cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

Show more
Advertising posts
1 702
Subscribers
-124 hours
+17 days
+6630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

✝ ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮቜን በድምፅ / በኊድዮ ለማግኘት ኚስር ( ክፈት ) ሚለውን ይጫኑ።
Show all...
ክፈት
ለመ🀄ላ🀄ል
Free FaceSwap🀖
Best DeepNude🙈
🀔 ዹማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ⁉ 📌 ሊቀ መዘምራን ቎ዎድሮስ ዮሎፍ 📌 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ 📌 ዘማሪ አርቲስት ይገሹም ደጀኔ 📌 ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ 📌 ቀሲስ ምንዎዬ ብርሀኑ 📌 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ 📌 ዘማሪ ዲ/ን አቀል መክብብ 📌 ዘማሪ ዲ/ን ሮቀል ማቲያስ 📌 ዘማሪት ምርትነሜ ጥላሁን 📌 ዘማሪት አቊነሜ አድነው 📌 ዘማሪት ዶ/ር ሔለን ተስፋዬ እና ዚሌሎቜንም ........... ዘማሪዎቜን መዝሙሮቜ እና አዳዲስ መዝሙሮቜን ለማግኘት ኚስር OPEN ዹሚለውን ይጫኑት። 👇 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ █ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █ █ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █ █ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █ ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
Show all...
💒 ስርዓተ ቀተ-ክርስቲያን 💒
⛪ ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ⛪
✝ መንፈሳዊ ትምህርት ✝
✝ ኪነ ጥበብ ብቻ ✝
✝ በማለዳ ንቁ !፪ ✝
✝ ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ ✝
💠 ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 💠
✝ ትንሳኀ ዘኢትዮጵያ ✝
✝ ዘ ተዋሕዶ ✝
🌷Harmee Tewaahidoo🌷
✝ ቀተ_ልሔም ~ Betelehem
✝ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ✝
💒 ኊርቶዶክሳዊ ወጣትነትና ሥነምግባር 💒
💒 መዝሙሹ ማህሌት 💒
🇚🇬  ደጉ ሳምራዊ  ✝
💒 ኑ በብርሀኑ እንመላለስ 💒
🔔 ዚተዋሕዶ መዝሙሮቜ 🔔
💠 በዓላት 💠
🖱መንፈሳዊ ፊልም 🖱
🖱መንፈሳዊ ግጥም 🖱
📯 ጥያቄዎቜ 📯
🔔 መዝሙር 🔔
🛰 EOTC Bot 🛰
🛰 Bot Official 🛰
█     ✞    𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒     ✞     █
🔔 ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮቜ 🔔
‌🇎‌🇷‌🇹‌🇭‌🇎‌🇩‌🇎‌🇜 ‌🇹‌🇪‌🇌‌🇊‌🇭‌🇩‌🇎
🏆 ዚተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈   ቻናሎቜ መገኛ 🏆
📌 ᎘ʀᎏⓂᎏ᎛ɪᎏɎ 📌
📩 ለመመዝገብ 📩
Free FaceSwap🀖
Best DeepNude🙈
በሕማማት ዚማይፀለዩ ፀሎቶቜ እንዳሉ ያውቃሉ ⁉ አሁኑኑ ገብተው ያንብቡት ለወዳጅ ዘመዶም ሌር ማሹግ አይርሱ። ➊ ☊ ዚሕማማት መጜሐፍ በPDF 📚 ➊ 🀲 በሕማማት ዹማይፀለይ ፀሎት አለ? ➊ 🀲 ለምን አይፀለይም? ➊ ✝ ማማተብ ለምን አይቻልም? ➊ 😘 መሳሳም ለምን አይቻልም? ➊ 🧎‍♂ በሕማማት ለምን እንሰግዳለን? ➊ 🧎‍♂ ስንሰግድስ ምን እያልን እንሰግዳለን? 👉🏜 ሙሉ ትምህርት ስለ ሕማማት 👈🏜 👇🏜👇🏜👇🏜 ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬ █  🔰 ✞  𝑶𝑷𝑬𝑵  ❖  𝑶𝑷𝑬𝑵  ✞ 🔰  █ █  🔰 ✞  𝑶𝑷𝑬𝑵  ❖  𝑶𝑷𝑬𝑵  ✞ 🔰  █ █  🔰 ✞  𝑶𝑷𝑬𝑵  ❖  𝑶𝑷𝑬𝑵  ✞ 🔰  █ █  🔰 ✞  𝑶𝑷𝑬𝑵  ❖  𝑶𝑷𝑬𝑵  ✞ 🔰  █ ▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
Show all...
💒 ስርዓተ ቀተ-ክርስቲያን 💒
⛪ ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ⛪
✝ መንፈሳዊ ትምህርት ✝
✝ ኪነ ጥበብ ብቻ ✝
✝ በማለዳ ንቁ !፪ ✝
✝ ታሪክ ዘ ኢትዮጵያ ✝
💠 ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 💠
✝ ትንሳኀ ዘኢትዮጵያ ✝
✝ ዘ ተዋሕዶ ✝
🌷Harmee Tewaahidoo🌷
✝ ቀተ_ልሔም ~ Betelehem
✝ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ✝
💒 ኊርቶዶክሳዊ ወጣትነትና ሥነምግባር 💒
💒 መዝሙሹ ማህሌት 💒
🇚🇬  ደጉ ሳምራዊ  ✝
💒 ኑ በብርሀኑ እንመላለስ 💒
🔔 ዚተዋሕዶ መዝሙሮቜ 🔔
💠 በዓላት 💠
🖱መንፈሳዊ ፊልም 🖱
🖱መንፈሳዊ ግጥም 🖱
📯 ጥያቄዎቜ 📯
🔔 መዝሙር 🔔
🛰 EOTC Bot 🛰
🛰 Bot Official 🛰
█     ✞    𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒     ✞     █
🔔 ዚኊርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙሮቜ 🔔
‌🇎‌🇷‌🇹‌🇭‌🇎‌🇩‌🇎‌🇜 ‌🇹‌🇪‌🇌‌🇊‌🇭‌🇩‌🇎
🏆 ዚተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈   ቻናሎቜ መገኛ 🏆
📌 ᎘ʀᎏⓂᎏ᎛ɪᎏɎ 📌
📩 ለመመዝገብ 📩
Free FaceSwap🀖
Best DeepNude🙈
🔎 #ማክሰኞ_ዚትምህርት_እና_ዚጥያቄ_ቀን ይህ ቀን ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ሰኞ በተናገሹው ባደሚገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀሚቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማሚበት ዕለት ነው በዚህም ምክንያት ዚጥያቄ እና ዚትምህርት ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ ሰኞ ቀን ጌታቜን በሚገማትን በለስ  መድሚቅ ሐዋርያት ሲደነቁ እምነት ያለው ሰው ሁሉን ማድሚግ እንደሚቜል ያስሚዳበት ዕለት ነው፡፡ ‹‹ ማለዳም ሲያልፉ በለሲቱን ኚሥርዋ ደርቃ አዩአት ጎጥሮስም ትዝ ብሎት መምህር ሆይ፥ እነሆ፥ ዚሚገምሃት በለስ ደርቃለቜ አለው። ኢዚሱስም መልሶ እንዲህ አላቾው፩ በእግዚአብሔር እመኑ እውነት እላቜኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደሚግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላቜኋለሁ፥ ዚጞለያቜሁትን ዚለመናቜሁትንም ሁሉ እንዳገኛቜሁት እመኑ፥ ይሆንላቜሁማል ለጞሎትም በቆማቜሁ ጊዜ፥ በሰማያት ያለው አባታቜሁ ደግሞ ኃጢአታቜሁን ይቅር እንዲላቜሁ፥ በማንም ላይ አንዳቜ ቢኖርባቜሁ ይቅር በሉት። እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታቜሁም ኃጢአታቜሁን ይቅር አይላቜሁም። ››ማር 11፥20-26 እያለ ያስተማሚበት ዕለት ስለሆነ ዚትምህርት ቀን ይባላል ሌላው ይህ ዕለት ጌታቜን  ሰኞ ዕለት  ካደሚጋ቞ው ነገሮቜ ተነስተው አይሁድ ጥያቄ ያቀሚቡበት ዕለት ነው ‹‹ ወደ መቅደስም ገብቶ ሲያስተምር ዚካህናት አለቆቜና ዚሕዝብ ሜማግሎቜ ወደ እርሱ ቀሚቡና በምን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት። ኢዚሱስም መልሶፊ እኔ ደግሞ አንዲት ነገር እጠይቃቜኋለሁፀ እናንተም ያቜን ብትነግሩኝ እኔ ደግሞ እነዚህን በምን ሥልጣን እንዳደርግ እነግራቜኋለሁፀ ዚዮሐንስ ጥምቀት ኚወዎት ነበሚቜ? ኹሰማይ ወይስ ኹሰው? አላ቞ው። . . . ›› /ማቮ 21 ፥23- 27/ ይህ ጥያቄ ጌታቜን ሲያደርጋ቞ው ዚነበሩ ተአምራትና ድንቅ ድንቅ ሥራዎቜ ዚካህናት አለቆቜን ስላስቀኗ቞ው ጌታቜንን ኚሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ለማጋጚት ዚቀሚቡት ጥያቄ ነበር ጌታቜን በቀተ መቅደስ ዹነበሹውን ገብያ ስለበተነው ዚነጋዎዎቹን  መደባ቞ውን ስለገለበጠ ነጋዮን ማባሚርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነውና በማን ሥልጣን አደሹኹው ብለው ጠዚቁት ጌታቜን â€¹â€¹á‰ áˆ«áˆŽ áˆ¥áˆáŒ£áŠ•â€ºâ€º á‰¢áˆ‹á‰žá‹ ጾሹ መንግሥት አቋም አለው በማለት ኚሮማ መንግሥት ዘንድ ለማሳጣት ነበር ዕቅዳ቞ው ጌታቜን ግን ዚፈሪሳውያንን ጠማማ አሳብ ስለሚያውቅ â€¹â€¹á‹šá‹®áˆáŠ•áˆµ áŒ¥áˆá‰€á‰µ áŠšá‹šá‰µ áŠá‹? áŠšáˆ°áˆ›á‹­ áŠá‹ á‹ˆá‹­áˆµ áŠšáˆá‹µáˆ­?›› áˆ²áˆ ጠይቋ቞ዋል፡፡ ጌታቜን ፈሪሳውያን ላቀሚቡለት ጥያቄ ቀጥተኛ ምላሜ አልሰጠም ምክንያቱም ጥያቄው ለኚሳሟቹ ዓላማ መሳካት አመቺ ሁኔታን ስለሚፈጥር ጥያቄውን በጥያቄ መልሶላ቞ዋል፡፡ እነርሱም â€¹â€¹áŠšáˆ°áˆ›á‹­ áŠá‹â€ºâ€º á‰¢áˆ‰á‰µ â€¹â€¹áˆˆáˆáŠ• áŠ áˆ‹áˆ˜áŠ“ቜሁበትም?›› áŠ¥áŠ•á‹³á‹­áˆ‹á‰žá‹á€ â€¹â€¹áŠšáˆ°á‹ áŠá‹â€ºâ€º á‰¢áˆ‰á‰µ ደግሞ ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ አባት ይፈሩት፣ እንደ መምህር ያኚብሩት ነበርና ሕዝቡ እንዳይጣሏ቞ው ስለፈሩ â€¹â€¹áŠšá‹ˆá‹Žá‰µ áŠ¥áŠ•á‹° ሆነ áŠ áŠ“ውቅም›› á‰¥áˆˆá‹ መለሱለት፡፡ እርሱም â€¹â€¹áŠ¥áŠ”ም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራቜሁም›› áŠ áˆ‹á‰žá‹ ኹዚህ ታሪክ ዚተነሳ ይሄ ቀን ዚጥያቄ ቀን ይባላል፡፡ https://t.me/tmhrteorthodox
Show all...
🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

​​​​ሥርዓተ ጞሎት ሰሙነ ሕማማት ኹሰኞ እስኚ ዕሮብ  ካህናት እያዜሙ እዚሰገዱ እኛም እዚተቀበልን እያዜምን ዚምንሰግድበትን   ሥርዓት ለማውቅ እና ለመፈፀም ኚስር ያንብቡ ❖ ዹጾሎተ ሐሙስና ዹዕለተ ዓርብ ሥርዓተ ጞሎት 👉 ኹሰኞ ጀምሮ እስኚ ዓርብ ድሚስ ባሉት ቀናት ውስጥ  በመጀመሪያ ዲያቆኑ ቀተ ክርስቲያኑን ሊስት ጊዜ ዞሮ ደወል ካሰማ በኋላ መቶ አምሳው ዳዊት ይታደልና ይደገማል፡፡ ዚሰባት ቀናት ውዳሎ ማርያምና አንቀጾ ብርሃን  እስኚ ይዌድስዋ  ድሚስ ታድሎ ይደገማል፡፡ ኚዚያም “እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ዓመ ኹመ ዮም ያብጜሐኒ ያብጜሕክሙ አግዚአብሔር በፍሥሓ ወበሰላም” ተብሎ አቡነ ይደገምና  በዐራቱም ወንጌላት መሠሚት ለእያንዳ቞ው በእዚዕለቱና  ሰዓቱ ዹተመደበውን አቡነ ካህናቱ በቀኝና በግራ እዚተፈራሚቁ  ይመራሉ፡፡ ካህናቱና ሕዝቡም ይቀበላሉ፡፡ በመቀጠል፡- (ትእዛዝ፡ ሕዝቡ በጞሎት በተሰበሰቡ ጊዜ ጠዋት ወይም በ3፣ በ6፣በ9፣ በ11ሰዓተ መዓልት መጀመሪያ ሕዝቡ እዚሰገዱና እዚተኚተሉ እንዲህ ይበሉ፡፡ ) ✥ "ለኹ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም ፡፡" ✥ "አማኑኀል አምላኪዚ ለኹ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም፡፡" ✥ " ኩ እግዚእዚ ኢዚሱስ ክርስቶስ ለኹ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም፡፡ " ✥ " ኃይልዹ ወጾወንዹ ውእቱ እግዚእዚፀ እስመ ኮንኚኒ ሚዳእዚ እብል በአኰ቎ት ፡፡" ትእዛዝ፡ በዚህ ጊዜ ካህኑ እዚተኚተሉ አቡነዘበሰማያት ይድገሙ ። ይህን ዹላይኛውን ጞሎት እያመላለሱ ኚአቡነ ዘበሰማያት ጋር 12 ጊዜ ይበሉ ❖ " ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም፡፡ ❖ "ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለማሕዹዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖"ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ስለልጣኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለኢዚሱስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ "ለክርስቶስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለሕማሙ  ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም፡፡ " ትእዛዝ፡- ይህ ሊስት ጊዜ እዚተመላለሰ ይባላል፡፡በመጚሚሻም ዹሚኹተለውን ሊስት ጊዜ እያመላለሱ ይበሉ፡፡ ❖ "ለኹ ይደሉ ኃይል፣ ወለኹ ይደሉ ስብሐት ወለኹ ይደሉ አኰ቎ት ኩ እግዚእዚ ኢዚሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም" ትእዛዝ፡- ካህኑ ‹ጞልዩ በእንተ ጜንዓ ዛቲ . . .› ብሎ በሚያነብ ጊዜ በዚምዕራፉ "እግዚኊ ተሳሃለነ" እዚተባለ ይሰገዳል፡፡ ትእዛዝ፡- ኹዚህ ሁሉ በኋላ ሕዝቡ ዚሚኚተሉትን ጞሎት በግራና በቀኝ ይበሉፀ "ክርስቶስ አምላክነፀ ዘመጜአ ወሐመ በእንቲአነ በሕማማቲሁ ቀዝወነፀ  ንሰብሖ ወናልዕል ስሞ ኅቡሚፀ እስመ ውእቱ ገብሚ መድኃኒተ በዕበዹ ሣህሉ" (በዐርብ) ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ ይባላል፡፡ ትእዛዝ፡- ቀጥሎም ሕዝቡ በሁለት ክፍል ሆነው ዹሚኹተለውን ጞሎት ሁለት ጊዜ በመኚታተል አንድጊዜ በማስተዛዘል ይበሉት፡፡ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ#ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ #አብኖዲ  ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶን #ናይን፣ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶን ፀ #ታዖስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ #ማስያስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ #ኢዚሱስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ #ክርስቶስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ #አማኑኀል ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ #ትስቡጣ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶን ትእዛዝ፡- ኹዚህ በኋላ ኪርያላይሶን አርባ አንድ ጊዜ ይባላል፡፡ ይኾውም  በአንድ ወገን 20 ጊዜ በሌላው ወገን 21 ጊዜ በጠቅላላው 41 ጊዜ ኪርያላይሶን  ኪርያላይሶን  ኪርያላይሶን  እዚተባለ ይሰገዳል፡፡ በመጚሚሻ ጊዜ፡- ✥ ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠሹ ኹመ ናምልኮ (እናመልኚው ዘንድ ለፈጠሹን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል)፡፡ ✥ ስብሐት ለማርያም እመ አምላክ እግእዝትነ ወመድኃኒትነ (እመቀታቜንና መድኃኒታቜን ለሆነቜ ለአምላክ እናት ለማርያም ምስጋና ይገባል)፡፡ ✥ ስብሐት ለመስቀለ ክርስቶስ ዕፀ መድኃኒት ኃይልነ ወፀወንነ(ኃይላቜን መጠጊያቜን ለሆነ ድኅነት ለተገኘበት ለክርስቶስ ምስጋና ይገባል)ፀፀ ጾሎተ ሃይማኖትን ሐመ  እስኚ ሚለው ድሚስ መድገም ነው፡፡  /ኹሰኞ እስኚ ሚቡዕ ይባላል/ #ሌር https://t.me/tmhrteorthodox
Show all...
🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

ዹሰሙነ ሕማማት ሰኞ፡- መርገመ በለስ ዚተፈጞመበት ዕለት ነው፡ ጌታቜንና አምላካቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግሥቱም ኚቢታኒያ ሲመጡ ተራበ፡፡ (ማር.11ፀ11-12) ቅጠል ያላት በለስ ኚሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀሚበፀ ነገር ግን ኹቅጠል በቀር አንዳቜ ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ኹአሁን ጀምሮ ማንም ኚአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ሚገማት። በለስ ዚተባለቜ ቀተ እስራኀል ናትፀ ፍሬ ዚተባለቜ ሃይማኖትና ምግባር ናትፀ ኚእስራኀል ፍቅርንፀ ሃይማኖትንፀ ምግባርን ፈለገ አላገኘምፀ እስራኀል (ሕዝበ እግዚአብሔር) መባልን እንጂፀ ደግ ሰው አይገኝብሜ ብሎ ሚገማትፀ በመርገሙ ምክንያት እርሱ ኚለያ቞ው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋባት በለስ ኊሪት ናትፀ ኊሪትን በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኊሪትና ነቢያትን ልሜር አልመጣሁም ልፈጜም እንጂ በማለት ፈጞማትፀ ሕገ ኊሪትን ኹመፈጾም በቀር በእርሷ ድኅነት አላደሚገባትምናፀ ፍሬ በአንቺ አይሁን አላትፀ ደኅነት በአንቺ አይደሚግብሜ ብሏታልና እንደመድሚቅ ፈጥና አለፈቜ፡፡ በለስ ኃጢአት ናትፀ ዚበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነቜ ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣልፀ ቆይቶ ግን ይመራልፀ ኃጢአትም ሲሰሩት ደስ ደስ ያሰኛልፀ ኋላ ግን ያሳዝናልፀ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ኚኃጥአን ጋር ዋለፀ ኃጥእ ኚመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰትፀ በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልኚት ፍሬ አላገኘባትም አለፀ በአንቺ ፍሬ አይገኝ ዚሚለውምፀ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ ዹሚቀር አይኑር ለማለት ነውፀ ስትሚገም ፈጥና መድሚቋም፣ በአዳም ምክንያት ያገኘቜን ዕዳ በደል በእርሱ ካሣነት እንደጠፋቜልን ለመግለጜ ነው፡፡ አንጜሆተ ቀተ መቅደስ ዚተፈጞመበት ዕለት ነው፩ ጌታቜን በለስን ኚሚገማት በኋላ ወደ ቀተ መቅደስ ሄደፀ ቀተ መቅደስ፣ ቀተ ጞሎት፣ ቀተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቀተ ምስያጥ (ዚንግድ ቀት) ሆኖ ቢያገኘው ቀ቎ ዚጞሎት ቀት ትባላለቜፀ እናንተ ግን ዚወንበዶቜ ዋሻ አደሚጋቜኋት ብሎ ዚሚሞጡበትን ሁሉ ገለበጠባ቞ውፀ ገርፎም አስወጣ቞ውፀ ይህም ዚሚያሳዚው ማደሪያው ቀቱ ዹነበርን ዚአዳም ልጆቜ ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታቜንን ሁሉ እንዳራቀልን ዚሚገልጜ ነው በዚህ በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በቀተክርስቲያን ተገኝተው ወዛቾው ጠብ እስኪል ድሚስ በነግህፀ በሠለስተ፣ በስድስቱ ሰዓትፀ በተሰዓቱ ሰዓትና በሠርክ መላልሰው ሲሰግዱና ሲጞልዩ ይሰነብታሉፀ በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉፀ ምክንያቱም ዚደሚሰብን መኚራ ኀዘኑን እና 5ሺ ኹ5መቶ ዘመን ዹሰው ልጅ በጹለማ ይኖር እንደነበሚ ለማዘኹር ነው #ሌር https://t.me/tmhrteorthodox
Show all...
🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

[በዓለ ሆሣዕና] ✍በመጋቀ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ ዹተለጠፈ) ♥ ሆሣዕና ማለት ዚዕብራይስጥ ቃል ነውፀ “ሆሻአና” ሲባል ትርጒሙም “አቀቱ አኹን አድን” ማለት ነውፀ ይኜ በዓለ ሆሣዕና ኹ9ኙ ዐበይት ዚጌታ በዓላት ውስጥ ሲኟን ክንፋቾው ትእምርተ መስቀል ዚሚሠራው ኪሩቀል ሱራፌል በፍርሀት በሚዐድ ኹነው ዘፋኑን ዚሚሞኚሙት ጌታ በትሕትና ኟኖ ጀርባዋ ላይ ትእምርተ መስቀል ባለባት በአህያና በውርንጫይቱ ተቀምጩ እዚተመሰገነ ወደ ቀተ መቅደስ ዚገባበት፣ ዚዘካርያስ ትንቢት ዚተፈጞመበት፣ ሕዝቡ ዘንባባ ይዘው ዚዘመሩበት፣ ሕፃናት በንጹሕ አንደበታ቞ው ሆሣዕና ብለው ያመሰገኑበት ታላቅ በዓል ነው፡፡ ♥ ይኜም ታሪክ በ4ቱ ወንጌላት ላይ ሲጻፍ በማቮ 21፡1 ላይ “ወደ ኢዚሩሳሌምም ቀርበው ወደ ደብሚ ዘይት ወደ ቀተ ፋጌ ሲደርሱ፥ ያንጊዜ ኢዚሱስ ኹደቀ መዛሙርቱ ሁለት ላኹ” ይላል፡፡ ♥ ቀተ ፋጌ ማለት ዚበለስ ቀት ማለት ሲኟን ኚኢዚሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ በሚወስደው መንገድ አቅራቢያ ያለቜ ትንሜ መንደር ናትፀ ኹሉን ዐዋቂ ዚኟነው ጌታም ጎጥሮስንና ዮሐንስን “በፊታቜሁ ወዳለቜው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም ዚታሰሚቜን አህያ ውርንጫም ኚርሷ ጋር ታገኛላቜሁፀ ፈትታቜሁ አምጡልኝ” በማለት እንደ ማዕምሹ ኅቡአትነቱ (ዹተሰወሹውን ዐዋቂነቱ) በመንደሯ ውስጥ ስለታሰሩት አህያና ውርንጫ አስቀድሞ ይነግራ቞ዋል፡፡ ♥ በተናቀቜ ግርግም በቀተልሔም በተወለደ ጊዜ ላምና አህያ ትንፋሻ቞ውን እንደገበሩለትፀ አኹንም በሰዎቜ በተናቀቜ አህያ በጌትነት ተቀምጩ እንዲመሰገንባት መርጧታል፡፡ ❀ በልደቱ ማንም ያልገባባት ዚማይገባባት ዚሕዝቅኀል ዚታተመቜ መቅደስ ዚተባለቜ ዘላለማዊት ድንግል እመቀታቜንን እንደመሚጠ ዛሬም በሆሣዕና ማንም ሰው ያልተቀመጠበት ውርንጫ እንዲያመጡ አዘዘ። ♩ ኚዚያም “ማንም አንዳቜ ቢላቜሁ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉፀ ወዲያውም ይሰዳ቞ዋል” በማለት ዚኹሉ ጌታ ርሱ መኟኑን አመለኚታ቞ውፀ በተሰጣ቞ው ሥልጣነ ክህነት ዚሕዝቡንም ዚአሕዛቡን ኀጢአት ዹማሰር ዚመፍታት ሰማያዊ ሥልጣነ ክህነት ዚተሰጣ቞ው ሐዋርያትን ዚሕዝብ ምሳሌ ዚኟነቜውን አህያይቱንና ዚአሕዛብ ምሳሌ ዚኟነቜው ውርንጫዋንም እንዲያመጡ አዟ቞ዋልና። ♥ ሊቁ ጀሮምም፡- “ደቀ መዛሙርቱ አህያይቱንና ውርንጫይቱን ለመፍታት ኹለት ኟነው መላካ቞ው ለሕዝብም ለአሕዛብም መላካ቞ው ያመለክታል፡፡” ይላል። ♥ ሊቁ አምብሮስ፡- “አህያዚቱን ለመፍታት ማንም አይኚለክላቜኁም ብሎ መላኩ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ዚሰጣ቞ው ዹማሰር ዚመፍታት ሥልጣን ሰማያዊ መኟኑን ያመለክታል፡፡” በማለት ልዩ ምስጢርን አስተላፎበታል። ♥ አምጥተው “ልብሳ቞ውንም በእነርሱ ላይ ጫኑ”ፀ በአህያዋና በውርንጫዋ ላይ ኮርቻ ሳይኟን ልብስ ማድሚጋ቞ው ኮርቻ ይቈሚቊራል ልብስ ግን አይቈሹቊርምና ዚማትቈሚቊር ሕግ ሠራኜልን ሲሉ። ዳግመኛም ልብስ በአካል ያለውን ኀፍሚት እንዲሰውር አንተም በደላቜንን ዚምትሰውርልን ይቅር ባይ ነኜ ሲሉ በማለት መተርጉማን ይተነትናሉ፡፡ በተጚማሪም ልብስ በልጅነት ይመሰላልና ዹተገፈፍነውን ዹጾጋ ልብሳቜን (ልጅነትን) ትመልስልናለህ ሲሉ ነው፹ ♥ ቅዱስ ኀፍሬም ይኜነን ሲተሚጉም "ልብሳ቞ውን አውልቀው ያነጠፉለት ሰዎቜ አሮጌውን ማንነታ቞ውን ትተው ዐዲሱን ልብስ ክርስቶስን መልበሳ቞ውን ያስሚዳል። ሐዋርያ ጳውሎስ “አሮጌውን ሰውነት አስወግዳቜሁ አዲሱን ሰው ልበሱት” እንዳለው (ኀፌ.4፣23) ይኾውም ጥምቀት ነው" ይላል። ♥ ኚኢዚሩሳሌም እስኚ ቀተ መቅደስ 16 ምዕራፍ ሲኟን መተርጒማነ ሐዲስ በትርጓሜ ወንጌል ላይ እንደሚገልጹት 14ቱን ጌታ በእግሩ ሲኌድ 2ቱን በአህያዋፀ በውርንጫዋ 3 ጊዜ ቀተ መቅደሷን ዞሯል፡- 14ቱ በእግሩ መኌዱ ዹ10ሩ ቃላት 4ቱ ዹ4ቱ ኪዳናት ምሳሌ፡፡ 2ቱ በአህያዋ መጓዙ ዹፍቅሹ እግዚአብሔርና ዹፍቅሹ ቢጜፀ 3ቱን በውርንጫዋ ተቀምጩ ቀተ መቅደሱን መዞሩ ዹ3ትነቱ ዚአንድነቱ ምሳሌ ነበር፡፡ ♥ ጌታ ንጉሠ ነገሥት ሲኟንፀ ኪሩቀል ሱራፌል ዙፋኑን በፍርሀት በሚአድ ዚሚሞኚሙት 24ቱ ካህናተ ሰማይ ዙፋኑን በፍርሀት ዚሚያጥኑለት ርሱ በትሕትና ዹዋህ ኟኖ በተናቁት በአህያና በውርንጫይቱ ላይ ተቀመጠፀ ይኜም ዚተናቁትን ሊያኚብር እንደመጣናፀ በዹዋሀን ምእመናን ልቡና እንደሚያድር ለማሳወቅ በነርሱ ተቀመጠ። በተጚማሪም መተርጉማን እንዳመሰጠሩት በአህያ ዹተቀመጠ አባሮ እንደማይዝ ሞሜቶ እንደማያመልጥ ርሱም ካልፈለጉት እንደማይገኝ ኚፈለጉት እንደማይታጣ በምስጢር አመለኚታ቞ው፡፡ ♥ በተጚማሪም አህያ ሲፈጥራት በጀርባዋ ላይ ትእምርተ መስቀል ያላት ናትና ትእምርተ መስቀል ያለባት እእርሷ እንድትፈታ ማዘዙ ኹ5 ቀን በኋላ በመስቀል ተሰቅሎ በሲኊል ዚታሠሩትን ዹሰው ልጆቜን ነጻ ሊያወጣ መጥቷልና አህያን መርጧታልፚ ♥ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ፡- ስለዚኜ ነገር በትርጓሜ ወንጌሉ ላይ “እነዚኜ እንስሳት መላውን ዹሰው ልጅ ይወክላሉ፡፡ ኹለቱም አህያ መኟና቞ውም ዹሰው ልጅ ክርስቶስ ኚመምጣቱ በፊት ዹነበሹውን አኳኋን ዚሚያስሚዳ ነው፡፡ ምክንያቱም አህያ በኊሪቱ ዘንድ ንጹሕ እንስሳ አይደለቜምፀ ብዙ ክብደት ያላት ዚማትወደድ እንስሳ ናትፀ ደካማ ናት፡፡ ሰውም እንደተናገርን ክርስቶስ ኚመምጣቱ በፊት እንዲኜ ነበሚ፡፡” በማለት አመስጥሯል፡፡ ♥ ሊቁ ቅ. ቄርሎስ ዘእስክንድርያም፡- “ፈጣሬ ኵሉ እግዚአብሔር ሰውን በምድር ላይ ጠቢብ አድርጐ ፈጥሮት ነበር፡፡ ማሰብና ማሰላሰል ዚሚቜል ፍጥሚት አድርጐ ፈጥሮት ነበር፡፡ ሰይጣን ግን አታለለው፡፡ ምንም እንኳን ሰው በሥላሎ አምሳል ቢፈጠርም መልኩን አበላሞው፡፡ ፈጣሬ ኵሉ እግዚአብሔርን ማወቅ ተሳነው፡፡ ክፉው ሰይጣን ሰውን እንስሳ እስኪመስል ድሚስ ክብሩን አዋሚደው፡፡ መዝሙሹኛው ዳዊት፡- “ሰውስ ክብሩን አላወቀምፀ ዹሚጠፉ እስሳትን መሰለ” ያለውም ስለዚኹ ነው (መዝ.49፡12)፡፡ በመኟኑም አህያይቱ ክብራ቞ውን አጥተው ተዋርደው ዚነበሩትን እስራኀል ዘሥጋን ትመስላለቜ፡፡ እስራኀል ኹሕጉ ጥቂት ነገርን ያውቃሉ፡፡ ኚነቢያትና ኚቅዱሳንም ትንሜ ያውቃሉ፡፡ ኚኹሉም በላይ ደግሞ ወደ አሚን ዚሚጠራ቞ውን ክርስቶስን አልታዘዙትም፡፡ “እኔ ዹዓለም ብርሃን ነኝ” ሲላ቞ውም እንደ አህያይቱ በድንቁርና ተይዘው እንደነበሚ ሲገልጥላ቞ው ነው፡፡ ውርንጫይቱ ደግሞ አሕዛብን ትወክላለቜ፡፡ ውርንጫ እኜልን ለመጫን እንደማታገለግል ኹሉ አሕዛብም ማኅደሹ እግዚአብሔር ኚመኟን ርቀው ነበርና፡፡” በማለት ገልጿል፡፡ ♥ ያን ጊዜ ኚሕዝቡም እጅግ ብዙዎቜ ልብሳ቞ውን በመንገድ ላይ አነጠፉ ይኜንም ማድሚጋ቞ው ስንኳን አንተ ዚተቀመጥኜባት አህያ መሬት መርገጥ አይገባትም ሲሉ ነበር። እንስሳዋ እንኳን ጌታ ቢቀመጥባት እንዲህ ክብር ያገኘቜ ኹሆነ ያደሚባ቞ው ቅዱሳንማ ዚሚገባ቞ው ክብር ምን ያህል ይሆን? ይልቁኑ 9 ወር ኹ5 ቀናት በማሕፀኗ ዚተሞኚመቜው ኚሥጋዋ ሥጋን ኚነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ሰው ዹሆነውን አምላክ ዚወለደቜው ዚቅድስት ድንግል ማርያም ክብርማ እጅጉን ታላቅ ነው። ❀ ጌታ ዚተቀመጠባት አህያ በክብር ወደ ኢዚሩሳሌም እንደገባቜ ጌታ ያደሚባ቞ው ምእመናን ደግሞ በታላቅ ክብር ወደ ኢዚሩሳሌም ሰማያዊት ይገባሉ።
Show all...
🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

❀ ሌሎቜም ኹዛፍ ጫፍ ጫፉን እዚቈሚጡ በመንገድ ላይ ያነጥፉ ነበር። ይኜም ዘንባባ ብዙ ምሳሌ ያለው ነውፀ ይኾውም በእስራኀል ያለው ሰሌን፣ ተምር፣ ዘይት ነበርና ያነን ቈርጠው አመስግነውታልፀ ይኜም ምሳሌነት ያለው ነውፀ ይኜም ሰሌን እሟኻማ እንደኟነ ትእምርተ ኀይል ትእምርተ መዊእ አለኜ ሲሉ ነውፀ እሳት ለብልቊ ይተወዋል እንጂ እንደማያቃጥለው ባሕርይኜ አይመሹመርም ሲሉ ነበር፡፡ ♥ ዳግመኛም ኹሰሌን ዝንጣፊ ጋር ተመሳሳይ ተምር ይዘዋል ይኜም ተምር ልዑል ነው አንተም ልዑለ ባሕርይ ነኜ ሲሉፀ ፍሬው አንድ እንደኟነ አንተም ዋሕደ ባሕርይ ነኜ ሲሉ፡፡ በእሟኜ ዹተኹበበ ነው ባሕርይኜ አይመሹመርም ሲሉ ነበር፡፡ ♥ ዚዘይት ዛፍ ነው ቢሉ ዘይት ጜኑዕ እንደኟነ ጜኑዐ ባሕርይ ነኜ ሲሉፀ ብሩህ ነው ብሩሀ ባሕርይ ነኜ በትምህርትኜም ዹሰውን ልቡናን ታበራለኜ ሲሉፀ ዘይት መሥዋዕት እንደሚኟን መሥዋዕት ትኟናለኜ ሲሉ ነበር፡፡ ♥ “ዚሚቀድሙትም ሕዝብ ዚሚኚተሉትም ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ዚሚመጣ ዚተባሚኚ ነውፀ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር” በማለት በአርያም መድኀኒት እንደኟነና እግዚአብሔር አብ “ዚምወድደው ልጄ ይኜ ነው” ብሎ መስክሮለት ዚመጣው ኢዚሱስ ክርስቶስ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን ዚሚያርቅ በሹኹተ ሥጋን በሹኹተ ነፍስን ዚሚያድል መኟኑን ኹሉም መሰኚሩለት፡፡ ♥ በእጅጉ ዹሚደንቀው ዹ40 ቀን ዹ80 ቀን ሕጻናት ዚፈጠራ቞ው ጌታ በአህያና በውርንጫ ተቀምጩ ባዩት ጊዜ በንጹሕ አንደበታ቞ው አንደታ቞ው ሚቶላ቞ው ጌታን ዘንባባ በመያዝ ሲያመሰግኑ በእጅጉ ይደንቅ ነበርፀ ነገር ግን ጞሐፍት ፈሪሳውያን ያደሚገውን ድንቃ ድንቅ በመቅደስም ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ እያሉ ዚሚጮኹትን ልጆቜ ባዩ ጊዜ፥ ተቈጥተው እነዚህ ዚሚሉትን አትሰማምን? አሉትፀ ኢዚሱስምፊ እሰማለሁፀ ኚሕፃናትና ኚሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ ዹሚለውን ቃል ኚቶ አላነበባቜሁምን? በማለት በሕጻናት እንደሚመሰገን ዚነርሱም ጌታ መኟኑን ኚዳዊት መዝሙር በመጥቀስ ነገራ቞ው፡፡ ♥ ሊቁ ያዕቆብ ዘሥሩግ ሰለዚኜ ምስጢር ሲገልጞው ፡- “ፍቅርኜ ኚዘባነ ኪሩብ አውርዶ በአህያ ጀርባ ላይ እንድትቀመጥ አስገደደኜ፡፡ ብዙ ዐይንና ብዙ ገጜ ካላ቞ው ኚሰራዊተ መላክእት ይልቅ በዲዳዋ አህያ ትመሰገን ዘንድ ወደደክ፡፡ በሰማይ ሰራዊት ሠሹገላ ተቀምጠኜ ክብርኜን ማሳዚት አልወደድክምፀ በውርንጫላይቱ ላይ ተቀምጠኜ ወደ ሰማይ ሰራዊት መኌድን መሚጥክ እንጂ፡፡ በአርያም እሳታውያን ዚሚኟኑ ኪሩቀል ያመሰግኑኻልፀ በምድርም ሕፃናት ይዘምሩልኻል፡፡ በአርያም ብርሃናውያን መላእክት በብርሃን ክንፋቾው መንገድኜን ያነጥፉልኻልፀ በምድርም ደቀ መዛሙርትኜ ልብሳ቞ውን አንጥፈው መንገድኜን አስተካኚሉ፡፡ ወዮ! አርያማዊ ሲኟን ምንም ሳይንቀን ይጐበኘን ዘንድ ኚአባቱ መጣ፡፡ ርሱም በገዛ ፈቃዱ ሰው እስኚ መኟን ደርሶ መጣ፡፡ በአህያ ላይ ተጭኖም ይጐበኘን ዘንድ መጣ፡፡ ነቢዩ ዘካርያስ ዚመንፈስ ቅዱስን እንዚራ ይዞ በደስታ ትንቢትን ለመናገር ይቻኰላል፡፡ እዚደሚደሚም ዚጜዮንን ልጅ ይጠራታል፡፡” በማለት አስተምሯል፡፡ ♥ ዚምስጋና ጌታ ኢዚሱስ ክርስቶስ በአህያዋና በውርንጫዋ ላይ ተቀምጩ ሕፃናትን ጚምሮ ዘንባባ ሰሌን በያዙት ኹሉ “ሆሣዕና በአርያም” እዚተባለ እዚተመሰገነ ወደ ቀተ መቅደስ ዚገባበትን ታላቁን በዓል ኚኹሉም ዓለም አስበልጣ በታላቅ ክብር ዚምታኚብርና ዚምታስተምሚው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ናት፡፡ ♥ ይኾውም ታላቁ ዚምስጋና ዕለት ሊደርስ ሲቃሚብ ስንዱዋ እመቀት አስቀድማ በቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ዚቊርባን ምስጋናፊ ✍ “ቩአ ኀቀሃ እግዚአ አጋዕዝት ወመናፍስት እንዘ ይጌዐን ዕዋለ አድግ ትሑት ” (ዚአጋዕዝትና ዚመናፍስት ጌታ በተዋሹደ አህያ ግልገል ተቀምጩ ወደ ርሷ ገባፀ በእግዚአብሔር ስም ዚሚመጣ ብሩክ ነው፡፡ አንተም ዚአማልክት አምላክ ዚእስራኀልም ንጉሥ እግዚአብሔር ቡሩክ ነኜ እያሉ ለሚያመሰግኑ ሕፃናት ኹሉ ጌትነቱን አሳዚፀ ዚሆሳዕናን ዑደት ለነርሱ ለደቀ መዛሙርቱ አሳዚፀ ቡርክ ርሱ በታላቅ ቃል እዚጮኻቜኊ ሆሣዕና በአርያም በሉ አላ቞ውፀ ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሳዕና በአርያምፀ ኚመድኀኒትነቱ ዚተነሣ ኚዚኜ አስቀድሞ ያልተደሚገ ኚዚኜም በኋላ ዹማይደሹግ ተአምራትንና መንክራትን አሳዚፀ ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሳዕና በአርያም... ) በማለት መድኀኒትነቱን ስትሰብክፀ ካህናትና ምእመናንም በአንድ ድምፅ በዚያ ዘመን ዚምስጋና ጌታ ኢዚሱስ ክርስቶስ በተመሰገነበት በዚኜ ልዩ ምስጋና “ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም” እያሉ በመዘመርፀ ፈጣሪያ቞ው ክርስቶስን ያመሰግናሉ። 💥 ኚዚያም በዋዜማው፩ ✍ “በዕምርት ዕለት በዓልነ ንፉሑ ቀርነ በጜዮን ወስብኩ በደብሚ መቅደስዚ እስመ ይቀ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር ሆሣዕና በአርያም ቡሩክ አንተ ንጉሠ እስራኀል” 👉 (በታወቀቜ በበዓላቜን ዕለት በጜዮን መለኚትን ንፉፀ በመቅደሮ ተራራም ስበኩ ይኜቺ ዕለት ዚእግዚአብሔር በዓል ናትፀ በአርያም መድኀኒት ዚተባልኜ ዚእስራኀል ንጉሥ አንተ ቡሩክ (መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን ዚምታርቅ በሹኹተ ሥጋ በሹኹተ ነፍስን ዚምታድል) ነኜ) በማለት ልዩ ምስጋናዋን ጀምራ እስኚ ሌሊቱ ድሚስ በልዩ ምስጋና እዚሰበኚቜው በኋላም ቀተ መቅደሱን በውርጫዋ ተቀምጩ እንደዞሚ በአራቱ መኣዝን ዚጌትነቱ ወንጌል እዚተነበበፀ ካህናቱን ምእመናንም በእጃ቞ው ዚዘንባባ ዝንጣፊን ይዘው “ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ያመሰግኑታል፡፡ ✍ በመጋቀ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ተጻፈ መልካም በዓል ይኹንልን። https://t.me/tmhrteorthodox
Show all...
🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

ሆሣዕና ዚዐብይ ጟም ስምንተኛ እሑድ(ሳምንት) ሆሣዕና ኚጌታቜን አምላካቜን ኹዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡ ጌታቜን áŠ áˆáˆ‹áŠ«á‰œáŠ• መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ኚኢዚሩሳሌም á‹ˆá‹°  ቀተ áˆ˜á‰…ደስ áˆˆáˆ˜áŒá‰£á‰µ á‰ áˆáˆˆáŒˆ ጊዜ á‹°á‰€ መዛሙርቱን á‹ˆá‹° ፊታቜው ባለው ሀገር "ሂዱና አህያ ኹውርጭላዋ ጋራ ታስራ ታገኛላቜው ፈታቜው እምጡልኝ። 'ምን ታደርጋላቜሁ?'  ዚሚላቜሁ  ሰው  ካለ  'ጌታ቞ው  ይፈልጋቾዋል'  በሉ"  ብሎ  ላካ቞ው  ኹዚህ  በኋላ  ደቀ  መዛሙርቱ እንዳዘዛ቞ው  ሄደው  ፈተው  አመጡለት  በዚያም  ዚተሰበሰቡት  ሁሉ  በአህዮቜ  ላይ  ልብሳ቞ውን  ጎዘጎዙለት  ጌታቜንም በሁለቱ  አህዮቜ  ላይ  ተቀመጠ  ኚሌሎቹ  እንስሳት  አህዮቜን  መርጩ  በአህዮቜ  ተቀምጧል፡ አህዮቜ  በመጜሐፍ  ቅዱስ ብዙ ታሪክ አላ቞ውና። ✅ዹበልአም አህያ ዚመልአኩን ክብር ለመግለጥ አፍ አውጥታ ተናግራለቜ። (ዘሁል 22+28) ✅ጌታቜን በተወለደ ጊዜ አህዮቜ ኚኚብቶቜ ጋር በበሚት እስትፋሳ቞ውን ገብሚዋል። (ቅዳሎ ማርያም) ዚሆሣዕና እህዮቜ ኹሁሉ ተመርጠው አምላካቜን ተቀምጊባ቞ዋል: 'ለምን ዚተዋሚዱት አህዮቜን መሹጠ?' ቢባል:- ፩. ደመናን አዝዞ : ነፋስን ጠቅሶ : በእሳት  መንኮራኩር ላይ ዚሚሚማመድ አምላክ ሲሆን ነገር  ግን ዚመጣው ትሕትናን  ለማስተማር : ዚትሕትና  ጌታ  መሆኑን  ለመግለጜ ነውና በአህያ ተቀመጠ። ፪.  ትንቢቱን  ለመፈጾም  <<አንቺ  ዚጜዮን  ልጅ  ሆይ  እጅግ  ደስ  ይበልሜ  አንቺ  ዚኢዚሩሳሌም  ልጅ  ሆይ  እልል  በዪ  እነሆ  ንጉሥሜ  ጻድቅና አዳኝ  ነው  ትሁትም  ሁኖ  በአህያም  በውርንጭላቱ  ላይ  ተቀምጩ  ወደ  አንቺ  ይመጣል  ሰሹገላውንም  ኚኀፍሬም ፈሚሱንም ኚኢዚሩሳሌም ያጠፋል>> ብሎ ዘካርያስ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ለመፈጾም ነው። ዘካ ፱÷፩ ፫.  ምሳሌውን  ለመግለጜ ምሳሌ-  ቀድሞ  ነቢያት  ዘመነ  ጞብእ  ኹሆነ  በፈሚስ  ተቀምጠው  ዘገር  ነጥቀው  ይታያሉ  ዘመነ  ሰላም  ኹሆነ  በአህያ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታዩ ነበርና ጌታቜንም ዘመነ ሰላም ነው ሲል በአህያ ተቀምጩ መጥቷል። ፬.  ምሥጢሩን  ለመግለጜ ምሥጢር-  በአህያ  ዹተቀመጠ  ሞሜቶ  አያመልጥም  አሳዶም  አይዝም  እሱም  ካልፈለጋቜሁኝ  አልገኝም  ኚፈለጋቜሁኝ አልታጣም ሲል በአህያ ተቀምጩ መጥቷል። ህድግት ዚእስራኀል ምሳሌ ህድግት ቀንበር መሾኹም ዚለመደቜ ናት= እስራኀልም ህግ መጠበቅ ለምደዋልና እዋል  ዚአህዛብ  ምሳሌ እዋል  ቀንበር መሾኹም አልለመደቜም=አህዛብም ህግ መጠበቅ አልለመዱምና  (አንድም)  ህድግት  ዚኊሪት  ምሳሌ ህድግት ቀንበር መሾኹም እንደለመደቜ=ኊሪትም ዚተለመደቜ ህግናትና እዋል  ዹወንጌል ምሳሌ እዋል  ቀንበር መሾኹም አልለመደቜም=ወንጌልም ያልተለመደቜ አዲስ ህግ ናትና በሁለቱም ላይ መቀመጡ ኊሪትንም ወንጌልንም ዚሰራሁ እኔ ነኝ ሲል ነው፡፡ ኚኢዚሩሳሌም እስኚ ቀተ መቅደስ ፲፮ ምእራፍ ነው ፲፬ቱን ምእራፍ በእግሩ ሂዶ ሁለቱን ምእራፍ በአህያይቱ ሂዷል በውርጭላይቱ ሁኖ ፫ ጊዜ ቀተ መቅደሱን ዙሯል ፲፬  ምእራፍ ዚአስርቱ  ትእዛዛትና  ዚአራቱ ኪዳናት ምሳሌፀ አስሩ  ምእራፍ ዚአስርቱ ትአዛዛት፣ አራቱ  ምእራፍ ዚአራቱ ኪዳናት ምሳሌ ነው፣ አራቱ  ኪዳናት ዚሚባሉት እነዚህ ናቾው፩ ኪዳነ  ኖህ  :  ክህነተ  መልኹ  ጌዎቅ  :ግዝሹተ  አብርሀም  እና ጥምቀተ ዮንሐስ ና቞ው፡፡ በአህያይቱ  ላይ ልብሳ቞ውን አንጥፈውለታል:: ልብስ  በአካል ያለውን ነውር ይሾፍናል አንተም ኚባ቎ አበሳ ነህ  ሲሉ። በአህያዋ  ላይ  ኳርቻ  ሳያደርጉ  ልብስ  አንጥፈውለታል :- ኳርቻ  ይቆሚቁራል  ልብስ  አይቆሹቁርም  ዚማትቆሚቁር  ህግ ሰራህልን  ሲሉ  ነው።  ስለምን ልብሳ቞ውን አነጠፉለት ቢባል ? በእዩ  ልማድ ነው ፡ እዩ  ዚተባለው  ሰው  በእስራኀል  ላይ  ሲነግሥ  እስራኀል  ልብሳ቞ውን  አንጥፈውለት  ነበሹና  በዚያ  ልማድ አንጥፈውለታል እኩሌቶቱ ደግሞ ዘንባባ አንጥፈውለታል ። 🌎 በዕለተ  ሆሳዕና  እስራኀላውያን  ለምን  ዚዘንባባ  ዝንጣፊፀ  ዹቮምር  ዛፍ  ዝንጣፊ  እና  ዚወይራ  ዛፍ  ዝንጣፊ  ይዘው  ዘመሩ?  (ማቮ. á³á©Ã·á©-፲፯፣  ማር. ፲፩÷፩-፲፣  ሉቃ.  ፲፱÷፳፱-ፎ፰፣  ዮሐ. ፲፪÷፲፪-፲፭) ዚዘንባባ ዝንጣፊ ✅ ዘንባባ ዚድል ምልክት ዚደስታ መግለጫ ዚምስጋና መስጫ ነው፡፡ ✔ይስሃቅ  በተወለደ  ጊዜ  አብርሃም ደስ ብሎት ዘንባባ ይዞ እግዚአብሄርን አመስግኖበታል። ✔ይስሐቅም ያእቆብን በወለደ ጊዜ    አምላኩን በዘንባባ አመስግኗል። ✔እስራኀል  ኚግብጜ  በወጡ  ጊዜ  በዘንባባ  ንሎብሆ  እያሉ  እህተ  ሙሮ  ማርያም  ኚበሮ  እዚመታቜ  አምላካ቞ውን አመስግነዋል፡፡ ✔ዮዲት  እስራኀልን  እዚገደለ  ያስ቞ገሚው  ሆለፎርኒስን  አንገቱን  ቆርጣ  በገደለቜው  ጊዜ  እስራኀል  ዮዲት  መዋኢት  ዮዲት ኀያሊት  ብለው በዘንባባ አመስግነዋታልና። ✅ዘንባባ ደርቆ እንደገና ህይወት ይዘራል ዹደሹቀ ሕይወታቜንን ዚምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው። ✅ዘንባባ ዹሰላም ምልክት ነው ዹሰላም አምልክ ነህ ሲሉ ነው። ✅ዘንባባ እሟሃማ ነው አንተ ህያው አሾናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው። ✅ዘንባባ እሳት አይበላውም ለብልቊ ይተወዋል እንጅ ጌታም አንተ ባህርይህ ዹማይመሹመር ነው ሲሉ ነው። ✅ዘንባባ  ዚነፃነት  ምልክት  ነው  ኚባርነት  ነፃ  ዚምታወጣን  አንተነህ  ሲሉ  ነው  አኛም  ይህን  በማሰብ  ዘንባባ  ይዘን ሆሳእና  በአርያም  እያልን እለቱን  እናስባለን፡፡ ዹቮምር ዛፍ ዝንጣፊ ✅ዹቮምር ዛፍ ፍሬ ጣፋጭ ነው፩ በሃጥያት ዹመሹሹውን ህይወታቜንን ዚምታጣፍጥልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው። ✅ ዹቮምር  ፍሬ  ዹሚገኘው  ኹዛፉ  ኚፍታ  ላይ  ነው:-  አንተ  አምላካቜን  ልዑለ  ባህሪ  ነህ  ኹፍ  ኹፍ  ያልክ  አምላክ  ነህ  ሲሉ ነው። ✅ ዹቮምር ዛፍ ፍሬ በውስጡ ያለው ፍሬ አንድ ነው አንድ አካል አንድ ባህሪ ነህ ሲሉ ነው። ✅ ዹቮምር ፍሬ በእሟህ ዹተኹበበ ነው ይህም ዚአንት ባህሪ ዹማይመሹመር በእሳት ዹተኹበበ ነው ሲሉ ነው። ዚወይራ ዛፍ ዝንጣፊ ✅ ዚወይራ ቅጠል ዹሰላም ማብሰሪያ ነው ሰላማቜንን ዚምታበስርልን ዚምታስገኝልን አንተ ነህ ሲሉ ነው፡፡ ✅ ዚወይራ ቅጠል ኚእንጚት ሁሉ ጜኑ ነው አንተም ጜኑ ሃያል አምላክ ነህ ሲሉ ነው። ✅ወይራ ለመብራት ያገለግላል ፍሬው ዘይት ያወጣል ኚወይራ ዹሚገኝ ዘይት ጹለማን አሾንፎ ብርሃን እንደሚሰጥ ሁሉ አንተም ጹለማ ህይወታቜንን ዚምታስወግድልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው። ✅ በኊሪት ግዜ ዚወይራ ዘይት ለመስዋአትነት ይቀርብ ነበር አንተም እንደ ዘይቱ ለመተላለፋቜን መስዋዕት ሆነህ ዚምትቀርብ አምላክ ነህ ሲሉ ነው። በመስቀል ላይ መስዋዕት ሆኗልና። ኚፊት ኹኋላ ያሉት "ሆሣዕና በዓርያም ለዳዊት ልጅ መድኀኒት መባል ይገባዋል" እያሉ አመስግነውታል ዚምስጋና ጌታም በአህዮቜ ተቀምጩ ወደ መቅደስ ገብቷል። በቅዳሎ ጊዜ ዚሚነበቡ ጥቅሶቜፊ -ዕብ ፱፥፲፩ እስኚ ፍጻሜ -፩ጎጥ ፬፥፩-፲፪ -ሐዋ ፳፰፥፲፩ እስኚ ፍጻሜ ምስባኩምፊ መዝ፰፥፪ "እመ አፈ ደቂቅ ወሕጻናት አስተዳሎኚ ስብሐተ በእንተ ጞላኢ ኚመትንሥቶ ለጾላዒ ወለገፋዒ" "ኚሕጻናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህልኝ፡፡ ስለ ጠላትና ቂመኛን ለማጥፋት" ወንጌሉም፩ ዮሐ፭፥፲፩-፲፫ ቅዳሎ ፊ ዘጎርጎርዮስ (ነአኵቶ)[በዕዝል ዜማ] https://t.me/tmhrteorthodox
Show all...
🇪🇹✝ዚኊርቶዶክስ ንግስ በአላት ✝🇪🇹

ትምህርተኊክቶዶክስ በዚህ ቻናል ኚተለያዩ ምንጮቜ ዹምናገኛቾዉን አስተማሪ ብለን ያሰብና቞ውን #ሀይማኖታዊ ትምህርቶቜ #ስብኚቶቜ #ታሪኮቜ #መዝሙሮቜ#ዚቀተክርስትያን ዜናዎቜ#ሀይማኖታዊ ፊልሞቜ ወ.ዘ.ተ ዚምናቀርብ ይሆናል ለሌሎቜ በማጋራት ዚበኩልዎን እንዲወጡ በልሉል እግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን። #ትምህርተኊርቶዶክስ @tmhrteorthodox

#ገብር_ኄር (#ዚዐቢይ_ጟም_ስድስተኛ_ሳምንት) ዚዐቢይ ጟም ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ገብር ኄር ይባላል፡፡ በዚህ ሳምንት ዹሚዘመሹው ዝማሬ፣ ዹሚሰበኹው ስብኚት፣ ዹሚሰጠው ትምህርት ገብርኄርን ዚሚያወሳ ነው። ማለትም ስለ ታማኝ አገልጋይ ነው፡፡ ዹማቮ.25፥14-25 ዹሚነግሹን ይህን ነው፩ “አንድ ባዕለ ጾጋ ሰው ባሪያዎቜን ጠርቶ ለአንዱ አምስት መክሊት ሰጠው፣ ሁለት መክሊት ዹሰጠውም አለ፣ አንድ መክሊትም ዹሰጠው አለ፡፡ ኹዚህ በኋላ ወደሩቅ አገር ሄደ፡፡ አምስት መክሊት ዹተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት አትርፎ አስር አደሚገ፡፡ ሁለት ዹተቀበለውም አትርፎ አራት አደሚገ፡፡ አንድ ዹተቀበለው ግን ሄዶ መሬቱን ቆፍሮ በሻሜ ጠቅልሎ ዚጌታውን መክሊት ቀበራት፡፡ ኚብዙ ጊዜ በኋላ ጌታ቞ው መጥቶ ተቆጣጠራ቞ው፡፡ አምስት መክሊት ዹተቀበለው ቀርቩ ጌታዬ አምስት መክሊት ሰጥተኞኝ ነበር እነሆ አምስት አተሚፍኩ አለው፡፡ “ገብርኄር ወምዕመን ዘበሁድ ምዕምነ ኮንኚ ዲበ ብዙህ እሰይመኚ ባዕ ውስተ ፍስሐሁ ለእግዚእኚ” “አንተ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሟምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡ ሁለት ዹተቀበለውም ቀርቩ ጌታዬ ሁለት መክሊት ሰጥተኞኝ ነበር እነሆ ወጥቌ ወርጄ ሌላ ሁለት አትርፌ አራት አድርጌአለሁ፡፡ “አንተ ታማኝ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሟምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡ አንድ መክሊት ዹተቀበለው ግን ቀርቩ “ጌታዬ አንተ ክፉና ጚካኝ ካልዘራህበት ዚምታጭድ ካልበተንህበት ዚምትሰበስብ እንደሆንክ ስለአወቅሁ መሬቱን ቆፍሬ ቀበርኋት እነኋት መክሊትህ” አለው፡፡ “አንተ ሰነፍ ባሪያ መክሊቮን በጊዜ ልትሰጠኝ በተገባህ ነበር እኔም ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍ በሰጠሁት ነበር”፡፡ ኑ ዹዚህን ሀኬተኛ መክሊት ውሰዱና አስር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ ላለው ይሰጡታል ይጚመርለታል ለሌለው ግን ያለውን ይቀሙታል፡፡ ኑ ይህን ሰነፍና ሃኬተኛ ባሪያ እጅ እግሩን አሥራቜሁ ጜኑዕ ጹለማ ወደአለበት ውሰዱት ጩኞትና ጥርስ ማፋጚት ወዳለበት ጚምሩት” አለ ማቮ. 25፥14-25፡፡ ባለ ጾጋ ዚተባለው ጌታ ነው፡፡ መክሊት ዚተባለው ልዩ ልዩ ዚአገልግሎት ጾጋ ነው፡፡ ያተሚፉት በሚገባ በታማኝነት ያገለገሉ ቅዱሳን ሰዎቜ ናቾው መክሊቱን ዹቀበሹው ደግሞ በታማኝነት በተሰጠው ጾጋ ማገልገል ሲገባው ያላገለገለ ነው፡፡ ጌታ቞ው ሊቆጣጠራ቞ው መጣ ማለት በዕለተ ምጜአት ለሁሉም በአገለገለው አገልግሎት ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ ያሳዚናል፡፡ ያገለገሉትን ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አላቾው ማለት ታማኝ አገልጋዮቜ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉና፡፡ ሰነፎቜ ደግሞ ጥርስ ማፋጚት ስቃይ ጜኑዕ ጹለማ ባለበት ሲዖል መግባታ቞ውን ዚሚያሳይ ነው፡፡ #ዹዕለተ_ሰንበት_መዝሙር_ኚጟመ_ድጓ መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይሹክቩ እግዚኡ በምግባሚ ሠናይ ወይሠይሞ ዲበ ኲሉ ንዋዩ ካዕበ ይቀሎ እግዚአብሔር ገብር ኄር ወምእመን ዘበውኁድ ምእመነ ኮንኚ ዲበ ብዙኅ እሠይመኚ ባእ ውስተ ፍሥሐሁ ለእግዚእኚ፡፡ ትርጉምፊ ጌታው በመልካም ሥራ ዚሚያገኘው በሐብቱ ኹሉ ላይ ዚሚሟመውፀ ዚታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው? ዳግመኛም እግዚአብሔር አንተ ዚታመንክ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ዚታመንህ ስለኟንህ በብዙ እሟምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ይለዋል፡፡ #መልዕክታት 2ኛ ጢሞ.2÷1-15 "ልጄ ሆይ÷ አንተም በጌታቜን በኢዚሱስ ክርስቶስ ጾጋ በርታ፡፡ በብዙ ምስክሮቜ ፊት ኚእኔ ዹሰማኾውን ትምህርት ለሌሎቜ ሊያስተምሩ ለሚቜሉ ለታመኑ ሰዎቜ እርሱን አስተምራ቞ው፡፡ ኢዚሱስ ክርስቶስን እንደሚያገለግል በጎ አርበኛ ሆነህ መኚራ ተቀበል፡፡" (ተጚማሪ ያንብቡ) 1ኛ ጎጥ.5÷1-11 "እንግዲህ እኔ ኚእነርሱ ጋር ሜማግሌ÷ ዚክርስቶስም መኚራ ምስክር÷ ደግሞም ሊገለጥ ካለው ክብር ተካፋይ ዹሆንሁ በመካኚላ቞ው ያሉትን ሜማግለዎቜን እማልዳ቞ዋለሁ፡፡ በእናንተ ዘንድ ያሉትን ዚእግዚአብሔርን መንጋዎቜ ጠብቁፀ ስትጠብቁአ቞ውም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ አይሁንፀ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ሚብ በመመኘትም አይሁን፡፡" (ተጚማሪ ያንብቡ) #ግብሚ_ሐዋርያት ዹሐዋ.1÷6-8 "እነርሱም ተሰብስበው ሳሉ÷ "ጌታ ሆይ÷ በዚህ ወራት ለእስራኀል ልጆቜ መንግሥትን ትመልሳለህን?” ብለው ጠዚቁት፡፡ እርሱም መልሶ እንዲህ አላ቞ው÷ “አብ በገዛ ሥልጣኑ ዹወሰነውን ቀኑንና ዘመኑን ልታውቁ አልተፈቀደላቜሁም፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወሹደ ጊዜ ኅይልን ትቀበላላቜሁፀ በኢዚሩሳሌምና በይሁዳ ሁሉ፣ በሰማሪያና እስኚ ምድር ዳርቻ ድሚስም ምስክሮ቞ ትሆኑኛላቜሁ።" #ምስባክ መዝ. 39÷8 "ኹመ እንግር ፈቃደኹ መኚርኩ አምላኪዚ፡፡ ወሕግኹኒ በማዕኹለ ኚርሥዚ፡፡ ዜኖኩ ጜድቀኚ በማኅበር ዐቢይ፡፡" ትርጉምፊ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ለማድሚግ መኚርሁ፥ ሕግህም በልቀ ውስጥ ነው። በታላቅ ጉባኀ ጜድቅህን አወራሁ #ወንጌል ማቮ. 25÷14-30 “መንገድ እንደሚሄድ÷ አገልጋዮቹንም ጠርቶ ሊያተርፉበት ገንዘቡን እንደ ሰጣ቞ው ሰው እንዲሁ ይሆናልናፀ ለእያንዳንዱ እንደ ቜሎታው ለአንዱ አምስት÷ ለአንዱ ሁለት÷ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወዲያውኑ ሄደ፡፡” (ተጚማሪ ያንብቡ) #ዚዕለቱ_ቅዳሎ ➛ ቅዳሎ ባስልዮስ https://t.me/tmhrtegeeze        ❍ㅀ         ⎙          âŒ²         ♡   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ      ˢᵃᵛᵉ      ˢʰᵃʳᵉ      ˡᶊᵏᵉ   
Show all...
✝(ትምህርተ ግዕዝ)✝

በዚህ ቻናልዚተለያዩ ትምህርቶቜ ያገኛሉ ኹነዚህም ውስጥ ✝ዚግዕዝ ትምህርት ✝ዚተለያዩመፅሐፉን ✝ ዚተለያዮ መንፈሳዊ ስብኚቶቜ ✝መንፈሳዊፊ ልሞቜ ወ.ዘ.ተ ያገኛሉ።