en
Feedback
MIRAF NEW Jobs22

MIRAF NEW Jobs22

Open in Telegram

MIRAF #join &share ያርጉና የሚፈልጉትን ስራ ያገኛሉ ። ስልክ ፦09 22 59 45 58 09 69 67 63 62

Show more
1 187
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እኔ_ማን_ነኝ_#ትልቅ_ህልም_#inspiration_#inspiration_#dawitdreams128k.m4a6.86 MB

ምናብ! በብዞቻችን ዘንድ ብዙም ትኩረት የተነፈገው ነገር ግን ህይወታችንን በፈለግነው መልኩ ለመቀየር ፈጣሪ ካደለን ስጦታወች በጣም ወሰኝ ዋነኛው ምናብ/imagination ነው። ምናባችንን መጠቀም ካልቻልን እዚህ አለም ላይ በስጋም ይሁን በመንፈሳዊ ህይወታችን ተሪ የሚባል አይነት ኖሮ ነው የምንኖረው ። የእምነት ዋነኛ መሳርያ ምናብ ነው ፤ በምናባችን ተጉዘን ፈጣሪ ይህን ያደርግልኛል በማለት እምነት በውስጣችን እንድንፈጥር ይረዳናል ፤ ምናብን ተጠቅመን የምንፈልገውን ነገር በውስጣችን ማሰብ ካልቻልን እምነት መፍጠር እንችልም። ወንድማችን አሸናፊ በደንብ አስቀምጦታል ስለ ምናብ ተጋበዙልን ተንቀሳቃሽ ምስሉን። መልካም ቀን ይሁንላችሁ! ኢቲኬር ምርጥ የዘመናችን የስኬት መሰላል🙏🙏🙏

0.75 KB

ኢቲኬር በዋናው ሔዶፊስ በዚህ ስዓት ይህን ይመስላል መልካም የተቀደሰና የተባረከ ቀን ይሁንልን🙏🙏🙏 ኢቲኬር ምርጥ የዘመናችን የስኬት መሰላል🙏

ውሎህ ምርጫ ነው! ፨፨፨፨/////////፨፨፨፨ ዛሬ ምርጫህ ሳትሆን ስጦታህ ነች። ስጦታህን የመጠቀምና የማባከን ምርጫው ግን ያንተ ነው። እንደ ስጦታ የምንጠቀመውና እንደምርጫ የምናልፍበት የህይወት መንገድ አለ። መረጥክም አልመረጥክም የመረጥከውን ትኖራለህ፤ ወደድክም ጠላህም በወደድከው መንገድ፣ ሚዛን በደፋልህ ጎዳና ትጓዛለህ። ሳልፈልገው አረኩት፣ ሳይመቸኝ መረጥኩት የሚባል ነገር የለም። ለፍላጎትህ መክፈል የሚገባህን ዋጋ ስላልከፈልክ የማትፈልገውን እያደረክ ትኖራለህ፤ ስላልተመቸህ ሌላ አማራጭ ለመሞከር ዝግጁ አልነበርክምና ባልተመቸህና ስሜት በማይሰጥ ሁኔታ ውስጥ እራስህን ታገኛለህ። አዎ! ጀግናዬ..! ውሎህ ምርጫ ነው። ማድረግ የሚገባህን ለማድረግ፣ መተው፣ መሻገር፣ ማለፍ የሚገባህን ለማለፍ ሁሌም ነፃ ነህ። ምንም እንኳን ቀንህ ስጦታ ብትሆንም የምታሳልፍባት መንገድ ግን ምርጫ ነው። በሚጠቅምህ ተግባር ማሳለፍ፣ በወደድከው ምርጫ መኖር፣ በሚመችህ አኳሃን ትርፋማ ማድረግ ያንተ ምርጫ ነው። ህልምህን እንደምትኖር የምታረጋግጠው በቀናት በሚደጋገሙ ተግባራትህ ነው። አንተ ዋጋ ሳትሰጠው፣ ትኩረት ሳታደርግበት፣ ጊዜ እንኳን ሳትመድብለት፣ ወደ ተግባር ሳትገባ የሚቀይርህ፣ የሚያሳድግህ፣ የሚያነሳህ በፍቃዱ የሚሰራለህ ቀን፣ ላንተ ብሎ የሚኖር ሃሳብም ሆነ ምኞት የለም። አዎ! ለቀንህ ስሜት ይኑርህ፤ ለውሎህ ተጠንቀቅ። የተሻለ ነገን ማለምህን ቀጥል ስራህን ግን ዛሬ ጀምር፤ ብሩህ ወደፊት ማለምህን ቀጥል እርምጃህን ግን አሁን አሃዱ በል። ዋጋ ያልተሰጣት ቀን በምንም ተዓምር ዋጋዋን ማሳደግ፣ ትርፋማ መሆንና ለውጤት መብቃት አትችልም። ዛሬ ህልምህ ላይ የምትዘምትበት መሳሪያህ ነው፤ አሁን የነገህን በር የምትከፍትበት ሁነኛ ቁልፍ ነው። ባለቤቱ ያላከበረውን ስጦታ አካባሪ አይላክለትምና ቀንህ ያንተ እንደሆነች አስብ፤ ትርጉም በመስጠት አክብራት፤ በቻልከው ልክ ጣርባት፤ እንዳስፈላጊነቱ እረፍባት፣ ፋታ ውሰድባት። ነገር ግን ሁሌም የትርፋማነትህ ግብዓት አድርጋት። ኢቲኬር ምርጥ የዘመናችን የስኬት መሰላል🙏🙏🙏

photo content

photo content
+1

photo content

ህልም እስከወዲያኛው ይሞታል ብዬ አላምንም። ነገር ግን ይቀበራል። ሳይሞት የሚቀበር ነገር ህልም ነው። የሰው ልጅ ያለ ህልም አይኖርም፤ አዲስ ጫማ ከመግዛት አንስቶ ሌላ ሰው እስከመሆን ድረስ ያልማል። አንዳንዴ ህልሙ እውን ሆኖለት የፈለገውን ሲያገኝ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ህልሙን በምክንያት ቀብሮ የኑሮ ጉዞውን ይቀጥላል። ህልም ሳይሞት ይቀበራል ያልኩት፤ ሰው በውስጡ “እንዲህ ማድረግ እኮ እፈልግ ነበር” እስካለ ድረስ ህልሙ እስትንፋስ አለው ብዬ ስለማምን ነው። “ቢሆን ኖሮ” የሚል ማንኛውም ሰው፤ ሳይሞት ነገር ግን ከብዙ ምክንያቶች እና አጋጣሚዎች ስር የተቀበረ ህልም አለው። እዚህ ላይ ግን አንድ ነገር ማስረገጥ እፈልጋለው፤ ብዙን ጊዜ “ህልም” ስንል፤ ሌሎች የሚያጸድቁት ትልቅነትንና በአደባባይ የሚታይን ክብር አይደለም።ሁላችንም የምንጋራው ትክክለኛ ህልም ፤ ኑሮዋችንን ሀሴት በሚሰጠን መልኩ መምራትና ከኑሮ ውስጥ ማትረፍ የምንችልውን ሁሉ ማትረፍን ነው። ያ ደግሞ ለሁላችንም የተለያየ ነው…… ሆኖም ግን ነገሮች ከአሰብናቸው በላይ ሲከብዱ፤ አስቀድመን ያላሰብንቸው ነገሮች ሲከሰቱ፤ ህልማችን ቅዠት ይመስለናል፤ ደስታ ይሰጠናል ብለን ያሰብነውን የህልም ኑሮ ወደታች ቀብረን፤ አጋጣሚ በሚቀድልን ቦይ መፍሰስ እንጀምራለን። ምንም እንኳን ከህልማችን እርቀን ብንጓዝም ፤ ሁሌም በውስጣችን “እንዲህ አስብ ነበር እኮ” ማለታችን ግን አይቀርም። ዘ ፒልግሪሜጅ የተሰኘው የፓውሎ ኮዌሎ መጽሀፍ ላይ፤ ሰው ህልሙን መግደል ሲጀምር፤ የሚከተሉትን ሶስት ምልክቶች ያሳላይል ይላል። 1- የመጀመሪያ ምልክት “ጊዜ የለኝም”ማለት ማብዛት ነው- ጸሀፊው “እጅግ ጊዜ የጠበባቸው ሰዎች ለሚፈልጉት ነገር ሁሌም ጊዜ ይኖራቸዋል፤ በአንጻሩ በጊዜያቸው ምንም የማይሰሩ ሰዎች ናቸው የቀኑን ማጠር የሚያማርሩት” ይላል። ለነገሩ ማን ነው በዚህ ምድር ላይ ከ 24 ሰዓታት በላይ የተሰጠው? ህልም ካለን ወይም ማድረግ የሚያስደስተን ነገር ካለ፤ ግዜ ፈጽሞ ችግር ሊሆን አይችልም። ጊዜ አጥቼ ነው ማለት ስንጀምር በእርግጥም ህልማችን ላይ ግድያ እየፈጸምን ነው። ቅድሚያ የምሰጠውን ነገር ማስተዋል ሲቻለን፤ እውነትም 24 ሰዓታት ለምንፈልገው ነገር በቂ መሆኑ ይገለጽልናል። 2 - ሁለተኛ ምልክት “እርግጠኝነታችን” ማብዛት ነው።- ይህ ማለት ከውጊያው በፊት ቀድመን ስንሸነፍ ነው። ሁሉን ነገር ተንብየን፤ የነገሩን ከንቱነት ለራሳችን ሰብከን፤ ከህይወት የሚገባንን ሳይሆን ጥቂቱን ብቻ መጠየቅ እንጀምራለን። ከጸሀፊው አንደበት የሚከተለውን ልጠቅስ ወደድኩኝ “we never see the delight, the immense delight in the hearts of those who are engaged in the battle. For them, neither victory nor defeat is important; what’s important is only that they are fighting the Good Fight.” “The good Fight” የሚለው ጸሀፊው፤ ልባችን የሚጠይቀንን ጥልቅ መሻት ሁሉ ነው። ለሚፈልጉት ነገር የሚዋጉ ሰዎች ፤ ድልና ሽንፈቱ አይደለም የሚያበረታቸው። የሚያበረታቸው ለሚፈልጉት ነገር መታገላቸው ብቻ ነው፤ እምነት እና ህልማቸውን ነው ጽናታቸው። የብዙዎቻችን ችግር ግን ድልና ሽንፈትን፤ እውቅናና መዘንጋትን መሰረት ማድረጋችን ነው። ከመንገዱ ጋር እንጂ ከመደረሻው ጋር ፍቅር ሊይዘን አይገባም። መንገዱን ስንወደው ነው መሄድ የማናቋርጠው። 3 - የመጨረሻው ምልክት – “ህይወት እንደ እሁድ ከሰዓት” መሆን ስትጀምር ነው- ይህ ማለት ሁሉን በጸጋ ተቀብለን ስንኖር፤ ከኑሮ የምንፈልገውን መጠየቅ ስናቆም፤ ህልማችን እየሞተ ነው ማለት ነው። እዚህ ላይ ነው ብዙዎቻችን የምሸወደው፤ እራሳችንን እንደበሳል ቆጥረን፤ የምናስበው ሁሉ የልጅነት ቅዠት ነው ብለን እናምናለን። ከውስጥ ግን ሁሌም በትንሹ የሚጮህ ድምጽ አለ “ቢሆን ኖሮ” የሚል – ይህ ድምጽ የህልማችን ጣር ነው። “We become our own worst enemy. We say that our dreams were childish, or too difficult to realize, or the result or our not having known enough about life. We kill our dreams because we are afraid to Fight the Good Fight.”-Paulo Coelho ሁሉንም እርግፍ አርጎ መተው ለግዜው ሰላም የሚሰጥ ይመስላል፤ ነገር ግን ከውስጣችን የምንፈልገው ነገር እውን እስካልሆነ ድረስ ሁሌም ሰላም መንሳቱ አይቀርም። ሳይሞት የምንቀብረው ህልማችን፤ እየፈነቀለ “ቢሆን ኖሮ” ያስብለናል። ህይወት አጭር ናት፤ የምንፈልገው እና የምናልመው ነገር ደስታን የሚሰጠን ከሆን በምክንያት አንቅብረው። ሶስቱን ምልክቶች ካየን፤ ህልማችንን ወዴት እንዳደረስነው እራሳችንን እንጠይቅ። ሸር__❤👇👇👇👇👇👇👇👇🙏 https://t.me/SiS2931

መስነፍ አያዋጣህም! በህይወትህ በጣም ወሳኙ አሁን የገጠመህ ችግር ወይ የሁኔታዎች ከባድ መሆን አይደለም፤ ያንተ ቆራጥነት ነው! ምን ድረስ ላመንክበት ለመጓዝ ወስነሀል ነው ጥያቄው! ረሀብ ቢሰማህ "ካገኘው እበላለው ካላገኘው ችግር የለውም" አትልም እኮ፤ ያንን ምግብ ለማግኘት በቆራጥነት ዋጋ ትከፍላለህ እንጂ አይንህ እያየ በረሀብ አትሞትም። አሁንም አይንህ እያየ መስነፍ የለብህም፤ ማመንታት የት ሊያደርስህ? ተነስና ዋጋ ክፈል! ለራስህ ብቻ ሳይሆን ለምትወዳቸውና ለብዙዎች የምትደርስ አስፈላጊ ሰው ነህ! ዳይ ወደ ተግባር! ሸር____❤👇👇👇👇👇👇👇👇🙏 https://t.me/SiS2931

1. የሰው ልጆች በመጀመሪያ በውልደት ወደዚህ አለም ሲመጡ የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከሚቀጥሉት አርባ አመታት በላይ የበለጠ ፋይዳ አለው።  ምክንያቱም የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከመሞት በፊት ያለው ትልቁ የህይወት ለውጥ ነው። 2. ፍርሃት የፈሪም የጀግናም መነሻ ነው። ፍርሃት ለፈሪ ጭንቀቱ ሲሆን፤ ለጀግና ደግሞ ጀብዱው ነው። 3. መማር ባለሙያ ያደርጋል፤ መኖር ደግሞ አዋቂ ያደርጋል። 4. ሰው የሆነውን የሚሆነው በአጋጣሚ አይደለም።አዋቂው ሰው ህፃኑ ልጅ በልጅ አዕምሮው የፃፈውን ተውኔት የሚተውን ተዋናይ ነው። የልጅ ጭንቅላት የተባለውን ይይዛል፤ አዋቂ ደግሞ የያዘውን ይተገብራል። አዋቂው ሲያለቅስ ወይም ሲያዝን እንደህፃን አባብይው። 5. ተስፋ የመኖር ምክንያት ነው።ሰውን እንዲኖር የሚያደርገው መለወጥ አለመለወጡ ሳይሆን የመለወጥ ተስፋው ነው። ቢሆንም ግን ህይወት ተከታታይ መሆኗን መገንዘብ ይጠቅማል። ዛሬ የምንኖረው በትላንት ምክንያት ነው። 6. ሰው መሆን ማለት ራቁታችንን ከተወለድን በኋላ፤ ከልብስ ጀምሮ አካላችንን ከሚሸፍኑት ሽፋኖች መላቀቅ ነው። ሰው ሰውነቱን የሚያጣው ራቁቱን ከእናቱ ማህፀን ሰው ሆኖ ተወልዶ በማህበረሰብ፣ በልብስ፣ በትምህርት፣ ሃይማኖት፣ በብሔር የመሰሉ ግዑዛን አልባሳትን በመደረብ ነው። 7. እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣረና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ስላልሆነ ነው። 8. ጎዳና ላይ የሚያድር ሰው ብርዱን ይለምዳል፣ ፀሃዩን ይታገሳል፣ አውሬ ያስለምዳል፤ ሰውን ግን ይፈራል። ቀኑን ሙሉ ብርድ ሳንፈራ ደረታችንን ገልጠን ራቁታችንን የምንውል ሰዎች፤ ልክ ሲመሽ የውጪ በር ቆልፈን፣ከዛ የሳሎን በር ቆልፈን፣ የጓዳ በር ቆልፈን፣ አልጋችን ውስጥ ገብተን ብርድልብስ ለብሰን፣ ብርድ ልብሱ እንዳይኮሰኩሰን አንሶላ ደርበን፣ አንሶላው እንዳይቀዘቅዘን የለሊት ልብስ ለብሰን ...በነዚህ ነገሮች ሁሉ ተከልለን እንተኛለን። ይህን እንዲሆን ደግሞ ያደረገው ፍርሃታችን ነው። 9. በታሪክ ውስጥ ትልቁ አምባገነን ታሪክ ራሱ ነው።ሁላችንም የታሪክ ተገዢዎች ነን። 10. የማታሸንፈውን ሰው ተጠያቂ ማድረግ የፈሪነት መፍትሔ ነው። 11. እውነት እኮ የጊዜና የቦታ ድምር ውጤት ነው። የራስን ሃሳብ ሌላው እንዲገባው ማድረግ ማለት ፤ የራሱን ሃሳብ ድንበር አልፈን የሃሳብና አስተሳሰብ ወረራ አካሄድን ማለት ነው። 12. የሚጠፋ ነገር ዐይንህ ስር ተቀምጦ ያለማየትን የመሰለ ዕውርነት የለም። አንዳንዴ ከሞት በኋላ ስለሚኖር መኖር እየጓጓን የውሸት ማመን የለብንም። ስለፀሎታችንን ምንነት በአንክሮ መፈተሽ ያስፈልጋል 13. ሰው የምታውቀው ፍጡር አይደለም። ሁልጊዜ ሰውን የምናውቀው ይመስለናል። እኔ ሐኪም ስከሆንኩና የአንድ ሰው አካል ቀድጄ ልቡን ስላየሁት ሰውን ያወኩት ይመስለኛል። ነገር ግን ሰው በየትኛውም ደረጃ የሚታወቅ ፍጡር አይደለም። በደረቁ ሳይንስ አጥንተህ ሰው ውስጥ ያለውን ፕሮቲን እንዴት እንደሚሰራ ስላወቅህ ሰውን አውቃለሁ ማለት አይቻልም። የመማር አንደኛው ችግር (በተለይ እኛ ሐገር) ቶሎ መታበይና የምናውቀው እውቀት እኛ ያመጣነው ሳይሆን ቀድሞ በሌሎች የተፈጠረ መሆኑን የመርሳት ችግር አለብን። እኛ ያወቅነው ከእኛ በፊት የመጡት የፈጠሩትን ነው። ይህንን እንረሳና እኔ ተምሬ ሳውቅ ራሴን አዋቂና ሐሳቡን እኔ የፈጠርኩት የመምሰል ችግር አለብን። 14. እያወቅክ ስትሔድ ትልቅልነትህን ሳይሆን ትንሽነትህን ነው የምትረዳው " ብዙ ነገር ለመማር መሞከር እይታህን ያሰፋል። የእይታህ አድማስ ሲሰፋ ደግሞ አንተ እያነስክ ነው የምትሄደው። ሰፊ ከሆነው ዓለም ውስጥ አንተ ምን ያህል ኢምንት እንደሆንክ ትረዳለህ። እያወቅክ ስትሄድ ትልቅነትህን ሳይሆን ትንሽነትህን ነው የምትረዳው። ሸር__👇👇👇👇👇👇👇❤️💪 https://t.me/SiS2931

ከማን_ጋር_ነው_የምትውለው_Ethiopian_Motivational_Speech_Inspire_Ethiopia.mp37.08 MB

ወደ_ተግባር_ግባ!_Ethiopian_Motivational_Speech_Inspire_Ethiopia_Manyazewal.mp310.69 MB

photo content

+1