫይረስ በሽታ የሆነውን ኮሮናን ይቅርና የማይታዩትን የርኵሳን መናፍስት በሽታን የምትፈውስ አይደለችምን!!?? እንኳን የሥጋ ደዌን ይቅርና የነፍ ደዌና በሽታን የምትፈውስ አይደለችምን!!?? እንዲሁም፤ ፠፠፠ ብዙ መምህራንና ሰባክያን ቤት ሆነን ብንጸልይ ችግር የለውም፤ አንዳንዶችም ምን ችግር አለው ይላሉ፤ በቤተ ክርስቲያን ሆኖ መጸለይ እቤት ሁኖ ከመጸለይ በእጅጉ ይለያል፤ አይወዳደርምም፡፡ ምክንያቱም በቤተ ክርስቲያን ሆኖ መጸለይ፤ * በመንፈስ ከእኛ ጋር የሚሆኑ ቅዱሳን በብዛት ያሉበት ነውና፣ * ጸሎቱ ሲነበብ መስማት፣ ዕጣኑን ማሽተትን ቴሌቪዥን አይተካውምና፤ * ቤተ ክርስቲያን በሕይወት ያሉና በሕይተ ሥጋ የተለዩ በኅብረት የሚቆሙባት ናትን፤ * ቤተ ክርስቲያን ሐሳብን ሰብስበን እንድንጸልይ ታደርጋለችና፤ * በቤተ ክርስቲያን የሚጸለይ ጸሎት ከተለያዩ ነገሮች አንጻር ተሰሚነቱ የጎላ ነውና፤ አንድን ጉዳይ በመልእክተኛ ማስፈጸምና ራሱ ፈጻሚጋር ሄዶ ፈጽምልኝ ማለት ይለያያልና!!፡፡

፠ ‹‹ዘበእንቲአሃን›› (በተለይም ሰሙነ ሕማማት ላይ) ሆነን መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለቤ/ን ሲል ያደረገውን አስበን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ቁንጫ የሚመጡትን፥ እንደ ትኋን የተጣ
+4
፠ ‹‹ዘበእንቲአሃን›› (በተለይም ሰሙነ ሕማማት ላይ) ሆነን መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለቤ/ን ሲል ያደረገውን አስበን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ቁንጫ የሚመጡትን፥ እንደ ትኋን የተጣበቁትን፥ እንደ ዝንብ የወረሯትን፥ እንደ ዕንቧይ የተቆለሉትን፥ እንደ ሕንፃ ሰናዖር እጃቸውን ያስረዘሙትን፥ እንደ ደዌ የተጠናወቷትን፥….የአስመሳይ ወንድሞችን #የቢጸ_ሐሳውያንን_ነገር_ጻፍን፡፡ እሉ እሙንቱ (እነርሱም)፤ ፨ ገብረ መስቀል ኃይለ መስቀል ፨ ግርማ ወንድሙ ፨ ዮሐንስ ተስፋማርያም ፨ እኅተ ማርያም (ስንዱ) ፨ አሰግድ ሣህሉና መሰሎቹ፡፡ ፠ ሃሌ ሉያ ዘበእንቲአሃ ለቤተ ክርስቲያን፤ ተጸፋእከ በውስተ ዐውድ፤ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር፡፡ ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ፤ ወተዐገሠ ምራቀ ርኵሰ፥ እንዘ ዘልቦ ዘአበሰ፤ አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ፡፡ (ትርጕም፤ ሃሌ ሉያ፤ ለቤ/ክ ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርሷን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡ ለእርሷ ሲል ታስሮ መጐተትን የቻለ፤ የበደለው በደል ሳይኖር ርኵስ ምራቅን ሲተፉበት የታገሰ፤ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡) /ቅ.ያሬድ፥ ድጓ/ ፠ ‹‹ሀ›› የሚል ፊድልን ብቻ የሚያውቅ ሰው ቀጣይ ‹‹ሁ›› የሚባል ፊደል አለ ሲባል ስለ ‹‹ሁ›› ፊደል ጠንክሮ ማወቅ፥ መማርና መጠየቅ እንጂ፤ የለም ፊደል ‹‹ሀ›› ብቻ ነው፤ ቀጣይ ‹‹ሁ›› የሚባል ፊደል የለም ብሎ መከራከር የለበትም፡፡ አስተያየት ከመስጠትዎም በፊት ስለማያውቁት ነገር አስተያየት አይስጡ፡፡ ፠ ተዐቀቡኬ እምሐሳውያን ነቢያት፤ ወእም ሐሳውያን ቢጽ፡፡ (ከሐሰተኞች ነቢያትና ከሐሰተኞች ወንድሞች ተጠበቁ፡፡) ፠ ለእመ ኮነ አማን በልዎ አማነ፤ ለእመ ኮነ ሐሰት በልዎ ሐሰተ፡፡ (እውነት የሆነውን እውነት፥ ሐሰት የሆነውን ሐሰት ነው በሉ)፨

#ጸሎተ_ሐሙስ_ወሕጽበተ_እግር_ ሐዋርያቲሁ ከበበ፥ እግረ አርዳኢሁ ሐፀበ፤ ኮኖሙ አበ ወእመ፤ ወመሐሮሙ ጥበበ፡፡ (ሐዋርያቱን ሾመ፤ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ፤ አባትና እናት ኾናቸው፤ ጥበብንም አ
+5
#ጸሎተ_ሐሙስ_ወሕጽበተ_እግር_ ሐዋርያቲሁ ከበበ፥ እግረ አርዳኢሁ ሐፀበ፤ ኮኖሙ አበ ወእመ፤ ወመሐሮሙ ጥበበ፡፡ (ሐዋርያቱን ሾመ፤ የደቀ መዛሙርቱን እግር አጠበ፤ አባትና እናት ኾናቸው፤ ጥበብንም አስተማራቸው፡፡) /ሊቁ ቅዱስ ያሬድ፣ ድጓ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል፫_ #ሰይጣን_ሰዎችን_እንዴት_እንደሚፈትንና_ኃይል_እንዴት_እንደሚያገኝ_የሐሰት_አባት_ሁኖ_ሳለ_ሰዎች_እንዴት_እንደሚያምኑትና_ባይፈልጉም_አምላካቸውን_እንደሚያመሰግኑና_እንደሚታዘዙ፡፡ በሳምር ሃገር ሰሉቅያ (አስቀሎና) በምትባል ቦታ ከሄሮድስ ወገን የሚሆኑ ጣዖት የሚያመልኩ ክፉዎችና ኀጢአተኞች ነበሩ፤ ሴቶችም ወንዶችም ከሚስቶቻቸውና ከባሎቻቸው ከልጆቻቸው ጭምር ተሰብስበው በየወሩ ወደ ጭፈራ ቤት የመግባት ክፉ ልማድ ነበራቸው፡፡ ቅዱስና ንጹሕ፥ ጻድቅና መስተጋድል፥ መነኰስና ካህን አባ ጳውሊ ከዚህች አገር ደርሶ፤ የዚያችን ሃገር ሰዎች ወደ ጭፈራ ቤት ሲሄዱ ባደረበት ጸጋ እግዚአብሔር የሰዎቹን የኀጢአት ሥራ አውቆ ፈጽሞ አዘነ፤ ወደ ዳንስ ቤቱ ተጠግቶም ከበር ቆመ ሰዎቹም መብራት አጥፍተው፥ ራቁታቸውን ሆነው በዱር እንዳሉና እንደጠገቡ ፈረሶች ሲጮሁ ሰማቸው፡፡ አባ ጳውሊም ወደ እግዚአብሔር እነዚህ ሰዎች ለሌሎች የኀጢአት አብነት እንዳይሆኑ ቅጣቸው፤ አጥፊ የሆነውንም ሰይጣን በኀይልህ አጥፋው እያለ በፍጹም ልቡ ጸለየ፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰማውና አጥፊ የሆነው ሰይጣን የሚንቦገቦግና የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ እንዲገለጽለት አደረገ፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ሰይጣንን አንተ ማነህ? ማንንስ ትፈልጋለህ? ሰይፍህ በእጅህ የተመዘዘው ለምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ የምትሻውን ንገረኝ እንጂ አንተ ማነህ አትበለኝ፤ ከፈጣሪህ የለመንከውን አንተ ታውቃለህና አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ የአንተን ሥራ የሚሠሩትን ወዳጆችህን (ጭፈራ ቤት ያሉትን) እንዴት ታጠፋለህ አለው፡፡ ሰይጣን፤ እኔ ከፈጣሪ ታዝዣለሁ፤ የአዛዤን ትእዛዝ እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም አለው፡፡ +አባ ጳውሊ፤ ብዙ ጥያቄ እጠይቅሃለሁና እንዳትዋሸኝ በሕያው በእግዚአብሔር ስም አምዬሐለሁ፥ አውግዤሃለሁ፥ በቅዱስ መስቀሉ አስሬያለሁ አለው፡፡ ሰይጣን፤ በሰዎች ላይ የማደርገውን ክፉ ሥራዬን ልትገልጽብኝ ነውን? የምትሻውን ጠይቀኝ፤ ትእዛዛህን አልተላለፈም ኀይሌ በጸሎህ ደክሟልና አለው፡፡ ++ አባ ጳውሊ፤ ከሰዎች በአንዱ አድረህ በኀጢአት ትጥለው ዘንድ አጋዥ የሚሆንህ ምንድን ነው? /ሔዋንን በእባብ አዳምን በሔዋን ማሳቱን ልብ ይሏል/ ሰይጣን፤ ሰው #በእግዚአብሔር_ሕግ_ጸንቶ ሳለ በማንም ላይ ማደር አይቻለንም፤ ከእግዚአብሔር ሕግ ትንሽ ፈቀቅ ቢል፤ እንዲሁም #በየጊዜው_ስሙን_ከልቡ_ባይጠራ (በፍጹም ሃይማኖት ሁኖ የማያማትብ፤ ሕፃን ቢሆንም ከመጠመቁ በፊትም እናቱ የማታማትብና የእግዚአብሔርን ስም የማትጠራ ከሆነ፤ ባለትዳሮችም ከመጋባታቸው በፊት በካህናት ጸሎት በሚጋቡ ጊዜ በሥጋ ወደሙ በመኝታቸው አንድ በሚሆኑ ጊዜም የአምላክን ስም የማይጠሩ ከሆነ) ያንጊዜ በሰው ላይ ለማደር ኀይል እናገኛለን፤ በእነርሱና በልጆቻቸውም ላይ እናድራባቸዋለን፤ እንሰለጥንባቸዋልን፤ ሰላምንና ፍቅርን እናሳጣቸዋለን፤ ኑሯቸው ጠብና ክርክር እንሞላበታለን፤ መጨረሻቸውም መለያየት ይሆናል አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ መላውን የዓለምን ሰዎች የምትፈትናቸው በምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ እንደምኞታቸው እንፈትናቸዋለን፤ ሥጋዊ ሐሳብን አሣምረን እናቀርብላቸዋለን፤ በከራት በትምክት እናቃጥላቸዋልን፤ እንቅልፍንና ዝሙት መመኘትን እናመጣባቸዋለን፤ ጾም እንዳይጾሙ፥ ጸሎት እንዳይጸልዩ እናደርጋቸዋለን፤ ከሥጋ ወደሙና ከመልካም ሥራ ሁሉ እናርቃቸዋለን፡፡ ዘወትር ይህን ዓለም በማሰብ (በስካር፥ በውሸት፥ በቂምና በቅናት፥ ሐሰት በመመስከር፥ ወርቅና ብርን በመውደድ፥ በስንፍና፥ ሰውን በመስደብ አእምሯቸው እንዲጠፋ እናደርጋለን፡፡ ቅዱሳንን ሳይቀር ልባቸው ከእግዚአብሔር ፍቅር እንዲርቅ፥ ቃልኪዳናቸውን እንዲተዉ በተለያዩ ምክንያት ባለን ኀይል እንዋጋቸዋለን አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ሰውን ታጠፋ ዘንድ ኀይልና ሥልጣን የምታገኘው እንዴት ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ #የእኛን ሐሳብ ተከትለው ኀጢአትን አዘውትረው በሚሠሩ ክፉዎችና አመንዝራዎች እንዲሁም ፈጽመው ንስሐ በማይገቡ ላይ ነው፡፡ የሚጠብቋቸው ቅዱሳን መላአክት ስለበደላቸውና ስለ ኀጢአታቸው ሲርቋቸው ያንጊዜ እኛ በእነርሱ ላይ እንበረታለን፡፡ #ክፉ ሥራንም ሁሉ ወደው እንዲሠሩ እናደርጋቸዋለን፡፡ መልካም በማስመሰል በሐሰተኛ ሕልም እናስታቸዋለን፡፡ እኛ እግዚአብሔርን መሳደብና መንቀፍ ባይቻለን ሰዎች ፈጣሪያቸውን ና ድንግል ማርያምን እንዲሁም ቅዱሳን መላእክትንና ቅዱሳን ሰዎችን ለመስደብና ለመንቀፍ እንዲነሳሡ እናደርጋቸዋለን፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ አንተ ሐሰተኛና የሐሰት አባቷ ሆነህ ሳለ /ዮሐ. ፰፥፵፬/ ሰዎች ቃልህን እንደት ያምኑሃል? አለው፡፡ ሰይጣን፤ አንተና እንዳንተ ያሉ ባታምኑኝም በኋላ ዘመን ብዙ ሰዎች በእኔ ቃል ያምናሉ፥ ምክሬን ይቀበላሉ፥ ጥበቤን ይፈልጋሉ፡፡ ያለ ጊዜዬ አኔን ማጥፋት የማይሻ ጌታ ክርስቶስን እንኳን ፈትኜዋለሁ አለው፡፡ እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ሰዐት ደርሷልና የታዘዝኩትን ፈጥኜ አደርግዘንድ ልቀቀኝና ልሂድ አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ እግዚአብሔርን በምታመሰግኑበት ጊዜ ጥቅማችሁ ምንድን ነው? አለው፡፡ ሰይጣን፤ በተፈጠርን ጊዜ ምስጋናው በአንደበታችን ተፈጥሯልና፤ ስሙ ኅቡዕ ለሚሆን ብርሃናትና ለፈጠረ ለእርሱ የምንሰግድበትና የምናመሰግንበት ሰዐት አለን እንጂ የምንጠቀመው ጥቅምና ክብር የለንም አለው፡፡ #ሰዐቱን ጠብቀን ካላመሰገንን መኖር አንችልም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ የምትሰግዱትና የምታመሰግኑት በፈቃዳችሁ ነውን? ወይስ ያለፈቃዳችሁ? አለው ሰይጣን፤ በግድ ነው እንጂ ደስ ብሎን አናመሰግንም አለው፡፡ ++አባ ጳውሊ፤ ደስ የማይላችሁ ለምንድነ ነው? አለው ሰይጣን፤ ከክብራችን ተዋርደን ጨለማ ከለበስን በኋላ ደስታ የለንም፤ ደስ ብሎንም አናመሰግንም፡፡ ስለዚህ እስከዛሬ ምስጋናውን አቋርጠን አናውቅም አለው፡፡ #ክፍል ፬.… ሰይጣን የቅዱሳን መላእክትን ቃል(ምሥጢር) እንደሚሰማና ከመደረጉ በፊት ለሰዎች በመናገር እንደሚያስት፤ ሰይጣን ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በዘመን ብዛት ሰውን ያሚያስትበት ብዙ ጥበብ እንዳለው፤ የክርስቶስ ሰው መሆን ከሰይጣን የተሰወረ እንደነበር፤ ሰይጣናት አለቃና ታዛዥ እንዳላቸው፤ ገሃነነም ስለመኖሩና ዲያብሎስ ለምን ንስሐ እንደማይገባ፤ ክፍል ፬.… ይቀጥላል ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

#፬ቱ #ስግደታት (በሰሙነ ሕማማት በ፯ቱ ጊዜያት የሚሰገድባቸው (#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት፡፡) ፠የሰሙነ ሕማማት ጸሎት የሚደረገው በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት መሠረትነት 7ት ጊዜ ነው፤ በ7ቱ ጊዜያትም 4ት ስገደታት አሉ፡፡ ለዚሁ አገልግሎት ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ7ቱ ጊዜያት ከፋፍሎ የደረሰው መልክአ ሕማማትም አብሮ በዜማ ይደርሳል፡፡ (መልክአ ሕማማትን ለብቻው አዘጋጅተን ለጥፈንላችኋል) ፠ደወልና ቃጭል ይመታል፤ ፠ጸሎታት(ሙሉ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት)ና (የኦሪትና የነቢያት) ምንባባት ይደርሳል፤ ፠የተአምር መቅድምና ምንባብ ይነበባል፤ የተአምራት መርገፍ በዜማ ይባላል፡፡ ፠የወንጌል አቡን በቅብብሎሽ ይደርሳል፤ ፠ምስባክ ይሰበካል ፥ ወንጌል ይነበባል፡፡ #፬ቱ #ስግደታት የምንላቸውም (እየሰገድን የምንላቸውም) ቃላት፡፡ ፠ #፩ኛ #ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤ *‹‹#ጸልዩ_በእንተ_ጽንዐ_ዛቲ_መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ ቃጭል ሲደውል፤ #ሕዝቡ_እየተቀበሉ_እግዚኦ_ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን) በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እየተዜመ ይሰገዳል፡፡ ፠ #፪ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለከ_ኃይል_ክብር_ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፮ት ፮ት ጊዜ (በድምሩ ፲፪ ጊዜ) ይበሉ፤ በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ ይሆናል፡፡/ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤ + ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ + አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤ + ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤ + ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤ + አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥ ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥ እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም፡ ፠ #፫ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለአምላክ_ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡ እንዲህ እያሉ ይበሉ፤ + ለአምላክ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለሥሉስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለማሕየዊ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለዕበዩ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለዕዘዙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለመንግሥቱ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለሥልጣኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለምኵናኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለኢየሱስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለክርስቶስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለሕማሙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ + ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡ ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡ +*+ ለከ ይደሉ ኃይል፥ ወለከ ይደሉ ስብሐት፥ ወለከ ይደሉ አኰቴት፥ +*+ ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡ ፠ #፬ኛ #ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን እየቀደሙ፤ በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡ * መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ ቤዘወነ፤ ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/ * #ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ #ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ * ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ * ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ * ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፣ #ትስቡጣ ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡ **** ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን ይኾናል፡፡ ፠ የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡ ፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#መስቀል_አደባባይ_ላይ_ምንድነው_የሚሠራው? ፠ በመዲናችን አዲስ አበባ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት የመስቀል ደመራ በዓል ከአራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በስተደቡብ ወረድ ብሎ በሚገኘው ቦታ ላይ (ቀድሞ ለአላሙዲን ፤ አሁን በቅርብ ደግሞ የአድዋ ቤተ መዘክር እየተሠራበት) የሚገኝበት ቦታ ላይ ይከበር እንደነበር መርስኤ ኀዘን ወልደቂርቆስ በዘመን ትዝታዬና ሌሎችም የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ፠ በግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት ደግሞ ከቤተመንግሥቱ በስተደቡብ ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን አጠገብ መኖሪያቸውን ያደረጉት (ቤታቸው የአሁኑ አዲስ አበባ ሙዝየም) ራስ ብሩ ወልደአረጋይ ከርስታቸው ከፍለው ለመስቀል ደመራ ማክበሪያ አደባባይ እንዲሆን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በሰጡት መሠረት የደመራው አደባባይ ከጊዮርጊስ ወደ አሁኑ መስቀል አደባባይ ተዛወረ፡፡ ፠ ደርግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ ከወረሳቸው የቤተክርስቲያኒቱ አደባባዮች እና ይዞታዎች አንዱ ይኸው መስቀል አደባባይ ሲሆን ስያሜውን ወደ ‹‹አብዮት አደባባይ"ነት በመቀየር የደመራውን ሥርዐት ከአደባባዩ ነጥሎ ወደ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መለሰው። ፠ ኢህአዴግ አዲስ አበባን ለመቈጣጠር አንድ ሳምንት ሲቀረው ሀገሪቱን ለ6ቀናት ብቻ በማስተዳደር የሚታወቁት ጀነራል ተሥፋዬ ገብረኪዳን አብዮት አደባባይ የሚለውን ስያሜ በመሠረዝ ወደቀደመ ስያሜው (መስቀል አደባባይ) መለሱት፡፡ ፠ ኢህአዴግ ሀገሪቱን ግንቦት ላይ ሲቈጣጠር ከአራት ወራት በኋላ የመስቀል ደመራ በዓል በጥንታዊ ይዞታው በአሁኑ መስቀል አደባባይ ተከበረ፤ እስከ አሁንም በዚሁ ቦታ ላይ እየተከበረ ይገኛል፡፡ ፠ ሰሞኑን እዚሁ መስቀል አደባባይ ላይ የግንባታ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንና ቻይናውያን ሥራ ተቋራጮች አጥር እያጠሩ እና የአፈር ምርመራ ጥልቅ ጉድጓዶች እየቆፈሩ መሆኑን አንዳንድ ምንጮእ እየዘገቡ ነው፡፡ ፠ መስቀል አደባባይ የሀገራችን የሃይማኖት፣ የባህል እና ፓለቲካዊ ተዋስኦ አደባባይ ሆኖ ሲያገለግል እንደመኖሩ፤ የመስቀል ደመራ ሥርዐትም በዩኔስኮ በቅርስነት ሃገራችን ካስመዘገበቻቸው አንዱ እንደመሆኑ፤ አሁን የተጀመረው ግንባታ ይህንኑ ከግምት ያስገባ (ልክ የአዲስ አበባ ቀላል የባባሩ ሐዲድ አደባበዩን አቋርጦት እንደሚሄደው እንዳይሆን)፤ ዲዛይኑም ከአዘቦት ማኅበራዊ አገልግሎቶቹ የተናበበ፤ በቦታው ላይ ታሪካዊት ባለቤትና በዋነኛነት ሃይማኖታዊ በዓሏ የምታከብረው ቤተ ክርስቲያናችንም ተሳታፊ መሆን ፥ መሆን፥ መሆን፥ መሆን፥ መሆን፥ አለበት!!! ፡፡ #ምን_ይደረግ ??????? /ምንጭ፤ ዮሐንስ መኮነን ከጻፈው ጽሑፍ ላይ ተሻሽሎ የቀረበ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#መልክአ_ሕማማት፤ (የ፯ቱ ጊዜያት ጸሎት) *መልክአ ሕማማት ማለት ስለ ጌታችን መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሕማም፥ መከራ፥ ስቃይ፥ የሚናገር መጽሐፍ ሲሆን፤ ደራሲው ታላቁ ሊቅና የደብረ ባሕርይ ጋሥጫ መምህር #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_ ነው፡፡ *መልክአ ሕማማት በባለ 3ት መስመር አርኬ የተደረሰ ግጥማዊ ድርሰት ሲሆን፤ የተደረሰውም በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት አንጻር በመሆኑ ‹‹#ጸሎት_ዘሰባዐቱ_ጊዜያት›› በሚል መጠሪያም ይጠራል፡፡ የእያንዳንዱ ጊዜ ድርሰትም በዋነኛነት 3ት ክፍሎችን የያዘ ነው፤ እነርሱም፤ 1ኛ) ስብሐተ እግዝእትነ ማርያም /የእመቤታችን ምስጋና/ 2ኛ) ስበሐተ ኢየሱስ ክርስቶስ /የኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና/ 3ኛ) ስብሐተ ሥሉስ ቅዱስ /የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና/ **በ7ቱ ጊዜያት ጸሎት ማድረስ እንደሚገባን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 118 ላይ ‹‹ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ ይላል››፤ አባቶቻችን ሐዋርያትም ይህንኑ ደንግገዋል፡፡ /ዲድስቅልያ 37፣ ቀሌምንጦስ 1ና 7፣ አቡሊዲስ 25ኛና 27ኛ፣ ባስልዮስ 28ኛ አንቀጽ፣ ፍትሐ ነገሥት ገጽ 21/፡፡ ፠ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መልክአ ሕማማትን ሲደርስም በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት የተፈጸሙትን ድጊቶች ከ3ቱ የየጊዜያቱ የድርሰቱ ክፍሎች ምስጋና (የማርያም፣ የጌታ፣ የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና) ጋር እያመሠጠረና እያራቀቀ፥ እያስዋበና ምሥጢር እያመጣ፤ እንደ ወርቅ እያንከባለለ፥ እንደ ሸማ እየጠቀለለ፥ በግጥም እያስጌጠ፥ በቃላት እየሰደረ፥ በዜማ እያሸበረቀ፥ መንፈስን እየመሰጠ፤ ነው የደረሰው፡፡ #የ7ቱ_የጸሎት_ጊዜያት_የሚባሉትም፤ ፠1ኛ) መንፈቀ ሌሊት(ሌሊት 6 ሰዐት)፤ ጌታችን የተወለደበት፥ የተጠመቀበት፥ የተነሣበትና ዳግመኛ የሚመጣበት ፥ … ሰዐት ነው፡፡ ፠2ኛ) ነግህ (ማለዳ፥ ጧት)፤ ጨለማን አርቆ ብርሃንን የሚያመጣበት፥ አባታችን ቅዱስ አዳም የተፈጠረበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጲላጦስ አደባባይ ፊት ቁሞ የተመረመረበት፥ …. ሰዐት ነው፡፡ ፠3ኛ) ሠለስት (ጠዋት ሦስት ሰዐት)፤ እናታችን ሔዋን የተፈጠረችበት፥ ነቢዩ ዳንኤል ጸሎት ያደረሰበት፥ እመቤታችን ከቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ሰምታ የጸነሰችበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡ ፠4ኛ) ቀትር (6 ሰዐት)፤ አጋንንት የሚሰለጥኑበት ሰዐት ስለሆነ እንዳይሰለጥኑብን፥ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ የሳተበት ስለሆነ እንዳንስት እንጸልያለን፡፡ በተጨማሪም ነቢዩ ሄኖክ ቤተ መቅደስን ያጠነበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በመስቀል ላይ የተሰቀለበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡ ፠5ኛ) ተስዓት (ዘጠኝ ሰዐት)፤ ቅዱስ ጴጥሮስና ዮሐንስ ለጸሎት ወደ ቤተ መቅደስ የወጡበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው የለየበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡ ፠6ኛ) ሠርክ (ዐሥራ አንድ ሰዐት)፤ ነቢዩ ኤልያስ መሥዋዕት የሰዋበት፥ ዕዝራ ጸሎትን ያቀረበበት፥ ሕዝቅያስ ጸልዮ ፀሐይን ወደ ዐሥር ደረጃዎች የመለሰበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ወደ በፈቃዱ ወደ አዲስ መቃብር የወረደበት፥ …… ሰዐት ነው፡፡ ፠7ኛ) ንዋም (የመኝታ ሰዐት)፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጌቴሴማኒ የጸሎትን ሥርዐት ያስተማረበት ፥ እንዲሁም ሌሊቱን በመላእክት ጥበቃ ከርኵሳን አጋንንት እንዲጠብቀን የምንጸለይበት …… ሰዐት ነው፡፡ #ለቡ(ልዩ ማስታወሻ)!! ይህ ታላቅ ጸሎት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስር ባሉ በሁሉም ገዳማትና አድባራት በሰሙነ ሕማማት የሚደርስ ሲሆን፤ በአንዳንድ ትላልቅ ገዳማት (እንደ ዋልድባ፣ ማኅበረ ሥላሴ፣ ደብረ ባሕርይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ወደብረ ጎል አቡነ በጸሎተ ሚካኤል) ያሉ መነኰሳትና መናንያን ግን ከዓመት እስከ ዓመት ጸሎቱን በዜማ /በንባብ/ ያደርሱታል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት፡፡ በሰሙነ ሕማማት የሚባሉትን በአጭሩ ስንቃኛቸው፡፡ (#ለዐርቡ_ጸሎት_እንደ_ዘማች_ስለሚያገለግል) ዐርብ ከምንለቀው የዐርቡ ጸሎት ጋራ አብረን የምንጠቀምበት ስለሆነ በቃል ጭምር አጥኑት፡፡ /ይህን ጽሑድ በአድካሚ ሁኔታ እንደ ንብ ቀስመንና ሰብስበን አዘጋጅተንላችኋል፤ ላልደሰረሰው አዳርሱ፤ ማተሚያ ቤት ያላችሁ አትማችሁ ስጡ፡፡/ ፠የሰሙነ ሕማማት ጸሎት የሚደረገው በ7ቱ የጸሎት ጊዜያት መሠረትነት 7ት ጊዜ ነው፡፡ ለዚሁ አገልግሎት ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ7ቱ ጊዜያት ከፋፍሎ የደረሰው መልክአ ሕማማትም አብሮ በዜማ ይደርሳል፡፡ (መልክአ ሕማማትን ለብቻው አዘጋጅተን ለጥፈንላችኋል) #የጸሎቱ_አደራረስ_ሥርዐትም ከዚህ እንደሚከተለው ነው፤ ፠ደወልና ቃጭል ይመታል፤ ፠ጸሎታት(ሙሉ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት)ና (የኦሪትና የነቢያት) ምንባባት ይደርሳል፤ ፠የተአምር መቅድምና ምንባብ ይነበባል፤ የተአምራት መርገፍ በዜማ ይባላል፡፡ ፠የወንጌል አቡን በቅብብሎሽ ይደርሳል፤ ፠ምስባክ ይሰበካል ፥ ወንጌል ይነበባል፡፡ #1ኛ_ስግደት፤ ‹‹ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ›› እያለ ቃጭል ሲያሰማ 22ት ጊዜ ‹‹እግዚኦ ተሣሃለነ›› እየተባለ ይሰገዳል፡፡ #2ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት›› የሚለውን በቅብብሎሽ 6ት ፥ 6ት ጊዜ (በድምሩ 12)፤ 7ኛውን በኅብረት እየተሰገደ ይባላል፡፡ #3ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለአምላክ ይደሉ›› የሚለውን 1ኛውን ዙር በቅብሎሽ፤ 2ኛውን ዙር እያስተዛዘሉ፤ ከስግደት ጋራ ይባላል፡፡ #4ኛ_ስግደት፤ ‹‹ክርስቶስ አምላክነ…›› የሚለውን በመሪና ‹‹ንሰብሖ ..›› ወናልዕል ስሞ የሚለውን በቅብብሎሽ ብለው በዚያው ቀጥለው፤ ‹‹ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን›› የሚለውን በመሪ 21 ጊዜ፤ በተመሪ 20 ጊዜ (በድምሩ 41 ጊዜ) እየተሰገደ ይደርሳል፡፡ ፠የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡ ፠ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#የሰሙነ_ሕማማት_ዕለታት_ስያሜዎች † #ሰኞ፤ መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ፤ አንጽሖተ ቤተ መቅዳስ የተፈጸመበት ሰኞ:: † #ማግሰኞ፤ የጥያቄና የትምህርት ቀን:: † #ረቡዕ፤ ምክረ አይሁድ፥ የዕን
#የሰሙነ_ሕማማት_ዕለታት_ስያሜዎች † #ሰኞ፤ መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ፤ አንጽሖተ ቤተ መቅዳስ የተፈጸመበት ሰኞ:: † #ማግሰኞ፤ የጥያቄና የትምህርት ቀን:: † #ረቡዕ፤ ምክረ አይሁድ፥ የዕንባ ቀን፥ የመልካም መዓዛ ቀን:: † #ሐሙስ፤ ጸሎተ ሐሙስ፥ ሕጽበተ ሐሙስ፥ የምሥጢር ሐሙስ፥ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ፥ የነጻነት ሐሙስ:: † #ዐርብ፤ የስቅለት ዐርብ:: † #ቅዳሜ፤ ቀዳም ሥዑር (ሹር ቅዳሜ)፤ ለምለሚቱ ቅዳሜ፥ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፥ ሰንበት ዐባይ፥ ቅዱስ ቅዳሜ፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w