en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 371 subscribers, ranking 5 616 in the Religion & Spirituality category and 2 192 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 371 subscribers.

According to the latest data from 25 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -4 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.07%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.16% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 085 views. Within the first day, a publication typically gains 1 254 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 26 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 371
Subscribers
-124 hours
+357 days
-430 days
Posts Archive
ኅዳር 24 እንኳን ለ የ24ቱ_ካህናተ_ሰማይ(ሱራፌል)_በዓል እና በቆብ አያትና የልጅ ልጅ የኾኑት #አቡነ_ተክለሃይማኖትና_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ ከካህናተ ሰማይ ጋር #የሥላሴን መንበር ላጠኑበት ዕለት በሰላም አደረሳቹህ ፡፡ ፨ካህናተ ሰማይ የዐውዶ ሡራሄ፤ ሎቱ ለባህቲቱ ይደሉ ስባሔ፨ /ሰዐታት/ #Share ያድርጉ ካህናት ሰማይ ከሠራዊተ #ሩፋኤል (ሊቃናት) ሃያአራት ሊቃናት መርጦ በመንበረ ስብሐት በመጋረጃዋ ውስጥ ዙርያዋን ክንፍ ለክንፍ ገጥሞ አቁሟቸዋል፡፡ ሕዝ 1 ፥11-12 ※ስማቸውን #ካህናተ_ሰማይ አላቸው የእሳትና የወርቅ ጽና አስያዛቸው ፤ የብርሃን አክሊል ጳዝዮን ከሚባል የብርሃን ዘውድ ደፋላቸው የብርሃን ዘንግ ማኀተሙ መስቀል የሆነ አስያዛቸው ፤ የብርሃን ላንቃ ኀብሩ መብረቅ የመሰለ አለበሳቸው ፡፡ ‹‹በዙፋኑ ዙርያ ሀያአራት ዙፋኖች ነበሩ፤ በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሀያ አራት ሽማግሌዋች ተቀምጠው ነበር›› ዮሐ ራዕ 4፥-5 ካሕናተ ሰማይ ( ሱራፌል ) የሐዲስ ኪዳን ካህናት ምሳሌዎች ናቸው ፡፡ እነዚያ በሰማይ ሲያገለግሉ የሐዲስ ኪዳን ካሕናት ደግሞ በምድር ያገለግላሉ ፡፡ ሰማውያኑ አክሊል ተቀዳጅተው ፣ መብረቅ ለብሰው ሲያገለግሉ ምድራውያኑ ደግሞ ለአክብሮተ ወንጌል ልብሰ ተክህኗቸውን ለብሰው ማዕጠንተ ወርቃቸውን ይዘው ጸሎታችንን ለማሳረግ ሲወጡ ሲወርዱ ይኖራል ፡፡ እነዚህ መላእክት ለምሕረት ወደዚህ አለም እንደሚመጡ ከልዑለ ቃል ኢሳይያስ እንረዳለን ይህም እግዚአብሔር ኢሳይያስን ይቅር ብሎ ሃብተ ትንቢትን ሲሰጠው የላከለት ከሱራፌል አንዱን ነው ፡፡ ኢሳ 6 ፥ 5 ※እነዚህም በአንድ ላይ በአጠኑ ጊዜ ከማዕጠንታቸው የሚወጣው ጢስ መልኩ #መብረቅ ፤ ድምጹ ነጎድጓድ ፣ መዓዛው መልካም የሆነ ነው ፡፡ ‹‹ ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሠዊያው አጠገብ ቆመ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሠዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምርው ብዙ ዕጣን ተሰጠው ፤ የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ወጣ››ዮሐ ራዕ 8 ፥3-5 ※የሚያጥኑት ምንድን ነው ቢሉ የጻድቃን ጸሎት ፤ የሰማዕታት ገድል ፣ የደጋግ ሰዎች ምግባር ነው ፡፡ በእናንተ እየጣጠነ ወደ እኔ ያርግ ( ይድርስ ) ብሏቸዋልና ፡፡ ያለ እነርሱም አቅራቢነት ጽድቅና ምጽዋት ወደ እግዚአብሔር አይቀርብም፡፡ የሥላሴን መንበር ካጠኑ ቅዱሳን ውስጥም ፤ ለምሳሌም ፤ በቆብ አያትና የልጅ ልጅ የኾኑት #አቡነ_ተክለሃይማኖትና_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን መንበር አጥነዋል ፨ አቡነ ዮሴፍ ዘጂፋት፣ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እንዲሁ አጥነዋል ፡፡ #Share ያድርጉ ፨ካህናተ ሰማይ የዐውዶ ሡራሄ፤ ሎቱ ለባህቲቱ ይደሉ ስባሔ፨ /ሰዐታት/ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

*ትምህርተ ንስሓ አስተምረን ንስሓ አባት እናሲዞት ፡፡ *ትምህርቱ ዓርብ ቅዳሜ እሑድ ምሽት 12፡30 ላይ ይሰጣል ፡፡ *ፈጥነው ይመዝገቡ ፡፡
*ትምህርተ ንስሓ አስተምረን ንስሓ አባት እናሲዞት ፡፡ *ትምህርቱ ዓርብ ቅዳሜ እሑድ ምሽት 12፡30 ላይ ይሰጣል ፡፡ *ፈጥነው ይመዝገቡ ፡፡

#በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤ ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም (ከክርስቶስ ልደት 980 ዓመታት በፊት በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን ታቦቷ የመጣው) ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም (በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ተመሠረተች) ✣ዝዋይ ደብረ ጽዮን ማርያም (ደቡብ ሸዋ) ✣ሳዶቅ አምባ ማርያም (በ1670 ዓ.ም. በአባ ሳዶቅ የተመሠረተች ፥ ሰሜን ተራሮች) ✣እንፍራንዝ ደብረ ጽዮን ማርያም (ጥንታዊዋ ደብር) ✣ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም (በወርቅና በዕንቊ ተደርጋ በራስ ውቤ የታነጸች፤ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠባት፤ ስሜን፣ ራስ ደጀን አጠገብ) ✣ ደብረ ጽዮን ማርያም (ነቀምት) ✣ ደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ቅድስት ማርያም (ባሕርዳር) ✣ አርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ማርያም ✣ ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ማርያም (እንግሊዝ ፥ ለንደን) /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤ ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም (ከክርስቶስ ልደት 980 ዓመታት በፊት በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን
+9
#በጽዮን_ስም_የተመሠረቱና_ዐቢይ_ዓመታዊ_ክብረ_በዓላቸው_ኅዳር_21_የኾኑ፤ ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም (ከክርስቶስ ልደት 980 ዓመታት በፊት በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን ታቦቷ የመጣው) ✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም (በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ተመሠረተች) ✣ዝዋይ ደብረ ጽዮን ማርያም (ደቡብ ሸዋ) ✣ሳዶቅ አምባ ማርያም (በ1670 ዓ.ም. በአባ ሳዶቅ የተመሠረተች ፥ ሰሜን ተራሮች) ✣እንፍራንዝ ደብረ ጽዮን ማርያም (ጥንታዊዋ ደብር) ✣ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም (በወርቅና በዕንቊ ተደርጋ በራስ ውቤ የታነጸች፤ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠባት፤ ስሜን፣ ራስ ደጀን አጠገብ) ✣ ደብረ ጽዮን ማርያም (ነቀምት) ✣ ደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ቅድስት ማርያም (ባሕርዳር) ✣ አርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ማርያም ✣ ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ማርያም (እንግሊዝ ፥ ለንደን) /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት: ኅዳር 21 ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን ወይም ታቦተ ሕጉ ) ጽዮንን ክበቧት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦቿንም ቅጠሩ፥ አዳራሿን ተመልከቱ፥ በብርታቷ የልባችሁን ተስፋ አኑሩ፡፡ /መዝ. 47፥12/ share እና like ያድርጉ #ኅዳር_21_የታቦተ_ጽዮን_(#ጽላተ_ኪዳን_ወይም_ታቦተ_ሕጉ_) #ዓመታዊ_ክብረ_በዓል_የምናከብርበት_ምክንያት_፤ ፩ኛ. በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን በሕዝበ አስራኤል(በአፍኒን ፊንሐስ) ኀጢአት ምክንያት፤ ታቦተ ጽዮን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካ፤ ዳጐን የተባለ የአሕዛብ ጣዖትን ቀጥቅጣ አድቅቃ ወደ እስራኤል የተመለሰችበት በመኾኑ፡፡ (1ሳሙ. ከ1-6) ፪ኛ. ታቦተ ጽዮን መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰሎሞን ወዳሠራው ቤተ መቅደስ (በዓለም ላይ እስካሁን ያልታየ ድግስ ደግሶ) የገባችበት እለት በመኾኑ፡፡ / (1ኛ ነገ. 8፥2፣ 2ኛ ዜና. 5፥1፣ ስንክሳር ዘሐምሌ 23) ፫ኛ. በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ (ዕብነ ሐኪም) አማካኝነት ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል የበኲር ልጆች ጋር በ318ቱ ሌዋውያን ካህናት ፥ በሊቀ ካህናቱ አዛርያስ እየተመራች ታቦተ ጽዮን ወደ ኢትዮጵያ የገባችበት በመኾኑ፡፡ /ክብረ ነገሥት፣ መጽሐፈ ምሥጢር፣ መጻሕፍተ ሰሎሞን ወሲራክ አንድምታ መቅድም፣ …/ ፬ኛ. ነቢያት ስለ እመቤታችን በተለያየ ኅብረ መልክእና አምሳል (ዕዝራ በቅድስት ሃገር መንፈሳዊት፣ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተ መቅደስ፣ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ፣ ……) ያዩበት በመኾኑ፡፡ /ሕዝ. 44፥1፣ መጽ. ዕዝራ/ ፭ኛ. በንጉሥ አፄ ባዜን (በ4 ዓ.ም. አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ዋልድባን፣ ደብረ ዐባይን፣…… ሌሎችንም የኢትዮጵያ መካናት በስደት ከልጇ ጋር ባርካ አኵስም ጽዮን ላይ መጥታ የገባችበትና የባረከችበት፤ በወቅቱም አኵስምና አካባቢዋ በብርሃን ጎርፍ የተጥለቀለቁበት በመኾኑ፤ /ታሪከ ዋልድባ፣ ታሪከ አኵስም፣ ድርሳነ ዑራኤል፣ ....) ፮ኛ. በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱሳን ጻድቃን ነገሥታት አብርሐ ወአጽብሐ አማካኝነት መሥዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት የቆየችው አኵሱም ጽዮን፤ ጽዮን ማርያም ተብላ ባለ 12 መቅደሶች ባሏት በወርቅና በዕንቊ ያሸበረቀች ቤ.ክ ሠርተው ቅዳሴ ቤቷ የተከበረበትና ክርስትና ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ የታወጀበት፡፡ ፯ኛ. በየጊዜው (በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ) ወደ ዝዋይ፣ ወደ ጣና ቂርቆስ፣ …… ተሰድዳ ቆይታ፤ ተመልሳ (ከዮዲት በኋላ በአንበሳ ውድምና፤ ከግራኝ በኋላ በአፄ ፋሲል የታነጹት ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን) ቅዳሴ ቤቷ የተከበረበት በመኾኑ፡፡ ፰ኛ. ወደ አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም በቦታው ርቀት ለመሳለም ላልቻሉ ክርስቲያኖች ዳግሚት ደብረ ጽዮን በዳግማዊ አፄ ምኒልክ አዲስ አለም ላይ የተሠራችበት በመኾኑ፡፡ ፱ኛ. ሴቶችም ወንዶችም የሚያስቀድሱበትና ያለ ዐምድ ዕፁብ ድንቅ በኾነና በሃግያ ሶፍያ ቤ.ክ. አምሳል የተሠራው የጽዮን ቤተ ክርስቲያን (ኅዳር 21 ጾም በመኾኑ ቅዳሴ ቤቷ የተከበረው ግን ጥር 30 ቀን 1957 ዓ.ም ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ዐፄ ኀይለ ሥላሴ፣ እቴጌ መነን፣ የታላቋ ብሪታንያ ንግሥት ግርማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥና ልዑል ፊልፕ በተገኙበት ቢሆንም) ቅዳሴ ቤት የተከበረበት በመሆኑ፡፡ ———— #ታቦተ_ጽዮንና #ጽዮን_ድንግል_ማርያም_፤ ፠ ታቦተ ጽዮንን፤ ሌዋውያን ከበዋት ውዳሴ፥ ዝማሬ ያቀርቡላት እንደነበረው፤ ✤ ዛሬም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ካህናትና ምእመናን ከሩቅ እና ከቅርብ ተሰብስበው በማኅሌት፥ በዝማሬ፥ በቅዳሴና በውዳሴ ያከብሯታል፡፡ ፠ ታቦተ ጽዮን በደብተራ ኦሪት በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ የኖረች ፥ የዮርዳኖስን ባሕር የከፈለች /ኢያሱ 3÷14-17/ ፥ ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች /ኢያሱ 6÷1-21/ ፥ ዳጎን የተባለ የፍልስጤማውያንን ጣዖት የቈራረጠች /1ኛ ሳሙ. 5÷1-5/ ፥ በድፍረት ሊነካ የሞከረውን ኦዛን የቀሰፈች /1ኛ ሳሙ. 6÷6/ ፥ በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች /2ሳሙ 6÷12/ ፥ ዳዊት የዘመረላት /2ሳሙ 6÷14/ ፥ ጠቢቡ ሰሎሞን በቤተ መቅደስ በክብር ያኖራት /1ኛ ነገ፣ 8÷1/ ፥ የእግዚአብሔር የክብር መገለጫ ናት፡፡ ✤ ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያምም ንጽሐ ጠባይዕ ሳያድፍባትና የቅድስና ባሕርይ ሳይጎድፍባት፤ (በማየት፣ በመስማት፣ በመዳሰሰ፣ በማሽተት አንዳችም እድፍ ጉድፍ ሳያገኛት) በንጽሕናና (በኀልዮ፣ በነቢብ፣ በገቢር) በቅድስና ጸንታ በኀጢአት ሳትለወጥ ኖራለች፡፡ /ውዳሴ ማርያም፣ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም፤ አንቀጸ ብርሃን፣ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ/ እንዲሁም ‹‹ምክንያታዊ ነውር ኃጢአት የሌለብሽ የኀጢአት ሸታ ያልደረሰብሽ ንጽሕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና ክብርት በልዕልና አንቺ ነሽ» ብሏታል ጠቢቡ ሰሎሞን /መሓ. 4÷7/ ፠ ታቦተ ጽዮን በከበረ ወርቅ እንደተሸለመች ✤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በንጽሐ ሥጋ፣ በንጽሐ ነፍስ እና በንጽሐ ልቡና የተሸለመች ያጌጠች ናት፡፡ ፠ ታቦተ ጽዮን የቃለ እግዚአብሔር ማደሪያ እንደሆነች፤ ✤ ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያምም ለአካላዊ ቃል ለእግዚአብሔር ወልድ ማደሪያ ኾናለች፡፡ «ድንግል ማርያም ሆይ ሰማይና ምድርን ለፈጠረ አምላክ ለእርሱ ማደሪያ ሆንሽ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀንሸ ቻልሽው ተሸከምሽው ሰማይና ምድር የማይወስኑትን ለመወሰን የታመንሽ አንቺ ነሽ» /ውዳሴ ማርያም፣ ቅዱስ ኤፍሬም/ ——- **** በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቃል ኪዳኑ ታቦት መካከል ጥልቅ የሆነ ምሥጢራዊ ትምህርት አለ፡፡ /ዘፀ. 25÷9-20/፡፡ ይህንንም በተመለከተ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል ምሥጢሩን ከምሥጢር አመሳጥሮ፤ እንደ ሸማ አንከባሎ፥ እንደ ወርቅ ከብልሎ እንዲህ አስቀምጥታል፤ «ታቦተ አምላከ እስራኤል ጽዮን ዘነገደት ምድረ ኢሎፍሊ፤ ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ፡፡ አመ ነገደት ቊስቋመ በኀይለ ወልዳ ከሃሊ፤ ወድቁ አማልክተ ግብፅ መናብርተ ሰይጣን ሐባሊ፤ ወተኀጉሉ ኲሎሙ ዘቦሙ አስጋሊ፡፡ ወደ ኢሎፍሊ ምድር ተማርካ የሔደች የእስራኤል አምላክ የቃል ኪዳኑ ታቦተ ጽዮን የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው፡፡ ድንግል ማርያምም ሁሉን ማድረግ ከሚችለው ከልጇ ጋር ግብፅ ወደሚባል ሀገር በሔደች ጊዜ የሐሰተኛ ሰይጣን ዙፋኖች የሆኑ የግብፅ ጣዖታት ፈረሱ ጠንቋይ አስጠንቋይ ያላቸው ሁሉ ዐፈሩ» /ኢሳ 19÷1፣ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል/ /በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/

ኅዳር 13 በዓለ እግዚአብሔር አብ ወአእላፍ መላእክት ፤ በደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ካቴድራል በድምቀት ይከብራል። የዚህ ደብር ታሪክ እነዲህ ነው፤ በደብሩ የሚገኝው የእግዚአብሔር አብ ታቦት በደብራችን በቀጨኔ ደብረሰላም ይገኝ ነበር፡፡ በታላላቅ አባቶችም ይህ ታቦት ወጥቶ ወደ አሁኑ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ ሥፍራ እንደሚሄድ የበቁ አባቶች አስቀድመው ይናገሩ ነበር፡፡ እንደተናሩትም ሐምሌ 29 ፤1969 ዓ.ም ታቦተ ሕጉ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወጥቶ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ቤት አረፋ፣ ቤተክርስቲያኑም እራሱን ችሎ እስኪቆም ድረስ የደብራችን የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም አገልጋዮች በቅዳሴ በማኀሌት በሰዓታት ያገለግሉ ነበር :: ከዚህም በኃላ ጥር 19 ቀን 1971 ዓ.ም የመጀመሪያው ቤተክርስቲያኑ አልቆ ተመርቋል፡ የቤተክርስቲያኑ ዲያቆናት ፣ ቀሳውስት እና መሪጌቶችም በጊዜያዊነት ተቀጠርው ነበር ሆኖም የአገልግሎት ፍቅር ያደረባቸው የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቃውንት አልግሎታቸውን አላቆሙም ነበር። ለታሪክ ያህል ታላቁ ሊቅ አለቃ ኤልያስ ነቢየ ልዑል ከመኖርያ ቤታቸው ቀጨኔ ድረስ በምጣት ለደብሩ ታላቅ አሰተዋጾዖ አድርገዋል። እሁን ያለው ሕንፃ ቤ.ክ የደብተራ ኦሪት እና የኖኀ መርከብን ቅርጽ ይዞ በቅድስቱ አካባቢ ያለው አሠራር ደግሞ ክቧን ቤ.ክ ሆኖ ተሰረቶ በ2009 ዓም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ተመረቋል፡፡ የቅዱሰ እግዚአብሔር አብ ታቦትም ኅዳር 13 እልፍ አእላፋት መላእክት በሚከሩበት ዕለት ይከብረል። በዚሁ ደብር ኅዳር 25 የሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በዓልም ይከበራል ( ታቦቱ በድርብነት አለ) የእግዚአብሔር ቸርነት የአእላፍ መላእክት ተራዳኢነት አይለየን! አሜን ። #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

#አንኳን_ለቅዱስ_አግዚአብሔር አብ በዓልና_ለአእላፍ_መላእክት_በዓለ_ሢመት እንዲሁም #ቅዱስ_ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 ጀምሮ እስከ 13 ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን ለሚለምንበት) በዓል በሰላም አደረሳቹህ፡፡ ፨ ፨ ፨ #ኀዳር_13 ቀን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሊቃውንት #አእላፍ መላእክት እየተባለ ይጠራል ፤ 99ኙ ነገደ መላእክት በአንድ ላይ የሚከብሩብት ቀን ነው እንዚህም ሥጋ የሌለቸው ረቂቃንና ለዓለም ሁሉ የሚማልዱ ናቸው ፡፡ #Share ያድርጉ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ 100 በክፍለ ነገድ 10 አድርጓቸዋል ፡፡ በ3 ሰማያትና በ10 ዓለማት ላይም ይገኛሉ፡፡ መላእክት ያሉባቸው ከተሞች #ኢዮር #ራማ #ኤረር ይባላሉ ፡፡ አሥሩ ነገዶች ከነአለቆቻቸው አንዲህ ናቸው 1. #አጋዕዝት (ቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል የነበረ ፤ አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ስር ናቸው) 2. #ኪሩቤል (አለቃቸው ቅዱስ #ኪሩብ ፤ ለበለጠ ኀዳር 7 የጻፍነውን ይመልከቱ) 3. #ሱራፌል (አለቃችወ ቅዱስ #ሲራፊ ፤ ለበለጠ ኀዳር 24 ይጠብቁን) 4. #ኃይላት (አለቃቸው ቅዱስ #ሚካኤል ) 5. #አርባብ (አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ) 6. #መናብርት (አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል) 7. #ሥልጣናት (አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ) 8. #መኳንንት (አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ) 9. #ሊቃናት (አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል) 10. #መላእክት (አለቃቸው ቅድስ አናንኤል) ናችው፡፡ ከእነዚህም ፨ አጋዕዝት ፣ኪሩቤል ፣ ሱራፌልና ኃይላት መኖርያቸው በኢዮር(3ኛው ሰማይ ) ነው ፡፡ ፨አርባብ ፣መናብርትን ሥልጣናት መኖርያቸው በራማ ነው ፡፡ ፨መኳንንት ፣ሊቃናት ፣ መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር ነው (1ኛው ሰማይ ) ———- (ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤ #ሚካኤል_ወገብርኤል፥ #ሱራፌልወኪሩቤል/፬ቱ እንስሳ/፥ #ዑር(ራ)ኤል_ወሩፋኤል /፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ/፥ #ሱርያል_ወፋኑኤል፥ #አፍኒን_ወራጕኤል፥ #ሳቁኤል_ወአቅናኤል፥ #ብርናኤል_ወሱባኤል፥ #ፍናኤል_ወሰላታኤል፥ #ሰዳካኤል_ወኤልናኤል፥ #አናንኤል_ወኢየሩማኤል፥ #ግርማኤል_ወድርማኤል ፥ #ድማህኤል_ወአድማኤል፥ #ሙራኤል_/ምናቴር_አብያቴር/፥ #ሱታ(ስቱ)ኤል_ወሱርያል፤ ……. ፨ ፨ ፨ ፨ የመላእክት ተፈጥሮ እመኀበ አልቦ ኀበ ቦ (ካለመኖር ወደመኖር ) ነው ፡፡ አይራቡም አይጠሙም ፤አይዋለደሙ ፣ አይሞቱም ፣ ዕረፍት የላቸውም ፤ምስጋናቸው እረፍታቸው ፤እረፍታቸው ምስጋናችው ነው አንጂ(አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ) እንዲል፡፡ ተፈጥሯቸው እጅግ ረቂቅ ነው፡፡ ተግባረቸውም ዘውተር እግዚአብሄርን ማመስገን ነው፡፡ —— #መላአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም ፤ ለመዓትም ይላካሉ፡፡ ምሕረትን ያወረዳሉ ፡፡ ልመናን ያሳርጋሉ ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ አንዲዚሁም ሁሉ ወቅትንም የሚቆጣጠሩ አሉ ፤ ስለ ሰው ልጆች ይማልዳሉ (ዘካ 1÷12 ) ምሥጢርም የሚገልፁም አሉ(ዳን 9÷21) መላእክት ተራዳኢም ናቸው (ኢያ 5÷13)፣ እነዳንሰናክል ይጠብቁናል (መዝ 90÷11 ) ፣ያድናሉ ( መዝ 33÷7 ) ፣የፀጋ ስግደትም ይገባቸዋል (መሳ 13÷20) በፍርድ ቀንም ኀጥአንን ከጻድቃን ያለያያሉ (ማቴ 25 ÷31) እነሆ እግዚአብሄር ይፈርድዘንድ ቅዱሳን መላእክቶቹን አስከትሎ ይመጣል እንዲል ፡፡ /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ፨፨፨ እልፍ አእላፋት ወትእልፊት ቅዱሳን ንጹሐን መላእክት ቆሙ በአገልግሎት ጸንተው በአንድነት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አምላክ በማለት፡፡ ምልጃቸው እና ጠብቆታቸው አይለየን አሜን ፡፡ —————— ኀዳር 13 ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹ፤ ከፎቶ ጋር …. 1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤ 2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤ 3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን (በሰሜን ሸዋ)፤ 4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ (አዲስ አበባ)፤ 5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) 6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ (አዲስ አበባ) /የቀ.ደ.ሰ መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሕትመት እና ሚዲያ ንዑስ ክፍል የተዘጋጀ ::/ #share .Facebook... https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool .YouTube... https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w .Telegram... https://t.me/medihanaelem http://tiktok.com/@finotehiwot www.finotehiwotsundayschool.com #Share #like