en
Feedback
FDRE Education and Training Authority

FDRE Education and Training Authority

Open in Telegram

በኢፌድሪ የትምህርትና ሥልጠና ባለስልጣን http://www.eta.et/ 9799 "በኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ነጻ የስልክ ጥሪ ማዕከል"

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel FDRE Education and Training Authority

Channel FDRE Education and Training Authority (@fdre_eta) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 582 subscribers, ranking 10 682 in the Education category and 1 865 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 582 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 422 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 32.65%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.96% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 068 views. Within the first day, a publication typically gains 2 595 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 13.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
በኢፌድሪ የትምህርትና ሥልጠና ባለስልጣን http://www.eta.et/ 9799 "በኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ነጻ የስልክ ጥሪ ማዕከል"

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

18 582
Subscribers
-624 hours
+1037 days
+42230 days
Posts Archive
#ጳጉሜ_3 #የጽናት_ቀን የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም
#ጳጉሜ_3 #የጽናት_ቀን የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

#ጳጉሜ_2 #የማንሠራራት_ቀን የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌ
#ጳጉሜ_2 #የማንሠራራት_ቀን የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የምሁራን እና ባለሙያዎች ምክክር ተካሄደ ======   ====   ==== === === የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ጥራትን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማረጋገጥና የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱን ይበልጥ ወጥና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ከባለሙያዎች፥ከዘርፉ ተመራማሪዎች እና ምሁራን ጋር ምክክር ተካሄደ። የምክክር መድረኩ ከነሐሴ 26-28/2018 ዓ.ም አዳማ ከተማ በሚገኘው በመልካ አዳማ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን፣ ከተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት፣ ከፌዴራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ቁጥር ባለሥልጣን የተውጣጡ ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና የጥራት አረጋጋጭ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። የምክክሩ ዋና ዓላማ እና የሦሥት ቀን  የቆይታ ዝርዝር መርሃ-ግብ በዶ/ር ሀብታሙ ተሾመ የባለስልጣኑ ስታንደርዳይዜሽንና ብሄራዊ ብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ቀርቧል። ዶ/ር ሀብታሙ በገለጹት መሠረት የምክክሩ ዋና ዓላማ እስከ አሁን ሲከናወን በነበረው በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት የማረጋገጫ ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶች ላይ ከምሁራን እና ባለድርሻ አካላት ጋር የመጀመሪያውን ምክክር በማካሄድ ብሔራው የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ቅድመ ሁኔታን ማመቻችት ነው። በመቀጠል የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው የምክክር መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም የትምህርትና ስልጠና ጥራት የሀገሪቱን የሰው ኃይል ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገትና የሀገር ግንባታ ውጤታማነት ከሚወስኑ ዋና ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ጠቁመው፣ ጥራትን ማረጋገጥ የአንድ ተቋም ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን የሁሉም የትምህርትና ስልጠና ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል። ዶ/ር አህመድ በተለይም የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በግልጽ መርሆዎች፣ በተወሰኑ መመዘኛዎችና በተቀናጀ አሠራር ላይ መመሥረት እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም በሀገሪቱ የሚተገበረውን የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት በማጠናከር የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የሚያቀርቡት ትምህርትና ስልጠና የሀገሪቱን ፍላጎትና የሥራ ዓለም ተጠቃሚነት የሚያሟላ እንዲሆን የሚያግዝ ማዕቀፍ መዘጋጀቱ ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል። በመድረኩ የባለሥልጣኑ የእውቅናና ስታንዳርዳይዜሽን ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዱንካና ንጉሳ ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጽሑፍ አቅርበዋል። በጽሑፋቸውም ባለሥልጣኑ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ እስካሁን የሠራቸውን የጥራት ማስጠበቅ ሥራዎች፣ በሂደቱ የታዩ ልምዶችና ክፍተቶች እንዲሁም በቀጣይ ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎች በስፋት ቀርበዋል። የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማሻሻል የሚጫወተውን ሚና በማጠናከር የተማሪዎችና የሰልጣኞች ብቃት፣ የተቋማት አፈጻጸም እና ከሥራ ዓለም ጋር ያለው ትስስር እንዲሻሻል ማድረግ ከሚጠበቁት ዋና ተግባራት መካከል መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል። ጽሑፉ ከቀረበ በኋላ የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረቡት ጉዳዮች ላይ በርካታ ጥያቄዎችን፣ ምልከታዎችንና የመፍትሔ ሃሳቦችን አንስተዋል። ተሳታፊዎቹ በተለይም የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ በተግባር ሲተገበር የሚያጋጥሙ ችግሮች፣ የተቋማት የጥራት ደረጃ አመዳደብ፣ የጥራት መለኪያዎች ግልጽነት፣ የተቋማት ተጠያቂነትና የባለድርሻ አካላት ሚና የመሳሰሉ ጉዳዮችን አንስተዋል። ለተሳታፊዎቹ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አህመድ አብተው እና ም/ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ዱንካና ንጉሳ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል። የተነሱት ሃሳቦችም በማዕቀፉ ዝግጅት ወቅት በጥንቃቄ እንደሚታዩ ተገልጿል። ዶ/ር አህመድ በበኩላቸው በምክክሩ የተሳተፉ ምሁራን ባቀረቡት ሙያዊ እውቀት፣ ልምድና ምልከታ ለሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉ ዝግጅት ጠቃሚ ግብዓት እንደሚገኝ ገልጸዋል። ምሁራንና ባለሙያዎች በተግባራዊ ልምዳቸውና በሙያዊ እውቀታቸው ላይ በመመሥረት የሚያቀርቡት ግብዓት ማዕቀፉ ተግባራዊ፣ ዘላቂና የሀገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ እንዲሆን የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስረድተዋል። ከጋራ ውይይቱ በኋላ ተሳታፊዎች በአራት ቡድን ተከፋፍለው ቀድሞ በተዘጋጁ ስምንት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል። ቡድኖቹ በተመደቡላቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየት፣ የችግሮችን መነሻ ምክንያቶችና ሊወሰዱ የሚገቡ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በመለየት በየቡድኑ የተነሱ ሃሳባቸውን በጋራ መድረክ ላይ አቅርበዋል። የቡድን ውይይቱም በሁለት ቀናት በስፋት የተካሄደ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ በተለያዩ አቅጣጫዎች የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓቱ እንዴት ሊጠናከር እንደሚችል የራሳቸውን ሙያዊ ሃሳብ አቅርበዋል። በቡድኖቹ የቀረቡት ሃሳቦችም በጋራ ውይይት ተገምግመውና ተጠናክረው ለማዕቀፉ ዝግጅት የሚያገለግሉ ግብዓቶች ተሰብስበዋል። በመድረኩ የተነሱት ሃሳቦች እና የቀረቡት ምክረ ሃሳቦች ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉን ለማዘጋጀት ጠንካራ መሠረት የጣሉ መሆናቸው ተገልጿል። በተለይም ከተለያዩ የሙያ መስኮች የመጡ ምሁራን የተለያዩ አመለካከቶችን ማቅረባቸው ማዕቀፉ በሰፊ ሙያዊ ምክክርና በተጨባጭ ልምድ ላይ እንዲመሠረት ያግዛል ተብሏል። የባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥር ኢንስፔክሽንና የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሺሻይ አማረ  በመድረኩ መጠናቀቂያ ላይ ከምሁራንና ከባለሙያዎች ጋር የተካሄደውን ውይይት አድንቀው፣ በውይይቱ የተገኙ ግብዓቶች ወደ ቀጣይ የማዕቀፍ ዝግጅት ሥራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል። በቀጣይም በምክክሩ የተሰበሰቡ ሃሳቦችንና ምክረ ሃሳቦችን በማደራጀት፣ በማጠናቀርና በመተንተን ለሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ዝግጅት እንደሚውሉ ተገልጿል። ይህም በሀገሪቱ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን በመቅረፍ፣ የጥራት ማረጋገጫ አሠራሩን ይበልጥ ወጥ፣ ግልጽ፣ ተጠያቂና ውጤታማ ለማድረግ እንደሚያግዝ ይጠበቃል። የሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፉ ዝግጅት የትምህርትና ስልጠና ጥራትን በተቀናጀ መልኩ ለማሻሻል፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን የጥራት ባህል ለማጠናከር እና ተማሪዎችና ሰልጣኞች በጥራት የተማሩና በብቃት የተሰለጠኑ የሰው ኃይል እንዲሆኑ ለማስቻል ጠቃሚ እርምጃ እንደሚሆን ይጠበቃል። በመሆኑም በአዳማ የተካሄደው የምሁራን ምክክር ሀገራዊ የጥራት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ዝግጅቱን ከሙያዊ እውቀት፣ ከተጨባጭ ልምድና ከባለድርሻ አካላት ምክረ ሃሳብ ጋር በማጣመር ለመተግበር የሚያስችል ጠንካራ መነሻ መፍጠሩ ተገልጿል።

#ጳጉሜ_1 #የእመርታ_ቀን የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራ
#ጳጉሜ_1 #የእመርታ_ቀን የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

#ጳጉሜ_2018 “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” ጳጉሜን፦ የስኬት ማጠቃለያ፣ የአዲስ ተስፋ መነሻ! እየተጠናቀቀ በሚገኘው የ2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን የሚያመላክቱ በርካታ ስኬቶች ተመዝግበ
#ጳጉሜ_2018 “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” ጳጉሜን፦ የስኬት ማጠቃለያ፣ የአዲስ ተስፋ መነሻ! እየተጠናቀቀ በሚገኘው የ2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞን የሚያመላክቱ በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል። እነዚህን ስኬቶች በማጠቃለል፣ የተገኙ ውጤቶችን በመገንዘብ እና ለቀጣይ የልማት ጉዞ በተስፋና በቁርጠኝነት ለመስካት የዘንድሮው ጳጉሜ በ**“የኢትዮጵያ ማንሰራራት” የጋራ መሪ መልዕክት ይከበራል። የጳጉሜ ቀናት ልዩ መልዕክት ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀን የተመዘገቡ የእድገትና የእመርታ ውጤቶችን የምናከብርበት። ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን ኢትዮጵያ በልማትና በእድገት የምትራመድበትን የማንሰራራት ጉዞ የምናጎለብትበት። ጳጉሜ 3 — የጽናት ቀን በፈተናዎች ውስጥ በጽናት በመቆም፣ የሀገር ግንባታ ጉዟችንን በቁርጠኝነት የምናስቀጥልበት። ጳጉሜ 4 — የኅብር ቀን በአንድነት፣ በመተባበርና በመከባበር የጋራ ሀገራዊ አቅማችንን የምናጠናክርበት። ጳጉሜ 5 — የነገ ቀን የተሻለች፣ የበለጸገችና ለትውልድ የምትተላለፍ ኢትዮጵያን ለመገንባት የነገ ራዕያችንን የምናድስበት። ጳጉሜ የሚያልፈውን ዓመት ብቻ የምንሰናበትበት ሳይሆን፣ የተሳካውን የምናጠናክርበት፣ ከተሳሳትነው የምንማርበት እና ለተሻለ ነገ በአዲስ ተስፋና በተጨማሪ ቁርጠኝነት የምንነሳበት ወሳኝ ወቅት ነው። “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” ስኬታችንን እናክብር፤ ትብብራችንን እናጠናክር፤ ነገያችንን በጋራ እንገንባ! #ጳጉሜ2018 #የኢትዮጵያ_ማንሰራራት #የእመርታ_ቀን #የማንሰራራት_ቀን #የጽናት_ቀን #የኅብር_ቀን #የነገ_ቀን #ኢትዮጵያ የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA

የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ አገልግሎት ለማግኘት እንዴት ማመልከት እንችላለን? ይህን ቪዲዮ ይከታተሉ👇👇 የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በአቤቱታ እና ቅሬታ አፈታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ ነሀሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለባለሥልጣኑ ሠራተኞች በአገልግሎት አሰጣጥ፣በአቤቱታ እና ቅሬታ አፈታ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡ የስልጠናው ዓላማ ከሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችና ሠራተኞች የደንበኛ አያያዝ ክህሎታቸውን አዳብረው የተቋሙን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና የደንበኞች እርካታን በተግባር እንዲያሳድጉ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በባለሥልጣኑ የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ደስታ ተ/አረጋይ ደንበኛን በፈገግታ፣ በትህትና እና በፍጥነት መቀበል የአገልግሎቱን ጥራት ግማሽ መንገድ የሚያሳካ መሆኑን ገልጸው አገልግሎት በሚሰጠበት ጊዜ ንቁ አዳማጭ መሆን ፤የተገልጋዩን ስሜት መረዳት ፤ግልጽ መረጃ መስጠት ፤ አዎንታዊ የአካል እንቅስቃሴ መገለጫ የሆኑትን ፈገግታና ትህትና ማሳየት፣ የሥራ ቦታን ለአገልግሎት ምቹና ዝግጁ ማድረግ ፣ ቀልጣፋ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲሁም ደንበኛን በአግባቡ የማስተናገጃ ደረጃዎች የሆኑትን አቀባበል፣ ፍላጎት መለየት፣አገልግሎትን በስታንዳርዱ ላይ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ፤አቅጣጫ መጠቆም እና ደንበኛን በአክብሮትና በፍቅር መሸኘት የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ፣ ቅሬታዎችን ለመፍታት እና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በስልጠናው ላይ ስለደንበኛ አያያዝ መሠረቶች፤ ስለደንበኛን የማስተናገድ ደረጃዎች፤ ስለቅሬታዎችን የመደራደር ዘዴ፤ስለደንበኞች እርካታመለኪያ እና ስለአስቸጋሪ ግንኙነቶች ማስተዳደር ዙሪያ ሰፋ ያላ ማብራሪያና ገለጻ ተደርጓል፡፡ የቀረቡትን መነሻ ሀሳቦች መሠረት በማድረግ በተደረገው ውይይት ላይ ለተነሱ ሐሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች በባለሥልጣኑ የጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት በአቶ ታምሩ መስፍን፣ የሥራ አዘመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ ታደሰ እና የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ በሆኑት አቶ ደስታ ተ/አረጋይ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡ የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

በዓለም ዓቀፍ፣ የማህበረሰብ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመና የበጎ አድራጎት ትምህርት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት መመሪያ 992/2016 መሠረት የማስፋፊያ ፈቃድ፡- ** ፈቃድ ተሰጥቶት በስራ ላይ ያለ የ
በዓለም ዓቀፍ፣ የማህበረሰብ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመና የበጎ አድራጎት ትምህርት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት መመሪያ 992/2016 መሠረት የማስፋፊያ ፈቃድ፡- ** ፈቃድ ተሰጥቶት በስራ ላይ ያለ የዓለም ዓቀፍ እና በውጭ ባለሃብት የተቋቋመ ትምህርት ቤት ደረጃውን ማሳደግ ሲፈልግ የኢንቨስትመንት ፈቃድን መሠረት አድርጎ ለባለሥልጣኑ ሲያመለክት የትምህርት ዓመቱ ከመጀመሩ ከ3 ወራት በፊት አስፈላጊው ምልከታ ተደርጎለት ጥያቄው አሳማኝ ሆኖ ሲገኝ የደረጃ ማሳደግ ፈቃድ ይሰጣል፤ *** ፈቃድ ተሰጥቶት በስራ ላይ ያለ የማህበረሰብ ትምህርት ቤት ደረጃውን ማሳደግ ሲፈልግ የትምህርት ዓመቱ ከመጀመሩ ከ3 ወራት በፊት ለባለሥልጣኑ በሚያቀርበው ጥያቄ መሠረት የትምህርት ቤቶች የሱፐርቪዥን ቡድን አስፈላጊው ምልከታ ተደርጎ ጥያቄው አሳማኝ ሆኖ ሲገኝ የማስፋፊያ ፍቃድ ይሰጣል። የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

በዓለም ዓቀፍ፣ የማህበረሰብ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመና የበጎ አድራጎት ትምህርት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት መመሪያ 992/2016 መሠረት ለዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ፍቃድ የሚሰጠው የሚከተሉት መስ
በዓለም ዓቀፍ፣ የማህበረሰብ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመና የበጎ አድራጎት ትምህርት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት መመሪያ 992/2016 መሠረት ለዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ፍቃድ የሚሰጠው የሚከተሉት መስፈርቶች ሲሟሉ ነው፡- -------------------------------------------------------------------------- የኢንቨስትመንትፍቃድ፤ የንግድ ፍቃድ፤ ወይንም የስራ ፍቃድ ስርዓተ-ትምህርቱ ከተዘጋጀበት በሀገሪቱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ለማስተማር የተሰጠ ፍቃድ ወይንም ስምምነት፤ የትምህርት ቤቱ መተዳደሪያ ደንብ እና መመስረቻ ሰነድ፣ ለትምህርት ቤት የሚመጥን አካዳሚያዊና አስተዳደራዊ አደረጃጀትን የሚያሳይ፣ ስለተማሪዎች የትምህርት ክፍያ መምህራን ሊያሟሉት ስለሚገባው : አነስተኛ መመዘኛ ፣ ነጻ የትምህርት እድል ስለሚሰጡበት ሁኔታ፣ የመምህራን እንዲሁም የተማሪዎች መብትና ግዴታ፣ የተማሪዎችን የቅበላ ስርዓት የሚመለከት ይዘት ያለው መተዳደሪያ ደንብ፤ የትምህርት ቤቱን ደረጃ የሚመጥን የትምህርት ቤት ግቢና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማደራጀቱን ሲረጋግጥ ፍቃድ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 መሠረት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በውጭ ሀገር ተምረው የመጀመሪያ ዲግሪ በሀገር ውስጥ መማር ለሚፈልጉ ማቅረብ ያለባቸው ህጋዊ ሰ
በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 መሠረት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በውጭ ሀገር ተምረው የመጀመሪያ ዲግሪ በሀገር ውስጥ መማር ለሚፈልጉ ማቅረብ ያለባቸው ህጋዊ ሰነዶች፡- የአቻ ግመታ አገልግሎትን ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው ቀጥሎ የተዘረዘሩትን ህጋዊ ሰነዶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የምስክር ወረቀት ወይም ዲፕሎማ፤ ማስረጃው በተገኘበት ሀገር የዲግሪ የትምህርት መስክ ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያለው የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የምስክር ወረቀት ወይም ዲፕሎማ እና ትራንስክሪፕት ፤ የአመልካቹ የትምህርት ማስረጃ ትምህርቱን ከተከታተለበት ሀገር ስርዓተ ትምህርት ውጪ በሌላ ሀገር ስርዓተ ትምህርት መሠረት ከሆነ የመግቢያ ውጤቱ የሚወሰነው አመልካቹ ትምህርቱን በተከታተለበት የትምህርት ስርዓት ውጤት አወሳሰን መሠረት ይሆናል፤ አመልካቹ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኝ እና የኢትዮጵያ መንግስት ፈቃድ በሰጠው ዓለም አቀፍ ወይም ማህበረሰብ ትምህርት ቤት የተማረ ከሆነ ከትምህርት ቤቱ የድጋፍ ደብዳቤ ያቀርባል፡፡ የኢፌዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት www. neta.gov.et ይከታተሉ።

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለነብዩ መሐመድ የልደት(ለመውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን! መልካም በዓል! የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና
ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለነብዩ መሐመድ የልደት(ለመውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን! መልካም በዓል! የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን

የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት የኘሮግራም ፈቃድ ዕድሳት ቅድመ ሁኔታዎች ----------------------------------------------------------------------- የፕሮግራሞቹ እድሣት /የፈቃድ እድሳት/ እንደ ፕሮግራም ቆይታው በተቋሙ ላይ በየጊዜው የሚደረግ ምርመራን መሠረት በማድረግ በየሶስት ዓመቱ የሚደረግ ሲሆን ይህንን ሳያመለክት የቀረ ማንኛውም ተቋም ፕሮግራሙ የማይታደስለት ይሆናል። ለተቋማት የኦዲት፣ እውቅና፣ ድጋፍና ኢንስፔክሽን ሊደረግ የሚችል ሲሆን በዚህም የተገኘው ሪፖርት መጨረሻ ላይ ለፈቃድ እድሣት በግብዓትነት የሚያገለግል ይሆናል። ከስልጠና ፕሮግራሙ ተመራቂዎች ውስጥ በፌደራል የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ብቁ ሆነው የተገኙትንና በግልም ሆነ በቅጥር ስራ ያገኙት ሰልጣኞች ብዛት ባለፉት ሦስት ዓመታት እየጨመረ የመጣ መሆኑን ማረጋገጥ። በፈቃድ ተመዝግበው ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሰልጣኞች ምዘና አፈጻጸም ከ50% በታች ያስመዘገበ ተቋም የፈቃድ እድሳት አይሰጠውም። የተቋሙ ራእይ፣ ተልእኮ፣ ዓላማና አሰራር ከትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ጋር የተጣጣመ መሆን አለበት። የሙያ ደረጃዎችንና ስርዓተ ትምህርትን፣የአሰልጣኞችን ብቃት፣ የማሰልጠኛ እቃዎችን ፣ የስልጠና መሳሪያዎችን ፣ ቁሳቁሶችንና የመረጃ መሳሪያዎችን አስመልክቶ የተቀመጡትን ዝቅተኛ መለኪያዎች ማሟላት ይኖርበታል። ለስልጠና ሂደቱ ይረዳ ዘንድ እንደየሙያ ዓይነቱ ባህሪ ተቋሙ በምቹ ቦታ እና የተሟላ ማስተማሪያ ክፍሎች/ሰርቶ ማሳያ ቦታ/ /Laboratory/ /work shop/ ያሉት ስለመሆኑና በአስፈላጊው የማሰልጠኛ መሳሪያዎች ስለመደራጀቱ ዝግጅቱ ሁሉ ይህን የሚያሳይ መሆን አለበት። የሙያ ምዘናን የማሣለፍ መጠን ስልጠና ካጠናቀቁት ውስጥ ቢያንስ 50 በመቶ የሚሆኑት የሙያ ምዘናን ማለፍ ይኖርባቸዋል። እየጨመረ የመጣ ወደ ስራ የተሰማሩ ምሩቃን መጠን፤ የተሻሻለ የሙያ ደረጃን ካለ ተከትሎ የተሻሻለ ስርአተ ትምህርትና የማስተማሪያ የማሠልጠኛና የመማሪያ ማቴሪያሎች፤ እየጨመረ የመጣ ብቃታቸው የተረጋገጠ መምህራን በደረጃና በመቶኛ፤ ስልጠና አጠናቀው የወጡ ባለሙያዎች ያሉበትን ሁኔታ የሚያሣይ የጥናት ሪፖርት (Tracer Study) ፤ ፈቃድ ባለው የሒሣብ ባለሙያ የተደረገ የኦዲት ሪፖርት፤ የተከማቸና የተሸጋገረ ቴክኖሎጂ፤ በአካባቢው ካለ ኢንዱስትሪ ጋር የተደረገ ከኘሮግራሙ ጋር ተዛማጅነት ያለው የመግባቢያ ስምምነት አተገባበር፤ በተቋሙ ድጋፍ አማካኝነት የተደራጁ የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ብዛት፤ የጥራት አመራር ስርአት /Quality Management System/ ትግበራ የሚያሳይ መረጃ፤ በዚህ የማረጋገጥ ሂደትም የአካባቢው የሰው ሀይል ገበያ መረጃ፣ የክትትል ሪፖርቶች፣ ጥራት ያለው የአመራር ስርአት ሪፖርትን አስመልክቶ የተሰጡ ግብረ መልሶች፣ አመላካች ጥናት ነው፡፡በተጨማሪም በዚህ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ለአካል ጉዳተኛ ሰልጣኞች ተገቢውን እድል የሰጠ ተቋም ከመደበኛው መስፈርት ተጨማሪ ነጥብ ያገኛል፡፡ ** በስልጠናው የተሳተፉ አካል ጉዳተኞች ብዛትና ከስልጠና በኋላ ስላሉበት ሁኔታ የሚገልፅ የጥናት ሪፖርት (Tracer Study) የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።

የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት የኘሮግራም ፈቃድ ዕድሳት ቅድመ ሁኔታዎች ----------------------------------------------------------------------- የፕሮግራሞቹ እድ
የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት የኘሮግራም ፈቃድ ዕድሳት ቅድመ ሁኔታዎች ----------------------------------------------------------------------- የፕሮግራሞቹ እድሣት /የፈቃድ እድሳት/ እንደ ፕሮግራም ቆይታው በተቋሙ ላይ በየጊዜው የሚደረግ ምርመራን መሠረት በማድረግ በየሶስት ዓመቱ የሚደረግ ሲሆን ይህንን ሳያመለክት የቀረ ማንኛውም ተቋም ፕሮግራሙ የማይታደስለት ይሆናል። ለተቋማት የኦዲት፣ እውቅና፣ ድጋፍና ኢንስፔክሽን ሊደረግ የሚችል ሲሆን በዚህም የተገኘው ሪፖርት መጨረሻ ላይ ለፈቃድ እድሣት በግብዓትነት የሚያገለግል ይሆናል። ከስልጠና ፕሮግራሙ ተመራቂዎች ውስጥ በፌደራል የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ብቁ ሆነው የተገኙትንና በግልም ሆነ በቅጥር ስራ ያገኙት ሰልጣኞች ብዛት ባለፉት ሦስት ዓመታት እየጨመረ የመጣ መሆኑን ማረጋገጥ። በፈቃድ ተመዝግበው ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሰልጣኞች ምዘና አፈጻጸም ከ50% በታች ያስመዘገበ ተቋም የፈቃድ እድሳት አይሰጠውም። የተቋሙ ራእይ፣ ተልእኮ፣ ዓላማና አሰራር ከትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ጋር የተጣጣመ መሆን አለበት። የሙያ ደረጃዎችንና ስርዓተ ትምህርትን፣የአሰልጣኞችን ብቃት፣ የማሰልጠኛ እቃዎችን ፣ የስልጠና መሳሪያዎችን ፣ ቁሳቁሶችንና የመረጃ መሳሪያዎችን አስመልክቶ የተቀመጡትን ዝቅተኛ መለኪያዎች ማሟላት ይኖርበታል። ለስልጠና ሂደቱ ይረዳ ዘንድ እንደየሙያ ዓይነቱ ባህሪ ተቋሙ በምቹ ቦታ እና የተሟላ ማስተማሪያ ክፍሎች/ሰርቶ ማሳያ ቦታ/ /Laboratory/ /work shop/ ያሉት ስለመሆኑና በአስፈላጊው የማሰልጠኛ መሳሪያዎች ስለመደራጀቱ ዝግጅቱ ሁሉ ይህን የሚያሳይ መሆን አለበት። የሙያ ምዘናን የማሣለፍ መጠን ስልጠና ካጠናቀቁት ውስጥ ቢያንስ 50 በመቶ የሚሆኑት የሙያ ምዘናን ማለፍ

የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት የኘሮግራም ፈቃድ ዕድሳት ቅድመ ሁኔታዎች የፕሮግራሞቹ እድሣት /የፈቃድ እድሳት/ እንደ ፕሮግራም ቆይታው በተቋሙ ላይ በየጊዜው የሚደረግ ምርመራን መሠረት በማድረግ በየሶስት ዓመቱ የሚደረግ ሲሆን ይህንን ሳያመለክት የቀረ ማንኛውም ተቋም ፕሮግራሙ የማይታደስለት ይሆናል። ለተቋማት የኦዲት፣ እውቅና፣ ድጋፍና ኢንስፔክሽን ሊደረግ የሚችል ሲሆን በዚህም የተገኘው ሪፖርት መጨረሻ ላይ ለፈቃድ እድሣት በግብዓትነት የሚያገለግል ይሆናል። ከስልጠና ፕሮግራሙ ተመራቂዎች ውስጥ በፌደራል የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ብቁ ሆነው የተገኙትንና በግልም ሆነ በቅጥር ስራ ያገኙት ሰልጣኞች ብዛት ባለፉት ሦስት ዓመታት እየጨመረ የመጣ መሆኑን ማረጋገጥ። በፈቃድ ተመዝግበው ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሰልጣኞች ምዘና አፈጻጸም ከ50% በታች ያስመዘገበ ተቋም የፈቃድ እድሳት አይሰጠውም። የተቋሙ ራእይ፣ ተልእኮ፣ ዓላማና አሰራር ከትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ጋር የተጣጣመ መሆን አለበት። የሙያ ደረጃዎችንና ስርዓተ ትምህርትን፣የአሰልጣኞችን ብቃት፣ የማሰልጠኛ እቃዎችን ፣ የስልጠና መሳሪያዎችን ፣ ቁሳቁሶችንና የመረጃ መሳሪያዎችን አስመልክቶ የተቀመጡትን ዝቅተኛ መለኪያዎች ማሟላት ይኖርበታል። ለስልጠና ሂደቱ ይረዳ ዘንድ እንደየሙያ ዓይነቱ ባህሪ ተቋሙ በምቹ ቦታ እና የተሟላ ማስተማሪያ ክፍሎች/ሰርቶ ማሳያ ቦታ/ /Laboratory/ /work shop/ ያሉት ስለመሆኑና በአስፈላጊው የማሰልጠኛ መሳሪያዎች ስለመደራጀቱ ዝግጅቱ ሁሉ ይህን የሚያሳይ መሆን አለበት። የሙያ ምዘናን የማሣለፍ መጠን ስልጠና ካጠናቀቁት ውስጥ ቢያንስ 50 በመቶ የሚሆኑት የሙያ ምዘናን ማለፍ ይኖርባቸዋል። እየጨመረ የመጣ ወደ ስራ የተሰማሩ ምሩቃን መጠን፤ የተሻሻለ የሙያ ደረጃን ካለ ተከትሎ የተሻሻለ ስርአተ ትምህርትና የማስተማሪያ የማሠልጠኛና የመማሪያ ማቴሪያሎች፤ እየጨመረ የመጣ ብቃታቸው የተረጋገጠ መምህራን በደረጃና በመቶኛ፤ ስልጠና አጠናቀው የወጡ ባለሙያዎች ያሉበትን ሁኔታ የሚያሣይ የጥናት ሪፖርት (Tracer Study) ፤ ፈቃድ ባለው የሒሣብ ባለሙያ የተደረገ የኦዲት ሪፖርት፤ የተከማቸና የተሸጋገረ ቴክኖሎጂ፤ በአካባቢው ካለ ኢንዱስትሪ ጋር የተደረገ ከኘሮግራሙ ጋር ተዛማጅነት ያለው የመግባቢያ ስምምነት አተገባበር፤ በተቋሙ ድጋፍ አማካኝነት የተደራጁ የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ብዛት፤ የጥራት አመራር ስርአት /Quality Management System/ ትግበራ የሚያሳይ መረጃ፤ በዚህ የማረጋገጥ ሂደትም የአካባቢው የሰው ሀይል ገበያ መረጃ፣ የክትትል ሪፖርቶች፣ ጥራት ያለው የአመራር ስርአት ሪፖርትን አስመልክቶ የተሰጡ ግብረ መልሶች፣ አመላካች ጥናት ነው፡፡በተጨማሪም በዚህ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ለአካል ጉዳተኛ ሰልጣኞች ተገቢውን እድል የሰጠ ተቋም ከመደበኛው መስፈርት ተጨማሪ ነጥብ ያገኛል፡፡ ** በስልጠናው የተሳተፉ አካል ጉዳተኞች ብዛትና ከስልጠና በኋላ ስላሉበት ሁኔታ የሚገልፅ የጥናት ሪፖርት (Tracer Study) የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።