en
Feedback
RAFIDIM

RAFIDIM

Open in Telegram

የእረፍት ቦታ

Show more
204
Subscribers
No data24 hours
+37 days
No data30 days
Posts Archive
የምናደርገውን ሁሉ ለጌታ እንደሆነ መቁጠር ለህይወታችንን ትርጉም ይሰጠዋል ብዬ አምናለሁ። የምንማረው፣ የምንሰራው፣የምንበላው እና የምናወራው ለጌታ ነው ብለን ማሰብ መቻል...እጅግ ጠቃሚ ነው።

ከኖር አይቀርማ....ለቀጣይ ትውልድ ምሳሌ ሆነ ኑሮ ይሁን....

photo content

ምናደርገው ሁሉ ስለጌታ እናድርግ

😁
😁

አይሁዳዊያን ከቄሳር በላይ የሆነውን ንጉስ ፈለጉ ነገር ግን ለአለም ሁሉ የሚታረድ ምስኪን በግ ሆነባቸው። ጦረኛውን መሲህ ፈለጉ ነገር ግን ራሱን መስዋእት የሚያደርግ ትሁቱን ባሪያ ለመቅረብ ተጠየፉ።
አይሁዳዊያን  ከቄሳር በላይ የሆነውን ንጉስ ፈለጉ ነገር ግን ለአለም ሁሉ  የሚታረድ ምስኪን በግ ሆነባቸው። ጦረኛውን መሲህ ፈለጉ ነገር ግን ራሱን መስዋእት የሚያደርግ ትሁቱን ባሪያ ለመቅረብ ተጠየፉ። ጠላቶቻቸውን ተዋግቶ የሚያሸንፍ በዳዊት መንበር ላይ የሚቀመጥ የያህዌ አምሳል ፈለጉ ነገር ግን በመከራ፣ በስቃይና በሞት ድል አድራጊ የሆነውን እውነተኛውን የክብር ጌታ ሰቀሉት። የፈለጉት ሌላ ያገኙት ሌላ። በማግኘት  ያልተጠቀሙ በመፈለግ ለህይወታቸው ያላገኙት በመስቀል የዋለ   ቅቡእ  የአምላክ ልጅ

ስንቶቻችን በሃገራችን ስለ ወጌላዊያን እንቅስቃሴ፤ መቼ እንደጀመረ እና በቆየባቸው አመታቶች ምንን ለውጥ እንዳመጣ፣ ለሃገራችን ምን አስተዋፆ እንዳበረከተ እናውቃለን? ይህንን መፅሃፍ ሳነበ በከፈሉት መስዋትነት እየተማረኩ፣ ባደረጉት አስተዋፆ እየኮራው፣ በሰሩት ስህተት እያዘንኩ፣ በኢትዪጲያ ኦርቶዶክ ቀሳውስት እየተናደድኩ....ብቻ ብዙ ነገር እየተማርኩ ያነበብኩት መፅሃፍ ነው። ከመካነ ኢየሱስ እና ከኢትዮጲያ ሊትራን እስከ ሙሉ ወንጌል ድረስ ደስ በሚል አቀራረብ የተፃፈ መፅሃፍ ነው። ማግኘት ከቻላችሁ ታነቡት ዘንድ ደስታዬ ነው።

ጌታ ሆይ 🙏 ለቤትህ እና ለስራህ የማደርጋቸውን ሁሉ በሙሉ ልቤ አደርግ ዘንድ እርዳኝ። በዚህ ወጣትነቴ ዘመን መሮጥ በሚገባኝ ያክል እሮጥ ዘንድ ከንተ ሃሳብ ውጪ ባለ ትዳር እንዳልታሰር ጠብቀኝ! አገልግለኝ በለህ የምታገለግልኝ ምንም ሳይጎልህ እንድሰጥህ የምትጠብቅ፤ ፍላጎቴን የማትጋፋ እስክፈቅድልህ ከበር የምትጠብቅ ጌታ እባክህ ለስራህ አቅናኝ።  እግሮቼ ለዘላለማዊህ ስራህ ይፍጠኑ፣ እጆቼ ለተቸገሩት በልግስና ይዘርጉ፣ አንደበቴ ስለጌትነትህ እና ስለአዳኝነትህ ያውጅ፣ አእምሮዬ ስለ ትልቅነትህ ያሰላስል። ኦ ጌታ ሆይ እባክህ የመንፈስህን ርሃብ ጨምርብኝ በቃል ስርን እሰድ ሰንድ የቃልህን ጥማት ስጠኝ። አሜን 🙏

Dereje_Kebede_ወረት_አያውቀው_ጌታዬ_ዘማሪ_ደረጀ_ከበደ_Weret_Ayawkew_Getaye_Lyr.mp310.19 MB

photo content

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ — የዮሐንስ ወንጌል 1:12

photo content

photo content

Mrkon Endagegne.mp36.54 MB

ቅዱስ አውግስጢኖስ “እርሱ የእኛን ዘላለማዊ ቁስል የፈወሰው በራሱ ላይ ያንን ሁሉ መከራ በታገሠበት ስፍራ ነው፤ እኛን ከዘላለም ሞት ያዳነን እርሱ በጊዜያዊ ሞት በሞተበት በዚያው መስቀል ላይ ነው”

photo content

Voice message01:16