en
Feedback
ግጥም 🇪🇹

ግጥም 🇪🇹

Open in Telegram

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ ግጥም እና የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።🙏🙏🙏 👏👏👏👏👏👏 ግጥሞቻችሁን ለመላክ እንዲሁም ለአስተያየት ይችን ይጠቀሙ @kidus15👍 ግሩፓችንን ይቀላቀሉ @kidapoimgroups

Show more
4 288
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+2830 days
Posts Archive
photo content
+2

ያሬዳዊ ግጥም) ያሬድ ከበደ ★★★ ጿሚውን ለይልን ★★★ እኛ አገልጋይህ ያንተ ደቀ መዝሙር የምንኖር በቃል ★★★ ይኸው ለቅበላ ገዝተን እንዳንበላ ስጋ ማልዶ ያልቃል ★★★ አየህልኝ አይደል እንደ ተቃውሞ ሰልፍ የነዳጅ ወረፋ ★★★ ከሚፆመው ይልቅ የማይፆመው በልጦ ሰልፍ ላይ ሲጋፋ ★★★ እኛ ያንተ ጥበብ የወንጌልህን ምንጭ ሌተቀን ምንጋት ★★★ ከበተስኪያን አፀድ አምነን ምንመራ በሙሴ ህግጋት ★★★ ካውደ ምህረት ቆመን ታቦት ተሸክመን * ህዝብና ርስትህን ባርክልን እያልን እምባ የምናፈስ ★★★ ሰው በምግብ ብቻ እንደማይኖር አውቀን ብንሞላም መንፈስ ★★★ መቼም ሰው ነንና ከኛ ማይጠበቅ ቢሆንም ስራችን ★★★ በስጋ ተማርኮ ስለተሸነፈ ፈራሹ ገላችን ★★★ ያየም የተመኘ እኩሌታ ፍርዱ እዳያስቀስፈን ★★★ ዐቢይን ከማይፆም ጿሚውን ለይና ከፊት አሰልፈን

(ያሬዳዊ ግጥም) ያሬድ ከበደ የሴቶች ቀን ቢከፋም ቢለማም ** ሀገር እያለችን ሀገር ለናፈቀን ስጋት ላደረብን መኖር ለጨነቀን * የባንዳራው ቀለም የእናት መቀነት ነው ተብላ ከተጠራች ሀገር በሴት አምሳል ** የሴቶች ቀን ተብሎ ባመት አንዴ ብቻ ለምን ይወደሳል?

ያሬድ ከበደ (ያሬዳዊ ግጥም) ✍️✍️ ✍️✍️ ሰው ይምሰለው እንጂ ፈጣሪ ሳይደግስ ከቶ መች ይጣላል **** ለምታጣጥር ነፍስ እስትንፋስን ዘርቶ ህይወት ይቀጥላል ** ሁሌም ትክክል ነው ይፈርዳል ይምራል መሳትን አያውቅም ** ይሁን ካለው ቀድሞ ንጋት ሳያበስር ጀምበር አያጠልቅም ✍️✍️✍️✍️✍️ መልካም ቀን

photo content

ያሬዳዊ ግጥም) ያሬድ ከበደ ያልተነገረለት ★★★ ባክሱም ራስ ጥበብ እንደ ሮሃ አለት ቀርፆን በራሱ ልክ ★★★ ድምበር አሻጋሪው ነፃ አውጪው ሙሴያችን እምዬ ምኒልክ ★★★ ለእናት ሀገር ፍቅር ከላይ በተቸረው ብርቱ ጥንካሬ ★★★ ያንገቱን ማህተብ ልቡ ላይ አትሞ የእምነት ቃል ፉካሬ ★★★ ጥንት አባቶቻችን የከፈሉት ዋጋ የተቀዳጁት ድል ወስዶኝ ወደ ትናንት ★★★ በድል የተፃፈ ቱባ ታሪክ ነበር ያለፉት ዘመናት ★★★ ድል አድራጊው ጀግና በደል እንዳይቆየን ብርቱ ፀፀት ተርፋን ★★★ ነጭ የበላይነት ያልነገሰበትን አወረሰን ዙፋን ★★★ ከንግስናው በላይ ከዙፋኑ ግርጌ አንድነት የዘራው ★★★ ኢትዮጵያ እንዳትፈርስ ወገን እንዳይጠፋ ሞቶ ለባንዲራው ★★★ በደምና ባጥንት መሰረት የጣለ የአፍሪካ ቀንዲል ★★★ ለጥቁር ህዝብ ታግሎ ከባርነት ግዞት ካንገቱ ቀና እንዲል ★★★ ዛሬም ነገም አልፎ ልክ እንደ ትላንቱ ታሪክ እንዲወሳ ★★★ ቅኔው ሲፈታለት ብድር መላሽ አርጎት ዉለታ እንዳይረሳ ★★★ ህያው ፅኑ እምነትህ ያላመነ ልቡን በፀሎት አግዛው ★★★ ማርያምን ነው ምልህ የዛሬውን ትውልድ ዳግም አንተ ግዛው

photo content

photo content

ያሬዳዊ ግጥም) 👉👉👉👉 ዛሬ *** የፍቅረኞች ቀን እያሉ ባመት አንዴ ቢዋቡበት * ለ ፍቅር ሲል የተሰዋው በመስቀል ላይ በዋለበት **** ቀይ አልባሳት ቀይ አበባ ቀዩ ምንጣፍ ቀዩ ወምበር **
ያሬዳዊ ግጥም) 👉👉👉👉 ዛሬ *** የፍቅረኞች ቀን እያሉ ባመት አንዴ ቢዋቡበት * ለ ፍቅር ሲል የተሰዋው በመስቀል ላይ በዋለበት **** ቀይ አልባሳት ቀይ አበባ ቀዩ ምንጣፍ ቀዩ ወምበር **** ከጎኑ ላይ የፈሰሰው ጠብታ ደም የአለም ሁሉ መዳን ነበር **** ታዲያ ለወደደው የኔ ላለው,,,,,, * ዋጋን መክፈል ላስተማረ አሳልፎ መስጠት ራስን * ለኔ ፍፁም ፍቅር ማለት ክርስቶስ ነው ክርስቶስን

{ያሬዳዊ ግጥም} ገጣሚ ያሬድ ከበደ 👉👉👉 ግዜ ቦታ ፍቅር ###### በልቤ ምርኩዝ ጫፍ የልብሽን ወሰን ቅጥሩን ተሻግሬ ** እስከፍፃሜው ጥግ የፍቅሬን ፅኑ እምነት ቃል ኪዳን አክብሬ ** አልቀርም እመጣለሁ ጠብቂኝ በተስፋ ** ከተማማልንበት የበተስኪያን አፀድ እንዳንጠፋፋ ** ጎህ ሳይቀድ ሰማዩ ሳይማልድ ፈጥኜ ፀሀይ ሳትበረታ ** ጥል አጥልቶ እንዳለ ሀሩሩን ቀድሜ ከቀጠርሽኝ ቦታ *** መጣው ስልሽ ውዴ,,,,,, ለፅኑ መውደዴ ውጥን ነው መንገዴ *** ከተነሳ አይቀርም ከዘገየ አይመጣም ** በሚል ልብሽ አምኖ ብቆይ አይበልሽ ቅር ** ምክንያቱም,,,,,,,, እምነትን ካዘለ በግዜ በቦታ አይለካም ፍቅር

አንተዬ አለምን ያስንቃል አንተን ያወቁ እለት ለኔ ቢያደርግህ ነው የገባሁት ስለት ዙራዬን አየሁት አይኔ ደቃ መሬት በምን ታጣፍጠው የናፍቆትን ምሬት ፈለኩህ እራብከኝ ባልጠግብህ እንኳን ለቅምሻም ስጠፋ እየኖርኩ መሰለህ ሞቼልህ እኮ ነው ሰርክ ነው ምደፋ ልቤን እርብሽ ሲላት ከአፀደ መቅደሱ ጉልበቴን መስበር ነው ለሁሉን ቻይ እርሱ ናፍቆቴ ሆይ አላውቅም ነበረ ልኩ በአንተ ገባኝ አሰብኩህና ድንገት ሳላስበው አይኔ ከድቶ አስነባኝ ናፈከኝ ያልኩ እንደው ቀለለብህ አይደል ቃል ወቶ ይጠፋል ልብ ነው ሚበደል ብቻ አሁንም ናፈከኝ ነው ምልህ እኔ አቅቶኛል እንዴት ልግለፅልህ ✍️የአብ..............

ወዳጄ ሰዎች እንዲያውቁልህ የምትገልጠው ህይወት አይኑርህ ምናልባት እንድታጣው ይጥራሉና over act አታድርግ የምትኖረውን በዝምታ ኑረው ጊዜ እውነት ነው አይሸፍንም ይገልጥሀል ያኔ አንተ ሳትሆን ድርጊትህ ሳይሆን ሰዎች ስላንተ ያወሩልሀል የይምሰል ኑሮም አትኑር እራስህን ከእውነት አታርቅ እውነት የከበረች ናትና ሰዎችንም ለመጉዳት አትግፋ ምናልባት ውድቀታቸውን ስጠብቅ ከከፍታ ታወጣቸዋለህና ያኔ አንተና ህሊናህ ትቀራላችሁ እና እውነትህ .............✍️የአብ

{ያሬዳዊ ግጥም} ያሬድ ከበደ ሀገሬ ** ያደፈ መዳፉን በንፁሀን እምባ ማልዶ እየታጠበ ##### ስንት አለ መሰለሽ ሆዱን እያሰፋ ሀገር ያጠበበ

ያሬዳዊ ግጥም) ።።።።።።።። ያሬድ ከበደ ፣፣፣፣፣፣ስጦታዬ፣፣፣፣፣፣ ባንተ የልደት ቀን ደመና ተገልጦ ሰማይ ፍክት ብሏል ፀአዳው ብሩህ ገና የመስከረም ዓደይ ፅገሬዳ መስሏል ጨረቃ ከዋክብት ምድሪቷን ሊያደምቁ ቁልቁል እያበሩ የብርሃን ጮራ እየፈነጠቀ ከበተስኪያን አፀድ ከቅጥር ደብሩ አንተን ለማወደስ ካህናት ዲያቆናት ማህሌት ቆመዋል ዜማን በቅላፄ እየደረደሩ የአብ አምሳያዋች ለውልደትህ ተብሲር ምስጋና ሲያደርሱ ቡራኬውን ባርከው ፅዋውን ተቃምሰው በዕድሜህ ቁጥር ልኬት ሻማ እየለኮሱ በዚህ ሁሉ መሀል የግብዣው ሰገነት እንደተከፈተ በትልቅ ሸራ ላይ ማረኪ ውብ ቃላት ተፅፏል ስላንተ የተፃፈው ስንኝ ከዕውቀት ሰሌዳ የጫረው ጠመኔ ሀረግ ሆሄ ፊደል ሰምና ወርቅ ቅኔ መሆኑን እያየው ውስጤን ሀሴት ሞልቶ እንደ ተደመምኩኝ እንኳን ተወልድክ ልል ይህን ግጥም ፃፍኩኝ

ያሬዳዊ ግጥም) ።።።።።።።። ያሬድ ከበደ ፣፣፣፣፣፣ስጦታዬ፣፣፣፣፣፣ ባንተ የልደት ቀን ደመና ተገልጦ ሰማይ ፍክት ብሏል *** ፀአዳው ብሩህ ገና የመስከረም ዓደይ ፅገሬዳ መስሏል * ጨረቃ ከዋክብት ምድሪቷን ሊያደምቁ ቁልቁል እያበሩ **** የብርሃን ጮራ እየፈነጠቀ ከበተስኪያን አፀድ ከቅጥር ደብሩ **** አንተን ለማወደስ ካህናት ዲያቆናት ማህሌት ቆመዋል ያሬዳዊ ግጥም) ።።።።።።።። ያሬድ ከበደ ፣፣፣፣፣፣ስጦታዬ፣፣፣፣፣፣ ባንተ የልደት ቀን ደመና ተገልጦ ሰማይ ፍክት ብሏል ፀአዳው ብሩህ ገና የመስከረም ዓደይ ፅገሬዳ መስሏል ጨረቃ ከዋክብት ምድሪቷን ሊያደምቁ ቁልቁል እያበሩ የብርሃን ጮራ እየፈነጠቀ ከበተስኪያን አፀድ ከቅጥር ደብሩ አንተን ለማወደስ ካህናት ዲያቆናት ማህሌት ቆመዋል ዜማን በቅላፄ እየደረደሩ የአብ አምሳያዋች ለውልደትህ ተብሲር ምስጋና ሲያደርሱ ቡራኬውን ባርከው ፅዋውን ተቃምሰው በዕድሜህ ቁጥር ልኬት ሻማ እየለኮሱ በዚህ ሁሉ መሀል የግብዣው ሰገነት እንደተከፈተ በትልቅ ሸራ ላይ ማረኪ ውብ ቃላት ተፅፏል ስላንተ የተፃፈው ስንኝ ከዕውቀት ሰሌዳ የጫረው ጠመኔ ሀረግ ሆሄ ፊደል ሰምና ወርቅ ቅኔ መሆኑን እያየው ውስጤን ሀሴት ሞልቶ እንደ ተደመምኩኝ እንኳን ተወልድክ ልል ይህን ግጥም ፃፍኩኝ

(ያሬዳዊ ግጥም) """""## የቃሉ ሰገባ ##""" ምጡቅ ማይደረስ የማይታይ ለሰው ድንቅ ስራዋቹ ማይመረመረው ምድርን ያለ ካስማ ሰማዩን ያለ ባላ ተጠቦ ተራቆ በውብ መዳፎቹ ከፈጠራት ኋላ በደሙ ቤዛነት ስሎ ያስቀመጣት ቅድስቷን ከተማ በቀስተ ደመና ህብረ ቀለማቱ ያለበሳት አርማ ግማደ መስቀሉን ከግሸኑ ከርቤ ደብራት አኑሮ ከግዮን ወንዝ ዳር መቅደስ ያነፀባት አለቷን ቦርቡሮ ፅላተ ሙሴንም በፂዮኗ ማርያም በክብር አሳድሮ ሳትፈርስ ሳትጠፋ ሊያኖራት በተስፋ በብሉይ ከትቦ ባ‘ዲስ ቃል ፀንሶ የባረካት ምድር በምፅአቱ ቀን የሚመጣ ለታ ቀድሞ እዳይቸገር ከክፉ ታድጎ ከልሎ ሚያዘልቃት በማዳኑ ጉያ የእግዜር ክታብ ኪዳን ሀገሬ ናት ጦቢያ

photo content

ያሬድ ከበደ ####### (ያሬዳዊ ግጥም) ★★★ የኛ ያንተ ነገር ★★★ ዞሮ ዞሮ መግቢያ የሁሉ ማረፊያ የመደሰት ጮቤ የሀዘን ማኩረፊያ ####### በቅጡ ሳንዘጋው ቤቷን በፉክክር በሁለት እጃችን አንግበን መፈክር ####### አንደኛው ለሰላም ሌላኛው ለክፋት በልባችን ተንኮል እየጫርን እሳት ####### ህይወት መዳብ ሆና በሞት ዋጋ መናር ግዛን ያልነው ሁሉ ሲሸጠን በዲናር ####### ከሞተው ጋር ስንሞት ከገዳይ ስንወግን ውስጣችን ሲደማ አረን ስንበግን የት ነበርክ አንተ ግን ? እኛማ,,,,,,,,, ዛሬም እንደወትሮ ባንተ ተስፋ ጥለን ሽቅብ ወደ ሰማይ አይናችንን ሰቅለን ###### ሌተቀን ስንፀልይ ዘመናት ስንሳል ከሳቃችን ቀድሞ እምባችን ይፈሳል ###### በሳቃችን መክሰም ጉንጫችን ረጠበ በእምባ ጅረት ዶፍ ##### አኬልዳማ ሆና ምድር ስትጨቀይ በንፁሀን ደም ጎርፍ ##### የተሳልነው ስለት ግምጃ ከርቤና እጣን ላምላክ ካልደረሰ ወይ ደግሞ ለሰይጣን ##### በድንግርግር ዓለም ሁለት ልብ ይዘን በቅጡ ላናምን ወዴት እንፀልይ ማንን እንለምን? ##### የላክልን መሲህ ሳይነጋ በጠዋት ለቀን ጅቦች ግብር ሲያደርገን መስዋት ##### በምድር ላይ ፍፁም እንደ አብርሃም የዋህ ሳይኖር ደግና ቅን በግ መሆን ሰለቸን ለመምሰል ይሳቅን ###### ያ,ሁሉ ቢሆንም የእዮብን ትዕግስት ላንችል ባትሰጠንም ስቃይ ጣር መከራ ##### ስለማይሳንህ በኛ ጣልቃ ገብተህ ታምራትን ስራ ##### በተስፋይቱ ምድር ትምቢት ይፈፀም ዘንድ በገባኸው ኪዳን ##### ዝምታህን ሰብረህ ድምፅህን አሰማ ኢትዮጵያን ለማዳን