en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 382 subscribers, ranking 5 568 in the Religion & Spirituality category and 2 195 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 382 subscribers.

According to the latest data from 04 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 23 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 22.11%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.42% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 401 views. Within the first day, a publication typically gains 1 449 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 20.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 382
Subscribers
-124 hours
-107 days
+2330 days
Posts Archive
35 የሚሆኑ በመናገሻ ከተማችን በአዲስ አበባ #የሊቀ_መላእክት_ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል የሚከብርባቸው ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት (ያልጠቀስናቸውን ጨምሩበት፤ ፎቶም ካላችሁ ላኩልን ወይም ለጥፉልን፡፡) ፠ መ.መ.ገ. መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤ ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤ ፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል) ፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮተቤ ዳግማዊ ቁልቢ ደብረ ልዑል ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ. ፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ አንቆርጫ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ፈረንሣይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ) ፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል) ፠ ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ጀሞ ሦስት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ. ፠ አቃቂ ጃቲ ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ ኮልፌ አጠና ተራ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል) ፠ የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ. ፠ደብረ ገሊላ ቅዱስ ዐማኑኤል ካቴድራል (በድርብነት ይከብራል) #share https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w https://t.me/medihanaelem

‹‹ወንድሞቻችን እኛስ እንደ ይሰሐቅ የተስፋ ልጆች ነን ፡፡›› ገላ 4 ፥ 28 በመጋቤ ሐዲስ ምስጢረ ሥላሴ ፤የታኅሣሥ 9 የዓርብ ጕባኤ በyoutube ገጻችን ይመልከቱ https://youtu.be/5sQdCht3JZc

#እንደ አበባ የሚያስደስት ባለሟልነትን ለተመሉ ከንፈሮችህና ፈጽሞ ከንቱን ለአልተናረ አፍህ ሰላምታ የሚገባህ አራቱን መዓዘነ ዓለም በአማላጅነትህ የምታስምር ጻድቅ አባታችን #አረጋዊ ሆይ ቅን ልቦናን አድለኝ የማይጎድል ምሉ ዕዉቀትንም ስጠኝ፡፡ #መልክአ_አቡነ_አረጋዊ https://youtu.be/3o4wj7Qqcaw

እንኳን አደረሳቹህ ፤ታኅሣሥ 13 ቅዳሴ ቤቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ::
+1
እንኳን አደረሳቹህ ፤ታኅሣሥ 13 ቅዳሴ ቤቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ::

አዲሱ የአ.አ ሐገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ #_ብጹእ_አቡነ_መልከጸዴቅ እና #_መምህር_አካለወልድ_ተሰማ የአ.አ ሐገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የሰንበት ት/ት ቤታችንን ውሳኔ አጸኑ ፡፡ ከዚህ በፊት
+1
አዲሱ የአ.አ ሐገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ #_ብጹእ_አቡነ_መልከጸዴቅ እና #_መምህር_አካለወልድ_ተሰማ የአ.አ ሐገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ፤ የሰንበት ት/ት ቤታችንን ውሳኔ አጸኑ ፡፡ ከዚህ በፊት መስከረም 28/01/2013 ዓ.ም በ1 ወር ጊዜ ውስጥ የሰ/ት/ቤቱ መማርያ ቦታ 600 ካሜ ቦታ እንዲሰጣቸው ተብሎ ውሳኔ ተወስኖ ወደ ደብራችን የተላከው ደብዳቤ አፈጻጸሙ ላይ ክፍተት በማሳየቱ ምክንያት በዛሬው ዕለት ታኅሳስ 12 / 2013 ዓ.ም በፍጥነት ወደ አፈጻጸም ገብተው በ #1_ሳምንት ጊዜ ውስጥ ሪፖርት እንዲያደርጉ ደብዳቤ ልከዋል፡፡ ጉዳዩ በፍጥነት ወደ አፈጻጸም እንዲገባ መመርያ ለሰጣችሁት ለአ.አ ሐገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ #_አቡነ_መልከጼዴቅ ፣ #_መምህር_አካለ ወልድ_ተሰማ እንዲሁም #_ለ_መምህር_ዳዊት ፤ሰንበት ት/ት ቤታችን ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ #share ያድርጉ

#ታኅሣሥ_12_የአቡነ_ሳሙኤል_በዓለ_ዕረፍት ✤✤ #ፀሐይ_ማር_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_(#ዘገዳመ_ዋሊ_) ✤✤ ፠ በሃገራችን በኢትዮጵያ በብቸኝነት በጌታችን የተመሠረተው ገዳመ ዋልድባ፤ ኋላ በአሕዛብ ጠፍቶ ነበርና በ13ኛው ክፍል ዘመን እንደ መሶብ ከፍ አድርገው በ4ቱም አቅጣጭ በ4 ወንዞች (በሰሜን ተከዜ፥ በምስራቅ እንስያ፥ በምዕራብ ዛሪማ ፥ በደቡብ እንዞና ወይቦ) ዙሪያውን ከልለውና አጥረው ያስባረኩ አባት ናቸው፡፡ ፠ አዲስ አበባና አካባቢውን ከ700ዓመታት በፊት በአንበሳ እየተጓጓዙ በስብከተ ወንጌል እርሻነት፥ በሥነ ምግባር ማለስለሻነት ያረሱ አባት ናቸው፡፡ ፠ ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን፣ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት የኾኑ ናቸው፤ ይህንንም ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ40ቀን ዕረፍታቸው በመካነ መቃብራቸው ተገኝተው መልክዓቸውን ደርሰውላቸዋ፤ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌተ ጽጌ ድርሰታቸው አውስተዋቸዋል፤ እንዲሁም በርካታ ቅዱሳን ደራስያን በየድርሰታቸው አንስተዋቸዋል፡፡ #ክቡር_መምህር፥ #የከበረ_መምህር፤ #መልአክ_ዘበምድር፥ #የምድር_መልአክ፤ #ካህን_ወድንግል፥ #ካህንና_ድንግል፤ #ፍጹም_ንጹሕ_ወልዑል፥ #ፍጹም_ንጹሕና_ልዑል፤ #ትጉህ_ወኅሩይ፥ #ትጉህና_ኅሩይ_የተመረጠ)፤ #ብእሴ_እግዚአብሔር፥ #የእግዚአብሔር_ሰው፤ #ለባሴ_ንጽሕና፥ #ንጽሕናን_የተላበሰ፤ #ወለብሰ_ብርሃናዌ፥ #ብርሃንን_የለበሰ፤ #ዘፈጸመ_ገድሎ_በሠናይ፨ #ገድሉን_በመልካም_ተጋድሎ የፈጸመ፨/ገድለ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ/ ፠ ከረድአቸው አባ ብንያሚና፤ ከጓደኞቻቸው ከአባ አንበስ ዘሐዘሎና ከአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ጋር በመኾን በወቅቱ ከነበሩት ርዕሰ አበው አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዘንድ ለመባረክ ወደ ዝቋላና ምድረ ከብድ የመጡና በረከትን የተቀበሉ ከሰሜን እስከ ደቡብ ኢትዮጵያ ያስተማሩ ናቸው፡፡ ፠ አናታቸው በሥጋ ሞት በሕፃንንታቸው ቢለይዋቸውም፤ በሕፃንነታቸው ጌታችን አውራ ጣቱን አትብቷቸዋል፡፡ ‹‹እንዘ ይተግህ ለጸልዮ ወያስተበርክ ለስኢል፤ መንኰብያቲሁ አጠበዎ ወልደ ማርያም ድንግል፡፡ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል፥ ሳሙኤል ዘዋልድባ መነኮስ ኀያል፡፡›› /እንዲል ነግሥ/ ፠ የተከዜ ወንዝ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትዕምርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ ፥ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ወደ ወንዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉም ሳይበላሽ ተሸግረዋል፡፡ ፠ ገባሬ ተዓምራት ወመንክራት የኾኑ፤ ⴲ ዝናብ በኾነ ጊዜ ዝሆኖች መጥተው እንደ ጥላ የሚያስጠልሉት፤ ‹‹ሳሙኤል አቡነ ሠረገላ ጸሎት፤ ጊዜ ርደቶሙ ለዝናማት፤ ዘከለሉከ ነጌያት፡፡›› እንዳለ መጽሐፈ ሰዐታት፤ ⴲ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ (ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት) ጋር መንበረ ጸባዖትን ለ12 ዓመታት አጥነዋል፤ በዚህም በጎንደር ደባርቅ አካባቢ የመሠረቱት ገዳማቸው አብ ጠራ(ህ) በሚል ተሰይሟል፡፡ ......................................የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ‹‹ሳሙኤል አቡነ ትሩፈ ምግባር፤ ዐምድ ጽኑዕ ፀወነ ሃገር፤ ወመልአክ ዘበምድር፡፡›› እንዲል መጽሐፈ ሰዐታት፣ ⴲ በዋልድባ ምድር ላይ ቀድሞ ውኃ የለም ነበርና፤ ፸ የሚጠጉ ምንጮችን በተለያዩ ቦታዎች አፍልቀዋል፡፡ ⴲ ቅዳሴ ማርያምን ወደ መሃል ሃገር ያመጡ፤ ⴲ ቅዳሴ ወውዳሴ ማርያምን ሲደግሙ ከመሬት ክንድ ከስንዝር ያህል ከፍ የሚሉ፡፡ ⴲ በአናብስት ዘባን ላይ የሚጫኑ፤ መጻሕፍቶቻችውንም በአናብስት ላይ የሚጭኑ፡፡ ⴲ እመቤታችን ነጭ ዕጣን (ስለ ምዑዝ ክህነታቸው) እንዲሁም ዕንቊ (ስለ ንጽህናቸው፣ ቅድስናቸውና ድንግልናቸው) የሰጠቻቸው። ⴲ በሰኔ 21 ቀን በቀደሱበት ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑ አንድ ክንድ ከስንዝር ከምድር ለቆ እንደ ደመና በአየር ላይ ቆሞ የታየላቸው፡፡ ⴲ ውኃውን ወደ ኀብስት የቀየሩና ከነ ደቀመዛሙርቶቻቸው የተመገቡ፤ ‹‹ሶበ አተቦ ለማይ በቅዳሴኪ እንዘ ይጼሊ፤ ረሰዮ ኅብስተ ጽጌ ሃይማኖት ሳሙኤል ዘሐቅለ ዋሊ፡፡ ምሕረተ ወፍትሐ ለተአምርኪ እኅሊ፤ ሥረዪ ኀጢአትየ ወዕፀብየ አቅልሊ፤ አስመ ኵሎ ገቢረ ማርያም ትክሊ፡፡›› /ማኅሌተ ጽጌ/ ‹‹ …አርአዮሙ ለመምህራን ዐበይተ ኀይላተ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በኀበ ተአኵተ፥ ወለማይኒ ረሰዮ ኅብስተ፡፡›› /ማኅሌተ ጽጌ/ የምንኵስና ተወረዱም፤ አባት አባትን ሲወልድ፤ መምህር መምህርን ሲተካ፥ ቅዱስ ቅዱስን ሲያፈራ፥ ገዳም ገዳምን ሲወልድ ነውና ቅሉ፤ የምንኵስና ተዋረዱም፤ ፠ ….. ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ መድኃኒነ እግዚእን፤ ፠ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ 7ቱን ከዋክብት /ፀሐይ አቡነ ሳሙኤልንና ሌሎች ቅዱሳንን/፤ ፠ ከ7ቱ ከዋክብት አንዱ ፀሐይ አቡነ ሳሙኤል ደግሞ ደቀ መዛሙርቶቻቸውን (አባ ተሥፋ ሐዋርያትን፥ አባ ዘሩፋኤልን፥ አባ ብንያሚን፥ አባ በኪሞስን፥ …… ሌሎች እልፍ አእላፋት መነኰሳትን አምንኵሰዋል፣ ሊቃውንትን አስተምረዋል፤ መምህራንና ደራስያንን ተክተዋል ….፤ በዚህም ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን ፥ ወላዴ መምህራን ወሊቃውንት አባ ሳሙኤል በመባልም ይታወቃሉ፡፡ #አቡነ_ሳሙኤል_፤ በአኵስም ከተማ አካባቢ በ1295 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው ዓመተ ማርያም ይባላሉ፡፡ በአኵስም ጽዮን ከነበሩት መምህራን ከፊደል ጀምረው የቅዱስ ያሬድን ጸዋትወ ዜማና ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን ተምረዋል፡፡ ወላጆቻቸው በልጅነታቸው በሞት ተለይተዋቸዋል፡፡ ከወላጆቻቸው ሞት በኋላ ወደ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘንድ ሔደው ደብረ በንኰል ገዳም ገቡ፡፡ በዚህም ገዳም እያገለገሉ በወቅቱ ከነበሩት ሊቃውንት የብሉያትና የሐዲሳትን ትርጓሜ እንዲሁም ሥርዐተ ምንኵስናን ተምረው ከገዳሙ አባት በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ ከሌሎች 11ድ ወንድሞቻቸው ጋር አብረው መነኰሱ፤ ቆባቸውም እንደ አቡነ አረጋዊ የድንጋይ ቆብ ነበር፡፡ በዚህም ገዳም እህል ሳይበሉ ቅጠል ብቻ እየተመገቡ ይኖሩ ነበር፡፡ እግራቸው እስኪያብጥም ድረስ ይሰግዱ ነበር፡፡ **ኋላ ወደ ጣና ገብተው ከቆብ ወንድማቸው ከአቡነ ያሳይ ጋር ለ12 ዓመታት በሱባኤ ቆዩ፤ **በስተመጨረሻም ጌታችን ወደ መሠረተውና በመሃልም ጠፍ ሆኖ ወደ ነበረው ብዙ ቅዱንን፣ መምህራንን፣ ሊቃውንትንና መናንያንን ወደ ወለዱበት ዋልድባ ገዳም ገብተው ለ70 ዓመታት ያህል ከዚህ ዓለም በምናኔ ተለይተው፣ ግርማ ሌሊቱን፥ ፀብአ አጋንንቱን ፥ ድምፀ አራዊቱን፥ የሌሊቱን ቊር፥ የቀኑን ሐሩር ታግሠው፣ ረሃቡንና ጽሙን ችለው፣ መላ ዘመናቸውን በጽድቅ ጎዳና ተጕዘው በ1395ዓ.ም ታኅሣሥ 12 ቀን በዋልድባ አቴና ገዳም ዐርፈዋል፡፡ #ባርከኒ አባ እንሣእ ጸሎተከ፤ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን፤ አባ ሳሙኤል ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፨ /ጸሎተ መሐረነ አብ/ #በታኅሣሥ ፲፪ በበዓለ ዕረፍታቸው ጊዜም፤ ሮም በጴጥሮስና በጳውሎስ ዕረፍት እንዳለቀሰች፤ ቅድስት ገዳማቸው ገዳመ ዋልድባ (ዋሊ) አልቅሳለች፨ ‹‹በከየት ወለሀወት ገዳምከ በሞትከ ዮም፤ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ ሉያ፤ ምድረ ዋልድባ ቅድስት ሰሚዓ ዜና ሞትከ፤ እንዘ አንተ ሰብእ ምድራዊ ወመልአክ ተሠመይከ፤ ካህነ አርያም ሳሙኤል መንበረ ሥላሴ ዘአጠንከ፤ አንበሳ ወነምር ይሰግዱ ለከ፤ ወይልህሱ ጸበለ እግርከ፤ ዕንቈ ወዕጣነ ማርያም አምጽአት ለከ፤ በቅዳሴሃ ሶበ ጸለይከ፤ በከየት ወለሐወት ገዳምከ።>> እንዲል ዚቅ፨ (ሥርዐተ ማኅሌቱን ላልደረሰው ያድርሱ)

#የመስቀል ወረብ (በቀራንዮ መካን ….) ፤ በደብረ ሰላም ሊቃውንት በዩቲዩብ ገጻችን ያድምጡ:: https://youtu.be/2QR7BR2Emg8

#ታኅሣሥ_12_የአቡነ_ሳሙኤል_በዓለ_ዕረፍት_ከሚከበርባቸው_ቦታዎች_ዋናዎቹ፤ ✤✤1. በሁሉም #የዋልድባ_ገዳም_ክፍልች_ (በውስጡ ባሉት 3ት ገዳማት፣ የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት፣ ጸሎት/ስዕል/ ቤቶች፣ የአትክልት ቦታዎችና ሞፈር ቤቶች)፤ እነዚህም፤ 1.1. ዋልድባ አብረንታንት መድኀኔ ዓለም ገዳም **1.2. ዋልድባ ዳልሽህ ገዳም (ዋልድባ ዳልሽህ አባ ሳሙኤል ገዳም) **1.3. ዋልድባ ሰቋር ገዳም (የኪዳነምሕረት፣ የቅዱስ ጊዮርጊስና የመድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን) **1.4. በዋልድባ አቴና (መቃብረ ሳሙኤል)፤ ሌሊቱንና ቀኑን ሙሉ ጧፍ እየበራ ገድላቸው እየተነበበ **1.5. በዋልድባ አባ ናፃ የአቡነ ተሥፋ ሐዋርያት ገዳም **1.6. በዋልድባ ደንደሮቃ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም **1.7. በዋልድባ ማይ ለበጣ ቤተ እግዚአብሔር **1.8. በዋልድባ ማይጋባ ቅዱስ ሚካኤል ገዳም **1.9. በዋልድባ ደለሳ ቆቋ አቡነ አረጋዊ ገዳም **1.10.በዋልድባ ማይ ሃርገጽ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም **1.11. በዋልድባ ዕጣኖ ማርያም ገዳም **1.12. በዋልድባ ዋልቅስ ኪዳነ ምሕረት **1.13. በዋልድባ አምብላ አቦ **1.14. በዋልድባ ስር ባሉ የስዕል ቤቶችና የአትክልት ቦታዎች (…..) ✤2. በተወለዱበት በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ጽዮን ማርያም፤ ✤3. ምንኵስናን በተቀበሉበት በደብረ በንኰል አቡነ መድኀኒነ አግዚእ ገዳም፤ (ሽሬ አጠገብ) ✤4. በቆብ ወንድማቸው በአባ ያሳይ መንዳባ መድኀኔ ዓለም ገዳም፤ (ጎርጎራ ፥ ጣና) ✤ 5. በቆብ አያታቸው በአቡነ ተክለሃይማኖት ደብረ ሊባኖስ ገዳም በውዳሴና በቅዳሴ (በደብረ ሊባኖስ ቅዳሴ በየቀኑ በማይቀደስበት፤ በዓመት ውስጥ ጥቂት ቀናት ብቻ በሚቀደሱበት ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የቅዳሴ ቀናቸው ከማይታጎሉ አንደኛውና ዋነኛው የአቡነ ሳሙኤል በዓለ ዕረፍት ነው) ፠፠ 5. አቡነ ሳሙኤል በመሠረቷቸውና ባስፋፏቸው ገዳማት፤ ✤5.1 #በደብረ_ዐባይ_አቡነ_ሳሙኤል_ገዳም_ /ሽሬ (እንዳባጉና) አጠገብ/ (#በኢትዮጵያ_የቅዳሴ_ዘደብረ_ዐባይ_ትምህርት_ዋና_ማስመስከሪያ)፤ እጅግ ደማቅ በኾነ ኹኔታ፡፡ ✤5.2 #በአብጠራ_(አብጠራህ) #አቡነ_ሳሙኤል_ገዳም_ /ጎንደር ፥ ደባርቅ/ (ከጎንደር ከተማ 100 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ የሚገኝ) ✤5.3 #በደብረ_ገነት_አቡነ_ሳሙኤል_ገዳም_ /አዲስ አበባ አቃቂ አጠገብ፥ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ያለበት ጋር/) በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ✤5.4 #በጎንደር_አዘዞ_አባ_ሳሙኤል_፡፡ ✤✤6. በተጨማሪም በስማቸው በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ይከበራል፤ ለአብነትም፤ በአዲስ አበባ በስማቸው በብቸኝነት በታነጸው #በቦሌ_ቡልቡላ_ምስካበ_ቅዱሳን_አቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ገዳም #በአዲስ_አበባ_ወረገኑ_ቅዱስ_ሚካኤል_እና_ጻድቁ_አቡነ_ሳሙኤል_ #በአዲስ_አበባ_ሲምሲ_ሚካኤል_(በድርብነት) #በታጠቅ_በዓለ_ወልድ_ቤ.ክ (በድርብነት ይከብራል) ፤/ ወደ መናገሻ መንገድ ሲሄዱ) #በአንጓ_ቀርነጃ_ታላቅ_ሴራ_ሳሙኤል_ #በነቀምቴ_አቡነ_ሳሙኤል_ #በዩኤስ_አሜሪካ_ቨርጂንያ_ሐመረ_ብርሃን_ቅዱስ_አባ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_ገዳም_ #ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባ ሳሙኤል/፫/ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ፡፡ ከቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደ/ት/ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት/ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem