en
Feedback
መፅሐፈ ሔኖክ (Metshafe Henok)

መፅሐፈ ሔኖክ (Metshafe Henok)

Open in Telegram

አባቶቻችን ለኛ ብዙ ነገርን ትተውልን አልፈዋል እኛም ቢያንስ የተውልንን እያወቅን (እያነበብን) እንዘክራቸዋለን መዳሕኒአለም ባከበራቸው መጠን እናከብራቸዋለን።

Show more
943
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+20
in 0 channels
November '240
in 0 channels
Get PRO
October '24
+21
in 0 channels
Get PRO
September '24
+127
in 0 channels
Get PRO
August '240
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '24
+54
in 0 channels
Get PRO
March '24
+19
in 0 channels
Get PRO
February '24
+19
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '230
in 0 channels
Get PRO
August '230
in 0 channels
Get PRO
July '230
in 0 channels
Get PRO
June '230
in 0 channels
Get PRO
May '230
in 0 channels
Get PRO
April '230
in 0 channels
Get PRO
March '230
in 0 channels
Get PRO
February '230
in 0 channels
Get PRO
January '230
in 0 channels
Get PRO
December '220
in 0 channels
Get PRO
November '220
in 0 channels
Get PRO
October '220
in 0 channels
Get PRO
September '220
in 0 channels
Get PRO
August '220
in 0 channels
Get PRO
July '220
in 0 channels
Get PRO
June '220
in 0 channels
Get PRO
May '220
in 0 channels
Get PRO
April '220
in 0 channels
Get PRO
March '220
in 0 channels
Get PRO
February '220
in 0 channels
Get PRO
January '220
in 0 channels
Get PRO
December '210
in 0 channels
Get PRO
November '210
in 0 channels
Get PRO
October '210
in 0 channels
Get PRO
September '210
in 0 channels
Get PRO
August '210
in 0 channels
Get PRO
July '210
in 0 channels
Get PRO
June '210
in 0 channels
Get PRO
May '210
in 0 channels
Get PRO
April '210
in 0 channels
Get PRO
March '210
in 0 channels
Get PRO
February '21
+31
in 0 channels
Get PRO
January '21
+53
in 0 channels
Get PRO
December '20
+1 091
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
21 December0
20 December+6
19 December0
18 December0
17 December+1
Channel Posts
Repost from Tariku Abera
ከኦርቶዶክስ እምነት ውጪ ያሉ ሰዎች እኛ ኦርቶዶክሳውያን ያላልነውንና የቤተክርስቲያን ትምህርት ያልሆነ አባባል ራሳቸው ፈጥረው በማውራት የክርስቶስን አዳኝነት ለቅዱሳን የሰጠን አስመስለው የሚያወሩት የሐሰት ትርክት ፍጹም ውሸትና ከአዕምሮ ጥበት የተነሳ የሚፈጥሩት ተራ ወሬ ነው። እንዲሁም የቤተክርስቲያኒቱን መጻሕፍት አጣመው በራሳቸው መንገድ በመተርጎም የሚያስተላልፋት የማወናበጃ መንገድ እጅግ አሳፋሪና የሰዎቹን የልብ ጥመት በግልጽ የሚያሳይ ነው። በኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ንጹሕ አስተምሮ ጸንተን እንድንመላለስ መንፈስ ቅዱስ ሁላችንን ይርዳን። መ/ር ታሪኩ አበራ ለሌሎችም ሼር አድርጉት

2
† የክርስቶስ አዳኝነትና የቅዱሳን አዳኝነት ልዩነት † ★ ሼር አድርጉትና ሰዎች ይማሩበት።★ ሰላም ለሁላችሁ ይሁን።ድኅነት(ላልቶ ይነበብ) ሁለት ዓይነት ነው።አንዱ የነፍስ ድኅነት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሥጋ ድኅነት ነው። በመጀመሪያ በሰው ነፍስ ድኅነት ላይ የክርስቶስን ሥልጣንና የቅዱሳን ድርሻ ምን እንደሆነ ለይተን እንመልከት። ማንኛውም ሰው በራሱ ፍጹም ስላልሆነና ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በራሱ ሥራ ብቻ መግባት ስለማይችል ይህንን የሰዎችን ድካምና ጉድለት የሚረዳ ልዑል እግዚአብሔር ከዘለዓለም ዘመናት በፊት ማለትም ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር በመለኮታዊ ዕቅዱ ለሰው ልጆች ሁሉ ፈዋሽ የነፍስ መድኃኒትን አዘጋጀ። ይህ የፍጥረት ሁሉ መድኃኒት እኛ ባልነበርንበት ዘመን የነበረ፣ እኛ ባልኖርንበት ዘመን ለእኛ መድኃኒት ሆኖ የኖረ ፣ የሚያምኑበትን ሁሉ ያድን ዘንድም በዘመን ፍጻሜ ከቅድስት ድንግል የተወለደ ፣ እኛን መስሎ ባሕርያችንን በሕርይው አድርጎ በሰው ሥጋ የተገለጠ ፣ በድካማችን የሚራራልን ሕያው መድኃኒት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።ኢየሱስ ክርስቶስ ብቸኛውና አቻ የሌለው የነፍሳችን መድኃኒት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ጸጋ፡ከዘለዓለም፡ዘመናት፡በፊት፡በክርስቶስ፡ኢየሱስ፡ ተሰጠን፥አኹን፡ግን፡በመድኀኒታችን፡በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡መገለጥ፡ታይቷል።"2ጢሞ 1፥9 ጸጋ የሚለው ከእግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሁሉ በነጻ የተሰጠውን መለኮታዊ ስጦታ ነው።ይህም በክርስቶስ ኢየሱስ መስቀል ማለትም በሕማሙና በመከራው ሁሉ የተፈጸመው ቤዛነት በሕያው የደም ኪዳን ለሰው ልጆች ሁለ ጽድቅን ያለ ዋጋ ያስገኘ የእግዚአብሔር ጽድቅ በመሆኑ ይህንን ሰማያዊ ስጦታ በእምነት ለሚቀበል ሁሉ እግዚአብሔር መዳኑን በልጁ ደም በኩል አስረግጦለታል።መጽሐፍ እንዲህ ይላል፦ « ሁሉ በድለዋል የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሏቸዋል በኢየሱስ ክርስቶስ በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ።» ሮሜ 3፥23 ታዲያ አዳኙ ክርስቶስ ከሆነ የምንጸድቀውም በእርሱ የማጽደቅ ሥልጣን ብቻ ከሆነ ቅዱሳንን ለምንድነው አዳኝ እያልን የምንጠራቸው? እግዚአብሔር በልዩ ክብር የመረጣቸው ቅዱሳን ደግሞ እነርሱም የሰው ልጆች መድኃኒት ይባላሉ፤ የእነርሱ መድኃኒትነት ግን ሰዎች ወደ እውነተኛው ሕያው የነፍስ አዳኝ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እንድንቀርብ ስለሚራዱ፣ በእግዚአብሔር ልጅ በክርስቶስ ኢየሱስ ደም ነፍሳችን ተቀድሳ የኃጢአት ሥርየትን እንድናገኝ እጅግ ስለሚተጉ ፣በመስቀል ላይ በተፈጸመው ሕያው ቤዛነት ልጅነትና ክብርን በማግኘት ወራሾች እንድንሆን በተለያየ መንፈሳዊ ጸጋቸው ስለሚራዱ ቅዱሳን ሁሉ የሰው ልጆች አዳኝ ተብለው በመጽሐፍ ቅዱስ ይጠራሉ። የቅዱሳን አዳኝነት በጸጋ ነው የምንልበት ምክንያትም በተሰጣቸው ልዩ ልዩ ጸጋ ሰዎችን ወደ ነፍሳቸው መድኃኒት ወደ ክርስቶስ ስለሚያቀርቡ ነው።ቅዱሳን በአጸደ ሥጋ (በምድር ) እያሉ በእጃቸው ተአምራትና በቃላቸው ትምህርት፣በጸሎትና ልመናቸው ሁሉ ብዙዎችን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ፣ከገቢረ ኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ከፈቃደ ሥጋ ወደ ፈቃደ ነፍስ እየመለሱ ለክርስቶስ ምርኮን ያበዙ ነበርና የሰው ልጆች አዳኝ ተብለው ተጠርተዋል። በያዕቆብ መልዕክት 5፥10 ላይ " ኃጢአተኛን ከተሳሳተባት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።" ይላል። ቅዱሳን ሐዋርያት፣ቅዱሳን ነቢያት ፣ጻድቃን ፣ሰማዕታት ሁሉ መላ ዘመናቸውን በምድር ላይ የኖሩት ሰዎችን ከስህተት መንገድ እየመለሱ ለጽድቅ የሚያበቃቸው ክርስቶስ ኢየሱስን በሰው ልብ ውስጥ በቃልና በተአምራት ሲሰብኩ ነበረና ቅዱሳን የሰው ልጆች መድኃኒት ይባላሉ። ራሱ እግዚአብሔር ቅዱሱን ነቢይ እንዲህ ብሎታል "እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌ ሰጥቼሃለሁ።" ኢሳ 49፥ 5-6 ቅዱስ ጳውሎስ በተሰጠው ጸጋ ለሰዎች መድኃኒት ለመሆን ያለፈበትን የትጋት ሕይወት እንዲህ ሲል ገልጾታል። "ደካማዎችን እጠቅም ዘንድ ለደካማዎች እንደ ደካማ ሆንኹ በሁሉ መንገድ አንዳንዶችን አድን ዘንድ ከሁሉ ጋር በሁሉ ነገር እንደነርሱ ሆንኹ።"1ኛ ቆሮ 9፥22 ቅዱስ ጳውሎስ እርሱ ብቻ ሳይሆን መንፈሳዊ ልጁ ቅዱስ ጢሞቴዎስም ሰዎችን ለማዳን በብርቱ እንዲተጋ እንዲህ ሲል መክሮታል ፦ " ለራስኽና፡ለትምህርትኽ፡ተጠንቀቅ፥በእነዚህም፡ጽና፤ይህን፡ብታደርግ፥ራስኽንም፡የሚሰሙኽንም፡ ታድናለኽና።" 1 ጢሞ 4፥16 አንባብያን በድጋሚ በጣም አስተውሉ ክርስቶስ የነፍሳችን አዳኝ የምንለው ማዳን የባሕርይ ገንዘቡ በመሆኑና መዳናችንን በመስቀል ላይ በደሙ ቤዛነት ስለፈጸመልን ደግሞም ወደ መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት ብቸኛው የድኅነት መንገዳችን እርሱ ስለሆነ ነው።ቅዱሳኑን ግን አዳኝ የምንላቸው ወደ ነፍሳችን አዳኝ ወደ ክርስቶስ እንድንቀርብ በትምህርትና በጸሎታቸው ስለሚራዱን ነው።ከዲያብሎስ እጅ እየነጠቁ ወደ ክርስቶስ ስለሚያቀርቡን ነው።ይህ የቅዱሳን ተግባር ከዚህ ዓለም በሥጋ ቢለዩም በአካለ ነፍስ ሆነውም የሚቀጥል ነው። «ሥራቸው ይከተላቸዋል» ተብሎ ተጽፏል። ራዕ 14፥13 በጸሎታቸው፣በልመናና በምልጃቸው ከዘለዓለም ቅጣት እንድንድን፣ለሰይጣንና ለመላዕክቱ ወደ ተዘጋጀው ዘለዓለማዊ የቅጣት ቦታ እንዳንወድቅ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንድንጠቀለል ስለሚራዱን የሰው ልጆች መድኃኒት ብለን እንጠራቸዋለን። ሄኖክ 9፥5 «ጻድቃን ከመላእክት ጋራ የሚኖሩበት ማደሪያቸውን ከቅዱሳንም ጋራ የሚኖሩበት ቦታቸውን ዓይኖቼ አዩ ስለሰውም ልጆች ፈጽመው ይለምናሉ ይጸልያሉ።» ሄኖክ 12፥8 «በሰማይ የሚኖሩ ጻድቃን ባንድ ቃል ሁነው ተባብረው ያመሰናግሉ ለሰው ፈጽመው ይለምናሉ» እኛ ኦርቶዶክሳውያን እመቤታችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምን፣ጻድቃን፣ሰማዕታት፣ቅዱሳን መላእክትን ሁሉ በምልጃችሁ አድኑኝ እያልን የምንማጸነው ከዲያብሎስ ወጥመድ፣ከዓለም ክፉ ምኞት፣ከሥጋ ፍትወትና በድፍረት ኃጢአት ከሚመጣብን መለኮታዊ ፍርድ ያድኑን ዘንድ ነው።ወደ ዘለዓለም ርስት የሚያስገባን ሕያው መድኃኒታችን ግን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው። ሁለተኛው የድኅነት ዓይነት ደግሞ የሥጋ ድኅነት ነው።ይሄ ድኅነት በጣም ቀላሉና ክርስቶስ በእርሱ አምነው በቅድስና ለሚመላለሱ የጸሎት ሰዎች ሁሉ የሰጠው ሥልጣን ነው ቅዱሳን ከተለያዩ የሥጋ ደዌና ሕመሞች የመፈውስ ሙሉ ሥልጣን ስለተሰጣቸው አዳኝ ብለን እንጠራቸዋለን።ማቴ 10፥1 ከሥጋ ደዌ ሰዎችን የማዳን ሥልጣን የእግዚአብሔር ቢሆንም ፣የፈውስ ጸጋ የተሰጣቸው ሰዎች ሁሉ አዳኝ ተብለው ይጠራሉ በምድራዊ ጥበብና ዕውቀት ሰዎችን ከበሽታቸው የሚፈውሰው የሕክምና ባለሙያዎችም ሳይቀር አዳኝ ተብለው ይጠራሉ። ዋናው ከነፍሳችን ድኅነት ጋር በተያያዘ ለሚነሳው የመድኃኒትነት ጥያቄ ግን ከላይ እንደተመለከትነው የክርስቶስ ስልጣንና የቅዱሳን የጸጋ አገልግሎት የተለያየ ነው።
374
3
No text...
819
4
† የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓርማ ትርጉም † ፩. #መደቡ_ነጭ መኾኑ፦ #ዘመነ_ሥጋዌ የምሕረት የደስታና የነፃነት ዘመን መኾኑን ያመለክታል። (ዮሐ.፳፥፲፪፤ የሐዋ. ሥራ ፩፥፲) ፪. የዓርማው ዙሪያ #በወይን_ዛላና_በስንዴ_ዘለላ የተከበበ መኾኑ፦ ምእመናን በቅዱስ ቊርባን አማካይነት ከእግዚአብሔር ጋር አንድነትን፥ ስርየተ ኃጢአትን፥ የዘለዓለም ሕይወትን የሚያገኙ መኾናቸውን ይገልጻል። (ዮሐ.፮፥ ፶፫-፶፰፤ ማቴ.፳፮፥፳፮-፳፱፤ መዝ.፬፥፯) ፫.በዓርማው መሐል ቀጥ ብሎ የቆመ #የዓርዌ_ብርት ምስል በበላዩ ላይ #መስቀል ከዚያም ከፍ ብሎ #አክሊለ_ክህነት አለው የዚኽ ትርጉም፦ ሕዝበ እስራኤል ዓርዌ ብርቱን ባዩ ጊዜ ከእባብ መርዝ እንደ ዳኑ ኹሉ መስቀል ላይ በተሰቀለ በጌታችን በአምላካችንና በመድኃኒታችን #በኢየሱስ_ክርስቶስ ያመኑ ኹሉ በዲያቢሎስ ምክንያት ከመጣባቸው ፍዳ ኃጢአት የሚድኑ መኾናቸውን መስቀሉ የቤተ ክርስቲያን የድኅነት ዓርማ መኾኑን። (ዘኍ.፳፩፥፰፤ ዮሐ.፫፥፲፬) ፬.#አክሊል፦ ቅዱሳን በሰማያዊ መንግሥት የሚቀዳጁትን አክሊለ ክብር እና ማኅተመ ጽድቅን ያመለከታል። (ዘጸ.፴፱፥፴፤ ፩ተሰ.፪፥፲፱፤ ፪ጢሞ. ፬፥፰፤ ፩ጴጥ.፭፥፲፬፤ ራእይ ፪፥፲፤ ፬፥፲፬) ፭.ኹለት መላእክት #የዘንባባ_ዝንጣፊ ና #ዓርዌ_ብርቱን ይዘው ይታያሉ ይህም ዘንባባ፦ በመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ መንፈሳዊ ደስታንና ድኅነተ ነፍስን ያመለክታል ቅዱሳን መላእክት የቤተ ክርስቲያን ጠባቂዎችና የመልካም ዜና አብሣሪዎች መኾናቸውን ያሳያል ዓርዌ ብርቱን ይዘው መቆማቸው ነገረ መስቀሉን አምኖና ሃይማኖቱን አጽንቶ ይዞ የሚኖር የዘለዓለም ድኅነትን የሚያገኝ መኾኑን ያመለክታል። (መዝ.፺፥፲፩፤ ሉቃ.፲፫፥፮-፱፤ ዕብ.፩፥፲፬) ፮.የዓርማው መሀል #ቅዱስ_መጽሐፍ ሆኖ፦ «#ነዋ_ወንጌለ_መንግሥት» የሚል ጽሑፍ በበላዩ አለበት የዚኽ ትርጉም፦ የቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖት ቀኖና እና ትውፊት በቅዱስ መጽሐፍ ትምህርት ላይ የተመሠረተ መኾኑን ያመለክታል፡፡ (ማቴ.፳፬፥፲፬) ፯.#የወይኑ፦ የስንዴው ዛላና ዘለላ በተገናኙበት ላይ የሚታየው ክብ ነገር፥ ዓለምን የሚወክል ኾኖ ዓለም #በክርስቶስ_መዳኑን ያመለክታል፡፡ (ዮሐ.፫፥፲፯) #የዓርማው_ክብር፤ ፩.ዓርማው፦ የቤተክርስቲያኒቱ ሉዓላዊ ክብር መገለጫ ስለኾነ በሀገር ውስጥም ኾነ በውጭ ሀገር የሚገኙ ቤተክርስቲያን መዋቅር አካላት በሙሉ ከዚኽ ዓርማ በቀር ሊጠቀሙ አይችሉም፡፡ ፪.የቤተ ክርስቲያኒቱ አካል ደብዳቤ ሆኖ ይህ ዓርማ የሌለበት ማኅተምና የማዘዣ የሚጠቀም ማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ ጽ/ቤት ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ምንጭ :- ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፬
745
5
+4
No text...
736
6
† ኦርቶዶክሳዊነት በጃፓን † † የጃፓን ዜጎች የኦርቶዶክስ እምነትን በፍቅር እየተቀበሉ ነው።† ★ በጃፓን ሃገር ቤተክርስቲያን መሥራት፣ክርስትናን መስበክ፣ተሰብስቦ መዘመርና መጸለይ በጥብቅ ተከልክሎ የቆየ ሕግ ቢሆንም አሁን ግን ሕዝቡ የጃፓንን የጣዖት አምልኮ እየተጸየፈ ቅድስት ኦርቶዶክስ እምነትን እየተቀበለ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እየተጠመቀ ነው።★ ★ በጃፓን ለዘመናት የኖረው እምነት ሺንቶይዝም የተባለ የቡድሃ እምነት መሠረት ያለው ጣዖት አምልኮ ነው።ጣዖቱ ከታች የምትመለከቱት ባለ ብዙ እጁ ነው።★ ★በአሁን ሰዓት የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በሕግ ራሷን አቋቁማ መደበኛ ስብሰባዎችንም እያካሄደች ሕዝቡን ከዲያብሎስ መንጋጋ እያላቀቀች ነው።★ የጃፓን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤም በቶኪዮ ተካሄዷል !!! በስብሰባው ላይ የምዕመናን ተወካዮችና የቤተክርስቲያኒቱ የአስተዳደር ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። ጉባኤውን የመሩት የጃፓኑ ሜትሮፖሊታን ዳንኤል መሆናቸው የተዘገበ ሲሆን የቶኪዮ ሊቀ ጳጳስ አባ ሱራፌልም ጭምር በጉባኤው የተሳተፉ መሆኑን ኦርቶዶክስ ኮግኔት የጃፓን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን። ሌሎች እንዲማሩበት ሼር አድርጉት መ/ር ታሪኩ አበራ
630
7
No text...
611
8
ወገኖቼ በጣም ልብ በሉ! ይህ መልዕክት ዛሬም ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ብዙ ትምህርት ይሰጣል ። ኢየሱስን ከማክበር ይልቅ ቅዱሳን መላዕክትን በላቀ ሁኔታ ማክበር የተለየ በረከት ያሰጠናል ብለን ለምናምን ሰዎች አመለካከታችንን እንድናስተካክል ማስተማሪያ ነው።ቅዱሳን መላዕክትን ማክበር ተገቢና በጣምም አስፈላጊ ሥርዐት ነው። በአፋችን ክርስቶስ አምላክ ነው እያልን በተግባር ግን ከክርስቶስ በላይ ለመላዕክት የመንፈጽማቸው ሃይማኖታዊ ተግብራት እንደ አይሁድ ክርስቲያኖች እኛንም ያስወቅሱናል።ብዙዎቻችሁ ታዝባችሁ ይሆናል ዛሬ ኢየሱስ ነው ሲባል ቤተክርስቲያን የሚሄደው ሰው በጣት የሚቆጠር ነው፤ ስለ ኢየሱስ ክብር ሲዘምርና የክርስቶስን ክብር ከፍ አድርጎ ሲገልጽ የሚውለው በጣም ጥቂት ነው።ዛሬ ገብርኤል ነው፣ወይም ሚካኤል ነው ሲባል ግን በየቤተክርስቲያኑ የሚተመውን ሕዝብ ስንመለከትና ከክርስቶስ በላይ ለመላዕክቱ ሲዘምር፣እልል ሲል፣ሲመሰክር የሚውለውን ሕዝብ ግን ስንመለከት ለክርስቶስ በልባችን የሰጠነው ቦታ ምን ያህል እንደሆነ በግልጽ ማሳያ ነው።እንደ አይሁድ በደሙ ካገኘነው ጽድቅ ይልቅ በሥጋዊ ሕይወታችን ያገኘናቸው ስጦታዎች እጅግ እንደላቁብን ማሳያ ነውና ሁላችን መዳንን እንወርስ ዘንድ ሕይወቱን በመስቀል የሰጠንን ጌታ ከማንም በላይ አልቀን በልባችን ዙፋን ላይ ልናነግሥ ይገባል። ክብርና ምሥጋና አምልኮና ጌትነት ለታረደው በግ ይሁን። መ/ር ታሪኩ አበራ ለሌሎችም ሼር አድርጉት
580
9
★የጥያቄው መልስ ይህ ነው።★ "ሁሉ፡መዳንን፡ይወርሱ፡ዘንድ፡ስላላቸው፡ለማገዝ፡የሚላኩ፡የሚያገለግሉም፡መናፍስት፡አይደሉምን ?"ዕብ 1፥14 † የዚህ መልዕክት ዋና ዓላማ ከዘለዓለም ሞትና እርግማን በደሙ ካዳናቸው ጌታ ይልቅ በአገልግሎት የተራዷቸውን መላዕክት በላቀ ክብር ይመለከቱ ለነበሩ የአይሁድ ክርስቲያኖች ማስተማሪያ ይሆን ዘንድ በቅዱስ ጳውሎስ የተጻፈ መልዕክት ነው።† ሰላም ለሁላችሁ ይሁን ።በቅድሚያ ለቀረበው ጥያቄ ተሳትፎ ያደረጋችሁ ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ የጥበብና የዕውቀትን ጸጋ ያብዛላችሁ። በርዕሱ ላይ የተቀመጠውን ኃይለ ቃል ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልዕክቱ ላይ ጽፎታል።የዕብራውያን መልዕክት የተጻፈው ከአይሁድ እምነት ወደ ክርስትና ለመጡ የመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ክርስቲያኖች ነው። አይሁድ በኤቦር ዕብራውያን፣በእስራኤል(ያዕቆብ) እስራኤላውያን፣በይሁዳ አይሁድ፣በፋሬስ ፈሪሳውያን፣በሳዶቅ ሰዱቃውያን እየተባሉ በቀደሙ አባቶቻቸው ስም የመጠራት ባህል አላቸው። በኤቦር ዕብራውያን የተባሉት ክርስቲያኖች ምንም እንኳ ክርስትናን እንደ አዲስ እምነት በቅዱሳን ሐዋርያት ስብከት ቢቀበሉም ቀድሞ የነበሩበት የይሁዲ እምነትና ባህል ቶሎ ከአዕምሯቸው ስላልወጣ ብዙ ነገር ይደበላለቅባቸው ነበር።በተለይ ነገረ -ድኅነት ቶሎ ሊገባቸውና ከውስጣቸው ጋር ሊዋሐድ አልቻለም ነበር።በክርስቶስ ደም እንዲሁ ያለዋጋ በጸጋ ያገኙትን ዘለዓለማዊ ድኅነት በእምነት መቀበል አቅቷቸው ጥለወት የመጡትን የይሁዲ እምነት ልማድ ይቀላቀልባቸው ነበር። ልክ ዛሬ አንዳንድ ክርስቲያኖች በክርስቶስ ደም ጽድቅን ያለዋጋ በጸጋ አግኝተሃል የምትጸድቀው ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሠራልህ የማዳን ሥራ ነው።ከአንተ የሚጠበቀው ይህንን በእምነት መቀበልና ይህ እምነትህን በመንፈስ ፍሬ መግለጥ ነው ሲባል አይደለም የምጸድቀው በራሴ ሥራ ነው እያለ የክርስቶስን ድካም ከንቱ ለማድረግ እንደሚሟገት ሁሉ አይሁድም በወንጌልና በክርስቶስ ላይ ያላቸው መረዳት ከኦሪቱ የቀደመ ዕውቀታቸው ጋር እየተደበላለቀ ይቸገሩ ነበር። መስዋዕተ ኦሪት ከመስዋዕተ አዲስ ይልቃል ብለው ያስቡ ነበር ፤ ከክርስቶስ ይልቅ ዓበይት ነቢያት፣ሊቃነ ካህናት ና አባቶቻቸው ይከብራሉ ብለውም ይቀበሉ ነበር፣ቅዱሳን መላዕክት ከክርስቶስ ይልቅ የላቀ ክብርና አገልግሎት እንዳላቸውም ያስቡ ነበር።በዚህ የተደበላለቀ መረዳት ውስጥ ለነበሩ ጀማሪ አማኞች ቅዱስ ጳውሎስ የጠራ የእምነት አመለካከት እንዲኖራቸው የዕብራውያንን መልዕክት ጽፎላቸዋል።መልዕክቱን የጻፈላቸው በ64 ዓ.ም ሮም ጣሊያን ለአገልግሎት ሳለ እንደሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይመሰክራሉ። ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክቱን እንዲህ በማለት ነው የጀመረላቸው፦ " ከጥንት፡ጀምሮ፡እግዚአብሔር፡በብዙ፡ዐይነትና፡በብዙ፡ጎዳና፡ለአባቶቻችን፡በነቢያት፡ተናግሮ፥ዅሉን፡ወራሽ፡ባደረገው፡ደግሞም፡ዓለማትን፡በፈጠረበት፡በልጁ፡በዚህ፡ዘመን፡መጨረሻ፡ለእኛ፡ተናገረን፤እርሱም፡የክብሩ፡መንጸባረቅና፡የባሕርዩ፡ምሳሌ፡ኾኖ፥ዅሉን፡በሥልጣኑ፡ቃል፡እየደገፈ፥ኀጢአታችንን፡በራሱ፡ካነጻ፡በዃላ፥በሰማያት፡በግርማው፡ቀኝ፡ተቀመጠ።" ይላል ዕብ 1፥1 ልብ በሉ! አይሁድ ከክርስቶስ በላይ በክብር አግዝፈው ይመለከቷቸው የነበሩ አባቶችንና ነቢያትን ሁሉ ቅዱስ ጳውሎስ በአንድነት ጠቅልሎ እኒህ ክርስቶስ እስኪ መጣ ድረስ እግዚአብሔር በልጁ የሚፈጽመውን ማዳን በልዩ ልዩ ዓይነት ምሳሌና መንገድ ያናግራቸው የነበሩ መንገድ ጠራጊዎች እንጂ እነርሱ የጽድቅ መንገድ እንዳልነበሩ በአጽንዖት ከገለጸላቸው በኋላ፤ በእግዚአብሔር የዘለዓለም ሐሳብ ውስጥ ዓለምን ለማዳን የቀጠራት ቀን ስትደርስ ግን የተነገረው ትንቢትና የተመሰለው ምሳሌ ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ እንደተፈጸመ፣ ሕዝብና አሕዛብን ሁሉ በፍቅር በሚወርሰው በልጁ የዓለም የድኅነት ምሥራች እንደተናገረ ያስረዳቸዋል። ይህ የነቢያት ትንቢትና የካህናት መስዋዕት ምሳሌ የሆነው ጌታ ከሁሉ የላቀ ክብር ያለው ሊቀ ካህን፣ በመለኮት ከአብ ጋር የሚተካከል የባሕርይ አምላክ ፣ዓለማትን በቃልነት የፈጠረ ደግሞም ዛሬም ዓለማትን በመለኮታዊ ቃል ደግፎ ያቆመ ኤልሻዳይ፣ የሰው ልጆችን ኃጢአት በደሙ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ የተቀመጠ የትንሳኤ በኲር ሕያው አምላክ መሆኑን ይነግራቸዋል። ቀጥሎ ደግሞ ከክርስቶስ ይልቅ ለመላዕክት ያላቀ ክብር ይሰጡ ነበረና እንዲህ ይላቸዋል፦ "ከመላእክት፡ይልቅ፡እጅግ፡የሚበልጥ፡ስምን፡በወረሰ፡መጠን፥እንዲሁ፡ከነርሱ፡አብዝቶ፡ይበልጣል።" ዕብ 1፥4 ይህም ማለት ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ የሚጠራ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በባህርይና በህልውና ተካክሎ የሚኖር የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ አምላክ ነው።መላዕክት ግን ከሥላሴ አካልና ባህርይ ጋር ምንም ተሳትፎ የሌላቸው የእግዚአብሔር አገልጋይ ተብለው የሚጠሩ ፍጡራን ናቸው።ስለዚህም ሥጋ የለበሰው ቃል እርሱም ክርስቶስ ከመላዕክት እጅግ አብዝቶ ይበልጣል። ሐዋርያው ይህንን ካለ በኋላ ነው ስለ ቅዱሳን መላዕክት መንፈሳዊ ተልዕኮ ሲገልጽ "ሁሉ፡መዳንን፡ይወርሱ፡ዘንድ፡ስላላቸው፡ለማገዝ፡የሚላኩ፡የሚያገለግሉም፡መናፍስት፡አይደሉምን ?" አለ ዕብ 1፥14 ይህ ማለት ሰው ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጸመለትን መዳን ይወርስ ዘንድ ለማገዝ የሚራዱ ተራዳህያን፣በጸሎትና በልመናቸው የሚያግዙ መንፈሳዊ ኃይላት፣ ከእግዚአብሔር ወደ ሰው መልዕክት በማምጣት የሚያገለግሉ፤ የሰዎችን ልመናና ጸሎት ደግሞ እግዚአብሔር እንዲቀበል በፊቱ ለልመና የሚቆሙ ታማኝ አገልጋዮች ናቸው ማለቱ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን መግለጽ የፈለገውም ቅዱስን መላዕክት በሰው ልጆች መዳን እጅግ የሚደሰቱ ፣የሚዘምሩ፣ በአንድ ኃጢአተኛ መመለስ ታላቅ ደስታን የሚያደርጉ አገልጋዮች ሲሆኑ አዳኙ፣አጽዳቂው ግን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ መሆኑን አውቀው የዕብራውያን ክርስቲያኖች የላቀውን ክብርና አምልኮ ለክርስቶስ ይሰጡ ዘንድ በጥበብ ያስተማረበት አንቀጽ ነው። መላዕክትን "መናፍስት" ያለበት ምክንያት ደግሞ እነርሱ ሥጋችንን ያልተዋሐዱ መንፈስ ሲሆኑ ክርስቶስ ግን የባሕርይ አምላክ ሳለ መለኮቱን ከሥጋችን ጋር አዋሕዶ በፍቅር የተዛመደን፣ባሕርያችንን ባሕርይው አድርጎ በምድራችን የተመላለሰ የፍቅር ጌታ መሆኑን ለመግለጽ ነው። መላዕክት ተፈጥሯዊ ባህርያቸው ከእሳትና ከመንፈስ ስለሆነ አንድም እንደ ነፋስ ረቂቅ እንደ እሳት ኃያላን ፍጥረታት ስለሆኑ መናፍስት ተብለው ይጠራሉ መናፍስት ለብዙ መጠሪያ ሲሆን መንፈስ ግን ለአንድ ነጠላ መጠሪያ ስም ነው። "መላእክቱን፡መንፈስ፡የሚያደርግ፥አገልጋዮቹንም፡የእሳት፡ነበልባል።ለዘላለም፡እንዳትናወጥ፡ምድርን፡በመሠረቷ፡ላይ፡መሠረታት።" መዝ 103፥4
477
10
★ በመንግሥት ቸልተኝነት ዛሬም የአማራ ሕዝብ በኦነግ እየተጨፈጨፈ ነው።★ ★ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ እባካችሁ ለወገኖቻችን ድምጻችንን እናሰማ አይቶ ዝም ማለት በደል ነው።★ በወለጋ ልዩ ስሙ ቶሌ ቀበሌ በሚባል ሥፍራ በርካታ ሴቶችና ህጻናት በአረመኔው ኦነግ ተጨፍጭፈዋል።ያለምንም በደላቸው አማራ በመሆናቸው ብቻ ዕድሜያቸውን ሙሉ ከኖሩበት መንደርና ቤታቸው ገብተው በሚዘገንን አገዳደል ገድለዋቸዋል።መንግሥት በዚህ አካባቢ እንዲህ ዓይነቱ ግድያ በተደጋጋሚ ሲፈጸም እየተመለከተ ለሕዝቡ አንዳችም ጥበቃ እያደረገ አይደለምና በሃገር ውስጥና በውጭ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እባካችሁ በወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግድያ አጥብቀን እንቃወም። ሼር በማድረግ ለሕዝብ አድርሱ መ/ር ታሪኩ አበራ
416
11
+3
No text...
524
12
Why out side the gate ? † የጥያቄው መልስ † "ኢየሱስ ደግሞ በገዛ ደሙ ሕዝቡን እንዲቀድስ ከበር ውጪ መከራን ተቀበለ " ዕብ 13፥12 ሰላም ለሁላችሁ ይሁን።ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም በሥጋ የተገለጠበት ዋነኛ ምክንያት ሥጋ ለባሽ የሆነ የሰው ዘር በሙሉ ፍጹም ድህነትና ዘለዓለማዊ ጽድቅ በእርሱ ቤዛነት ያገኝ ዘንድ ነው። በኦሪቱ የመሥዋዕት ሥርዐት የበግና የጊደሮች ደም ለኃጢአት ሥርየት የሚፈሰው በኢየሩሳሌም በሚገኘው የመገናኛው ድንኳን ነበር ።ማንኛውም ሰው ኃጢአት ቢሰራና ሥርየት ማግኘት ቢፈልግ በግ ይገዛና ወደ መገናኛው ድንኳን ወስዶ በካህኑ ፊት እየተናዘዘ እጁን በበጉ ላይ ይጫናል።በጉም የሰውዬውን ኃጢአት ይሸከምና ይሰዋል በበጉ ደም መምፍሰስም የግለሰቡ ኃጢአት ይቅር እንዲባል ተደርጎ የበጉ ደም በመሰዊያው ላይ ተረጭቶ ኃጢአተኛው ይቅርታ እንዳገኘ ተነግሮት ወደ ቤቱ ይመለሳል።የበጉ የማያስፉልጉ የሰውነት ክፍሎች ደግሞ ተሰብስበው ከኢየሩሳሌም ከተማ ውጪ እንዲቃጠሉ ይደረጋል። ዘሌ 4 ፥1-35፣ዘፀ 29፥1 ከከተማ ውጪ ያለው የቆሻሻ መጣያ ሥፍራ የመስዋዕቱ አመድ የሚደፋበት፣በለምጽ የተመቱ ሰዎችና በለምጽ የተያዙ ሰዎች ያረከሷቸው ተብለው የሚታመኑ ዕቃዎች ሳይቀር ተሰብስበው የሚጣልበት ሥፍራ ነው። ዘሌ 14 ፥35- 45፡፣ዘኁ 5፥1 ይህ ከከተማዋ በር ውጪ ያለው ሥፍራ በኃጢአት የረከሰ ሥፍራ ተብሎ የሚታወቅ ነው። ክርስቶስ ከከተማዋ ውጪ የተሰቀለበት ምክንያት ሁለት ነው አንደኛው ኃጢአትን ራሱን ለመግደል ነው።የክርስቶስ ደም የፈሰሰው ኃጢአተኞችን ለማንጻት ብቻ ሳይሆን ኃጢአትን ራሱ አቅመ ቢስ አድርጎ ከደሙ ኃይል በታች የሆነ ምውት ያደርገው ዘንድ ነው። በመስቀል ላይ የፈሰሰው የክርስቶስ ደም ሕያውና ቅዱስ ደም ስለሆነ ኃጢአትና ርኩሰት ፣በደልና ርግማን የተባሉ ነውሮች ባሉበት ቦታ ከከተማዋ ውጪ ተሰቅሏል።ለዚህ ነው የሞት መውጊያ ተሰብሯል ተብሎ የተጻፈው የሞት መውጊያ ብረት ኃጢአት ነው።1ቆሮ 15፥ 56።ጌታ የኃጢአትን ኃይልና ስልጣን ነው በደሙ ያደቀቀው፣በአዲስ ኪዳን ማንኛውም ኃጢአት ከክርስቶስ ደም በታች ነው።የክርስቶስን ደም አልፎ የሚወቅሰን፣የሚከሰን አንዳችም ኃጢአት የለም። እግዚአብሔር ለፍርድ እንኳ ቢፈልገን ከእኛ በደልና ኃጢአት ይልቅ በፊቱ ገዝፎና ልቆ የሚታየው ያመንበት የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው።"የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻል" ተብሎ ተጽፏል።1ዮሐ 1፥7 በኦሪቱ ጊዜ ግን እንዲህ አልነበረም ከሰዎች ጽድቅ ይልቅ ገዝፎ የሚታየው በደላቸው ነበር።የበግና የጊደሮች ደም ሰዎችን ለጊዜው ያነጹ ነበር እንጂ ኃጢአትን ራሱን የመግደልና በፍርድ ዙፋን ፊት ኃጢአትን አቅም ቢስ የማድረግ ኃይል አልነበራቸው።ለዚህ ነው ነቢዩ ኢሳይያስ “ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው።” በማለት መሪር ሐዘኑን የገለጸው።ኢሳ 64፡6 የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ሥጋ ተዋሕዶ ሲገለጽ ግን ዋነኛ ዓለማው በስሙ አምነው በመስቀል ላይ የፈጸመውን ቤዛነት በእምነት ለተቀበሉ ሁሉ መዳንን እንዲያው ያለዋጋ በጸጋ ይሰጥ ዘንድ ስለሆነ ይህ አባታዊ ፍቅሩንና ምትክ የሌለውን የመስቀል ውለታውን ዕለት ዕለት የሚያስቡ ሰዎች ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆነ በልባቸው ስለሚሳል ኃጢአትን አብዝተው ይጸየፏታል፣ርኩሰትን አምርረው ይጠሏታል፣ከክፉ የኃጢአት ግብር ጋር ለመተባበር ነፍሳቸው ፈቃደኛ አትሆንም።ምናልባት በሥጋ ድካም በኃጢአትና በበደል እንኳ ቢወድቁ ፈጥነው በንስሐ ወደ ክርስቶስ ሲመለሱ በእምነት የተቀበሉት የደሙ ኃይል ኃጢአታቸውን አቅመ ቢስ አድርጎ ከፍርድና ከኩነኔ ያድናቸዋል። ስለዚህ ክርስቶስ ከከተማ ዉጪ ተሰቀለ ተብሎ የተነገረበት ምክንያት ኃጢአትንና የኃጢአትን ኃይል በሞቱ መግደሉን ለማብሰር ነው።ክብር ለስሙ ይሁን። ሁለተኛው ክርስቶስ ከከተማ ውጪ የተሰቀለበት ምክንያት ከእንግዲህ በመገናኛው ድንኳን ዕለት ዕለት በሚሰው በበጎችና በጊደሮች ደም መታረቅ አበቃ ለዓለሙ ሁሉ የሚሆን አንድና ዘለዓለማዊ መስዋዕት አማናዊው የእግዚአብሔር በግ እኔ መጥቻለሁ ሲል ነው። በኦሪቱ የመሥዋዕት ሥርዐት ሊቀ ካህኑ በዓመት አንድ ጊዜ ስለራሱና ስለ ሕዝቡ ኃጢአት የበግ መስዋዕት በመሰዋት የበጉን ደም ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ይዞ በመግባት ምህረትና ይቅርታን ይለምናል።ሕዝቡ ግን ኃጢአት በሰራ ቁጥር በግ እየነዳ ስለሚሄድ በየቀኑ በመገናኛው ድንኳን በግና ፍየል ይዞ የሚመጣ ኦሪታዊ እጁን በበጉ ላይ እየጫነ በመናዘዝ መስዋዕት እያሳረደ ይሄዳል።ክርስቶስን ይህንን ሁሉ ስርዓትና የእንስሳት እልቂት ለማቆም አንድ ጊዜ ለዓለሙ ሁሉ የሚበቃ ዘለዓለማዊ መስዋዕት ሆኖ ከከተማው ውጪ ተሰውቷል።ከከተማው ውስጥ ቢሰቀል ኖሮ ዓለም የዳነው በክርስቶስ ደም ሳይሆን እኛ በሰዋነው የበግና የጊደሮች ደም ነው ብለው እንዳይመጻደቁ ጌታ ከከተማ ውጪ ተሰቀለ በሌላም በኩል ጌታ በጎችና ጊደሮች በሚሰውበት በከተማው ውስጥ ተሰቅሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ የክርስቶስ ደም ብቻ ሳይሆን የበጎችም ደም አብሮ ለመስዋዕት መቅረብ አለበት የሚሉ ተከራካሪዎች ይነሱ ነበር።ልክ በዘመነ ሐዋርያት አይሁድ ወንጌል እንበለ ኦሪት ጥምቀት እንበለ ግዝረት አትረባም አትጠቅምም እያሉ የሐዋርያትን ትምህርት እንደ ተቃወሙ ማለትም ወንጌል ያለ ኦሪት ጥምቀት ያለ ግዝረት አያድንም እንዳሉ መስዋዕተ ክርስቶስ እንበለ መስዋዕተ በግዕ አይጠቅምም ባሉ ነበር።ያለ በግ መስዋዕት የክርስቶስ ደም ብቻውን አይድንም እያሉ በክርስቶስ ደም ላይ ደባል የሚፈጥሩ ሰዎች እንዳይነሱ ክርስቶስ ከከተማ ውጪ ተሰቅሎ አንዱና ብቸኛው የዓለሙ ሁሉ አዳኝ እርሱ ብቻ መሆኑን አሳይቶናል።ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት ሙሉ ሐሳቡን የገለጸው።ዕብራውያን 12 ከቁጥር 11 ጀምሮ "ሊቀ፡ካህናት፡ስለ፡ኀጢአት፡ወደ፡ቅድስት፡የእንስሳዎችን፡ደም፡ያቀርባልና፤ሥጋቸው፡ግን፡ከሰፈሩ፡ ውጭ፡ይቃጠላል። 12፤ስለዚህ፥ኢየሱስ፡ደግሞ፡በገዛ፡ደሙ፡ሕዝቡን፡እንዲቀድስ፡ከበር፡ውጭ፡መከራን፡ተቀበለ። 13፤እንግዲህ፡ነቀፌታውን፡እየተሸከምን፡ወደ፡ርሱ፡ወደሰፈሩ፡ውጭ፡እንውጣ፤ 14፤በዚህ፡የምትኖር፡ከተማ፡የለችንምና፥ነገር፡ግን፥ትመጣ፡ዘንድ፡ያላትን፡እንፈልጋለን። 15፤እንግዲህ፡ዘወትር፡ለእግዚአብሔር፡የምስጋናን፡መሥዋዕት፥ማለት፡ለስሙ፡የሚመሰክሩ፡የከንፈሮችን፡ ፍሬ፥በርሱ፡እናቅርብለት።" ወገኖቼ ክርስቶስ ዛሬም በሕያው ፍቅሩ ስለሚፈልገን ከዓለም ርኩሰትና ከሥጋ ምኞት ተለይተን ወደ ሕይወታችን ጠባቂና ወደ መዳናችን ራስ ፈጥነን እንውጣ በእርሱ ዘንድ ፍጹም ሰላምና እረፍት አለ።የክርስቶስ መሆንና ለስሙ ክብርን እየሰጡ እርሱን ከፍ ከፍ ማድረግ አይሁዳዊ ጠባይ በደማቸው ከተተከለባቸው የስም ክርስቲያኖች ብዙ ነቀፌታና ከንቱ ዘለፋ ቢኖርም እኛ ግን የእምነታችን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት የሆነው ክርስቶስን ተመልክተን ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።በጉ መብራቷ የሆነላት የሰማዊቱ ኢየሩሳሌም ወራሾች ነንና ለበጉ የሚገባውን አምልኮና ዝማሬ ዕለት ዕለት በፊቱ እንሰዋለት። ራዕ 21፥21 ክብርና ምሥጋና አምልኮና ውዳሴ ለታረደው በግ ይሁን። መ/ር ታሪኩ አበራ ለሌሎችም ሼር አድርጉት
452
13
ክርስቶስ በባሕርይው ሕያውና ፍጹም ዘለዓለማዊ አምላክ ነው፤ በመለኮታዊ ባሕርይው ሞት በመንግስቱም ሽረትና ውላጤ የሌለበት አልፋና ዖሜጋ ነው፤ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር ከባሕርይ አባቱ ከአብ እና ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በቅድምና በቃልነት የነበረ ግዙፉንና ረቂቁን ዓለም የሚታየውን እና የማይታየውን ፍጥረት በቃልነት የፈጠረ ጊዜ የማይቆጠርለት የጊዜ ፈጣሪ ድንቅ አምላክ ነው። ለድኅነተ ዓለም በአጭር ቁመትና በጠባብ ደረት ተወስኖ በሥጋ የተገለጠ፣በመንፈስ የጸደቀ፣ለመላዕክት የታየ፣በአሕዛብ የተሰበከ፣በዓለም የታመነ፣በክብር ያረገ ደግሞ ሕያው ሆኖ ለዘለዓለም የሚኖር ኤልሻዳይ ነው።የቃል ገንዘብን ከሥጋ ጋር ያዋሐደ የሥጋንም ገንዘብ ከቃል ጋር ያዋሐደ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ ጌታ ነው። በዕብ 7፥28 ላይም «ለዘለዓለም ፍጹም የሆነው ልጅ» በሚል ኃይለ ቃል የተገለጸው ይህ ለአኗኗሩ «እስከ» የሚባል ዘመን የሌለው ድንቁ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ስለዚህ ክህነቱም ከእርሱ ጋር አብሮ የሚኖር ዘለዓለማዊ ስለሆነ በዕለተ አርብ አንዴ ለዘለዓለም የፈጸመው የክህነት አገልግሎትም ለዘለዓለም ሲያስታርቅና ሲያድን ይኖራል መጽሐፍ እንዲህ ይላል«እርሱ ግን ለዘለዓለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።»ዕብ 7፥24 እዚህ ላይ ሁላችን ልናስተውለው የሚገባ ሁለት ድንቅ ቃል አለ «ሲያማልድ ይኖራል» የሚለውና «ያድናል» የሚሉትን ቃላት በጥልቀት ልንመረምር ይገባል፤ ሁለቱንም የሚፈጽመው አንዱ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ ጌታ ነው፤ በሰዎች አዕምሮና በመላዕክት ኅሊና ተመርምሮ በማይደረስበት ረቂቅ ተዋሕዶ ሁለት አካልን አንድ አካል ሁለት ባሕርይን አንድ ባሕርይ አድርጎ የሚኖር ዕፁብ ድንቅ ጌታ ነው፤ ስለሆነም በሥጋው ወራቱ ከብርቱ ጩኽትና ዕንባ ጋር ያቀረበው ምልጃ ስለ እነርሱም የተባሉትን ከክርስቶስ መወለድ በፊት የነበሩትንና በዘመኑ የነበሩትን ኦሪታውያን እንዲሁም ዛሬም ድረስ በእነርሱ መንገድና አስተሳሰብ ያሉትን ሁሉ አምነው እስከመጡ ድረስ ከእግዚአብሔርነቱ ጋር ሲያማልድ ይኖራል፤በክርስቶስ ቤዛነትና አዳኝነት አምነው በስሙ የተጠመቁትን ደግሞ ለዘለዓለም ሲያድናቸው ይኖራል።ምልጃው አንድ ጊዜ የተፈጸመ ነገር ግን ለዘለዓለም ሕያው መተረቂያ ሆኖ የቆመ የዘለዓለም የኃጢአት ማስተስሪያ ነው። ሮሜ 3፥25 «ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ» ተብሎ ተጽፏል። ዕብ 9፥24 በሰዓታት ጸሎታችንም ላይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ ሲል አስቀምጦታል« ሊቀ ካህናት ዘይቀውም ሎሙ ለቅዱሳን በደብተራ ስምዕ እንተ እግዚአብሔር ተከላ ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ» «እግዚአብሔር በተከላት በምስክር ድንኳን /በሰማያዊቷ መቅደስ/ ለአማኞች የሚቆምላቸው ሊቀ ካህናት እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።» በቤተክርስቲያናችን የነገረ ሃይማኖት ማስተማሪያ በሆነው ታላቅ መጽሐፍ ሃይማኖተ አበው ላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል « ከእርሱ በቀር ብቻውን ኃጢአትን ማስተስረይ የሚቻለው የታመነ አስታራቂ ማነው? ለማስታረቅ ኃጢአትን ለማስተስረይ ያቀረበው መስዋዕትስ ምንድነው? መስዋዕት ለመሆን የነሳው ሥጋውን ብቻ ነው እንጂ. ..እርሱ ወደዚህ ዓለም ወርዶ ባህርያችንን ባህርይ አድርጎ ሊቀ ካህናት (አስታራቂ) ሆነን።» ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ ምዕ.63፥14፣16 ክርስቶስ ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀን ስንል ሁለት የተለያዩ አካላት ኖረው አንዱ ታራቂ ሌላው አስታራቂ፣አንዱ የበላይ ሌላኛው የበታች መስሎን እንዲህ ዓይነት የተሳሳተ አመለካከት ፈጽሞ በሕሊናችን ሊሳል አይገባም፤ እግዚአብሔር የሚለው ስም የአብ፣ የወልድ፣ የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት መጠሪያ መለኮታዊ ስማቸው ነው፤ እግዚአብሔር አንድ ነው አብ የምንለው ልብ ፣ወልድ የምንለው ቃል፣ መንፈስ ቅዱስ የምንለው እስትንፋስ ነው፤ በተለየ አካሉ ቃል ሥጋ ሆኖ በምድራችን ተገልጦ እስከ መስቀል ድረስ ለድኅነተ ዓለም ራሱን ዝቅ አድርጎ ቢጓዝም ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ ከስልጣን ዝቅ አላለም፤ የፀሐይ ብርሃን ወደምድር ሲወርድ ከፀሐይ አካል ፈጽሞ እንደማይለይ ሁሉ ቃል ሥጋ ሆኖ ወደ ምድር ሲመጣና ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር በምድራችን ሲመላለስ ከዘባነ ኪሩብ ከየማነ አብ ለዓይን ጥቅሻ ያህል እንኳ አልተለየም ፤ስለዚህ እግዚአብሔር በክርስቶስ ኢየሱስ ዓለሙን ከራሱጋር አስታረቀ ተብሎ የተጻፈው ቃል ረቂቁ መለኮት በተዋደው በግዙፉ ሥጋ በኩል ዓለሙን ከራሱ ጋር ማስታረቁን የሚያስረዳ ድንቅ የሥጋዌ ምሥጢር ነው።ታራቂም፣ አስታራቂም፣ መታረቂያም አንዱ ራሱ እግዚአብሔር ነው። 3. #ኢየሱስ ክርስቶስ በመሐላ የጸና ሊቀ ካህናት ነው። ክፍል 2 ይቀጥላል። መ/ር ታሪኩ አበራ ሼር በማድረግ ሌሎችም እንዲማሩበት አድርጉ።
603
14
እንደ ክፉ ሥራቸው ፍዳቸውን ክፈላቸው መዝ 93 || መምህር ዘበነ ለማ https://youtube.com/watch?v=oVJTtwuORa0&feature=share
1 005
15
https://youtu.be/PHDDjwZ2BLw
1 062
16
No text...
1 073
17
የአስመራጭ ኮሚቴው ዋና መስፈርት፣ የቋንቋ ችሎታ ሳይኾን፣ የብሔር ማንነት መኾኑ ምንም ያህል ችግር ቢኾን፣ ከዚያ በላይ ሥራውን አጠያያቂ የሚያደርገውና ተቀባይነት ሊያሳጣው የሚችለው፣ ለካህናት እና ለምእመናን ምስክርነት ድብቅ ማድረጉ ነው፡፡ ይህ አድራጎቱ፣ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያንና በአበው ትውፊታዊ ልማድ የተደገፈ አይደለም፡፡ ተጠቋሚዎችን መርጦ እንዲያቀርብ በሠየመው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤም፣ ዝርዝራቸውን ይፋ እንዳያደርግ የተሰጠው መመሪያም የለም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ለኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የተጠራው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፣ ነገ ሰኞ፣ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. የመክፈቻ ጸሎቱን በማካሔድ፣ ከነገ በስቲያ፣ በአስመራጭ ኮሚቴው ከሚቀርቡለት 18 ተጠቋሚ ቆሞሳት ዘጠኙን፣ በምስጢራዊ ድምፅ አሰጣጥ በመምረጥ፣ ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. ክፍት በኾኑና አንገብጋቢ ችግር ባለባቸው፣ ሰባት የኦሮሚያ ክልል እና ኹለት የደቡብ ክልል አህጉረ ስብከት ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ይዘጋጃል፡፡ በተሾሙባቸው አህጉረ ስብከት ለሚገኙ ካህናት እና ምእመናን፣ መንፈሳዊ አባት እና መሪ ሊኾኑ የሚመረጡ ኤጲስ ቆጶሳት፣ በዕውቀታቸው እና በሕይወታቸው የተመሰከረላቸው ሊኾኑ ይገባል፡፡ መንጋውን ለመጠበቅ፣ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል በሚሾሙ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ላይ፣ ምእመናን ያላቸው ሱታፌ ከፍተኛ ነው፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን የመጨረሻ የወሳኝነት ሥልጣን ባገናዘበ መልኩ፣ ተሿሚዎች ይገባቸዋል ተብለው ለሹመቱ ብቁ እንደኾኑ የሚረጋገጠው፣ በምእመናን ምስክርነት ነው፡፡ ከሥርዐት መጻሕፍት አንዱ መጽሐፈ ቀሌምንጦስ፣ ኤጲስ ቆጶስ ኾኖ እንዲሾም የመረጡት ሰው፣ ሹመቱ የሚሰጠው በሀገረ ስብከቱ ሰዎች ስምምነት ይኹን፤ ይላል፡፡ ሢመተ ኤጲስ ቆጶስ፥ ለሕዝብ በቁዔት እንጂ ለግል ጥቅም ስላልኾነ፣ የሚሾምለት ሀገረ ስብከት ሕዝብ፣ ይገባቸዋል ብሎ ምስክርነት መስጠት እና በአባትነት መቀበል አለበት፡፡ +++ ድብቁ አፈትልኮ ወጣ! በአንጻሩ፣ ባለፈው ዐርብ በተካሔደው ሳምንታዊው የቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ፣ ስለ ኮሚቴው የሥራ ክንውን ማብራሪያ ከሰጡት ሰብሳቢው ብፁዕ አባ ሳዊሮስ ግልጽ እንደኾነው ግን፣ በቀጥታ ለቅዱስ ሲኖዶሱ አቅርቦ ከማስመረጥ በቀር፣ ከዚያ በፊት ለካህናት እና ለምእመናን እንደማያሳውቅ አቋም ተይዞበታል፡፡ ይህን ተከትሎ፣ በመረጃ አነፍናፊዎች በተደረገ ጥረት፣ አስመራጭ ኮሚቴው፣ በዋናነት የብሔር ማንነትን መሠረት አድርጎ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጥቆማ ብቻ ያለግልጽ መስፈርት በድብቅ ሲሰበሰብ የቆየውና ያለካህናት እና ምእመናን ምስክርነት ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ለማቅረብ ያዘጋጀው፣ የ20 ተጠቋሚ ቆሞሳት ስም ዝርዝር አፍትልኮ ወጥቷል፡፡ ይህንም ዝርዝር ከአንዳንድ የመጀመሪያ ደረጃ መረጃዎች ጋራ ይፋ ማደረግ አስፈላጊ ኾኖ ተገኝቷል፡፡ አፈትልኮ የወጣው የቆሞሳቱ ዝርዝር ሲታይ፣ የጥቅመኝ ልጥቀምኽ፣ የእከከልኝ ልከክልኽ ዐይነት ቅርበት እና ጥቅመኝነት የገነነበት እንደኾነ ግልጽ ነው፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው፣ በተጠቋሚዎቹ ትምህርት እና ግብረ ገብነት ባይሸማቀቅባቸውና ቢተማመንባቸው ኖሮ፣ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እና ወልዳ ዳንዲ አቦቲን ጨምሮ፣ በርካታ የአገልግሎት ማኅበራት፣ የቆሞሳቱን ስም እና ማንነት ይፋ እንዲያደርግ ሲጠይቁ፣ በቀኖናው እና በሕጉ መሠረት ምላሹ አዎንታዊ እና ፈጣን በኾነ ነበር፡፡ ከዝርዝሩ እንደሚታየው፣ የተመሰገኑ ጥቂቶች ያሉበትን ያህል በሚበዙት፡- ሱሰኛ ሰካሮች፣ ንጽሕ የጎደላቸው ዘማውያን፣ ደናግል ያልኾኑ ወላድያን፣ መፍቀሬ መናፍቃን የኾኑ ሕጹጻን፣ ሕገ ወጥ ደላሎች፣ በአስተዳደራቸው የተመረሩ ምእመናን ከሓላፊነት ያበረሯቸው አማሳኞች…ስላለመኾናቸው በካህናት እና ምእመናን ሐቀኛ ምስክርነት ምርመራ ሊጣራባቸው ይገባል፡፡ ከቅዱስ ሲኖዶስ ምርጫ አስቀድሞ፣ ስማቸው እና አገልግሎታቸው ለካህናት እና ምእመናን ተገልጾ፣ በታችኛው የክህነት ማዕርግ ሳሉ ስለነበራቸው ሕይወት፣ ትምህርት፣ አገልግሎት፣ ግብረ ገብነት ሊመሰከርላቸው ወይም ሊመሰከርባቸው ያስፈልጋል፡፡ ከኮሚቴው አባላት አንዱ፣ “ያለማሳወቅ መብት አለን፤ ማን ነው የሚያዝዘን?” እንዳሉት አይዶለም!! ለቤተ ክርስቲያን ሊሾሙላት እንጂ ሊሾሙባት አይገባምና ይህ መረጃ የሚደርሳችኹ እና የምታውቋቸው ካህናት እና ምእመናን ኹሉ በአፋጣኝ ድምፃችኹን ለቅዱስ ሲኖዶስ አካላት ልታሰሙ ይገባል፡፡ ©አደባባይ ሚዲያ
1 007
18
ያፈተለከ መረጃ፡- በድብቅ ተጠቁመው ለማዕርገ ኤጲስ ቆጶስ ሹመት እንዲቀርቡ በአስመራጭ ኮሚቴው በምስጢር የተያዙ ቆሞሳት ዝርዝር አፈትልኮ ወጣ!! (ሰኔ 25/2015 ዓ.ም.) ግልጽ የመመዘኛ መስፈርት! በጥቆማ የተመለመሉትንና ከተመለመሉት በመስፈርቱ ተጣርተው ለምርጫ የታጩትን ከቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ አስቀድሞ ለካህናት እና ለምእመናን የማሳወቅ ሥራ አልተሠራም!! በሃይማኖት፣ በምግባር እና በዕውቀት ሕጸጻቸው የተነሣ፣ የሚታወቅ ነውር እና ነቀፋ ያለባቸውን፣ ይቅርና ለማዕርገ ኤጲስ ቆጶስነት ላሉበት የክህነት መዓርግ ያልተገቡትን፣ የመንፈስ ቅዱስን ሹመት በመደለያ እና በወገንተኝነት ለማግኘት የሚማስኑትን በዕጩነት ማቅረብ፣ ቤተ ክርስቲያንን ክፉኛ መበደል እንደኾነ ለአፍታም መዘንጋት የለበትም!! ** ከማክሰኞ ሰኔ 27 ቀን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ምርጫ አስቀድሞ፣ ካህናት እና ምእመናን ኹሉ፣ ስለ ተጠቋሚዎቹ የሚያውቁትን በይፋ እና በሐቅ መግለጽ መንፈሳዊ ግዴታቸው ነው!! #መንደርደሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ በግንቦት 2015 ዓ.ም. በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤ ስብሰባው፣ ዘጠኝ ዐዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ሰባት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ያሉበት አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙ ይታወሳል። ዐዲስ ኤጲስ ቆጶሳት የሚመደብባቸው ዘጠኙ አህጉረ ስብከት፡- ምዕራብ ወለጋ፣ ምሥራቅ ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ምዕራብ አርሲ(ሻሸመኔ)፣ ድሬዳዋ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ፣ ቡኖ በደሌ፣ ጌዴኦ፣ ቡርጂ እና አማሮ፣ እንዲሁም ዳውሮ ኮንታ አህጉረ ስብከት ናቸው፡፡ የዕጩ ኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴው አባላት፡- ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በሰብሳቢነት፣ ብፀዕ አቡነ ሕርያቆስ በጸሐፊነት ሲመሩት፣ ብፁዕ አቡነ ኄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እና ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በአባልነት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ደግሞ በአስረጅነት ይገኙበታል፡፡ ባለፈው ወር ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ሥራውን በይፋ የጀመረው አስመራጭ ኮሚቴው፣ ከሰኔ 1 ቀን 2015 ዓ.ም. አንሥቶ ደግሞ፣ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ብቻ ተጠቋሚ ቆሞሳትን በደብዳቤ እየተቀበለ ምልመላውን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ ኮሚቴው የተሰጠውን ሥራ ማጠናቀቁንና ሰኔ 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ሪፖርት ማቅረቡን የጠቀሰው የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፥ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ፣ ከሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እንዲገኙ በቋሚ ሲኖዶስ የተወሰነውን ጥሪ አስተላልፏል። በዚኽ ምልዓተ ጉባኤ፣ አስመራጭ ኮሚቴው፥ በዘጠኙ የኦሮሚያ እና የደቡብ ክልሎች አህጉረ ስብከት የሚመደቡ ዘጠኝ ተሿሚዎችን ለመለየት የመጨረሻዎቹን 18 ዕጩዎች እንደሚያቀርብ ታውቋል፡፡ ለየሀገረ ስብከቱ ጥንድ ጥንድ ኾነው የቀረቡት ተጠቋሚዎቹ፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን መሠረት፣ በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ምስጠራዊ ድምፅ አሰጣጥ በድምፅ ብልጫ ይመረጣሉ፤ እኩል ድምፅ ያመጡ ቢገኙ፣ በስማቸው ላይ ጸሎት ተደርጎ ዕጣው የወደቀለት ይመረጣል፡፡ በምርጫው ማግሥት፣ የተመረጠትን ቆሞሳት በልዩ ልዩ ሥልጠናዎች የማዘጋጀት ሥራ ሲከናወን ቆይቶ፣ ለሹመቱ በተወሰነው ቀን፣ ተገቢው ጸሎት ተደርጎ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አንብሮተ እድ፣ “ብፁዕ አባ እገሌ ኤጲስ ቆጶስ ዘሀገረ እገሌ” እየተባሉ ማዕርገ ኤጲስ ቆጶስነት ይሾማሉ፡፡ ከጥቆማ እስከ ምርጫ የቤተ ክርስቲያን አካላት ሱታፌ ጠቅላላ ሒደቱ ይህ ኾኖ ሳለ፣ ይህ ጽሐፍ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ አስመራጭ ኮሚቴው፥ በዕጩነት ስለተጠቆሙት ቆሞሳት ስም እና ማንነት፣ ከደረሱት ጥቆማዎች ውስጥ እያጣራ ስለሚያሳልፍበት መስፈርት፣ አንዳችም የገለጸው ነገር የለም። አስመራጭ ኮሚቴው፥ የኤጲስ ቆጶሳትን ምርጫ ምሥጢራዊ ማድረጉ፣ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን፣ በተቀደሰው የአበው ትውፊት የሚደገፈም የሚበረታታም ተግባር አይደለም። የኤጲስ ቆጶስ ሢመት፣ ለክርስቶስ መንጋ ጥበቃ ተግባር የሚሰጥ ሰማያዊ ሓላፊነት እንጂ፣ ለምድራዊ ክብር እና ጥቅም ቋምጠው የሚቀበሉት ሥጋዊ ሹመት አይደለም፡፡ ምንም እንኳን ወደ ምርጫ የተገባው በፖለቲካዊ ግፊት ጭምር በመኾኑ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው ቢታወቅም፤ የአካባቢውን ባህል እና ቋንቋ የሚያውቁ አባቶች መታጨት እንዳለባቸው ቢታመንበትም፣ አንድያውን ወደለየት የደም እና አጥንት ቆጠራ ገብቶ ቤተ ክርስቲያንን ለፈተና አሳልፎ የሚሰጥ ተግባር እንዳይፈጸም ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል። የሚመረጡት አባቶች፥ ሃይማኖት ከምግባር የተስማማላቸው፣ የተማሩ፣ በገዳማዊ ሕይወት የተፈተኑ፣ መንጋውን በመንፈሳዊ ዕውቀት የሚያጸኑና ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ፣ የአስተዳደር ችሎታ እና ልምድ ያላቸው ሊኾኑ ይገባል። በርግጥ እንዲህ ዐይነት አባቶች በቀላሉ የሚገኙ አይደሉም፤ ቢገኙም አይገባንም ብለው ይሸሻሉ እንጂ ሹሙን ብለው የሿሚዎችን ደጅ አያጣብቡም። የጽድቅ ሕይወታቸው የተገለጠ ቢኾንም፣ በብዙኀኑ እንዳታወቅባቸው ራሳቸውን ስለሚሰውሩ ታዋቂዎች አይደሉም። ስለኾነም፣ ከጥቆማ ጀምሮ እስከ ምርጫ ድረስ፡- ገዳማውያን አባቶች፣ ጉባኤ ዘርግተው የሚያስተምሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ማኅበረ ምእመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ሊጠየቁና ሊሳተፉበት ይገባቸዋል። ይህም፣ ደጋግ አባቶችን ከፍ ወዳለው ማዕርግ ለማምጣት ከማገዙም በላይ፣ በተፃራሪው፣ ለዚኽ መዓርግ የማይበቁትን ለመለየትም ይጠቅማል። በተለይም፣ የሚታወቅ ነውር እና ነቀፋ ያለባቸውን፣ ላሉበት የክህነት መዓርግ ተገቢ አይደሉም ተብለው በሃይማኖት፣ በምግባር እና በዕውቀት የሚነቀፉትን፣ ሹመት ለማግኘት ጉቦ እና መደለያ የሚሰጡትን በዕጩነት ማቅረብ፣ ቤተ ክርስቲያንን መበደል እንደኾነ፣ ለአፍታም መዘንጋት የለበትም። ቋንቋዊ ማንነትን ብቻ መሠረት አድርገው፣ ለኮታ ማሟያ ለመግባት የሚቋምጡ ሹመት ፈላጊዎች፣ በሠፈርተኝነት አሳብ የእኔ የሚሉትን ለማስመረጥ የሚደክሙ አባቶች እንዳሉ በሚገባ እናውቃለን። ይህ፣ ፈጽሞ ከአባትነት የማይጠበቅ ክፉ ግብር ነው። አስመራጭ ኮሚቴው፣ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚስፋፋበትን አግባብ ብቻ መሠረት በማድረግ፣ ለአገልግሎቱ የሚመጥኑ መነኰሳትን በዕጩነት ከማቅረብ ባለፈ፣ በአንድም በሌላም መልኩ ግፊቶችን ተቋቁሞ ሥራውን መፈጸም ይጠበቅበታል። ዝርዝራቸውን ይፋ እንዳያደርግ ለኮሚቴው የተሰጠ መመሪያም የለም ኮሚቴው፣ ሥራውን አጠናቅቆ ለቅዱስ ሲኖዶስ ከማቅረቡ በፊት፣ ለኮሚቴው የደረሱ ጥቆማዎች፣ ተጠቋሚዎቹን ያጠራበትን መስፈርት፣ የቀሩ ሥራዎችንና ከምእመናንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሚሻቸውን ድጋፎች ግልጽ ማድረግ ይገባዋል። ይህን በመገንዘብ፣ የዕጩ ኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ፣ ግልጽ መስፈርት እንዲያስቀምጥ፣ በዚያም መሠረት መልምሎ እና አጣርቶ የለያቸውን ተጠቋሚዎች ለካህናት እና ለምእመናን በይፋ እንዲያሳውቅ፣ በወሳኝ የቤተ ክርስቲያን አደረጃጀቶች፣ ቀኖናውንና ሕጉን መሠረት ያደረገ ጥያቄ በልጅነት መንፈስ ቢቀርብለትም፣ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሏል፡፡
784
19
እችላለሁ ካልህ ትችላለህ!? ክርስቲያን "ሁሉን እችላለሁ" ይላል ወይ? አዎ ይላል:: ግን ከፊቱ የሚቀር ሐረግ አለ:: "ኃይልን በሚሠጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ" (ፊል. 4:13) በራስ መተማመንም እግዚአብሔርን ከለላ በማድረግ ብቻ ነው:: "በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን በራስህም ማስተዋል አትደገፍ" ምሳ. 3:5 ስለዚህ በእግዚአብሔር መታመን በራስ ከመታመን በላይ ነው:: Confidence ከሚለው ይልቅ Godfidence የሚል አዲስ ቃል ሳይገልጸው አይቀርም:: የተፈጥሮ ጸጋህን እወቅ በሚል በጎ መነሻ የተጀመረው "ነኝ ካልኩ ነኝ" የሚለው መፈክር አሁን ላይ ምድርን እየበጠበጠ ይገኛል:: ሰዎች "ውብ ነኝ ጎበዝ ነኝ ፤ ደፋር ነኝ" ብለው ራሳቸውን በኃይል እንዲሞሉና አቅማቸውን እንዲረዱ ማድረጉ ባልከፋ ነበር:: መጽሐፍ ቅዱስ ላይም "ጥቁር ነኝ ግን ውብ ነኝ" "ድሆች ስንሆን ሌሎችን ባለጸጎች እናደርጋለን" "እንገፋለን እንጂ አንወድቅም" "እንጨነቃለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም" የሚሉ ሰው ከድካሙ ውስጥ ኃይሉን እንዲያይ የሚያደርጉ በጎ ቃላት አሉ:: "ውብ ነኝ ፤ ደፋር ነኝ ፤ጀግና ነኝ" የሚለው ግን ገደብ አልፎ ወንዱ "ሴት ነኝ" ሴትዋ "ወንድ ነኝ" እስከማለት ደረሰ:: I identify as a woman የሚሉ ጎረምሶች I identify as a man የሚሉ ልጃገረዶች ተነሡ:: አልፎ ተርፎ ትዳር ለምኔ ብለው የሰው ልጅ ሕልውናን የሚያስቀጥለውን የቤተሰብ ተቋም ገደል ሊከቱ መሮጥ ጀመሩ:: ሕፃናትን ስለዝሙት ጥበብ የሚያስተምሩ ጾታቸውን እያጠራጠሩ የሚያወዛግቡ ግፈኞችም በዙ:: ውስጥህን አታምቀው ነኝ ካልክ ነህ ተብለው ብዙዎች ነኝ ያሉትን ለመሆን በቀዶ ህክምና ፍዳቸውን እያዩ ነው:: Youtube ዕድሜ አይሠጠውም እንጂ በጉዳዩ ላይ የተሠሩ ዘጋቢ ፊልሞች እጅግ ልብ ይሠብራሉ:: አልበርት አንስታይን "ሰው የሚችለውን ነገር ከማወቅ በላይ የማይችለውን ማወቁ ይጠቅመዋል" ብሎ ነበር ፍጡር እንደመሆናችን አደርጋለሁ ያልነውን ሁሉ ላናደርግ እንችላለን:: "ዛሬ ወይም ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን፡ የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና። ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፋሎት ናችሁና። በዚህ ፈንታ፦ ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን፡ ማለት ይገባችኋል" ያዕ. 4:13 ሰውዬው ወደ ሥራ ሲሔድ ከአንድ ወዳጁ ጋር ተገናኘ:: "ወዴት እየሔድክ ነው?" አለው:: "እግዚአብሔር ቢፈቅድ ገበያ ውዬ ልመጣ ነው" አለው:: ባለ ሥራው "ምን እግዚአብሔር ቢፈቅድ ትላለህ? ገበያ ልሔድ ነው አይበቃም?" ብሎ አሾፈበትና ተለያዩ:: ባለ ሥራው ወደ ሥራው ሲሔድ ሌቦች ጠብቀው ደብድበውት እጁ ተሠብሮ ሥራ በመግባት ፈንታ ሐኪም ቤት ዋለ:: ከሐኪም ቤት እጁን በፋሻ አንጠልጥሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ "እግዚአብሔር ቢፈቅድ ገበያ ውዬ ልመጣ ነው" ያለው ሰውዬ ጋር ተገናኙ:: "ውይ ወንድሜን ምነው ምን ነካህ" ብሎ የጉዳቱን ሁኔታ በዝርዝር ጠይቆ ከተረዳ በሁዋላ ታማሚውን "ታዲያ አሁን ወዴት እየሔድህ ነው?" ሲለው የጠዋቱ ትዕቢቱ ተንፍሶ እንዲህ አለ :- "እግዚአብሔር ከፈቀደ ወደ ቤቴ እየሔድሁ ነው" ሐዋርያው " ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን፡ ማለት ይገባችኋል። አሁን ግን በትዕቢታችሁ ትመካላችሁ፤ እንደዚህ ያለ ትምክህት ሁሉ ክፉ ነው" ያለው ለዚህ ነው:: ያዕ.4::15-16 ፎቶ :- ቅዱስ ጳውሎስ ኃይልን በሠጠው በክርስቶስ ሁሉን የቻለበት የሰማዕትነቱ አደባባይ
857
20
https://youtu.be/0MKoY2ywgsU
615